ru
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 572 подписчиков, занимая 8 384 место в категории Технологии и приложения и 2 165 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 572 подписчиков.

Согласно последним данным от 23 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 0, а за последние 24 часа — -2, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 25.89%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 15.48% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 026 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 408 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 9.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
EEP Communication

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 24 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.

15 572
Подписчики
-224 часа
-37 дней
Нет данных30 день
Архив постов
ተቋማቱ በጋራ ለመስራት በሚያስችሏቸው የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሄዱ .......///.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት በጋራ መስራት በሚችሉባቸው የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡ ምክክሩ ሁለቱ ተቋማት ከዚህ ቀደም በጋራ ያከናወኗቸውን ሥራዎች ለመገምገምና ቀጣይ የሥራ ግንኙነቶች በሚጠናከሩበት ሁኔታ ላይ ያለመ ነው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በውይይቱ ወቅት እንደተናገሩት ተቋሙ የኃይል ልማት ዘርፉን ለማሳደግ የሚያስችሉ የተለያዩ ሜጋ ፕሮጀክቶችን በመገንባት ላይ ይገኛል። ተቋሙ በሚያከናውናቸው የኃይል መሠረተ ልማት ግንባታዎች ላይ የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት አሻራ የጎላ መሆኑንም አንስተዋል። እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ ተቋማቱ የዘረጉትን የኢ.አር.ፒ ቴክኖሎጂ በመጠቀም የመረጃ ልውውጥ ሥርዓታቸውን ማሳለጥ ይገባቸዋል። ከዚህ ቀደም ከአሰራር ሥርዓትና አገልግሎት አሰጣጥ ጋር ተያይዘው ይነሱ የነበሩ ችግሮች ዳግም እንዳይከሰቱ ለማድረግ ከሁለቱ ተቋማት የተውጣጣ ቡድን በማዋቀር መስራት እንደሚገባም አመልክተዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጀነሬሽን ቢዝነስ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወ/ኪዳን በበኩላቸው የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት አሁን ለደረሰበት የግንባታ ምዕራፍ የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት አስተዋፅዖ ከፍተኛ ነው ብለዋል። በኃይል ልማት ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ ሜጋ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት ተቋሙ ቅድሚያ ሰጥቶ እገዛ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል። ተቋማቱ በፋይናንስ የመረጃ ልውውጥ ላይ ያላቸውን የአሰራር ቅልጥፍና ማዘመን እንደሚጠበቅባቸው የጠቀሱት ደግሞ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ፋይናንስና ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ ናቸው። በኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት የሺፒንግ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ካፒቴን ወንድወሰን ካሳ የተቋማቸውን አሁናዊ ገፅታ አስመልክተው ገለፃ አድርገዋል። ተቋማቸው በሀገራዊ የኃይል መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ላይ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ በመሆኑ ኩራት እንደሚሰማቸውም ነው የተናገሩት። ከኮንቴነር ኪራይ፣ ከደረቅ ወደብ አጠቃቀም እና ከፋይናንስ እንዲሁም ከአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት ጋር ተያይዘው ለሚነሱ ችግሮች መፍትሔ ለመስጠት ተቋማቱ ከመቼውም ጊዜ በላይ ተቀራርበው መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል። በኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የጭነትና አስተላላፊነት ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሻረው ከበደ በበኩላቸው ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት የግንባታ ዕቃዎች በወቅቱ የሚቀርቡ ከሆነ የማጓጓዝ ሥራዎችን በፍጥነት ለማከናወን ተቋማቸው ዝግጁ መሆኑን ገልፀዋል። በውይይቱ ላይ የሁለቱ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

photo content
+9

የማመንጫ ጣቢያውን ደህንነት ለማስጠበቅ ያለመ ውይይት እየተካሄደ ነው ……..///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመልካ ዋከና የውሃ የኃይል ማመንጫ ጣቢያን ደህንነት ማስጠበቅ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከኦሮሚያ ክልል እና ከምዕራብ አርሲ የዞን የመስተዳድር አካላት  ጋር በሻሸመኔ ከተማ ውይይት ማካሄድ ጀምሯል። በተቋሙ የኮርፖሬት ገቨርናንስ እና ኮምፒሊያንስ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ደጉማ ነዳ  እንደገለጹት ውይይቱ በግድቡ ጥብቅ ወሰን ውስጥ በሚከናወን እርሻ  ምክንያት በግድቡ ላይ እየደረሰ ባለው ጉዳት፣ ከግድብ ውሃ አጠቃቀም፣ ከይዞታ ማረጋገጫ እና ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዞ የሚነሱ ችግሮችን ለመፍታት ያለመ ነው። የማመንጫ ጣቢያው የይዞታ ማረጋገጫ ባለማግኘቱ በበጋ ወራት የጣቢያውን ጥብቅ ወሰን በማለፍ እርሻዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመዋል። ይህም ጣቢያው በደለል እንዲሞላ ከማድረጉም በላይ የግብርና ተረፈ ምረቱ ወደ ጣቢያው በመግባት ውሃ ወደ ተርባይኖቹ እንዳያልፍ በማድረግ የጣቢያውን የኦፕሬሽን ሥራ እና ደህንነት ላይ ስጋት መደቀኑን ተናግረዋል። ተቋሙ በጣቢያው ላይ እያጋጠሙት ያሉ ችግሮችን ለመፍታት ከአካባቢው የመስተዳድር አካላት እና ማህበረሰቡ ጋር ተቀራርቦ ለመስራት ዝግጁ መሆኑንም አብራርተዋል። ከዚሁ በተጨማሪም ተቋሙ እያከናወናቸው ባሉ የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎች እና ለአካባቢው ማህበረሰብ  በሠራቸው የልማት ሥራዎች ዙሪያ ውይይት እየተደረገ ነው። በውይይቱ ላይ የተቋሙና የጣቢያው ኃላፊዎችን ጨምሮ የኦሮሚያ የገጠር ልማት ክላስተር፣ የዞንና ወረዳ መስተዳድር አካላት እየተሳተፉ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 25 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ባለፉት ስድስት ወራት በሰባት ማከፋፈያ ጣቢያዎች የመቆጣጠሪያ ቅየራ ተከናወኗል …....///….…. በ2017 የመጀመሪያ ግማሽ በጀት ዓመት በሰባት ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ዘመናዊ ስዊች ጊር ወይም መቆጣጠሪያ የመቀየር ሥራ መከናወኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ገለጸ፡፡ በዘርፉ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ እንደገለፁት በ2017 በጀት ዓመት የ37 ማከፋፈያ ጣቢያዎች የመቆጣጠሪያ ሥርዓት በዘመናዊ የመቆጣጠሪያ ለመቀየር ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት የሰባት ማከፋፈያ ጣቢያዎችን የባለ 15 እና 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች በዘመናዊ መቆጣጠሪያዎች የመቀየር ሥራ ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ ሲሆን በ21 ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ደግሞ የሲቪል ሥራና የዕቃ ማጓጓዝ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በአሸጎዳ፣ በድሬድዋ ሦስት፣ በጅጅጋ፣ በባህርዳር ሁለት፣ በዲላ እና በጋሸና ማከፋፈያ ጣቢያዎች በግማሽ በጀት ዓመቱ የቅየራ ሥራው መጠናቀቁን ተናግረዋል፡፡ የሚቀየረው ስዊች ጊር በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ያጋጥም የነበረውን የጥገና ስራ በማስቀረት እና የኃይል መቆራረጥን በመቀነስ የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝነት እንደሚያሳድግ ገልጸዋል፡፡ የመቆጣጠሪያ ብሬከሩ ሙሉ በሙሉ ዝግ ሆኖ የሚሰራ በመሆኑ ከአቧራ፣ ከእርጥበት ብሎም ከውጫዊ አየር ተጠብቆ ረጅም ጊዜ እንደሚያገለግል ገልጸው ከአሁን ቀደም ኋላ ቀር በሆነ ቴክኖሎጂ ሲሰራበት የነበረውን አሰራር በማስወገድ የማከፋፈያ ጣቢያዎችን አቅም የሚያሳድግ እና አሰራሩን የሚያዘምን ነው ብለዋል፡፡ በተቋሙ የማከፋፈያ ጣቢያዎች የጥገና ባለሙያና የማዘመን ሥራው አስተባባሪ አቶ ሚሊዮን በለጠ በበኩላቸው የስዊች ጊር ቅየራው በጊዜያዊ ሌሎች የመቆጣጠሪያ ሥርዓት በመዘርጋት ኃይል ሳይቋረጥ እየተከናወነ መሆኑንም አብራርተዋል፡፡ የቅየራ ስራው በተቋሙ ባለሙያዎች መከናወኑን የገለጹት አቶ ሚሊዮን ይህም የባለሙያዎችን አቅም ከማሳደግ በተጨማሪ ለውጭ ኩባንያ ይከፈል የነበረውን ወጭ ከ50 በመቶ በላይ ያስቀረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አስተባባሪው እንዳሉት የዘመናዊ መቆጣጠሪ ብሬከሩን ከሚያቀርበው ኩባንያ ጋር በመተባበር የባለሙያዎች አቅም ግንባታ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል፡፡ ብሬከሮች በሚቀየሩባቸው ማከፋፈያ ጣቢዎች አካባቢ የክሬን አገልግሎት የሚሰጡ ድጅቶች አለመኖር፣ ለሲቪል ግንባታ የሚያገለግሉ ግብዓቶች እጥረት እና ዕቃዎችን ወደ ጣቢያ ለማድረስ የመንገድ ችግር በሥራው ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳደራቸውን ገልጸዋል፡፡ ተቋሙ በሦስት ምዕራፎች በ75 ማከፋፈያ ጣቢዎች ላይ የማዘመን ሥራ ለማከናወን አቅዶ እየሰራ ሲሆን እስከ አሁን የ25 ማከፋፈያ ጣቢዎች ሥራ ተጠናቋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 25 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

የፕሮጀክቱ ግንባታ 78 ነጥብ 2 በመቶ ደርሷል ……...///………. የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታ 78 ነጥብ 2 መድረሱን የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ገለጹ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ፈቃዱ አብርሃም እንደገለጹት 100 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከዴንማርክ መንግሥት በተገኘ ብድር እና ዕርዳታ ከ146 ሚሊዮን ዩሮ በላይ በጀት ግንባታው የተጀመረው ታህሳስ 8 ቀን 2013 ዓ.ም ነው። ፕሮጀክቱ እያንዳንዳቸው 3 ነጥብ 46 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ የማመንጨት አቅም ያላቸው 29 የንፋስ ተርባይኖች ሲኖሩት የ22 ተርባይኖች ተከላ መጠናቀቁንና የ20ዎቹ ተርባይኖች የቅድመ ፍተሻ ሥራ መከናወኑን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የኃይል ማመንጫው የባለ 230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ የሲቪል ሥራ ከ95 በመቶ በላይ እንዲሁም የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራ ከ60 በመቶ ደርሷል። እያንዳንዱን ተርባይን የሚያገናኙ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች በሥራ ተቋራጩ ምክንያት መዘግየት አፈጻጸሙም 54 በመቶ ላይ እንደሚገኝና አጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም 78 ነጥብ 2 መድረሱን አስታውቀዋል። የግንባታው ሥራ ተቋራጭ ሲመንስ ጋሜሳ ሪኒዌብል ኢነርጂ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ኤድዋርዶ ጎንዛሌዝ እንደገለጹት ኩባንያቸው በኢትዮጵያ መሰል ፕሮጀክት ሲገነባ የመጀመሪያው ቢሆንም በሰሜን አፍሪካ ጨምሮ በበርካታ የዓለም ሀገራት የንፋስ ኃይል ማመንጫዎችን በመገንባት ልምድ እንዳለው ገልጸዋል፡፡ አሁን ላይ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም መልካም በሚባል ደረጃ ላይ የሚገኝ መሆኑንና ቀሪ ሥራዎችን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ትኩረት ሰጥተው እየሰሩ መሆኑንም አስረድተዋል። የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች የአፈፃፀም ክትትልና ቁጥጥር ተወካይ ሥራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ሰሎሞን ተረፈ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ የንፋስ ኃይል ማመንጫውን 29 የንፋስ ማማዎች ተከላ ፣ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፍያ ጣቢያ፣ 38 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የባለ 33 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ሥራዎችን ያጠቃልላል፡፡ ከእያንዳንዱ የንፋስ ማማዎች ኃይል ተቀብሎ ወደ ማከፋፈያ ጣቢያ የሚያስገባው የባለ 33 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር ከሚዘረጋው 38 ኪሎ ሜትር ውስጥ የ25 ኪሎ ሜትሩ ሥራ መጠናቀቁን ተወካይ ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል፡፡ ያለቁ የንፋስ ማማዎችን በማገናኘት በአጭር ጊዜ ኃይል በማምረት ወደ ግሪድ ለማስገባት የማጠናቀቅያ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 24 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

በኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀሙ የስርቆት ወንጀሎች እየቀነሱ ነው ……….///….…. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ የሚፈፀሙ የስርቆት ወንጀሎችን ለመከላከል በተሰራው ሥራ ውጤት እየተገኘ መሆኑን በተቋሙ የኃይል መሰረተ ልማት ደህንነት፣ ክትትልና ቁጥጥር ቢሮ ገለጸ፡፡ የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ እንደገለጹት በኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ የሚፈጸሙ የስርቆት ወንጀሎች በሀገር ደረጃ ለመከላከል በጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅጣጫ ተሰጥቶበታል፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎትም ለክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች እና ለሚመለከታቸው የፀጥታ ዘርፍ ተቋማት ኃላፊዎች በኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ እየተፈፀመ ያለው ስርቆት የሀገሪቱ ብሔራዊ የደህንነት አጀንዳ መሆኑን የማስገንዘብ ሥራ መስራቱን ተናግረዋል። ተደጋጋሚ የስርቆት ወንጀል የሚፈፀምባቸው እና ትኩረት የሚሹ  21 መስመሮች መለየታቸውንና ተቋሙ ከብሔራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር ጠንካራ የመረጃ ልውውጥ ስርዓት መዘርጋቱን ገልፀዋል፡፡ የሥራ ክፍሉ ባለፉት ስድስት ወራት ከተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ጋር በመሆን በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ከሚገኙ የክልል፣ ዞንና ወረዳ አመራሮች እንዲሁም የሃይማኖት አባቶች፣ የኀገር ሽማግሌዎችና አባገዳዎች በኃይል ማስተላለፊያ መሰረተ ልማቶች ስርቆት ዙሪያ  ሰባት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮችን ማካሄዱን ጠቅሰዋል፡፡ እንደ አቶ ዋለ ገለፃ በውይይት መድረኮቹ በተሰራው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ የቁጥጥር ሥርዓቱ ከመጠናከሩም በላይ የየአካባቢው ማህበረሰብ በመሰረተ ልማቶቹ ላይ ያለው የእኔነት ስሜት እያደገ መጥቷል፡፡ ባለፉት ስድስት ወራት በኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ የተፈፀመው ስርቆት ካለፉት ዓመታት ተመሳሳይ ጊዜያት ጋር ሲነፃፀር እየቀነሰ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡ በቀጣይም የታየውን መሻሻል አጠናክሮ ለማስቀጠል እና የየአካባቢው ማህበረሰብ የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች በባለቤትነት ስሜት እንዲጠብቅ የሚያግዙ ስልቶች መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል፡፡ የሥራ ክፍሉ አደረጃጀቱን በማጠናከር በሁሉም ቋንቋዎች የግንዛቤ ፈጠራ ሥራውን አጠናክሮ ለማስቀጠል እየሰራ ነው ያሉት አቶ ዋለ ከረጅም ጊዜ ዕቅድ አንጻር የጎረቤት ሀገራትን ልምድ ታሳቢ በማድረግ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ለመተግበር እየሰራ መሆኑንም አስገንዝበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 24 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ለጣቢያ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች በእሳት አደጋ መከላከልና መቆጣጠር ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ ……….///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከማዕከላዊ 3 ሪጅን ለተውጣጡ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃላፊዎችና ባለሙያዎች በእሳት አደጋ መከላከልና መቆጣጠር ዙሪያ ስልጠና መስጠቱን የሪጅኑ ጥገናና ኦፕሬሽን ኃላፊ ገለፁ። ኃላፊው አቶ ታደሰ ገብሬ እንደተናገሩት ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ጋር በመተባበር ከሪጅኑ ለተውጣጡ ከ30 በላይ የጣቢያ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች በመሠረታዊ የእሳት እና ድንገተኛ አደጋ መከላከል ዙሪያ ለሁለተኛ ጊዜ ስልጠና ተሰጥቷል። ሥልጠናው በተግባርና በንድፈ ሀሳብ ተደግፎ መሰጠቱን የጠቆሙት ኃላፊው የሥልጠናው ዓላማ በሪጅኑ ውስጥ ባሉ ማከፋፈያ እና የማስተላለፊያ መስመር ጣቢያዎች ላይ በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ የሚከሰቱ የእሳት አደጋዎችን አስቀድሞ ለመከላከል ያለመ ነው ብለዋል። የስልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው የእሳት አደጋን አስቀድሞ መከላከል በሚቻልባቸውና ሲከሰትም መተግበር ስላለባቸው የደህንነት ማስጠበቂያ ሥራዎች ዙሪያ በቂ ግንዛቤ እንደተፈጠረላቸውም ተናግረዋል። ስልጠናው ሪጅኖች ከሚያከናውኗቸው ሥራዎች ጋር በተያያዘ ሊያጋጥሙ የሚችሉ አደጋዎችን ለመከላከል አስፈላጊ በመሆኑ በቀጣይ በሁሉም የኃይል ማመንጫና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለሚገኙ ባለሙያዎች እንዲሰጥ ጠይቀዋል፡፡   ለሰልጣኞች የምስክር ወረቀት የሰጡት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የስልጠና ማዕከል ኃላፊ ኮማንደር አለማየሁ ጦፋ ሰልጣኞች ባገኙት እውቀት የሥራ ቦታቸውን ደህንነት በማስጠበቅ ድንገተኛ የእሳት አደጋዎች ሊከላከሉ እንደሚገባ አብራርተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

photo content

በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች በተከናወኑ የጥገና ሥራዎች የኃይል ምርት አፈጻጸምን ማሳደግ ተችሏል …….///……... በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ላይ በራስ አቅም የተከናወኑ የጥገና ሥራዎች የግማሽ በጀት ዓመቱን የኃይል ምርት አፈፃፀም ማሳደጋቸውን የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የዕቅድ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ጥሩወርቅ ሽፈራው እንደገለጹት በ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት በተለያዩ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ላይ በርካታ የጥገና ሥራዎች በራስ አቅም ተከናውነዋል፡፡ በተከዜ እና በጢስ አባይ 2 ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች በብልሽት ምክንያት የቆሙ ተርባይኖችን እንዲሁም በግልገል ጊቤ 2 ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የኖዝል ጫፍ ጥገና በራስ አቅም በማከናወን የጣቢያዎቹን የኃይል ምርት ማሻሻል መቻሉን ጠቁመዋል። እንደ ሥራ አስኪያጇ ገለፃ የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎች ላይ ተጽዕኖ በማያሳድር እና የግድቦችን ደህንነት ለመጠበቅ እንዲያስችል የሞሉ ግድቦችን ውሃ የማስተንፈስ እንዲሁም የኃይል ማመንጨት ሂደቱን የሚያስተጓጉሉ የተንሳፋፊ ሳሮችን የመከላከል ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ ለኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የመለዋወጫ ዕቃዎችን ለማቅረብ ከቮይት ሃይድሮ፣ ኤመርሰን ኮንትሮል እና ዶንግፋንግ ኤሌክትሪክ እንዲሁም ዲራክ አውቶሜሽን ከተባሉ የውጭና የሀገር ውስጥ ኩባንያዎች ጋር የማዕቀፍ ግዥ ውል በመፈራረም ሲሰራ መቆየቱን አስታውሰዋል፡፡ ከጥገና ሥራዎቹ ጎን ለጎን የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን የአሰራር ሥርዓት ለማዘመን የሚያስችሉ ተግባራት መከናወናቸውንም ነው ወ/ሮ ጥሩወርቅ የተናገሩት፡፡ በጣቢያዎቹ የጥገና አስተዳደርን ለማዘመን የሚያግዙ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ጨምሮ የተሽከርካሪ አስተዳደር፣ የሥራ ፍሰትን የመቆጣጠር እና የጤናና ደህንነት አሰራሮች ተግባራዊ መደረጋቸው ጠቅሰዋል። በጣቢያዎቹ በራስ ኃይል የተከናወኑ የጥገና ሥራዎች የኃይል ምርት አፈጻጸሙን በማሳደጋቸው ባለፉት ስድስት ወራት 13 ሺህ 504 ነጥብ 2 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል እንዲመነጭ አስችሏል። ይህም የዕቅዱን 15 ነጥብ 6 በመቶ ብልጫ ያለው መሆኑን ነው ወ/ሮ ጥሩወርቅ ያብራሩት፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ጣቢያው የደበኞችን የኃይል ጥያቄ እየመለሰ ነው …..….///……….. የወልቂጤ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ከደንበኞች የሚቀርቡ የኃይል ጥያቄዎችን እየመለሰ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ተናገሩ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ሙጀረብ የኑስ እንደተናገሩት ማከፋፈያ ጣቢያው ካለው 360 ሜጋ ዋት ኃይል ውስጥ 102 ሜጋ ዋት ኃይሉ ደንበኞችን ሲጠብቅ ቆይቷል፡፡ ጣቢያው ያለውን አቅም ለመጠቀም ከባለድርሻ አካላት ጋር በተሰራው ሥራ አሁን ላይ እስከ 80 ሜጋ ዋት ኃይል የሚጠቀሙ ተጨማሪ ደንበኞችን ማግኘት መቻሉን ጠቁመዋል፡፡ ከኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች መካከል የቢተን ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ድርጅት ሱፐርቫይዘር ሚስተር  ጂየን ሊየን በበኩላቸው ከጣቢያው የጠየቁትን ኃይል በአጭር ጊዜ በማግኘታቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡ ተቋሙ ለሰጣቸው ፈጣን ምላሽ እና ላደረገላቸው ትብብር አመስግነው በቀጣይም በመካከላቸው የሚኖረውን ትብብር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

photo content
+6

የማከፋፈያ ጣቢያውን ግንባታ እስከ መጪው ሐምሌ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው …….///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ እየተገነቡ ካሉ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ የሆነው የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ግንባታን እስከ መጪው ሐምሌ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡   ሥራ አስኪያጁ አቶ ቴዎድሮስ ጋሻው እንደገለጹት የማከፋፈያ ጣቢያው ከቆቃ-ገላን ከተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር ላይ በመቀጠል 14 ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች እና እያንዳንዳቸው ባለ 63 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው አራት ትራንስፎርመሮች እንዲኖሩት ተደርጎ እየተገነባ ነው፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያውን የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች ለማስቀመጥ የሚያግዙ ከ290 በላይ የመሠረት ቁፋሮና የኮንክሪት ሙሌት እንዲሁም የአራት ትራንስፎርመሮች ማስቀመጫ ግንባታዎች መጠናቀቃቸውን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት የሲቪል ሥራዎች ስለተጠናቀቁ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች በመርሀ ግብሩ መሰረት ሳይት ከደረሱ ቀሪ የተከላ ሥራዎች በተያዘው እቅድ መሰረት እንደሚከናወን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ የኦፕሬተሮች መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ተጠናቆ የማጠናቀቂያ ሥራዎች እየተከናወኑ ስለመሆናቸውም ጠቅሰዋል፡፡ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈጻፀም 48 ነጥብ 5 በመቶ መድረሱን የጠቆሙት አቶ ቴዎድሮስ ቀሪ የመንገድ፣ የመቆጣጠሪያ ክፍሉ ግንባታ እና የፍሳሽ ማስወገጃ እንዲሁም የኤሌክትሮ ሚካኒካል ሥራዎችን የማካካሻ እቅድ በማውጣት ፕሮጀክቱን እስከ መጭው ሐምሌ 2017 ዓ.ም ድረስ ሙሉ ለሙሉ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ስለመሆኑም ተናግረዋል፡፡ የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ባለስልጣን ለሚያስገነባው ስማርት ሲቲ በተለያዩ ምዕራፎች እንዲቀርብለት ከሚፈልገው 575 ሜጋ ቮልት አምፔር ኃይል ውስጥ ፕሮጀክቱ በመጀመሪያው ምዕራፍ 252 ሜጋ ቮልት አምፔር ኃይል ለማቅረብ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል። የማከፋፈያ ጣቢያውን ጨምሮ 2 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር ርዝመት ላለው የማስተላለፊያ መስመር የግንባታ ሥራ የሚያስፈልገው ወጪ በገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ባለስልጣን እየተሸፈነ ነው። ፕሮጀክቱ ለ181 ዜጎች ጊዜያዊና ቋሚ የሥራ ዕድሎች ፈጥሯል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 20 ቀን 2017 ዓ.ም