uk
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Відкрити в Telegram

EEP Communication

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 15 554 підписників, посідаючи 8 399 місце в категорії Технології та додатки та 2 163 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 15 554 підписників.

За останніми даними від 20 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 12, а за останні 24 години на 7, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 26.73%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 14.92% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 4 157 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 320 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 10.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
EEP Communication

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 21 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Технології та додатки.

15 554
Підписники
+724 години
+77 днів
+1230 день
Архів дописів
photo content
+6

የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን አቅም ለማሳደግና ለማዘመን እየተሰራ ነው .....///...... የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን አቅም ለማሳደግና ለማዘመን እየሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡ በተቋሙ የማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽን አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን ወ/ማርያም እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ በ24 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የ15 አና 33 ኪሎ ቮልት ስዊችጊሮችን ለማዘመን ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል። በበጀት ዓመቱ ያለፉት ወራት በሆርማት፣ አዋሽ 7 ኪሎ፣ ወልቂጤ፣ ኮምቦልቻ፣ ወላይታ ሶዶ አንድ እና ዓለም ከተማ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የማዘመን ሥራው ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን አብራርተዋል። ተጨማሪ ደንበኞችን ማስተናገድ የማይችሉ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን በመለየት የአቅም ማሳደግ ሥራዎች በመከናወን ላይ እንደሚገኙ ዳይሬክተሩ አንስተዋል። በአሁኑ ወቅትም በሱሉልታ፣ ኮምቦልቻ ሁለት፣ ለገጣፎ፣ ጅማ እንዲሁም በሚዛን እና ባሌ ሮቤ ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ከ50 እስከ 250 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው ትራንስፎርመሮች እየተተከሉ እንደሚገኙ አብራርተዋል፡፡ የአቅም ማሳደግ ያስፈልጋቸዋል ተብለው በተለዩ ሌሎች የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ተመሳሳይ ሥራዎችን ለማከናወን የትራንስፎርመር ግዥ በሂደት ላይ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ለጥገና አገልግሎት የሚያገለግሉ መለዋወጫ ዕቃዎች፣ የ15 እና 33 ኪሎ ቮልት ብሬከሮች፣ ባትሪዎች እንዲሁም የሆለታ እና ደዴሳ ማከፋፈያ ጣቢያዎችን የቮልቴጅ መዋዥቅ ለማስተካከል የሚረዳ የSVC መለዋወጫ ዕቃዎች እና የከፍተኛ ቮልቴጅ መለዋወጫ ዕቃዎች በተቋሙ መጋዘን መኖራቸውን ገልፃዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ የዕቃ ማንሻ ክሬኖችን ጨምሮ ለኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች አስፈላጊ የሆኑ ሌሎች የመለዋወጫ ዕቃዎችንና መሣሪያዎችን ለማሟላት በግዥ ሂደት ላይ ይገኛሉ፡፡ በማከፋፈያ ጣቢያዎች ያለአግባብ የተቀመጡ ንብረቶችን በሥርዓት ለማስቀመጥ የሚያስችሉ 17 የዕቃ ግምጃ ቤቶች በስምንት ሪጅኖች ላይ እየተሰሩ ሲሆን ከነዚህም መካከል የከምሴ፤ ኮምቦልቻ ሁለት፤ አንፎ ሜዳ፤ ጅጅጋ እና የሐዋሳ ሁለት ማከፋፈያ ጣቢያ የዕቃ ግምጃ ቤቶች መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል። በመጀመሪያው ሩብ ዓመት የአደጋ ጊዜ የከፍተኛ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን (emergency restoration tower) ወደ ሥራ ለማስገባት የባለሙያዎችን አቅም የሚያሳድግ የተግባር ላይ ሥልጠና በመስጠት አሁን ላይ ሥራው ሙሉ በሙሉ በራስ አቅም እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል። ለተቋሙ ፈተና የሆነውን የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ የብረት ምሰሶ ስርቆት ለመከላከልና በግሪድ ሥርዓቱ ላይ የሲስተም መረበሽ እንዳያጋጥም ችግሩ በስፋት የሚስተዋልባቸው ቦታዎችን በመለየት የፍተሻ ሥራዎች በትኩረት እየተከናወኑ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡ ተቋሙ በ13 ሪጅኖች 145 ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ያስተዳድራል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 16 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+1

ጣቢያው ከዕቅድ በላይ ማመንጨቱን ገለፀ …….///…….       የግልገል ጊቤ 1 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት አራት ወራት 440 ነጥብ 3 ጊጋ ዋት ሠዓት ኤሌክትሪክ ማመንጨቱን አስታወቀ፡፡ የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ ንጉሳ እንደገለጹት ጣቢያው 425 ነጥብ 7 ጌጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ ለማመንጨት አቅዶ 440 ነጥብ 3  ጌጋ ዋት ሰዓት በማመንጨት ከዕቅዱ በላይ 3 ነጥብ 42 በመቶ አሳክቷል፡፡ ጣቢያው ያመነጨው ኃይል ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት  ጋር ሲነጻጸር የ24 በመቶ ብልጫ ማሳየቱን አቶ ደሳለኝ   ገልፀዋል፡፡ አስፈላጊ የጥገና ሥራዎች ቀድመው በመከናወናቸው፣  ሁሉም ተርባይኖች በሙሉ አቅማቸው በመስራታቸው  እና ግድቡ በቂ የውሃ በመያዙ አፈፃፀሙን ከፍ ማለቱን አቶ ደሳለኝ አክለው ተናግረዋል ። እንደ ኃላፊው ገለፃ የጣቢያውን ደህንነት ለመጠበቅና  በበጀት ዓመቱ የታቀደውን የኤሌክትሪክ ኃይል ምርት ለማምረት የሚያስችሉ በቂ የጥገና ሥራዎች ተሰርተዋል፡፡ ለበጀት ዓመቱ የታቀደው የኃይል ምርት ለማሳካት ግድቡ በቂ ውሃ መያዙን  ጠቁመዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 16 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+2

የስኳር ህመምን ለመከላከል ጤናማ የኑሮ ዘይቤ መከተል ይገባል .......///........ የስኳር ህመምን ለመከላከል ጤናማ የኑሮ ዘይቤ መከተል እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል  የጤና አገልግሎት ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ክሊኒኩ የዓለም የስኳር ህመም ቀንን አስመልክቶ ከአዲስ ህይወት ጠቅላላ ሆስፒታል ጋር በመተባበር ነፃ የስኳር ህመም እና ተዛማጅ በሽታዎች የቅድመ ልየታ ምርመራ እና የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርቶችን በተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት እና በአዲስ አበባ ዙሪያ ለሚገኙ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች ሰጥቷል። የተቋሙ የጤና አገልግሎት ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ መሠረት ሙሉጌታ  እንደገለፁት የቅድመ ልየታ ምርመራ እና የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርቱ ለድንገተኛ ህልፈት በሚዳርጉ የስኳር እና ሌሎች ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች የሚጠቁ ሠራተኞችን ቁጥር ለመቀነስ ያለመ ነው። በዓለም አቀፍ ደረጃ ለድንገተኛ ህልፈት በሚዳርጉ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች የሚጠቁ የህብረተሰብ ክፍሎች ቁጥር እየጨመረ መጥቷል። የቅድመ ልየታ ምርመራው የስኳር ህመም እና ተዛማጅ በሽታዎችን አስቀድሞ በመለየትና አስፈላጊውን የህክምና ክትትል በማድረግ መከላከል እንዲያስችል መሆኑንም ተናግረዋል። ክሊኒኩ ሠራተኞች ጤንነታቸው ተጠብቆ በሥራቸው ውጤታማ እንዲሆኑ ለማስቻል የተለያዩ ጤና ተኮር መርሃ ግብሮችን ቀርፆ እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝም ነው የተናገሩት። በአዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል ጠቅላላ ሐኪም ዶ/ር ሜሮን ደበበ እንደተናገሩት በዓለም ላይ በስኳር ህመም የሚያዙ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ይገኛል። የስኳር ህመም የሚከሰተው ሰውነት አስፈላጊውን ስኳር በትክክል መጠቀም ሳይችል ሲቀር መሆኑን ያነሱት ዶ/ር ሜሮን ታካሚዎች አስፈላጊውን ህክምና እና እንክብካቤ ካገኙ በተሟላ ጤንነት የመኖር ዕድል እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡ የስኳር ህመም ዓይነት አንድ፣ ዓይነት ሁለትና በእርግዝና ጊዜ የሚከሰት በመባል በሦስት እንደሚከፈል ገልፀው የዓይነት አንድ የስኳር ህመም ቆሽት የተባለው የሰውነት ክፍል የሚያመርተው የኢንሱሊን ንጥረ ቅመም አነስተኛ መሆን አሊያም ማምረት ሲያቆም የሚከሰት እንደሆነ አብራርተዋል፡፡ እንደ ዶ/ር ሜሮን ገለፃ የስኳር ህመም ከተከሰተ በኋላ ተገቢውን ህክምናና ክትትል አለማድረግ ለልብ፣ ለኩላሊት እና ለነርቭ እንዲሁም ለዐይነ ስውርነት ሊያጋልጥ ይችላል፡፡ ከፍተኛ የሆነ የካርቦሃይድሬት መጠን ያላቸውን እና በፋብሪካ የተመረቱ ምግቦችን አብዝቶ መመገብ፣ ቅባትነት ያላቸውን ምግቦች ማዘውተር፣ አልኮል አብዝቶ መጠጣት እና ሲጋራ ማጨስ እንዲሁም የሰውነት ክብደት ደረጃን አለመቆጣጠር ለስኳር በሽታ አጋላጭ መሆናቸውንም ነው የገለፁት፡፡ ሰውነታችን ያለውን የስኳር መጠን በማወቅ፣ የመከላከያ ዘዴዎችን በመጠቀም፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በማድረግ እንዲሁም ጤናማ ሥርዓተ ምግብን በመከተል የስኳር ሕመምን መከላከል እንደሚገባም ዶ/ር ሜሮን አመልክተዋል።                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                        💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 12 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ቀድሞ መከላከል እንደሚያስፈልግ ተገለፀ ……///….. ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ሥርጭት ለመቀነስ የመከላከያ ዘዴዎችን ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጤና አገልግሎት ቢሮ አስታወቀ፡፡ ለአዳማ አንድ እና ሁለት ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሠራተኞች ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን አስመልክቶ የምርመራና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ በመርሐ ግብሩ ላይ ላይ የጤና አገልግሎት ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ መሠረት ሙሉጌታ እንደተናገሩት እንደ ስኳር እና ደም ግፊት ያሉ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ሥርጭት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመሩ ይገኛል፡፡ ከ70 በላይ ለሚሆኑ የሁለቱ ኃይል ማመንጫ ሠራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና የሰጡት የዮያ አጠቃላይ ሆስፒታል የማርኬቲንግ ኃላፊ እና ጠቅላላ ሐኪም ዶክተር ሮሒ ከበደ በየጊዜው እያደገ የመጣውን የስኳር በሽታ ቀድሞ ለመከላከል የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ እና የተመጣጠነ የአመጋገብ ስርዓት መከተል እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ የስኳር በሽታ የተለያዩ ደረጃዎች እንዳሉት የገለፁት ዶክተር ሮሒ ቶሎ ቶሎ የሽንት መምጣት፣ የምግብ ፍላጎት መጨመር እና የዐይን ብዥታ ዋና ዋና የስኳር በሽታ ምልክቶች መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡ የስኳር በሽታ እና የደም ግፊት በሽታዎች ተወራራሽ ባህሪ ያላቸው በመሆናቸው እንደጋንግሪን፣ የልብ ህመም እና የኩላሊት በሽታዎችን ስለሚያስከትሉ አስቀድሞ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል ብለዋል፡፡ የሆስፒታሉ አስተዳደር ኃላፊና የማህበረሰብ ጤና ስፔሻሊስት ንጉሴ ከበደ በበኩላቸው ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ለመከላከል ከአልኮል መጠጥ መራቅ፣ አትክልት ፍራፍሬ አዘወትሮ መመገብ፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማድረግ እና ሲጋራ አለማጨስ ወሳኝ እርምጃዎች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ቀድሞ መከላከል ተመራጭ ዘዴ መሆኑን የገለፁት ኃላፊው በበሽታው የተያዙ ሰዎች ለስኳር በሽታም ሆነ ለደም ግፊት የሚታዘዙ መድሃኒቶችን በአግባቡ መውሰድ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት፡፡ በአዳማ አንድ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በተካሄደው በዚህ መርሐ ግብር ለ52 ሠራተኞች የደም ግፊት እና የስኳር በሽታ ምርመራ ተከናውኗል፡፡                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                        💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 11 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+9

photo content

𝗧𝗵𝗲 𝗘𝗮𝗿𝘁𝗵’𝘀 𝗣𝘂𝗹𝘀𝗲: 𝗛𝗼𝘄 𝗘𝘁𝗵𝗶𝗼𝗽𝗶𝗮 𝗶𝘀 𝘁𝗮𝗽𝗽𝗶𝗻𝗴 𝗶𝗻𝘁𝗼 𝗚𝗲𝗼𝘁𝗵𝗲𝗿𝗺𝗮𝗹 𝗣𝗿𝗼𝗺𝗶𝘀𝗲 What if the key to a sustainable future lies deep beneath our feet? Ethiopia is answering that question with visionary policy and bold investment in geothermal energy turning the Earth’s inner heat into a beacon of clean power. Read more 👇 https://www.linkedin.com/feed/update/urn:li:activity:7397234113319059456 💡 "Clean Energy for a Better Life!" 📌Facebook: https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌Telegram: https://t.me/EEPCommuication 📌X: https://twitter.com/EEPethiopia 📌 LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power-የኢትዮጵያ-ኤሌክትሪክ-ኃይል 📌YouTube: https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌TikTok: https://tiktok.com/@ethio_power 📌 Website: https://www.eep.com.et

ተቋሙ በአደጋ ሰለባ ለሆኑ ቤተሰቦች ድጋፍ እንደሚያደርግ ገለፀ ……..///…..… ከወራት በፊት ወደ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሲጓጓዝ ወድቆ በነበረው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ትራንስፎርመር ህይታቸውን ላጡ እና የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው ሰዎች እና ቤተሰቦቻቸው ድጋፍ ለማድረግ መወሰኑን በተቋሙ የዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡ የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደገለፁት በአዲስ አበባ መውጫ እንጦጦ ፍተሻ አካባቢ ከወራት በፊት በደረሰው አደጋ የአራት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በሁለት ሰዎች ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡ የደረሰውን ጉዳት ተከትሎ የዕቃ አቅራቢ ኩባንያው በወቅቱ  ለአደጋው ሰለባዎች እና ቤተሰቦች የካሳ ክፍያ መፈፀሙን ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልም እንደ ተቋም ማህበራዊ ኃላፊነቱን ከመወጣት አንፃር ለተጎጂ ቤተሰቦች ድጋፍ እንዲያደርግ በተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ ይሁንታ ማግኘቱን ገልፀዋል፡፡ እንደ ኃላፊው ገለፃ የተጎጂ ቤተሰቦችን የኑሮ ሁኔታ እና በሥራ ላይ ያሉ የካሳ ክፍያ ህጎችን ባገናዘበ መልኩ  ተቋሙ ለተጎጂዎች እና ለቤተሰቦቻቸው ከአምስት ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ ወስኗል፡፡ በተጨማሪም ለተጎጂ ቤተሰቦች እና ልጆቻቸው በተቋሙ የሥራ ዕድል እንዲመቻችላቸው እንዲሁም በትምህርት ላይ ያሉ ልጆቻቸው ትምህርታቸውን  እስኪያጠናቅቁ ድረስ  ዘለቄታዊ ድጋፍ ለማድረግ ተቋሙ እንደሚሰራ ጠቁመዋል፡፡   እንደ አቶ ሙላት ገለፃ የተጎጂ ቤተሰቦች ህጋዊ የወራሽነት መብታቸውን የሚያረጋግጥላቸውን የፍርድ ቤት ውሳኔ ለተቋሙ ሲያቀርቡ የተፈቀደው ድጋፍ ተግባራዊ ይደረግላቸዋል፡፡                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                        💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 10 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+7

ተቋሙ የኃይል ሽያጭ እና ስትራቴጂካዊ አጋርነትን የሚያጠናክሩ ሥምምነቶች ተፈራረመ ….…///…… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከቻይናው ጂሲኤል ግሩፕ ሆልዲንግ ሊሚትድ ጋር የኃይል ሽያጭ እና የሀገሪቱን የኃይል ዘርፍ ለማጠናከር በሚያስችሉ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ሥምምነት ተፈረመ፡፡ ሥምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እና የጂሲኤል ግሩፕ ሆልዲንግ ሊሚትድ ምክትል ፕሬዝዳንት ሹቢን ኒው እንዲሁም በኩባንያው የኢትዮጵያ ፒክ ግሮው ሆልዲንግ ሊሚትድ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ዮንግ ያንግ ተፈራርመዋል፡፡ የኃይል ሽያጭ ሥምምነቱ ጂሲኤል ግሩፕ ሆልዲንግ ሊሚትድ ከኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ጋር በመተባበር በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አካባቢ ለሚገነባው የዳታ ማይኒንግ ማዕከል ኃይል ለማቅረብ የሚያስችል መሆኑን በሰነዱ ተመልክቷል፡፡  ሥምምነቱ ከኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ባለፈ በተለያዩ የኃይል ልማት ዘርፎች፣ በኤሌክትሪክ ተሸከርካሪ ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያ ግንባታ እና በአቅም ግንባታ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል መሆኑም ተገልጿል፡፡  ተቋማቱ በሀገሪቱ የኢነርጂ ዘርፍ ላይ ትኩረቱን የሚያደርግ የኃይል ሥርዓት  ምርምር ኢንስቲትዩት ለመመስረት የሚያስችል መሆኑን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ሰነዱ ላይ ተጠቁሟል፡፡ ሥምምነቱ ኩባንያው በታዳሽ ኃይል ማመንጫ ላይ ያለውን የካበተ ልምድ በመጠቀም በሀገሪቱ  በፀሐይ እና በንፋስ የኃይል ልማት ዘርፎች ላይ በጋራ ለመስራት ያስችላል፡፡ በተያያዘም በህዳሴ ግድብ አካባቢ የዳታ ማይኒንግ ለማልማት የሚያስችል ስምምነት በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) እና በጂሲኤል ግሩፕ ሆልዲንግ ሊሚትድ የኢትዮጵያ ፒክ ግሮው ሆልዲንግ ሊሚትድ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ዮንግ ያንግ ተፈርሟል፡፡ በሥምምነቱ ላይ የኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ቦርድ ሰብሳቢ አብርሃም በላይ (ዶ/ር)  ጨምሮ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እንዲሁም የጂሲኤል ግሩፕ ሆልዲንግ ሊሚትድ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                      💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 9 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

ማርበርግ ቫይረስ (Marburg Virus Disease) ….///…. ሠላም ውድ የገጻችን ተከታታዮች እንደምን ሰንብታችኋል፡፡ ከሰሞኑ በጅንካ አካባቢ የተወሰኑ ሰዎችን ያጠቃ በቫይረስ የሚመጣ አደገኛ ወረርሽኝ የተከሰተ ሲሆን መንስዔው የማርበርግ ቫይረስ መሆኑን ተረጋግጧል። እኛም የተቋሙ ሠራተኛ ሥለ ቫይረሱ በቂ ግንዛቤ እንዲኖረው ለማድረግ ከተቋሙ የጤና አገልግሎት ቢሮ ያገኘነውን መረጃ ለአንባቢያን በሚመች መልኩ እንደሚከተለው አቅርበነዋል፤ መልካም ንባብ! የማርበርግ ቫይረስ እንዴት ይተላለፋል? የማርበርግ ቫይረስ ስርጭት የሚጀምረው በቫይረሱ ከተያዙ የሌሊት ወፎች እና አካባቢያቸው ወደ ሰው ሲተላለፍ ነው። በሌሊት ወፍ ሽንት፣ ኩስ እና ምራቅ የተበከሉ ነገሮችም ቫይረሱን ሊያስተላልፉ ይችላሉ። ቫይረሱ አንዴ ሰው ጋር ከደረሰ በኋላ ከሰው ወደ ሰው ይተላለፋል። ቫይረሱ የሚዛመተው ከታመመ ሰው ደም እና የሰውነት ፈሳሽ (ትውከት፣ ሰገራ፣ ሽንት፣ ምራቅ፣ ላብ፣ የጡት ወተት፣ የብልት ፈሳሽ ወዘተ) ጋር በቀጥታ ንክኪ ነው። በቫይረሱ የተያዘ ሰው የተጠቀመባቸውን መርፌ፣ ቁሳቁሶች፣ የተነካኩ ልብሶች ወዘተ ቫይረሱን ያስተላልፋሉ። በግብረ ስጋ ግንኙነትም ይተላለፋል። አስከሬንም መንካት ቫይረሱን ያስተላልፋል። የማርበርግ ቫይረስ ህመም ምልክቶች ምንድን ናቸው? ቫይረሱ ወደሰውነታችን ከገባ በኋላ የሰውነት የበሽታ ተከላካይ ህዋሶችን በማጥቃት በፍጥነት ይራባል፣ ይሰራጫል። የማርበርግ ቫይረስ ህመም የመጀመሪያ ምልክቶች እንደሌሎች ቫይረሶች ሁሉ ጉንፋን መሰል እንደ ከፍተኛ ትኩሳት፣ ራስ ምታት፣ ጉሮሮ መቁሰል፣ የጡንቻና የመገጣጠሚያ ህመም እና ድካም ናቸው።እነዚህ ምልክቶች ከታዩ ከጥቂት ቀናት በኋላ ጠንከር ያለ ማቅለሽለሽ፣ ማስታወክ፣ ተቅማጥ እና የሆድ ህመም የመሳሰሉ የጨጓራና አንጀት ህመም ምልክቶች ያሳያሉ። በመቀጠል በሽታው እየገፋ ከባድ ምልክቶች ይመጣሉ። በቆዳ ላይ፣ አፍና አፍንጫ ወይም የውስጥ የአካል ክፍል ላይ ደም መፍሰስ ያመጣል። ህመሙ እየጸና ሲሄድ የደም ግፊት ከልክ በታች መቀነስ፣ የጉበት፣ ኩላሊት እና ሌሎችም የሰውነት ክፍሎቻችን ይጎዳሉ። ሲብስ የብዝሃ-አካል መድካም ያመጣል። ከቫይረሱ የተረፉ ሰዎች ሙሉ ለሙሉ እስኪያገግሙ ድካም፣ ቁርጥማት እና የስነ ልቦና ጫና ሊሰማቸው ይችላሉ። የማርበርግ ቫይረስ ምርመራዎች የቫይረስ ህመሙን ለማረጋገጥ የማረጋገጫ ምርመራ ያስፈልጋል - የቫይረሱን ዘረመል የሚለዩ ፕ ሲ አር ሞለኩዩላር ምርመራዎች. የታካሚ ናሙናዎች እጅግ በጣም አደገኛ ስለሆኑ እነዚህ ምርመራዎች የሚከናወኑት በብሔራዊ የባዮሴፍቲ ፕሮቶኮሎች መሠረት በልዩ ላቦራቶሪ ማእከሎች ውስጥ ብቻ ነው። ማርበርግ ህክምና አለው? ህክምናው በአብዛኛው የሚያካትተው የሰውነት ፈሳሽ በግሉኮስ መተካት፣ በባለሙያ ክትትል ማድረግ እና ተጓዳኝ ችግሮችን ማከም ላይ ያተኩራል። እንዳስፈላጊነቱ የትኩሳት ማብረጃ እና የህመም ማስታገሻ መስጠት ይገባል። በጣም ደም መፍሰስ ላጋጠማቸው የደም ልገሳ ሊፈልጉ ይችላሉ። ከእነዚህ የህክምና ድጋፎች ባሻገር የሚሰጡ የጸረ-ቫይረስ ህክምናዎች የሉም። እስካሁን ለማርበርግ የተረጋገጠ እና ፍቃድ ያገኘ ጸረ-ቫይረስ መድሃኒት የለም። ማርበርግ ክትባትም አልተገኘለትም። በምርምር ደረጃ ያሉ ጥቂት እጩ የማርበርግ ክትባቶች ጥናት እየተሰራባቸው እና እየበለጸጉ እንደሚገኝ የሚጠቅሱ መረጃዎች አሉ። የማርበርግ ቫይረስ መከላከል መንገዶች በሽታው እንዳይዛመት ዋና መከላከያ መንገዱ በቫይረሱ የተጠረጠረን ሰው መለየት ነው። በበሽታው ከተያዙ ግለሰብ የሰውነት ፈሳሾች ጋር ንክኪን ማስወገድ ይገባል። የታመመን ሰው በቤት ለማከም ከመሞከር ይልቅ ወዲያዉኑ ወደጤና ተቋም ሄዶ እንዲታከም ማድረግ የተሻለ ነው። እያንዳንዱ ሰው እጁን በአልኮል ወይም በሳሙና በደንብ በመታጠብ ንጽህና መጠበቅ አለበት። ከታማሚ ሰው ጋር ንክኪ ያላቸውን አልባሳት፣ እቃዎችና እና ምንጣፎችን በክሎሪን በረኪና ዘፍዝፎ ማጽዳት ይገባል። በጤና ተቋማትም ከመደበኛ ጥንቃቄዎች ባሻገር የኢንፌክሽን መከላከያ እርምጃዎች ካልተተገበሩ የጤና ባለሙያዎች ለከፍተኛ አደጋ ይጋለጣሉ። የተሳለጠ የቅድመ ልየታ ስርአት መዘርጋት ይፈልጋል። ከጓንት እና ማስክ በተጨማሪ አይን እና ፊት መከላከያ ማድረግ ያስፈልጋል። የተለያዩ ኤሮሶል ብናኞችን የሚፈጥሩ የህክምና ፕሮሲጀሮች ሲሰሩ የአየር ወለድ ጥንቃቄዎች (ለአብነትም N95 ማስክ) መተግበር አለባቸው። የመርፌ እና ሌሎች ቆሻሻ አወጋገድም ጥንቃቄ ይፈልጋል። በማህበረሰብ ውስጥ ደህንነቱ የተጠበቀ የቀብር ሥነ ሥርዓቶች መተግበር አለባቸው። በበሽታው ምክንያት የሞተ ሰውን አስከሬን አለመንካት። በባለሙያ በሚገባ በአስከሬን መጠቅለያ እንዲሸፈን በማድረግ ወዲያውኑ በባለሙያ መቅበር ይመከራል። የማርበርግ ቫይረስ ምን ያህል አሳሳቢ ነው? ማርበርግ ቫይረስ ገዳይነቱ ከኮሮና ቫይረስ ጋር ሲወዳደር በጣም ከፍተኛ ቢሆንም ቅሉ በጠንካራ የመከላከል እርምጃዎች መቆጣጠር የሚቻል ህመም ነው። የሚተላለፈው ከሰውነት ፈሳሾች ጋር በቅርበት በመነካካት እንጂ በገበያ፣ በአውቶብስ ወይም በመንገድ ላይ በቅጽበታዊ አልፎ ሂያጅ ግንኙነት አይደለም። አሁናዊ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከሆነ ማርበርግ እንደኮሮና ወይም ጉንፋን በቀጥታ አየር ወለድ ተላላፊ አይደለም። የማርበርግ ተዛማችነት (transmission rate, Ro) መጠነኛ ነው። ለማነጻጸር ያህል በቅርቡ ከነበረው ኮቪድ ቫይረስ ጋር እንኳ ብናወዳድረው የኮቪድ የመዛመት / የስርጭት ምጣኔው ከሁለት እስከ ሶስት እጥፍ ከማርበርግ ይበልጣል። ይህ ማለት አንድ በማርበርግ የተያዘ ሰው በአማካኝ ሌሎች ስንት ሰዎችን ሊበክል ይችላል ተብሎ ሲሰላ ትንሽ ነው ማለት ነው። ሌላው የቫይረሱ ጥሩ ጎኑ ደግሞ አንድ በማርበርግ የተያዘ ሰው ቶሎ አስተላላፊ አይሆንም። ኡደቱ ቀርፋፋ ነው።ማጠቃለያ መልእክት ሁለም የተቋሙ ሰራተኞች እራሳቸውን እና ቤተሰቦቻቸው ከዚህ አስከፊ በሸታ እንድንጠብቅ ፤አስፈላጊ ዉን የመከላከያ እርምጃ እንዲወስድ እንዲሁም የበሽታው ምልክት ሲታይ ቶሎ ወደ ህክምና ተቋማት መሄዱ ያስፈልጋል ። በሀይል ማመንጫ ጣቢያ የሚገኙ ጤና ባለሙያዎች አስፈላጊ ጥንቃቄ በማድረግ ስለበሽታው ምንነት ግንዛቤ እንዲሰጡ በተጨማሪም ከበሽታው ጋር ተመሳሳይ ምልክት ሲኖሩ በፍጥነት ወደ ሚመለከተው ጤና ተቋም እንድትልኩ እናሳስባለን ። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 9 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

ማርበርግ ቫይረስ (Marburg Virus Disease) ….///…. ሠላም ውድ የገጻችን ተከታታዮች እንደምን ሰንብታችኋል፡፡ ከሰሞኑ በጅንካ አካባቢ የተወሰኑ ሰዎችን ያጠቃ በቫይረስ የሚመጣ አደገኛ ወረርሽኝ የተከሰተ ሲሆን መንስዔው የማርበርግ ቫይረስ መሆኑን ተረጋግጧል። እኛም የተቋሙ ሠራተኛ ሥለ ቫይረሱ በቂ ግንዛቤ እንዲኖረው ለማድረግ ከተቋሙ የጤና አገልግሎት ቢሮ ያገኘነውን መረጃ ለአንባቢያን በሚመች መልኩ እንደሚከተለው አቅርበነዋል፤ መልካም ንባብ! የማርበርግ ቫይረስ እንዴት ይተላለፋል? የማርበርግ ቫይረስ ስርጭት የሚጀምረው በቫይረሱ ከተያዙ የሌሊት ወፎች እና አካባቢያቸው ወደ ሰው ሲተላለፍ ነው። በሌሊት ወፍ ሽንት፣ ኩስ እና ምራቅ የተበከሉ ነገሮችም ቫይረሱን ሊያስተላልፉ ይችላሉ። ቫይረሱ አንዴ ሰው ጋር ከደረሰ በኋላ ከሰው ወደ ሰው ይተላለፋል። ቫይረሱ የሚዛመተው ከታመመ ሰው ደም እና የሰውነት ፈሳሽ (ትውከት፣ ሰገራ፣ ሽንት፣ ምራቅ፣ ላብ፣ የጡት ወተት፣ የብልት ፈሳሽ ወዘተ) ጋር በቀጥታ ንክኪ ነው። በቫይረሱ የተያዘ ሰው የተጠቀመባቸውን መርፌ፣ ቁሳቁሶች፣ የተነካኩ ልብሶች ወዘተ ቫይረሱን ያስተላልፋሉ። በግብረ ስጋ ግንኙነትም ይተላለፋል። አስከሬንም መንካት ቫይረሱን ያስተላልፋል። የማርበርግ ቫይረስ ህመም ምልክቶች ምንድን ናቸው? ቫይረሱ ወደሰውነታችን ከገባ በኋላ የሰውነት የበሽታ ተከላካይ ህዋሶችን በማጥቃት በፍጥነት ይራባል፣ ይሰራጫል። የማርበርግ ቫይረስ ህመም የመጀመሪያ ምልክቶች እንደሌሎች ቫይረሶች ሁሉ ጉንፋን መሰል እንደ ከፍተኛ ትኩሳት፣ ራስ ምታት፣ ጉሮሮ መቁሰል፣ የጡንቻና የመገጣጠሚያ ህመም እና ድካም ናቸው።እነዚህ ምልክቶች ከታዩ ከጥቂት ቀናት በኋላ ጠንከር ያለ ማቅለሽለሽ፣ ማስታወክ፣ ተቅማጥ እና የሆድ ህመም የመሳሰሉ የጨጓራና አንጀት ህመም ምልክቶች ያሳያሉ። በመቀጠል በሽታው እየገፋ ከባድ ምልክቶች ይመጣሉ። በቆዳ ላይ፣ አፍና አፍንጫ ወይም የውስጥ የአካል ክፍል ላይ ደም መፍሰስ ያመጣል። ህመሙ እየጸና ሲሄድ የደም ግፊት ከልክ በታች መቀነስ፣ የጉበት፣ ኩላሊት እና ሌሎችም የሰውነት ክፍሎቻችን ይጎዳሉ። ሲብስ የብዝሃ-አካል መድካም ያመጣል። ከቫይረሱ የተረፉ ሰዎች ሙሉ ለሙሉ እስኪያገግሙ ድካም፣ ቁርጥማት እና የስነ ልቦና ጫና ሊሰማቸው ይችላሉ። የማርበርግ ቫይረስ ምርመራዎች የቫይረስ ህመሙን ለማረጋገጥ የማረጋገጫ ምርመራ ያስፈልጋል - የቫይረሱን ዘረመል የሚለዩ ፕ ሲ አር ሞለኩዩላር ምርመራዎች. የታካሚ ናሙናዎች እጅግ በጣም አደገኛ ስለሆኑ እነዚህ ምርመራዎች የሚከናወኑት በብሔራዊ የባዮሴፍቲ ፕሮቶኮሎች መሠረት በልዩ ላቦራቶሪ ማእከሎች ውስጥ ብቻ ነው። ማርበርግ ህክምና አለው? ህክምናው በአብዛኛው የሚያካትተው የሰውነት ፈሳሽ በግሉኮስ መተካት፣ በባለሙያ ክትትል ማድረግ እና ተጓዳኝ ችግሮችን ማከም ላይ ያተኩራል። እንዳስፈላጊነቱ የትኩሳት ማብረጃ እና የህመም ማስታገሻ መስጠት ይገባል። በጣም ደም መፍሰስ ላጋጠማቸው የደም ልገሳ ሊፈልጉ ይችላሉ። ከእነዚህ የህክምና ድጋፎች ባሻገር የሚሰጡ የጸረ-ቫይረስ ህክምናዎች የሉም። እስካሁን ለማርበርግ የተረጋገጠ እና ፍቃድ ያገኘ ጸረ-ቫይረስ መድሃኒት የለም። ማርበርግ ክትባትም አልተገኘለትም። በምርምር ደረጃ ያሉ ጥቂት እጩ የማርበርግ ክትባቶች ጥናት እየተሰራባቸው እና እየበለጸጉ እንደሚገኝ የሚጠቅሱ መረጃዎች አሉ። የማርበርግ ቫይረስ መከላከል መንገዶች በሽታው እንዳይዛመት ዋና መከላከያ መንገዱ በቫይረሱ የተጠረጠረን ሰው መለየት ነው። በበሽታው ከተያዙ ግለሰብ የሰውነት ፈሳሾች ጋር ንክኪን ማስወገድ ይገባል። የታመመን ሰው በቤት ለማከም ከመሞከር ይልቅ ወዲያዉኑ ወደጤና ተቋም ሄዶ እንዲታከም ማድረግ የተሻለ ነው። እያንዳንዱ ሰው እጁን በአልኮል ወይም በሳሙና በደንብ በመታጠብ ንጽህና መጠበቅ አለበት። ከታማሚ ሰው ጋር ንክኪ ያላቸውን አልባሳት፣ እቃዎችና እና ምንጣፎችን በክሎሪን በረኪና ዘፍዝፎ ማጽዳት ይገባል። በጤና ተቋማትም ከመደበኛ ጥንቃቄዎች ባሻገር የኢንፌክሽን መከላከያ እርምጃዎች ካልተተገበሩ የጤና ባለሙያዎች ለከፍተኛ አደጋ ይጋለጣሉ። የተሳለጠ የቅድመ ልየታ ስርአት መዘርጋት ይፈልጋል። ከጓንት እና ማስክ በተጨማሪ አይን እና ፊት መከላከያ ማድረግ ያስፈልጋል። የተለያዩ ኤሮሶል ብናኞችን የሚፈጥሩ የህክምና ፕሮሲጀሮች ሲሰሩ የአየር ወለድ ጥንቃቄዎች (ለአብነትም N95 ማስክ) መተግበር አለባቸው። የመርፌ እና ሌሎች ቆሻሻ አወጋገድም ጥንቃቄ ይፈልጋል። በማህበረሰብ ውስጥ ደህንነቱ የተጠበቀ የቀብር ሥነ ሥርዓቶች መተግበር አለባቸው። በበሽታው ምክንያት የሞተ ሰውን አስከሬን አለመንካት። በባለሙያ በሚገባ በአስከሬን መጠቅለያ እንዲሸፈን በማድረግ ወዲያውኑ በባለሙያ መቅበር ይመከራል። የማርበርግ ቫይረስ ምን ያህል አሳሳቢ ነው? ማርበርግ ቫይረስ ገዳይነቱ ከኮሮና ቫይረስ ጋር ሲወዳደር በጣም ከፍተኛ ቢሆንም ቅሉ በጠንካራ የመከላከል እርምጃዎች መቆጣጠር የሚቻል ህመም ነው። የሚተላለፈው ከሰውነት ፈሳሾች ጋር በቅርበት በመነካካት እንጂ በገበያ፣ በአውቶብስ ወይም በመንገድ ላይ በቅጽበታዊ አልፎ ሂያጅ ግንኙነት አይደለም። አሁናዊ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከሆነ ማርበርግ እንደኮሮና ወይም ጉንፋን በቀጥታ አየር ወለድ ተላላፊ አይደለም። የማርበርግ ተዛማችነት (transmission rate, Ro) መጠነኛ ነው። ለማነጻጸር ያህል በቅርቡ ከነበረው ኮቪድ ቫይረስ ጋር እንኳ ብናወዳድረው የኮቪድ የመዛመት / የስርጭት ምጣኔው ከሁለት እስከ ሶስት እጥፍ ከማርበርግ ይበልጣል። ይህ ማለት አንድ በማርበርግ የተያዘ ሰው በአማካኝ ሌሎች ስንት ሰዎችን ሊበክል ይችላል ተብሎ ሲሰላ ትንሽ ነው ማለት ነው። ሌላው የቫይረሱ ጥሩ ጎኑ ደግሞ አንድ በማርበርግ የተያዘ ሰው ቶሎ አስተላላፊ አይሆንም። ኡደቱ ቀርፋፋ ነው።ማጠቃለያ መልእክት ሁለም የተቋሙ ሰራተኞች እራሳቸውን እና ቤተሰቦቻቸው ከዚህ አስከፊ በሸታ እንድንጠብቅ ፤አስፈላጊ ዉን የመከላከያ እርምጃ እንዲወስድ እንዲሁም የበሽታው ምልክት ሲታይ ቶሎ ወደ ህክምና ተቋማት መሄዱ ያስፈልጋል ። በሀይል ማመንጫ ጣቢያ የሚገኙ ጤና ባለሙያዎች አስፈላጊ ጥንቃቄ በማድረግ ስለበሽታው ምንነት ግንዛቤ እንዲሰጡ በተጨማሪም ከበሽታው ጋር ተመሳሳይ ምልክት ሲኖሩ በፍጥነት ወደ ሚመለከተው ጤና ተቋም እንድትልኩ እናሳስባለን ። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 9 ቀን 2018 ዓ.ም

በጣቢያው የሚከናወነው የማስፋፊያ ሥራ አዲስ ለሚገነባው የማዳበሪያ ፋብሪካ ኃይል ለማቅረብ ይረዳል ‎…......///…...... ‌‎በጎዴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እየተከናወነ የሚገኘው የማስፋፊያ ሥራ በኢትዮጵያ  መንግሥት እና በዳንጎቴ ግሩፕ አማካኝነት ለሚገነባው የማዳበሪያ ፋብሪካ አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ እንደሚረዳ የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ‎ ‎ሥራ አስኪያጁ አቶ ጌዲዮን አበራ እንደገለፁት በማከፋፈያ ጣቢያው እየተከናወነ የሚገኘው የማስፋፊያ ሥራ ተጨማሪ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ኃይል ለማግኘት የሚረዳ ነው። ‎ ‎የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው የማስፋፊያ ሥራ ሲጠናቀቅ በአካባቢው ለሚገነባው የማዳበሪያ ፋብሪካ  ኤሌክትሪክ እንደሚያቀርብ ነው የተናገሩት።  ‎ ‎በጣቢያው ተጨማሪ 25 ሜጋ ቮልት አምፒር የመጫን አቅም ያለው ትራንፎርመር ለማስቀመጥ የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውንም ነው የጠቀሱት። ‎ ‎ጣቢያው ከራይቱ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ኃይል ተቀብሎ በ132 ኪሎ ቮልት ለቀብሪደሃር እንዲሁም በ33 ኪሎ ቮልት ለጎዴ፣ ሀዳዋይ እና  አዳዲሌይ ከተሞች እና በዙሪያው ለሚገኙ አካባቢዎች ኃይል እያቀረበ ይገኛል። ‎ ‎የማስፋፊያ ግንባታው በሪጅኑ አቅም መከናወኑን የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ ይህም አዳዲስ መሐንዲሶች እና የቴክኒክ ባለሙያዎች ልምድና የዕውቀት ሽግግር እንዲያገኙ መልካም አጋጣሚ መፍጠሩን አብራርተዋል። ‎ ‎በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው እየተከናወነ የሚገኘው የማስፋፊያ ሥራ ሲጠናቀቅ የጎዴ ከተማን የኢንቨስትመንት ፍሰት ከማሳደጉም ባሻገር ለኤሌክትሪክ ፍላጎት ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት ያስችላል ብለዋል። ‎ ‎እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያውን የማስፋፊያ ሥራ በአንድ ወር ውስጥ አጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ለማድረግ እየተሰራ ነው።                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                      💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 9 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3