en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 692 subscribers, ranking 8 014 in the Technologies & Applications category and 2 155 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 692 subscribers.

According to the latest data from 30 August, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 145 over the last 30 days and by 2 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 31.28%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.96% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 909 views. Within the first day, a publication typically gains 2 661 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 31 August, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 692
Subscribers
+224 hours
+187 days
+14530 days
Posts Archive
ፕሮጀክቱ በአካባቢው ያለውን የኃይል ጥያቄ በአግባቡ ለመመለስ ያግዛል …….///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአርባ ምንጭ ዙሪያ ተገንብተው በመጠናቀቅ ላይ የሚገኙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር
+7
ፕሮጀክቱ በአካባቢው ያለውን የኃይል ጥያቄ በአግባቡ ለመመለስ ያግዛል …….///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአርባ ምንጭ ዙሪያ ተገንብተው በመጠናቀቅ ላይ የሚገኙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች በአካባቢው አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ እንደሚያስችሉ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የአርባ ምንጭ ሪጅን ገለፀ። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ገረመው ወንድምሁነኝ እንደገለፁት አሁን ላይ የአርባ ምንጭ ከተማን ጨምሮ የጋሞ ዞን የተለያዩ አካባቢዎች በከተማው ውስጥ ከሚገኘው የነባሩ የባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል በማግኘት ላይ ይገኛሉ። የማከፋፈያ ጣቢያው በዞኑ ለሚገኙ ኢንዱስትሪዎች፣ ለአገልግሎት ሰጭና መንግስታዊ ተቋማት እንዲሁም ለነዋሪው ኃይል የማቅረብ አቅም ቢኖረውም በአንድ አቅጣጫ ብቻ ኃይል የሚያገኝ በመሆኑ መስመሩ በተለያዩ ምክንያቶች ችግር ሲያጋጥመው የኃይል መቋረጥ ይስተዋልበት እንደነበር አስታውሰዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ፕሮጀክቱ-በአካባቢው-ያለውን-የኃይል-ጥያ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et የካቲት 27 ቀን 2018 ዓ.ም

በተቋሙ የዉስጥ አቅም በተከናወነ ሥራ 60 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ማዳን ተችሏል …..….///…….. በኢትዮ-ኬንያ ኢንተር ኮኔክሽን የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የችግር ጠቋሚ (fault l
+4
በተቋሙ የዉስጥ አቅም በተከናወነ ሥራ 60 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ማዳን ተችሏል …..….///…….. በኢትዮ-ኬንያ ኢንተር ኮኔክሽን የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የችግር ጠቋሚ (fault locater) መሳሪያን ተግባራዊ ለማድረግ በውስጥ አቅም በተከናወነ የማስተካከል ሥራ 60 ሺህ የሚደርስ የአሜሪካ ዶላር ማዳን መቻሉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። በተቋሙ የኢንጅነሪንግ ቢዝነስ ዘርፍ ሬዚደንት ኢንጂነር አቶ ቴዎድሮስ አያሌው እንዳስታወቁት በከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ላይ ችግር ሲፈጠር የሚጠቁመው መሳሪያ ከአራት ዓመታት በላይ ሥራ ሳይሰራ ቆይቷል። በተደጋጋሚ ተሞክሮ ዉጤታማ ያልሆነውን የችግር ጠቋሚ መሳሪያ የገጠመውን ችግር ለመለየት በተደረጉ ምርመራዎች እና ፍተሻዎች መሳሪያው በግንባታ ወቅት የቴክኒክ ችግር እንዳለበት መረጋገጡን ገልጸዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በተቋሙ-የዉስጥ-አቅም-በተከናወነ-ሥራ-60-ሺህ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et የካቲት 27 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮቹ የፍተሻ እና ሙከራ ሥራ ተጠናቀቀ .…….///……. የብሔራዊ ኤሌክትሪክ ደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አካል የሆኑት የወላይታ ሶዶ ቁጥር 2 - አርባ ምንጭ ቁጥር 2
+8
የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮቹ የፍተሻ እና ሙከራ ሥራ ተጠናቀቀ .…….///……. የብሔራዊ ኤሌክትሪክ ደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አካል የሆኑት የወላይታ ሶዶ ቁጥር 2 - አርባ ምንጭ ቁጥር 2 ባለ 230 ኪሎ ቮልት እና የአርባ ምንጭ ቁጥር 2 - አርባ ምንጭ ቁጥር 2 ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች የሙከራ እና ፍተሻ ሥራ መጠናቀቁን ፕሮጀክት ጽ/ቤቱ አስታወቀ። የፕሮጀክቱ ተወካይ ሥራ አስኪያጅ አቶ አንዱዓለም መላኩ እንዳስታወቁት የመስመር ዝርጋታዎቹ አዲስ የተገነቡትን የወላይታ ሶዶ ቁጥር 2 ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማስፋፊያ እና የአርባ ምንጭ ሁለተኛ ባለ 230 ኪሎ ቮልት አዲስ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እንዲሁም የአርባ ምንጭ ቁጥር 1 ባለ 132 ኪሎ ቮልት ማስፋፊያ ግንባታዎችን ለአገልግሎት ዝግጁ ለማድረግ የሚያስችሉ ናቸው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-የማከፋፈያ-ጣቢያው-የማስፋፊያ-ሥ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et የካቲት 27 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል የማከፋፈያ ጣቢያው የማስፋፊያ ሥራ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ …..///….. የወላይታ ሶዶ ቁጥር 2 ባለ 400/230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ የማስፋፊያ ግንባታ ሥራ በተያዘለት የጊ
+4
የኃይል የማከፋፈያ ጣቢያው የማስፋፊያ ሥራ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ …..///….. የወላይታ ሶዶ ቁጥር 2 ባለ 400/230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ የማስፋፊያ ግንባታ ሥራ በተያዘለት የጊዜ ገደብ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የብሔራዊ ኤሌክትሪክ ደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት አስታወቀ። የፕሮጀክቱ ተወካይ ሥራ አስኪያጅ አቶ አንዱዓለም መላኩ እንደገለፁት በማከፋፈያ ጣቢያው ተጨማሪ 230 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማቅረብ የሚያስችል የማስፋፊያ ሥራ በማከናወን በዛሬው ዕለት ለአገልግሎት በቅቷል። በማስፋፊያ ሥራው እያንዳንዳቸው 250 ሜጋ ቮልት አምፒር የመጫን አቅም ያላቸው ሁለት ትራንስፎርመሮች ተከላ መከናወኑንም ነው የተናገሩት። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-የማከፋፈያ-ጣቢያው-የማስፋፊያ-ሥ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et የካቲት 26 ቀን 2018 ዓ.ም

ማከፋፈያ ጣቢያዎቹ በከተማዉ አስተማማኝ ኃይል እንዲኖር አስችለዋል …….///…… በወላይታ ሶዶ ከተማ አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙት ሁለቱ የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች በሶዶ ከተማ እና በዙሪያ
+7
ማከፋፈያ ጣቢያዎቹ በከተማዉ አስተማማኝ ኃይል እንዲኖር አስችለዋል …….///…… በወላይታ ሶዶ ከተማ አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙት ሁለቱ የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች በሶዶ ከተማ እና በዙሪያው አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ማስቻላቸውን የከተማዋ ከንቲባ አስታወቁ። ከንቲባዋ ወይዘሮ እታገኝ ኃይለማሪያም እንዳስታወቁት ለከተሞች እና ለኢንቨስትመንት መስፋፋት፣ ለሥራ ዕድል ፈጠራ እንዲሁም ለቱሪዝም ዕድገት የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ከፍተኛ ድርሻ አለው። በከተማዋ የሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለኢንዱስትሪዎች እና ለአገልግሎት ሰጪ ተቋማት በቂ ኃይል እያቀረቡ እንደሚገኙ በማንሳት የኃይል አቅርቦቱ ለከተማዋ መስፋፋት፣ በኢንቨስትመንት፣ በአገልግሎት አሰጣጥ እና በነዋሪዎች የዕለት ተዕለት ኑሮ ላይ አዎንታዊ ለውጥ እያመጣ መሆኑንም ተናግረዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ማከፋፈያ-ጣቢያዎቹ-በከተማዉ-አስተማማኝ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et የካቲት 26 ቀን 2018 ዓ.ም

ማከፋፈያ ጣቢያዎቹ በከተማዉ አስተማማኝ ኃይል እንዲኖር አስችለዋል …….///…… በወላይታ ሶዶ ከተማ አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙት ሁለቱ የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች በሶዶ ከተማ እና በዙሪያ
+6
ማከፋፈያ ጣቢያዎቹ በከተማዉ አስተማማኝ ኃይል እንዲኖር አስችለዋል …….///…… በወላይታ ሶዶ ከተማ አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙት ሁለቱ የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች በሶዶ ከተማ እና በዙሪያው አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ማስቻላቸውን የከተማዋ ከንቲባ አስታወቁ። ከንቲባዋ ወይዘሮ እታገኝ ኃይለማሪያም እንዳስታወቁት ለከተሞች እና ለኢንቨስትመንት መስፋፋት፣ ለሥራ ዕድል ፈጠራ እንዲሁም ለቱሪዝም ዕድገት የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ከፍተኛ ድርሻ አለው። በከተማዋ የሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለኢንዱስትሪዎች እና ለአገልግሎት ሰጪ ተቋማት በቂ ኃይል እያቀረቡ እንደሚገኙ በማንሳት የኃይል አቅርቦቱ ለከተማዋ መስፋፋት፣ በኢንቨስትመንት፣ በአገልግሎት አሰጣጥ እና በነዋሪዎች የዕለት ተዕለት ኑሮ ላይ አዎንታዊ ለውጥ እያመጣ መሆኑንም ተናግረዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ማከፋፈያ-ጣቢያዎቹ-በከተማዉ-አስተማማኝ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et የካቲት 26 ቀን 2018 ዓ.ም

የማከፋፈያ ጣቢያውን አቅም የማሳደግ ሥራ እየተከናወነ ነው …….///………. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሰሜን ምዕራብ ሪጅን ሥር የሚገኘውን የአዘዞ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ አ
+4
የማከፋፈያ ጣቢያውን አቅም የማሳደግ ሥራ እየተከናወነ ነው …….///………. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሰሜን ምዕራብ ሪጅን ሥር የሚገኘውን የአዘዞ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ አቅም ለማሳደግ የሚያስችል ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ይገርማል ማሩ እንደገለፁት ጣቢያው አገልግሎት መስጠት ከጀመረበት 1995 ዓ.ም. ጀምሮ የአካባቢውን የኃይል ፍላጎት በማሟላት ረገድ ከፍተኛ ሚና ሲጫወት ቆይቷል፡፡ በአሁኑ ወቅት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያውን የኦፕሬሽን አቅም ለማሳደግ በባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች የዘመናዊ መቆጣጠሪያ ብሬከር ቅየራ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የማከፋፈያ-ጣቢያውን-አቅም-የማሳደግ-ሥራ-2&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et የካቲት 25 ቀን 2018 ዓ.ም

በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓቶችን ለጥገና ሥራዎች መተግበር ይገባል .......///….… በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓቶችን ለጥገና ሥራዎች ተግባራዊ ማድረግ እ
+5
በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓቶችን ለጥገና ሥራዎች መተግበር ይገባል .......///….… በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓቶችን ለጥገና ሥራዎች ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጀነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወልደኪዳን የተመራ የባለሙያዎች ቡድን በአዳማ አንድ እና ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የመስክ ምልከታ አድርጓል። የመስክ ምልከታው ተቋሙ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎቹን ውጤታማነት፣ ደህንነት እና ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓት ለማሳደግ የጀመረው ስትራቴጂካዊ የክትትል አካል መሆኑ ተገልጿል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በኃይል-ማመንጫ-ጣቢያዎች-ዘመናዊ-የአሰራ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et የካቲት 24 ቀን 2018 ዓ.ም

ለመላው ኢትዮጵያውያን በሙሉ እንኳን ለ130 ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ በሠላም አደረሳችሁ! ጀግኖች አያት ቅድመ አያቶቻችን ህይወታቸውን ገብረው ነፃነት እንዳቀዳጁንና ጀግንነት እንዳወረሱን ሁሉ ተቋማችን ለሀገራችን እድገት አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማድረግ በርካታ መስዋዕትነት የሚጠይቁ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል። ከእነዚህም መካከል በመላው ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ድጋፍ እውን የሆነው የመላ አፍሪካውያን ኩራት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ይጠቀሳል። በህዳሴ ግድብ ላይ የተጀመረውን የድል አድራጊነት ስኬት በሌሎች ፕሮጀክቶቻችንም ላይ በመድገምና አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አቅርቦት እንዲኖር በማድረግ ለሀገራችንን ዕድገት የበኩላችንን ድርሻ መወጣታችንን እንደምንቀጥል እምነቴ የፀና ነው። በዓሉ በሁሉም ዘርፍ የምናሸንፍበትና የአንድነት እንዲሆንልን ከልብ እመኛለሁ፡፡ አሸብር ባልቻ፣ ዋና ሥራ አስፈፃሚ

image_2026-03-01_14-50-18.png6.10 KB

ዐድዋ እና ሕዳሴ፦ ትናንት በደም፣ ዛሬ በላብ የተገነባ የሉዓላዊነት ድልድይ! 🇪🇹 በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ሁለት ታላላቅ "የማይቻል" የሚመስሉ ድሎች አሉ። አንደኛው በጠመንጃ ወራሪን ድል ያደረግንበት የዐድዋ ድል ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ በገንዘባችን፣ በዕውቀታችንና በላባችን ድህነትንና ኢፍትሐዊነትን ድል ለማድረግ በቁርጠኝነት የሰራንበት የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ላይ ያስመዘገብነው ድል ነው። 🇪🇹 አባቶቻችን በዐድዋ ተራሮች ላይ ለዓለም ያስተማሩት ትምህርት "ለነፃነት ዋጋ መክፈል!" የሚል ነበር። ያ ድል ኢትዮጵያን በአፍሪካ ብቻ ሳይሆን በመላው ዓለም የተጨቆኑ ሕዝቦች ተስፋ አደረጋት። ዐድዋ ባይኖር ኖሮ ዛሬ ስለ ሉዓላዊነትና ስለ ኢኮኖሚ ነፃነት የምናወራበት የጸና ሀገር ባልኖረን ነበር። 🇪🇹 የኢኮኖሚ ነፃነት ማማ ተምሳሌት ተደርጎ የሚወሰደው የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ደግሞ የዐድዋ ድል የ21ኛው ክፍለ ዘመን ቀጣይነት ማሳያ ነው። ትናንት "ቅኝ አልገዛም" እንዳልን ሁሉ፣ ዛሬ ደግሞ በሕዳሴው ግድብ አማካኝነት "የተፈጥሮ ሀብቴን በራሴ ፈቃድና ፍላጎት እንጂ በሌሎች ይሁንታ አልጠቀምም" ብለን የመልማት መብታችንን ለዓለም አረጋግጠናል። የግድቡ ኃይል ማመንጨት መጀመር ኢትዮጵያ ከድህነት ቀንበር ለመውጣትና የአፍሪካ የኢኮኖሚ ብርሃን (Economic Beacon) ለመሆን የጀመረችው ጉዞ ስኬት ነው። 🇪🇹 ትናንት አባቶቻችን አጥንታቸውን ከስክሰው ደማቸውን አፍሰው ይህችን ሀገር አቆይተውልናል፡፡ የዛሬው ትውልድ ደግሞ ላቡን አፍሶ ግድቡን በመገንባት ለኢትዮጵያ ብሩህ የተስፋ አድማስ ፈንጥቋል። የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የዐድዋ ድል ባለቤት የሆነችውን ኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ባለድል እና የመጪው ጊዜ ኃያል የማድረግ ቃል ኪዳን ነው። ስለሆነም ዐድዋን ማክበር ማለት የአባቶችን ጀግንነት ማድነቅ ብቻ አይደለም፤ እንደ አባቶቻችን ለሀገር የሚጠቅም አሻራ ማሳረፍም ጭምር ነው። የሕዳሴው ግድብ የሁላችንም ኩራትና የዐድዋ መንፈስ በተግባር የገለጽንበት የታሪካችን አዲሱ ምዕራፍ ነው! የዐድዋ የድል መንፈስ በሕዳሴው ግድብ ላይ ተደግሟል! 🇪🇹 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et የካቲት  22 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

ከዐድዋ እስከ ህዳሴ - የክብርና የሉዓላዊነት ቀጣይነት! 🇪🇹🛡🌊 "ዐድዋ የአፍሪካ ድል ነው። አፍሪካውያን ቅኝ ግዛት ፈጽሞ እንደማይቀበሉ ያሳዩበት ድል ነው።" (የመደመር መጽሐፍ፣ ገጽ 266) የዘንድሮው የዐድዋ ድል በዓል “ከአኩሪ ታሪክ ወደ ብሩህ አድማስ" በሚል ታላቅ መሪ ቃል ይከበራል። ይህ መሪ ቃል ትናንት በጀግኖች ደምና አጥንት የተጠበቀችውን ሀገር ዛሬ በዘላቂ ሰላምና በልማት ወደ ሁለንተናዊ ሉዓላዊነትና ከፍታ ለማሻገር ያለንን ፅኑ ቁርጠኝነት የሚገልጽ ነው። ዐድዋ እና ህዳሴ፦ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች 📌 የዐድዋ ድል ወታደራዊ ድል ብቻ ሳይሆን፣ ኢትዮጵያውያን ለፍትሕና ለእኩልነት ያላቸውን ጽኑ አቋም ለዓለም ያሳዩበት ነው። ዛሬም ይህ የዐድዋ መንፈስ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ላይ በደመቀ ሁኔታ ተደግሟል። 🇪🇹 አባቶቻችን በዐድዋ ምድር በ"ቅኝ አልገዛም!" ብለው ወራሪን እንዳሳፈሩ ሁሉ፣ ዛሬም የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅና ኃይል ማመንጨት መጀመሩ ኢትዮጵያ በሀብቷ የመጠቀም ተፈጥሯዊ መብቷን ለማስከበር ያሳየችው "የዘመኑ ዐድዋ" ነው። ይህ ግድብ ኢትዮጵያ ኢፍትሐዊነትን እና የኢኮኖሚ የእጅ አዙር ቅኝ አገዛዝን የማትቀበል ሀገር መሆኗን ዳግም ለዓለም ያረጋገጠችበት ትልቅ ሀገራዊ ድል ነው። 🇪🇹 ጀግኖች አባቶቻችን ነፃ ሀገር አውርሰውናል፤ እኛ ደግሞ የበለፀገችና በብርሃን የተሞላች ሀገር ለልጆቻችን ለማውረስ በሕዳሴው ግድብ መሠረት ጥለናል። ይህ ጉዞ ከአኩሪ ታሪክ የተነሳና ወደ ብሩህ አድማስ የሚያመራ የድል ሰንሰለት ነው። ትናንት በጦር ሜዳ ሉዓላዊነታችንን አስከብረን እንዳልተንበረከክን፣ ዛሬ ደግሞ በልማትና በኢኮኖሚ ነፃነታችንን በማረጋገጥ ወደ ሁለንተናዊ ከፍታ እየተጓዝን ነው። የሕዳሴው ግድብ የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን፣ ልክ እንደ ዐድዋ ሁሉ የጥቁር ሕዝቦችና የመላው አፍሪካውያን የልማት ተስፋና ኩራት ነው። 🇪🇹 ስለሆነም ዐድዋ የነፃነታችን መጀመሪያ እንደሆነው ሁሉ የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም የኢኮኖሚ ከፍታችን እና የመቻላችን ማረጋገጫ ነው። ትናንት በጥይት ድል አደረግን፤ ዛሬ በዕውቀትና በሀብታችን ድል እያደረግን ነው! ክብር ለዐድዋ ጀግኖች! ሞገስ ለሕዳሴ ግድብ ገንቢዎች! 🇪🇹 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et የካቲት  22 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

የተግባር ፈተና ጥሪ ማስታወቂያ ..........///.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቧንቧ ጥገና ሰራተኛ (Plumber Technician) የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ጥ
የተግባር ፈተና ጥሪ ማስታወቂያ ..........///.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቧንቧ ጥገና ሰራተኛ (Plumber Technician) የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ጥር 15 ቀን 2018 ዓ.ም የውጭ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱ አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል የፅሁፍ ፈተና ተፈትናችሁ የማለፊያ ነጥብ ያመጣችሁ ከተራ ቁጥር 1 እስከ 19 የስም ዝርዝራችሁ የተገለጸው ተወዳዳሪዎች የካቲት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 የተግባር ፈተና ስለሚሰጥ በሰው ኃይል ቅጥርና ምደባ ቢሮ እንድትገኙ እናሳውቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et የካቲት  19 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ ..........///.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኤሌክትሪክ መኪና ቻርጅ አድራጊ ቴክኒያሽን (Technician-I EV Battery Charger) የስራ መደ
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ ..........///.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኤሌክትሪክ መኪና ቻርጅ አድራጊ ቴክኒያሽን (Technician-I EV Battery Charger) የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ጥር 08 ቀን 2018 ዓ.ም የውጭ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ በዚሁ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ የካቲት 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ ብረታ ብረት ፊትለፊት በሚገኘው በዋናው መ/ቤት የስብሰባ አዳራሽ የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et የካቲት 19 ቀን 2018 ዓ.ም

የታሪፍ ድርድር ማዕቀፍን ለማዘመን የሚያስችል የጥናት ማስጀመሪያ ፕሮግራም ተካሄደ ….///…. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከደቡብ ኮሪያ ሪፐብሊክ መንግሥት ጋር የኤሌክትሪክ ታሪፍ ድርድር ማዕቀፍን ለማዘመን የሚያስችል የጥናት ማስጀመሪያ መርሀ ግብር በዛሬው ዕለት አካሂዷል፡፡ በጥናት ማስጀመሪያ መርሀ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ኢትዮጵያና ደቡብ ኮሪያ የኃይል ልማት ዘርፍን ለማሳደግና ለማዘመን በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ በትብብር ሲሰሩ መቆየታቸውን ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ ከታዳሽ ኃይል ኤሌክትሪክ ለማመንጨት የሚያስችል ሰፊ ሀብት ቢኖራትም አሁን ላይ የኃይል ተደራሽነት ሽፋኑ 54 በመቶ ብቻ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የታሪፍ-ድርድር-ማዕቀፍን-ለማዘመን-የሚያ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et የካቲት 17 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9