en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 695 subscribers, ranking 8 036 in the Technologies & Applications category and 2 171 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 695 subscribers.

According to the latest data from 03 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 143 over the last 30 days and by -1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 27.84%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.00% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 369 views. Within the first day, a publication typically gains 2 511 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 04 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 695
Subscribers
-124 hours
+47 days
+14330 days
Posts Archive
በአፋር ክልል የወደቁት ሰባት የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች የስርቆት ሙከራ ተደርጎባቸዋል ……..///……. በአፋር ክልል አዋሽ ሰባት ከተማ አቅራቢያ ሚያዚያ 30 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀን 8፡50 አካባቢ በከባድ ንፋስ የወደቁት የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች የስርቆት ሙከራ ተደርጎባቸው እንደነበር  በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ  2 ሪጅን አስታወቀ። በሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጎሳዬ ደምሴ እንዳስታወቁት ወደ ቦታው የተንቀሳቀሰው የጥገና ቡድን የወደቁት የብረት ምሰሶዎች የመፈታታት ሙከራ ተደርጎባቸው እንደነበር በምልከታ አረጋግጠዋል። ምሰሶዎቹ በወደቁበት አካባቢ ብሎኖችን  ለመፍታት ሲጠቀሙባቸው የነበሩ የተለያዩ መፍቻዎች መገኘታቸውን ተናግረዋል። ከአዳማ 2 - አዋሽ ሰባት የተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር የሚሸከሙት የብረት ምሰሶዎች የወደቁት ከባድ ንፋስ ቀላልቅሎ በጣለ ዝናብ ቢሆንም መነሻ ምክንያቱ ግን የስርቆት ሙከራ እንደነበር አቶ ጎሳዬ አስታውቀዋል። የጥገና ባለሙያዎች የወደቁትን የብረት ምሰሶዎች በመፈታታት መልሶ ለማቆም ሥራዎች መጀመራቸውንና በዚህ በየተነሳ የተቋረጠ ኃይል አለመኖሩን ገልፀዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 2 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

ንፋስ ቀላቅሎ የጣለው ዝናብ ለሰባት የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች መውደቅ ምክንያት ሆኗል ……..///……. በአፋር ክልል አዋሽ ሰባት ከተማ አቅራቢያ ትናንት ሚያዚያ 30 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀን 8፡50 አካባቢ ከባድ ንፋስ ቀላቅሎ የጣለው ዝናብ በከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ ጉዳት ማድረሱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ  2 ሪጅን አስታወቀ። በሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጎሳዬ ደምሴ እንዳስታወቁት ንፋሱ ከአዳማ 2 - አዋሽ ሰባት የተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር የሚሸከሙ ሰባት የብረት ምሰሶዎችን ጥሏል፡፡ አሁን ጉዳት በደረሰባቸው የብረት ምሰሶዎች አቅራቢያ ሁለት የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች በተፈጸመባቸው ስርቆት ከሳምንታት በፊት መውደቃቸውን አስታውሰዋል። እንደ ሥራ አስኪጁ ገለጻ አሁን ላይ የወደቁት ሰባት ምሰሶዎች ቀደም ሲል  የተሰረቁትን ሁለት ምሰሶዎች ጠግኖ መስመሩን ኃይል ለመስጠት እየተሰራ ባለበት ወቅት መሆኑ ችግሩን የከፋ ያደርገዋል። የደረሰውን ችግር ስፋት ለመለየት እና የወደቁትን የብረት ምሰሶዎች ለመጠገን እንዲቻል የጥገና ባለሙያዎች ወደ ስፍራው ማቅናታቸውን ገልጸዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 1 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

የሥራ ክፍሎች ለሚያቀርቡት የሕግ ድጋፍና ምክር ጥያቄ ተገቢው ድጋፍ እየተሰጠ ነዉ ……..///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሕግ አገልግሎት መምሪያ በሁሉም የሥራ ዘርፎች ሕግና መመሪያን መሠረት
የሥራ ክፍሎች ለሚያቀርቡት የሕግ ድጋፍና ምክር ጥያቄ ተገቢው ድጋፍ እየተሰጠ ነዉ ……..///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሕግ አገልግሎት መምሪያ በሁሉም የሥራ ዘርፎች ሕግና መመሪያን መሠረት ያደረገ የአሠራር ሥርዓት ለማስፈን ቁርጠኛ መሆኑን የመምሪያው ተወካይ ዳይሬክተር አስታወቁ። ዳይሬክተሯ ወይዘሮ መስከረም በቀለ እንደገለፁት የሥራ ክፍሎች ላቀረቡት 166 የሕግ ድጋፍና ምክር ጥያቄ ተገቢ ድጋፍ ተደርጓል፡፡ መምሪያው የባለሙያዎችን አቅምን በማሳደግ የተቋሙን ጥቅም ለማስጠበቅ፣ ገጽታውን ለመገንባትና መልካም ስሙን ለማጎልበት እንደሚሰራ ዳይሬክተሯ አረጋግጠዋል፡፡ በተቋሙ ውስጥ ንቃተ ህግ እንዲያድግ በማድረግ የህግ ተገዢነትን ማሳደግ ትኩረት የሚሰጠው መሆኑንም ወ/ሮ መስከረም ተናግረዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 1 ቀን 2017 ዓ.ም

#examResult የፈተና ውጤት ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር-4ኛ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር መጋቢት 22 ቀን 2017 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡
+2
#examResult የፈተና ውጤት ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር-4ኛ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር መጋቢት 22 ቀን 2017 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ በዚሁ መሰረት ሚያዚያ 17 ቀን 2017 ዓ.ም የጽሁፍ ፈተና ተፈትናችሁ በመንገድ ትራንስፖርት በሚፈቅደው ህግ እና ደንብ መሰረት 74 እና ከዚያ በላይ ውጤት ያመጣችሁ ለተግባር ፈተና ያለፋችሁ ሲሆን ከተራ ቁጥር 1 እስከ 20 ስማችሁ የተገለጸው ተወዳዳሪዎች ግንቦት 07 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት እና ከተራ ቁጥር 21 እስከ 40 ስማችሁ የተገለጸው ተወዳዳሪዎች ግንቦት 08 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ በሚገኘው ዋናው መ/ቤት ተሽከርካሪ ጥገና አስተዳደር ቢሮ የተግባር ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳውቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የየኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 30 ቀን 2017 ዓ.ም

የሠራተኞችን ጤናና የሥራ ላይ ደህንነት ለማስጠበቅ በትኩረት እየተሰራ ነው ……..///……… በአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የግንባታ ሥራ ላይ የሚሳተፉ ሠራተኞችን ጤናና የሥራ ደህንነት ለመጠበቅ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የፕሮጀክቱ ሥራ ተቋራጭ አስታወቀ፡፡ የተቋራጩ ሲመንስ ጋሜሳ ኩባንያ የአካባቢ፣ የሥራ ቦታ ጤናና ደህንነት አማካሪ አቶ ቻላቸው ሽፈራው እንደተናገሩት በፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ ሠራተኞች የሥራ ደህንነታቸውና ጤንነታቸው ተጠብቆ እንዲሰሩ ለማድረግ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ ከፕሮጀክቱ ባህርይና ከማሽነሪዎች እንቅስቃሴ ጋር ተያይዞ ሠራተኞች ለአደጋ ተጋላጭ እንደሚሆኑ በመገንዘብ የሥራ ስጋት ምርመራ መከናወኑንም አንስተዋል፡፡ በዚህም የጤናና የአደጋ ሥጋቶችን በመለየት አደጋዎችን ቀድሞ ለመከላከል የሚያስችል አሰራሮችን በመዘርጋት ወደ ሥራ መገባቱን ጠቁመዋል፡፡ ስለ አሰራር ሥርዓቱ፣ ስለ አደጋ አጋላጭ ሁኔታዎች እና አደጋን እንዴት መከላከል እንደሚቻል ሥራ ከመጀመራቸው በፊት ለሠራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ እንደሚሠጥ አማካሪው አስረድተዋል፡፡ እንደ ሥራው ባህሪ ለሠራተኞች የአደጋ መከላከያ መሳሪያዎች እንደሚቀርቡና በአተገባበሩ ላይም ክትትል እንደሚደረግ አመልክተዋል፡፡ እንደ አቶ ቻላቸው ገለፃ በፕሮጀክቱ ላይ ለሚያጋጥሙ አደጋዎች አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል የመጀመሪያ እርዳታ መስጫ ማዕከል ከማቋቋም ጀምሮ የጤናና ከፍተኛ አደጋዎች ሲከሰቱ ሠራተኛው የህክምና አገልግሎት የሚያገኝበት አሰራር ተዘርግቷል፡፡ ሠራተኛው የሥራ ላይ ደህንነት ህጎችን ባህል በማድረጉ እስከ አሁን ባለው የግንባታ ሂደት ከቀላል ጉዳቶች ውጭ ምንም አይነት የከፋ ጉዳትና ሞት ሳይከሰት ፕሮጀክቱ ወደ ማጠናቀቂያ ምዕራፍ መድረሱን አረጋግጠዋል፡፡  💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 29 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆነን የተሰጠንን ኃላፊነት እየተወጣን ነው ……..///……. ሴትነት እና የአየር ሁኔታ አስቸጋሪነት ሳይበግረን የተሰጠንን ተቋማዊ ኃላፊነት እየተወጣን ነው ሲሉ በሰሜን ምስራቅ
+4
በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆነን የተሰጠንን ኃላፊነት እየተወጣን ነው ……..///……. ሴትነት እና የአየር ሁኔታ አስቸጋሪነት ሳይበግረን የተሰጠንን ተቋማዊ ኃላፊነት እየተወጣን ነው ሲሉ በሰሜን ምስራቅ ሪጅን 2 የሰመራ ማከፋፈያ ጣቢያ የኦፕሬሽን ሠራተኛ ወ/ሮ ነጃት እሸቱ ተናገሩ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች በማንኛውም የአየር ሁኔታ እና መልክዐ ምድር የሚሰሩ በመሆናቸው ሰመራ ማከፋፈያ ጣቢያ ስመደብ በሙሉ ፍላጎት እና በልበ ሙሉነት ሥራዬን እንደምወጣ ቁርጠኛ ነበርኩ ብለዋል፡፡ አሁን በሚሰሩበት ማከፋፈያ ጣቢያ ሌሎች ሁለት እህቶቼ አብረውኝ ስለሚሰሩ ሴትነት ሳይበግረን በከፍተኛ የሥራ ሞራል እና መተሳሰብ ሥራቸውን እየፈፀሙ ስለመሆኑ ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሰሜን ምስራቅ 2 ሪጅን አስር የአካባቢዉን ተወላጆች አወዳድሮ በማሰልጠን በኦፕሬተርነት እንዲያገለግሉ መድቧል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 28 ቀን 2017 ዓ.ም

የእንጨት ምሰሶው በብረት ምሰሶ ተተክቶ መደበኛ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል .........///....... በስርቆት ምክንያት ወድቆ የነበረውና በእንጨት ምሰሶ ተተክቶ ጊዜያዊ አገልግሎት ሲሠጥ የነበረ
+3
የእንጨት ምሰሶው በብረት ምሰሶ ተተክቶ መደበኛ  አገልግሎት መስጠት ጀምሯል .........///....... በስርቆት ምክንያት ወድቆ የነበረውና በእንጨት ምሰሶ ተተክቶ ጊዜያዊ አገልግሎት ሲሠጥ የነበረው  የኮምቦልቻ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር በብረት ምሰሶ ተተክቶ መደበኛ  አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምስራቅ አንድ ሪጅን አስታወቀ። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ በድሩ አህመድ እንደገለፁት በኮምቦልቻ ከተማ አቅራቢያ በተፈፀመው ዝርፊያ  ምክንያት  ወድቆ  የነበረው  የብረት ምሰሶ ቀድሞ በነበረው ሁኔታ መልሶ እንዲተከል ተደርጓል። በዝርፊያ ምክንያት ኃይል ተቋርጦ የነበረው መስመር  ወደ መደበኛ አገልግሎት እንዲመለስ ላደረጉ የሪጅኑ የጥገና ባለሙያዎች አቶ በድሩ ምሰጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ የኮምቦልቻ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር የብረት ምሰሶ ሚያዝያ 5 ቀን 2017 ዓ.ም  ስርቆት ተፈፀሞበት  እንደነበር መግለፃችን ይታወሳል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 28 ቀን 2017 ዓ.ም

ሪጅኑ በክልሉ መቋቋሙ የክልሉን የኃይል ጥያቄ ለመመለስ አስችሏል ……..///…….. ለአፋር ክልል በቅርበት አገልግሎት እንዲሰጥ የተቋቋመዉ የሰሜን ምስራቅ 2 ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ የክልሉን የኃይል ጥያቄን ለመመለስ ማስቻሉን የሪጅኑ ዳይሬክተር አስታወቁ፡፡ ዳይሬክተሩ አቶ ሀሰን መሀመድ እንዳስታወቁት በክልሉ የሚገኙት የሰመራ፣ አፍዴራ እና ዲቼቶ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ቀደም ሲል ተጠሪነታቸዉ በደሴ ለሚገኘው የሰሜን ምስራቅ 1 ሪጅን ነበር፡፡ ይህም የኤሌክትሪክ መቋረጥ ሲያጋጥም በአፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት አዳጋች እንደነበር አስታዉሰዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምስራቅ 2 ሪጅን በሰመራ እንዲቋቋም መደረጉ የኤሌክትሪክ ብልሽት ሲያጋጥም አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት፣ የኃይል መቆራራጥን ለመቀነስ፣ በክልሉ የሚገኙ የተለያዩ አምራች እና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ሥራዎቻቸዉን እንዲያከናዉኑ ለማድረግ መደላደልን ፈጥሯል ብለዋል፡፡  ከተቋቋመ አንድ ዓመት ከስምንት ወራትን ያስቆጠረዉ ሪጅኑ የክልሉን ሰማንያ በመቶ አካባቢዎችን ተደራሽ በማድረግ የተሻለ የኃይል አቅርቦቱ እንዲኖር ማድረጉን አመልክተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 28 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

በወልቂጤ ማከፋፈያ ጣቢያ በገጠመ ችግር የተነሳ ኃይል በወሊሶና አካባቢው የኃይል መቋረጥ አጋጥሟል ………///……… ከወልቂጤ ማከፋፈያ ጣቢያ በሚወጣ የስርጭት መስመር ላይ ባጋጠመ ችግር የተነሳ የጣቢያ
በወልቂጤ ማከፋፈያ ጣቢያ በገጠመ ችግር የተነሳ ኃይል በወሊሶና አካባቢው የኃይል መቋረጥ አጋጥሟል ………///……… ከወልቂጤ ማከፋፈያ ጣቢያ በሚወጣ የስርጭት መስመር ላይ ባጋጠመ ችግር የተነሳ የጣቢያው ባለ 230/66/33 የፓወር ትራንስፎርመር ላይ ችግር ተከስቷል፡፡ በዚህ የተነሳ ከወልቂጤ በ33 ኪሎ ቮልት ኃይል የሚያገኙት አገና፣ ጉንችሬ፣ ጦላይ፣ እምድብር እና ዘቢዳር ቢራ ፋብሪካ እንዲሁም በ66 ኪሎ ቮልት ኃይል የሚያገኙት ወሊሶና አካባቢው፣ ቱሉቦሎና አካባቢው፣ ጦላይና  አካባቢ ኃይል ተቋርጣል፡፡ በትራንስፎርመሩ ላይ የገጠመውን ችግር ለመለየት እና ለችግሩን መፍትሔ ለመስጠት የማዕከላዊ 3 ሪጅን የጥገና ባለሙያዎች ወደ ሥፍራው ተንቀሳቅሰዋል፡፡ በመሆኑም ችግሩ እስኪቀረፍ ድረስ ሌሎች አማራጮችን በመጠቀም በትዕግስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 24 ቀን 2017 ዓ.ም

የኤሌክትሪክ ኃይል ለክልሉ ዕድገት መነቃቃት መሰረት ጥሏል ……….///……… ኤሌክትሪክ ለአፋር ክልል ኢኮኖሚዊ ዕድገትና ማህበራዊ መነቃቃት መሰረት መጣሉን የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ ተናገሩ፡፡ የቢሮ ኃላፊዋ ወ/ሮ አይሻ መሀመድ እንደተናገሩት የኤሌክትሪክ ኃይል ለሰው ልጅ ከሚያስፈልጉ መሰረታዊ ግብዓቶች ውስጥ ወሳኝ በመሆኑ አፋሮች እንደ ዓይን ብሌናቸው የሚያዩት ነው፡፡   ባለሀብቶች በክልሉ ኢንቨስት ለማድረግ በቅድሚያ የሚጠይቁት የኃይል አቅርቦትን በመሆኑ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በክልሉ እያከናወነ ያለው የኃይል መሰረተ ልማት ሥራ ለባለሃብቶች መተማመኛቸው መሆኑን አንስተዋል፡፡ በክልሉ ያለው ሰላም የኤሌክትሪክ ኃይል መሰረተ ልማቶችን ደኅንነት ለማስጠበቅ ትልቅ ድርሻ ያለው በመሆኑ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅርበት እንደሚሰሩ የቢሮ ኃላፊዋ አረጋግጠዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በክልሉ ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል ባለሀብቶችን እየሳበ መሆኑን የገለፁት ወ/ሮ አይሻ  በቀጣይ እያደገ የሚሄደውን የኃይል ፍላጎቱ ለማሟላት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ፈጣን ምላሽ እንዲሚሰጥ እምነታቸውን ገልፀዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 25 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

የማከፋፈያ ጣቢያውን ብሬከሮች ወደ ጂ አይ ኤስ ብሬከሮች የመቀየር ሥራ እየተከናወነ ነው …….///…….. በሻሸመኔ ባለ 132/33/15 ኪሎ ቮልት ማከፋፊያ ጣቢያ ረጅም ዓመት ያገለገሉ መቆጣጠሪያዎችን በዘመናዊ የጂ አይ ኤስ መቆጣጠሪያዎች የማዘመን ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለፁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ምሕረቱ ግዛው እንደገለጹት ጣቢያው ከ1966 ዓ.ም. ጀምሮ አገልግሎት ሲሰጡ የቆዩ መቆጣጠሪያዎችን በዘመናዊ የጂ አይ ኤስ ብሬከሮች በመቀየር የኃይል መቆራረጥን ለመቀነስ እየተሰራ ነው። ማከፋፈያ ጣቢያው ካለው 60 ሜጋ ዋት የመጫን አቅም በአሁኑ ወቅት 50 ሜጋ ዋት እየጫነ መሆኑን የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ  በጣቢያው የተጀመረው የ15 ኪሎ ቮልት መቆጣጠሪያዎችን የማዘመን ሥራም ወደመጠናቀቁ ተቃርቧል ብለዋል። የጣቢያ የኦፕሬሽን ሰራተኛ አቶ ሰጠኝ ተስፋዬ በበኩላቸው የቆዩ መቆጣጠሪያዎችን ዘመኑ በደረሰበት የመቆጣጠሪያ ቴክኖሎጂ መቀየራቸው ከኃይል መቋረጥ ጋር ተያይዘው የሚፈጠሩ ችግሮችን እንደሚፈታ ተናግረዋል። መቆጣጠሪያዎችን የማዘመንና የመቀየር ሥራው በተቋሙ ሠራተኞች መከናወኑ የሠራተኞችን ክህሎትና ዕውቀት በማሳደግና ወጪን በመቀነስ ረገድ ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖረው ገልፀዋል። የሻሸመኔ ማከፋፈያ ጣቢያ 50 እና 25 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው ሁለት ፓወር ትራንስፎርመሮች፣ አራት ገቢ መስመሮች እንዲሁም ዘጠኝ ባለ 15 እና ሦስት ባለ 33 ወጭ መስመሮች አሉት፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው ለመቱ፣ ለዋርካ፣ ለሮጲ፣ ለወንዶ ገነት፣ ለአርሲ ነገሌ፣ ለኮፈሌ ፣ ለሻሸመኔ ከተማ እና አካባቢዉ የኤሌክትሪክ አቅርቦት እየሰጠ ይገኛል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የየኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 25 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

የጣቢያውን አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች በትኩረት ሊሰሩ ይገባል .......///….... የአላማጣ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ የጣቢያው የኦፕሬሽንና ጥገና ባለሙያ ገለፁ። ባለሙያው አቶ ሙሉጌታ አሰፋ እንደገለፁት ጣቢያው ለረጅም ዓመታት አገልግሎት እየሰጠ የቆዬ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት በኦፕሬሽን እና ጥገና ሥራዎች ላይ አሉታዊ ጫና እየተፈጠረ ይገኛል። የጣቢያው የመቆጣጠሪያ ሥርዓት የአገልግሎት ዘመኑን ያጠናቀቀ በመሆኑ ለተደጋጋሚ የኃይል መቆራረጥና ብልሽት እየተዳረገ እንደሚገኝም ነው ያነሱት። እንደ ባለሙያው ገለፃ የጣቢያውን አቅም ለማሳደግና ደህንነቱን አስተማማኝ አድርጎ ለማስቀጠል የዘመናዊ ስዊችጊር ቅየራ ሥራዎች ሊሰሩ ይገባል። እስከ 140 ሜጋ ዋት ድረስ ኃይል የመሸከም አቅም ያለው የአላማጣ ማከፋፈያ ጣቢያ ለሰሜንና ሰሜን ምስራቅ አካባቢዎች ኤሌክትሪክ በማቅረብ በኩል ድርሻው የጎላ ነው። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ሁለት ባለ 63 ሜጋ ቮልት አምፔር  አውቶ ትራንስፎርመሮች እና ሁለት ባለ 20 ሜጋ ቮልት አምፔር እንዲሁም አንድ ባለ 25 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው አምስት ትራንስፎርመሮች አሉት። ጣቢያው ከባህር ዳር ኃይል ተቀብሎ በ230 ኪሎ ቮልት ለኮምቦልቻ፣ መኾኒና አሸጎዳ እንዲሁም በ66 ኪሎ ቮልት ለማይጨው፣ ሰቆጣና ላሊበላ ኤሌክትሪክ እየሰጠ ይገኛል፡፡ ባለሙያው እንደገለፁት ጣቢያው ካሉት አራት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች መካከል አንዱ ብቻ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኝ ሲሆን ቀሪዎቹ ሦስት መስመሮች ለኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች ዝግጁ ተደርገው ተቀምጠዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የየኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 24 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

በማከፋፈያ ጣቢያዉ የብሬከር ቅየራ እየተከናወነ ነው …….///……. የይርጋለም ቁጥር 1 ባለ 132 ኪሎ ቮልት የማከፋፊያ ጣቢያን ለማዘመንና የኦፕሬሽን ሥራውን ለማቀላጠፍ የሚያስችል የመቆጣጠሪያ ወይም ብሬከር ቅየራ እየተከናወነ መሆኑን የጣቢያው ኃላፊ ገለፁ፡፡ ኃላፊው አቶ ፈይሰል ዋቤ እንደገለፁት የደንበኞችን ፍላጎት ለማሟላት የማከፋፈያ ጣቢያዉን አቅም የማሳደግና የማሻሻል እንዲሁም መቆጣጠሪያዎችን የማዘመን ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያዉ ሦስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት እና ሦስት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ሲኖሩት ለይርጋለም ከተማና አካባቢው፣ ለይርጋለም ችፑድ ፋብሪካ፣ ለአፖስቶ፣ ለሀንጠጤ፣ ለለኩ ከተማ፣ ሀገረ ሰላም፣ በንሳ ዳዬ እና በዙሪያቸው ላሉ አካባቢዎች ኃይል እያቀረበ መሆኑን ኃላፊው ገልፀዋል፡፡ በደቡብ አንድ ሪጅን የማከፋፊያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና ክፍል ሥራ አስኪያጅ አቶ ያለው አማረ በበኩላቸው የብሬከር ቅየራው ኃይል ሳይቋረጥ እየተከናወነ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ቀደም ሲል በሪጅኑ በሚገኙት በሻኪሶና ሻሸመኔ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ባለ 33 ኪሎ ቮልት መቆጣጠሪያዎች ቅየራ መከናወኑን አስታውሰው በአሁኑ ወቅት በዲላ፣ ሻሸመኔና በይርጋለም ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያዎች ተመሳሳይ ሥራ እየተከናወነ እንደሆነ አብራርተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 24 ቀን 2017 ዓ.ም