EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 560 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 357,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 160 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 560 名订阅者。
根据 26 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 27,过去 24 小时变化为 -7,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 26.05%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.01% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 053 次浏览,首日通常累积 2 491 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 8。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 27 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 560
订阅者
-724 小时
+147 天
+2730 天
帖子存档
15 550
የማከፋፈያ ጣቢያውን አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው
….….///….…
በድሬዳዋ ቁጥር ሦስት ባለ 230/132/33/15 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የመቆጣጠሪያ ክፍል የአቅም ማሳደግና ማሻሻል ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ።
ሥራ አስኪያጁ አቶ አበባው አበራ እንደገለፁት እየተከናወነ የሚገኘው የአቅም ማሳደግና የማሻሻያ ሥራ የማከፋፈያ ጣቢያውን የኦፕሬሽን ሥራዎች ለማዘመን የሚያግዝ ነው።
የአቅም ማሳደግና የማሻሻያ ሥራው በማከፋፈያ ጣቢያው ለረጅም ዓመታት አገልግሎት ሲሰጡ የቆዩትን መቆጣጠሪያዎች በሌላ ዘመናዊ የመቆጣጠሪያ መሳሪያ ለመቀየር ያለመ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
አቶ አበባው እንደገለፁት ቀደም ሲል የነበረው የጣቢያው መቆጣጠሪያ በአየር የሚሰራ (vacume switchgear ) ሲሆን በአሁኑ ወቅት ሊቀየር በሂደት ላይ የሚገኘው መቆጣጠሪያ ደግሞ በጋዝ የሚሰራ ጂ.አይ.ኤስ (Gas Insulated System) ነው፡፡
በአየር የሚሰራው መቆጣጠሪያ የኃይል መቋረጥ ችግሮች ሲያጋጥሙ የጥገና ሥራ በተቀላጠፈ መልኩ ለማከናወን አስቸጋሪ ሁኔታዎች እንደሚፈጠሩ አቶ አበባው አስታውሰዋል።
የመቆጣጠሪያው መቀየር የኃይል መቆራረጥንና በጥገና ሥራዎች ላይ ሊያጋጥሙ የሚችሉ የመዘግየት ችግሮችን በመቅረፍ የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎችን በቀላሉ ለማከናወን እንደሚረዳም ነው ሥራ አስኪያጁ የጠቆሙት።
በአሁኑ ወቅት ለብሬከር ቅየራ ሥራው የሚያስፈልጉ የሲቪል ሥራዎች መጠናቀቃቸውን ያብራሩት አቶ አበባው የጂ.አይ.ኤስ ተከላ ሥራውን በሪጅኑና ከዋና መስሪያ ቤት በተውጣጡ የቴክኒክ ባለሙያዎች ጥምረት ለማከናወን እየተሰራ ይገኛልም ብለዋል።
የማሻሻያ ሥራው በዋናነት በ33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ላይ እየተከናወነ እንደሚገኝ ያነሱት አቶ አበባው ይህም የጣቢያውን የኦፕሬሽን ሥራዎች ዘመኑ በደረሰበት ቴክኖሎጂ ለማከናወን ያስችላል ብለዋል።
የ15 እና 33 ኪሎ ቮልት መቆጣጠሪያዎች ለበርካታ ዓመታት አገልግሎት ሲሰጡ በመቆየታቸው ለኃይል መቆራረጥ ምክንያት እየሆኑ እንደሚገኙ አንስተዋል።
እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በጣቢያው በ33 ኪሎ ቮልት ሦስት ወጪ መስመሮች የሚገኙ ሲሆን መስመሮቹም ለቱሬ ሲሚንቶ፣ ለፓዮኔር ሲሚንቶ እና ለሸሙ የሳሙና ፋብሪካ እንዲሁም ለሐረር የንፁህ መጠጥ ውሃ መስመር ኃይል እያቀረቡ ይገኛሉ።
በ15 ኪሎ ቮልት አንድ ወጪ መስመር እንደሚገኝ የጠቀሱት አቶ አበባው መስመሩም ለመልካ ጀብዱ፣ ኩባ ካምፕና ለማረሚያ ቤት ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
የተጀመረውን የ33 ኪሎ ቮልት የዘመናዊ ብሬከር ቅየራ በአጭር ጊዜ ውስጥ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ዝግጁ ለማድረግ እየተሰራ ይገኛል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 16 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
+1
ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ለብሔራዊ ቡድን ታዳጊ ተጫዋቾችን አስመረጠ
…….///…….
ከ20 ዓመት በታች ለሚካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ለብሔራዊ ቡድን ሁለት ታዳጊ ተጫዋቾችን አስመረጠ።
በታንዛኒያ ለሚካሄደው የሴካፋ ዞን ማጣሪያ አንዋር በድሩ እና ቢኒያም በቀለ በብሔራዊ ቡድኑ ውስጥ ተካተው ልምምዳቸውን በመስራት ላይ ይገኛሉ።
ከተጫዋቾቹ በተጨማሪ የክለቡ የፊዚዮቴራፒ ባለሙያ ሽመልስ እንዳለ ጥሪ ተደርጎለት ለብሔራዊ ቡድኑ አገልግሎት በመስጠት ላይ ነው።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከ17 ዓመት በታች ታዳጊ ቡድን ሐዋሳ ከተማ እየተካሄደ ባለው የኢትዮጵያ ሻምፒዮና በመሳተፍ ላይ ይገኛል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 15 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
#EEP #EBC
ፍኖተ ብርሃን የቴሌቪዥን ፕሮግራም በተቋማችን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴዎች ላይ በማተኮር በልዩ አቀራረብ ለዕይታ በሚመች ሰዓት ወደ እናንተ ይደርሳል።
ዘወትር ሐሙስ ምሽት ከ3:00 - 3:30 ሰዓት በአማርኛ ቋንቋ በኢቲቪ የዜና ቻናል ይጀምራል፡፡
ይጠብቁን!
https://youtu.be/9M6hY77wTEI
የዩቲዩብ ቻናላችንንም ሰብስክራይብ ያድርጉ!
https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 15 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
ተቋሙ ምቹና ዘመናዊ ተሽከርካሪዎችን በማቅረብ የሠራተኞችን እርካታ ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው
……..///……..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሠራተኞቹ ምቹና ዘመናዊ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎችን በማቅረብ የሥራ ላይ እርካታቸውን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ አስታወቀ።
ተቋሙ ከ215 ነጥብ 3 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ ከበላይነህ ክንዴ ግሩፕ የገዛቸውንና በዋናው መስሪያ ቤት ለሚገኙ ሠራተኞች የሰርቪስ አገልግሎት የሚሰጡ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ግዢ መፈፀሙን የንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ዘርፍ ገልጿል።
የዘርፉ ተወካይ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ከሊል ሺፋ እንደገለፁት ተቋሙ በአሁኑ ወቅት በ22 የተለያዩ መስመሮች ለሠራተኞች የሰርቪስ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኝ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 14ቱ ተሽከርካሪዎች የኪራይ ናቸው።
በዚህም ተቋሙ ለሰርቪስ ኪራይ በወር ከ1 ሚሊየን እንዲሁም ለነዳጅና ለተለያዩ የጥገና ሥራዎች ከ1 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ እያደረገ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎቹ ግዢ ለተቋሙ ወጭ ቅነሳ ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖራቸው ያነሱት አቶ ከሊል የትራንስፖርት አገልግሎት ለማሟላት እየተደረገ ያለው ጥረት ሠራተኛው ተረጋግቶ ሥራውን እንዲያከናውን እንደሚያግዘው ተናግረዋል።
ተቋሙ ከኩባንያው ለመግዛት ሥምምነት ካደረገባቸው 12 የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች መካከል አራት አውቶብሶችንና 5 መካከለኛ አውቶብሶችን የተረከበ ሲሆን በቀጣይም አንድ መካከለኛ አውቶብስና ሁለት ሚኒባሶችን እንደሚረከብ ገልፀዋል።
የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎቹን ለሚረከቡ ሹፌሮች በኩባንያው በኩል ተጨማሪ የቴክኒክና ተያያዥ ሥልጠናዎች እንደሚሰጥም ተናግረዋል።
ለኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎቹ የቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያ ቦታ መረጣ ተከናውኖ ቻርጀሮቹ የሚቀመጡበት የመሰረት ሥራ እየተሰራ ነው ያሉት አቶ ከሊል ጣቢያው በሚኖሩት ሁለት የቻርጅ ማድረጊያ መሳሪያዎች 4 ተሽከርካሪዎችን በአንድ ጊዜ በ45 ደቂቃ ውስጥ ለመሙላት የሚያስችል አቅም እንዳለውም ነው ያብራሩት።
ተቋሙ በሀገር ውስጥ የተገጣጠሙ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ግዥ መፈፀሙ ከግዥ በኋላ የሚካሄዱ የጥገና ሥራዎችን በአምራቹ በኩል እንዲከናወኑ በማድረግ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በወቅቱ ለመፍታት ያግዛል ብለዋል።
እንደ አቶ ከሊል ገለፃ በቀጣይ ለተቋሙ ሥራ የሚያገለግሉ አነስተኛና መለስተኛ ተሸከርካሪዎችን በኤሌክትሪክ በሚሰሩ ተሸከርካሪዎች ለመቀየር ዝግጅት እየተደረገም ይገኛል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 15 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
+4
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሲቪል ኢንጅነር 1ኛ የስራ መደብ መጋቢት 11 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በወጣው ማስታወቂያ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ መስከረም 23 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ እና የሂሳብ ማሽን (Calculator) በመያዝ አምስት ኪሎ በሚገኘው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡
ማሳሰቢያ፡- በፈተና ሰዓት የእጅ ስልካችሁን (ሞባይል) መጠቀም የማይቻል
መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 15 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
በሳፕ ምዕራፍ 2 ትግበራ ላይ የልምድ ልውውጥ ተካሄደ
………///………
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሰራርን ለማዘመን እየተተገበረ ባለው የሳፕ ሲስተም የምዕራፍ 2 ትግበራ ላይ በኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል የተጠቃሚዎች ስልጠና የልምድ ልውውጥ አካሄዱ፡፡
በልምድ ልውውጥ መድረኩ ላይ በትግበራ ሂደት የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች ላይ ውይይቶች ተካሂዷል፡፡
የውይይት መድረኩ ያስጀመሩት በሰው ሀብት ዘርፍ የሰው ኃይል ሥልጠናና ልማት ማዕከል ሥራ አስኪያጅ አቶ ደምስ ሰይፉ እንደተናገሩት በተቋሙ 19 ሞጁሎችን በምዕራፍ 2 ለመተግበር ዕቅድ ተይዟል፡፡
ከዕቅዱ 95 በመቶ የሚሆነው በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የጥገና ሂደት ላይ ያተኮረ ነው ብለዋል፡፡
በተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት 377 ወንድና 68 ሴቶች በድምሩ ለ 445 ሠራተኞች በሞጁሎቹ ላይ የተጠቃሚዎች ሥልጠና መሰጠቱን ገልፀዋል፡፡
በኃይል ማመንጫዎች ዘርፍ የቴክኒካል ድጋፍ ሥራ አስኪያጅ አቶ አብዱ ይማም በበኩላቸው የፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል ትግበራን በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች መስጠት መቻሉ እያንዳንዱ ሰልጣኝ ግንዛቤውንና ክህሎቱን እንዲያዳብር አድርጎታል፡፡
የመተግበሪያ መበልፀግ እና የዲጂታል መማማሪያ እንዲኖር የማድረግ ሥራዎችን በየጣቢያዎች በመስራት ትግበራውን ማዳበር መቻሉንም ተናግረዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ተግባራዊ ከተደረጉት ኢኒሼቲቮች ውስጥ የፈተና ምዘናና ውጤት አሰጣጥ፣ የአንድሮይድ መተግበሪያ ማበልፀግ እና የዕውቀት አስተዳደር ሥርዓትን በማሻሻል ሳፕ እየተተገበረ እንደሚገኝ አቶ አብዱ አስረድተዋል፡፡
በልምድ ልውውጥ መድረኩ ላይ ከተቋሙ የተለያዩ ክፍሎች የተውጣጡ 35 የሳፕ አስተግባሪዎች ተሳትፈዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 15 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
ተቋሙ ለሠራተኞች ሰርቪስ የሚያገለግሉ የኤሌክትሪክ አውቶብሶችን ተረከበ
……..///……..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከበላይነህ ክንዴ ግሩፕ የገዛቸውን የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪ አውቶቡሶችን ተረክቧል።
ተቋሙ ከኩባንያው ለመግዛት ስምምነት ካደረገባቸው 12 ተሸከርካሪዎች መካከል በዛሬው ዕለት አራት አውቶቡሶችንና አምስት መካከለኛ አውቶብሶችን የተረከበ ሲሆን በቀጣይም አንድ መለስተኛ አውቶቡስና ሁለት ሚኒባሶችን የሚረከብ ይሆናል፡፡
አውቶብሶቹን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጅነር አሸብር ባልቻ ከበላይነህ ክንዴ ግሩፕ ባለቤትና የቦርድ ሰብሳቢ ከአቶ በላይነህ ክንዴ ተረክበዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ አውቶቡሶችን በተረከቡበት ወቅት እንደተናገሩት ተቋሙ ንፁህና ታዳሽ የኤሌክትሪክ ኃይል በማምረት ለሀገር ውስጥ ፍጆታና ለጎረቤት ሀገራት እያቀረበ ይገኛል፡፡
በአሁኑ ወቅት መንግሥት በፖሊሲ ደረጃ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ጥቅም ላይ እንዲውሉ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ተቋሙ ፖሊሲውን ለመደገፍና በዘርፉ የተሰማሩ አምራቾችን ለማበረታታት እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
በዚህም የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ መግባታቸውን ተከትሎ የሚያጋጥሙ የተሸከርካሪ ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያዎችን እጥረት ለመቅረፍ ተቋሙ ከግል ባለሀብቶች ጋር በመቀናጀት ለመገንባት ስትራቴጂ መቀረፁንና ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በትብብር እየሰራ እንደሆነ አስረድተዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ጥቅም ላይ እንዲውሉ መንግሥት የተለያዩ ድጎማዎችን እያደረገ እንደሚገኝ ያነሱት ኢንጂነር አሸብር ኩባንያው ዕድሉን በመጠቀም በሀገር ውስጥ የተገጣጠሙትን ተሽከርካሪዎች ተጠቃሚ በመሆኑ መደሰታቸውን ገልፀዋል፡፡
ተቋሙ ከኩባንያው የተረከባቸው ተሸከርካሪዎች ለሠራተኛው ምቹ የሰርቪስ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያግዙ ገልፀው በቀጣይም ለተቋሙ ሥራ የሚያገለግሉ አነስተኛና መለስተኛ ተሸከርካሪዎችን በኤሌክትሪክ መኪና ለመቀየር እየተሰራ እንደሆነ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አስታውቀዋል፡፡
እንደ ኢንጂነር አሸብር ገለፃ የበላይነህ ክንዴ ግሩፕ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ እያደረገ ያለውን የገንዘብ ድጋፍ ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች ፋብሪካዎችን በማቋቋም በሀገሪቱ የሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ የራሱን አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል፡፡
"ኩባንያውን ማገዝና መደገፍ ኢትዮጵያን መደገፍ ነው" ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው ተቋሙም ይህን በመገንዘብ ለባለሀብቱ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል፡፡
የበላይነህ ክንዴ ግሩፕ ባለቤትና የቦርድ ሰብሳቢ አቶ በላይነህ ክንዴ በበኩላቸው ኩባንያቸው በአውቶሞቲቭ መገጣጠሚያና የምግብ ማቀነባበሪያ ዘርፎች ላይ እየተሳተፈ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡
ኩባንያው ከዚህ በፊት ይታወቅበት ከነበረው የነዳጅ ተሸከርካሪዎች የመገጣጠም ሥራ በማስፋት ካለፉት ስድስት ወራት ወዲህ 500 የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን በመገጣጠም ለገበያ ማቅረቡን አስታውቀዋል፡፡
የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን በመጠቀም በኩል የተለያዩ አሉባልታዎች እንደሚደመጡ የተናገሩት አቶ በላይነህ ድህነትን ድል ለማድረግ ቴክኖሎጂው ላይ እምነት በመጣል መጠቀም እንደሚገባም ነው ተናገሩት፡፡
ሀገሪቱ በዓመት ለነዳጅ 5 ቢሊዮን ዶላር እንደምታወጣ የተናገሩት አቶ በላይነህ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ መግባታቸው ለነዳጅ የሚወጣውን ወጪ ከማስቀረት ባለፈ የአየርና የድምጽ ብክለትን ለማስወገድ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኩባንያው የተገጣጠሙትን የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች መጠቀም መጀመሩ ሌሎች ተቋማትና ግለሰቦች በተሸከርካሪዎቹ ላይ አመኔታ እንዲኖራቸው ዕድል እንደሚፈጥርም አመልክተዋል፡፡
የተሸከርካሪዎቹ ባትሪ ለ15 ዓመታት እንደሚያገለግል የጠቀሱት ባለሀብቱ ኩባንያው ለባትሪ የ8 ዓመት እንዲሁም ለሞተር የ5 ዓመት ዋስትና እንደሚሰጥም አስረድተዋል፡፡
ተሸከርካሪዎችን በአግባቡ ለመጠቀም ተቋሙ ለአሽከርካሪዎች አስፈላጊውን ጥቅማ ጥቅም ማሟላት እንደሚኖርበትና አሽከርካሪዎቹም በአግባቡ እንክብካቤ ሊያደርጉላቸው እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
ኩባንያው ተሸከርካሪዎቹን ከማቅረብ ባለፈ ለአሽከርካሪዎች አስፈላጊውን ስልጠና ለመስጠት፣ የመለዋወጫ ዕቃዎችን ለማቅረብና በቀጣይ በማንኛውም መስክ ከተቋሙ ጋር በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 14 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
“ተቋሙ ቀድሞ መዘጋጀቱ የሚመሰገነ ነው” - የበደሌ ቢራ ፋብሪካ ሥራ አሰኪያጅ
……..///………
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቂና አስተማማኝ ኃይል ለደበኞቹ ለማቅረብ አስቀድሞ ተዘጋጅቶ መጠበቁ የሚበረታታና የሚመሰገን ተግባር መሆኑን በሄኒከን የበደሌ ቢራ ፋብሪካ ስራ አሰኪያጅ ተናገሩ፡፡
ሥራ አስኪያጁ አቶ ረቢወያ ለገሰ እንደገለፁት ፋብሪካው የሚጠቀመውን በቂና ያልተቆራረጠ ኃይል በአቅራቢያው ከሚገኘው የበደሌ ማከፋፈያ ጣቢያ እያገኘ ከመሆኑም ባለፈ በኃይል አቅርቦት በኩል ለሚያጋጥማቸው ማንኛውም ችግር ከተቋሙ ሠራተኞች ቀና ትብርና ፈጣን ምላሽ ስለሚያገኙ ሊመሰገን ይገባል፡፡
ፋብሪካውን ለማዘመን የሚያስፈልገውን ተጨማሪ ኃይል በአስተማማኝ ሁኔታ ለማቅረብ ተቋሙ አስቀድሞ መዘጋጀቱ ደበኞቹን ከአላስፈላጊ ወጪና ስጋት እንደሚያድን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡
የበደሌ ማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሲሳይ ቀኖ በበኩላቸው በማከፋፈያ ጣቢያው በተለያዩ ጊዜያት የተከናወኑ የማዘመን እና የማሻሻያ ሥራዎች በአሁኑ ወቅት ያለምንም የኃይል መቆራረጥ የደበኞቹን እርካታ በጠበቀ መልኩ ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡
ጣቢያው ከ150 ሜጋ ዋት በላይ የመሸከም አቅም ቢኖረውም በአሁኑ ወቅት ለደበኞቹ እያቀረበ ያለው 30 ሜጋ ዋት ያልበለጠ ኃይል በመሆኑ የደንበኞችን የኃይል ጥያቄ በአስተማማኝ ሁኔታ የሚመልስ አቅም እንዳለው ጨምረው ገልጸዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 13 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
#EEP #EBC
ፍኖተ ብርሃን የቴሌቪዥን ፕሮግራም በተቋማችን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴዎች ላይ በማተኮር በአዲሱ ዓመት፣ በልዩ አቀራረብ ለዕይታ በሚመች ሰዓት ወደ እናንተ ይደርሳል።
ዘወትር ሐሙስ ምሽት ከ3:00 - 3:30 ሰዓት በአማርኛ የቴሌቭዥን ፕሮግራም በዜናዎች ቻናል
ዘወትር እሁድ ምሽት ከ12:10 - 12:40 ሰዓት በኦሮምኛ የቴሌቭዥን ፕሮግራም ቋንቋዎች ቻናል።
ዘወትር ዓርብ ምሽት ከ2:30 - 3:00 ሰዓት በአማርኛ ቋንቋ በብሄራዊ ሬዲዮ ይቀርባል።
በቅርብ ቀን ይጠብቁን!
https://www.youtube.com/watch?v=FzCdm5sI5KU
የዩቲዩብ ቻናላችንንም ሰብስክራይብ ያድርጉ!
https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 13 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
“ፕሮጀክቱን ታሳቢ ያደረጉ የኢንቨስትመንት ያደረጉ ጥያቄዎች እየቀረቡ ነው” - የማሻ ከንቲባ
……..////…..
የማሻ ባለ 230/33 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ፕሮጀክትን ታሳቢ ያደረጉ የኢንቨስትመንት ጥያቄዎች ለከተማው መስተዳደር እየቀረቡ መሆኑን የማሻ ከተማ ከንቲባ ገለጹ፡፡
ከንቲባው አቶ ሰራዊት አየነው እንደገለፁት አካባቢው የግብርና ምርቶች በስፋት የሚመረትበት እንደመሆኑ የተለያዩ የግብርና ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎችን የሚገነቡ የግል አልሚዎችን የሚስብ እምቅ ሀብት አለው፡፡
በአሁኑ ወቅትም የማከፋፈያ ጣቢያ መገንባቱን ታሳቢ ያደረጉ የማር ማቀነባበሪያ እና የአቡካዶ ዘይት መጭመቂያ ፋብሪካ ግንባታ የጀመሩ የግል አልሚዎች እንዳሉ ገልጸዋል፡፡
የማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ ለዘመናት የቆየውን የአካባቢውን ህብረተሰብ የኃይል አቅርቦት ጥያቄ ለመመለስም ሆነ ለከተማው አጎራባች ወረዳዎች ዘርፈ ብዙ የልማት ችግሮችን ለመፍታት ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ከንቲባው ተናግረዋል፡፡
ፕሮጀክቱ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ የከተማው መስተዳደርም ሆነ የአካባቢው ማህብረሰብ እንደ ዓይኑ ብሌን በመጠበቅ አስፈላጊውን ትብብር እያደረገ እንደሚገኝ የገለጹት አቶ ሰራዊት ይህ ትብብርም ጣቢያው አገልግሎት መስጠት ሲጀምርም የበለጠ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁመዋል፡፡
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የማሻ አገልገሎት መስጫ ማዕከል ሥራ አስኪያጅ አቶ ኢሞ ወኒቶ እንደገለጹት ከ70 ኪሎ ሜትር በላይ ትላልቅ ዛፎችን አቋርጦ ከመቱ ማከፋፈያ ጣቢያ የሚመጣው አንድ ባለ 33 ኪሎ ቮልት መስመር በማዕከሉ ለሚገኙት 2400 ደንበኞች ያልተቆራረጠ ኃይል ለማድረስ ፈታኝ እንደነበር አስረድተዋል፡፡
በመሆኑም ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ከማስቻሉም ባሻገር ደንበኞችን ለማስፋት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት ያላቸውን ተስፋ ተናግረዋል፡፡
የማሻ ባለ 230/33 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ ከአዲስ አበባ በ636 ኪ.ሜ. ርቀት በደቡብ ምዕራብ ህዝቦች ክልል በሸካ ዞን ማሻ ከተማ እየተገነባ ይገኛል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 13 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በፕሪሚየር ሊጉ ባደረገው የመጀመሪያ ጨዋታ ሽንፈት ገጥሞታል
.......///.......
በድሬዳዋ ከተማ በተጀመረው የዘንድሮ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን ከወላይታ ዲቻ ጋር ባካሄደው ጨዋታ 3 ለ 2 በሆነ ውጤት ተረቷል።
በዛሬው ዕለት ከቀኑ 10 ሰዓት በተከናወነው በዚህ ጨዋታ ኳስን ተቆጣጥሮ በመጫወት እና ወደፊት በማጥቃት ረገድ ወላይታ ዲቻ የተሻለ ነበር።
በአንፃሩ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ አልፎ አልፎ በመልሶ ማጥቃት ካደረገው እንቅስቃሴ በስተቀር በመከላከል ላይ የተመሠረተ አጨዋወት ነበር ተግባራዊ ያደረገው።
የወላይታ ዲቻን የማሸነፊያ ጎሎች ተስፋዬ መላኩ፣ ካርሎስ ዳምጠው እና ጌታሁን ባፍ በራሱ ግብ ላይ ሲያስቆጥር ኢትዮ ኤሌክትሪክን ከሽንፈት ያልታደጉትን ጎሎች እዮብ ገ/ማርያም እና አቤል ሀብታሙ ከመረብ አሳርፈዋል።
ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ባለፈው ዓመት በተከናወነው የከፍተኛ ሊግ ውድድር አንደኛ በመሆን ወደ ፕሪሚየር ሊጉ መመለሱ ይታወሳል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 12 ቀን 2017 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
