en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 686 subscribers, ranking 8 039 in the Technologies & Applications category and 2 170 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 686 subscribers.

According to the latest data from 04 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 132 over the last 30 days and by -4 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 26.82%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.99% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 208 views. Within the first day, a publication typically gains 2 509 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 9.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 05 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 686
Subscribers
-424 hours
+57 days
+13230 days
Posts Archive
ማከፋፈያ ጣቢያው አቅሙን ለማሳደግ እየሰራ ነው ........///......... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰበታ ሁለት ባለ 400 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ አቅሙን ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን ገለጸ። የጣቢያው ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ አየልኝ እንደገለጹት በባለ 400 ኪሎ ቮልት በሀገሪቱ የመጀመሪያው የነበረው ማከፋፈያ ጣቢያው በ2002 ዓ.ም ወደ ሥራ ሲጀምር በዋናነት የግልገል ጊቤ 2 ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ኃይል ተቀብሎ ለማስተላለፍ ነው። ጣቢያው ከግልገል ጊቤ 2 በገላን ማከፋፈያ ጣቢያ በኩል እንዲሁም ከጊቤ 3 ኃይል ማመንጫ ጣቢያ እና ከሆለታ ማከፋፈያ ጣቢያ በ 400 ኪሎ ቮልት አራት ገቢ መስመሮች ሲኖሩት ካራ ቆሬ አካባቢ ለሚገኘው ሰበታ አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ  እንዲሁም ለኢትዮ ጅቡቲ የባቡር መስመር በ230 ኪሎ ቮልት ጥምር መስመር ኃይል እንደሚሰጥ ተናግረዋል። በማከፋፈያ ጣቢያው ዙሪያ ለሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎችና ለፋብሪካዎች በ33 ኪሎ ቮልት ኃይል የሚሰጥ ሲሆን ከ34 በላይ ወጪ መስመሮች እንዳሉት ገልጸዋል፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው እያንዳንዳቸው 250 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው ሁለት አውቶ ትራንስፎርመሮች እንዳሉት የጠቆሙት አቶ ሙሉጌታ በሦስት መስመር ወደ 60 ሜጋ ዋት አካባቢ ኃይል ለዳታ ማይኒንግ ድርጅት እያቀረበ ይገኛል ብለዋል፡፡ የሰበታ ሁለት ማከፋፈያ ጣቢያ በ 400 ኪሎ ቮልት ጥምር መስመር ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመነጨውን ኃይል ከሆለታ ማከፋፈያ ጣቢያ ተቀብሎ ወደ ብሔራዊ የኃይል ቋት እያስገባ እንደሚገኝ አብራርተዋል። በቀጣይም የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝነት ለመጨመር አንድ ተጨማሪ አውቶ ትራንስፎርመር እና ለአካባቢው ማሕበረሰብ አገልግሎት የሚሰጥ አንድ ፓወር ትራንስፎርመር ከውጪ ለማስገባት በሂደት ላይ መሆኑን ገልጸዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 29 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

በማመንጫ ጣቢያው የዕቃ ግምጃ ቤት የካይዘን አሰራር ተግባራዊ ተደርጓል ……..///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጊቤ ሦስት የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የዕቃ ግምጃ ቤቶች የካይዘን አሰራር ሥርዓት ተግባራዊ መደረጉን ጣቢያው አስታወቀ። የጣቢያው የጥገና ባለሙያ አቶ እሸቱ አበራ እንደተናገሩት የኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎችን ለማቀላጠፍ የሚያግዝ የካይዘን የአሰራር ሥርዓትን በዕቃ ግምጃ ቤቶች ተግባራዊ በማድረግ ውጤታማ ሥራ ተከናውኗል። የካይዘን የአሰራር ሥርዓት ከመተግበሩ በፊት የዕቃ ግምጃ ቤቶቹ ደረጃቸውን ያልጠበቁና ዕቃዎቹም በተለያዩ ቦታ በዘፈቀደ የተቀመጡ እንደነበረ አስታውሰዋል። በዚህም ዕቃዎቹ በሙቀትና በተለያዬ ምክንያቶች በአጭር ጊዜ ከመበላሸታቸውም በተጨማሪ ለሥራ ሲፈለጉ በቀላሉ የማይገኙ በመሆኑ ውጤታማ የኦፕሬሽን እና የጥገና ሥራዎችን ለማከናወን አዳጋች ነበር ብለዋል። ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት በካይዘን የአሰራር ሥርዓት ግንዛቤ ያላቸው ባለሙያዎች ተመድበው ወደ ሥራ መገባቱን ጠቁመዋል። እንደ ባለሙያው ገለጻ በጣቢያው በሚገኙ ሦስት የዕቃ ግምጃ ቤቶች ላይ የሚሰሩና የሚወገዱ የመለዋወጫ ዕቃዎችና መሣሪያዎችን በመለየት በዓይነታቸውና በአገልግሎት ዘመናቸው መሰረት ከሦስት ወር በላይ ጊዜ በመውሰድ የማደራጀት ሥራ ተሰርቷል። ይህም ጣቢያው ያሉትንና የሌሉትን የመለዋወጫ ዕቃዎች ለይቶ እንዲያውቅ በማስቻሉ ቀደም ሲል ዕቃዎቹን ለመፈለግ ይወስድ የነበረውን ጊዜና በብልሽት ምክንያት ያጋጥም የነበረውን አላስፈላጊ ወጭ ማስቀረት መቻሉን ተናግረዋል። የጣቢያው የዕቃ ግምጃ ቤት ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ  ማርታ ጉንቴ በበኩላቸው ከሦስት ወር በላይ ጊዜ በመውሰድ የተደራጁት ዕቃዎች ዓይነትና ዝርዝር መረጃዎች መለያ ተሰጥቷቸው ተመዝግበው መቀመጣቸውን ገልጸዋል። ይህም በግምጃ ቤቱ ውስጥ ያሉ ዕቃዎችን ለማወቅ፣ ያለቁ ዕቃዎችን ለማሟላት እና የሚገቡ ዕቃዎችን በዓይነታቸው አደራጅቶ በማስቀመጥ ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት ማስቻሉን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከአራት ዓመት በፊት ከኢትዮጵያ ካይዘን ኢንስቲትዩት ጋር የካይዘን ትግበራ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሞ ወደ ሥራ መግባቱ ይታወሳል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 29 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ሪጅኖች ተቋማዊ ለውጡን በሚያሳካ መልኩ ሥራዎችን ሊያከናውኑ ይገባል ........///........ ሪጅኖች ተቋማዊ ለውጡን በሚያሳካ መልኩ የኦፕሬሽን ሥራዎችን ሊያከናውኑ እንደሚገባ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ አሳሰበ። ዘርፉ የሪጅኖችን የዘጠኝ ወራት እቅድ አፈጻጸም በመገምገም ቀጣይ የሥራ አቅጣጫ ሰጥቷል። በተቋሙ የትራንስሚሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አንዷለም ሲዓ እንደተናገሩት ተቋሙ የተጣለበትን ሀገራዊ ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት እንዲያስችለው ተቋማዊ ለውጥ እየተገበረ ይገኛል። በበጀት ዓመቱ መጨረሻ ውጤታማ አፈጻጸም ለማስመዝገብ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ያልተከናወኑ ተግባራትንና በሚቀጥሉት ሦስት ወራት ለማከናወን የታቀዱ ሥራዎችን በማካተት የመቶ ቀን ዕቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ሥራ እንዲገባ አሳስበዋል። ዕቅዱን በሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ የጋራ በማድረግ ወደ ሥራ እንዲገባ ያሳሰቡት አቶ አንዷለም ዕቅዱ ሪጅኖች ያሉበትን የአፈጻጸም ደረጃ የለየ፣ ችግሮችንና የመፍትሄ አቅጣጫዎችን ያስቀመጠ፣ የሥራ ቅደም ተከተልንና ባለቤት የለየ ሊሆን ይገባል ብለዋል። በመቶ ቀን ዕቅዱ በተለያዩ ምክንያቶች የግሪድ መሳሳት ባጋጠሙ ቦታዎች ላይ አስፈላጊ ሥራዎችን በመስራት ግሪዱን ወደነበረበት አቅምና አቋም ለመመለስ ትኩረት እንዲሰጥ አቅጣጫ አስቀምጠዋል። የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን የኦፕሬሽን ሥራዎችን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመፈጸም ሪጅኖች ከሠራተኞች ጋር መግባባት መፍጠርና መፍጠንን ማዕከል በማድረግ እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል። የማዕከላዊ አንድ ሪጅን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ደረጀ ገዛኸኝ እንደገለጹት የግምገማ መድረኩ ተቋማዊ ለውጡን ሪጅኖች በምን መልኩ ማስኬድ አለባቸው በሚለው ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ የፈጠረ ነው። መድረኩ በሪጅኖች ባለፉት ዘጠኝ ወራት ያጋጠሙ ችግሮችን ለይቶ በቀጣይ ለመፍታት እና በበጀት ዓመቱ መጨረሻ የተሻለ ለውጥ ለማስመዝገብ ዕድል የሚፈጥር መሆኑንም ገልጸዋል። የሰሜን ምስራቅ ሁለት ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ሀሰን ሙሐመድ በበኩላቸው የግምገማ መድረኩ የነበሩ ጠንካራ ጎኖችን በማጎልበት እንዲሁም የክትትልና የቁጥጥር ሥራዎችን በማጠናከር በቀጣይ በምን መልኩ መሰራት አለበት በሚለው ዙሪያ በቂ ግንዛቤ ያገኘንበት ነው ብለዋል። እንደሪጅን ያሉ ችግሮችን እና መልካም አጋጣሚዎችን በመለየት የአጭርና የረጅም ጊዜ መፍትሄዎችን አስቀምጦ ስጋቶችን በቀነሰ መልኩ ለተቋማዊ ለውጡ ስኬት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 27 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

ሪጅኖች የኦፕሬሽን ሥራዎችን በማቀላጠፍ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር መስራት አለባቸው …..///…. የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽን ሥራ በማቀላጠፍ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር መስራት እንደሚገባ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሳሰቡ። የትራንስሚሽን ቢዝነስ 13ቱም የሪጅን ሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ተገምግሟል፡፡ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ አንዷለም ሲዓ እንደተናገሩት ግምገማው የሪጅኖች የኦፕሬሽን ሥራ ያለበትትን ደረጃ ለማወቅ፣ እርስ በእርስ ለመማማር፣ ከኦዲት ጋር ተያይዞ የተሰሩ ማሻሻያዎችን ለማየት እና አመራሩ በአፈፃፀሙ ላይ የጋራ ግንዛቤ ኖሮት ሥራዎችን እንዲሰራ ዕድል ለመፍጠር ነው፡፡ ዘርፉ እንደ አዲስ ከተዋቀረ በኋላ ቀደም ሲል በችግር መልክ ሲነሱ የቆዩና መፍትሄ ያላገኙ ጉዳዮችን በመለየት በዘላቂነት ለመፍታት እንዲሁም የኦፕሬሽን አሰራሮችን ለማዘመንና ለማሻሻል ቴክኖሎጅዎችን መጠቀም በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ እየሰራ ነው ብለዋል፡፡ አቶ አንዷለም አክለውም ሪጅኖች የኦፕሬሽን ሥራዎችን በማቀላጠፍ እንዲሁም ከአካባቢ መስተዳድር አካላትና ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የዲስትሪክት ኃላፊዎች ጋር በመቀናጀት የኃይል ተደራሽነቱን ለማሳደግ ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡ የዘርፉ የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈፃፀም በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን የዕቅድና ክትትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ታገል ደገፉ ቀርቧል፡፡ የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝነት ለማሳደግ የሚያስችሉ የቅድመ መከላከል፣ የትንበያ፣ የፍተሻ ጥገና ሥራዎች በማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፍያ ጣቢያዎች ላይ መከናወናቸው በሪፖርቱ ተመላክቷል፡፡ በሰመራና በአዲጋላ ማከፋፈያ ጣቢያዎች በጭነት ልዩነት ወቅት ቮልቴጅን ለመቀጣጠር የሚረዳ መሣሪያ (shunt reactor) በመትከልና ወደ ኦፕሬሽን በማስገባት የአፋር ክልልና የጅቡቲን የኤክስፖርት ኮሪደር እንዲሁም የባቡር ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን አስተማማኝና ያልተቆራረጠ ኃይል እንዲያገኙ ማድረግ መቻሉም ተጠቁሟል፡፡ የዘመናዊ የመቆጣጠሪያ ብሬከሮች ተከላ እንዲሁም በስርቆት ምክንያት የሚወድቁ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን መልሶ የመገንባት ሥራዎች በራስ አቅም በማከናወን ወጭና ጊዜ መቆጠብ መቻሉም በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡ የመለዋወጫ እቃዎች ተመዝግበው መቀመጣቸው፣ በአስራ ስድስት ማከፋፈያ ጣቢዎች ላይ ላይ የፕሮቴክሽን ማሻሻያ ሥራዎችን በመስራት የብሔራዊ የኃይል ቋቱን ደህንነት ከፍ በማድረግ አላስፈላጊ የኃይል መቆራረጦችን መቀነስ ተችሏል፡፡ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ስርቆት መጨመር፣ በጸጥታ ችግር ምክንያት የተለያዩ መስመሮች ለረዥም ጊዜ ተቋርጠዉ መቆየት፣ የከፍተኛ ኃይል ትራንስፎርመር እጥረት እና በማሰራጫ መስመሮች ላይ በሚያጋጥም አደጋ ምክንያት የሚወጡ መስመሮች እና ትራንስፎርመሮች መጨመር በዘጠኝ ወራት ያጋጠሙ ተግዳሮቶች መሆናቸውም በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈፃሚ አቶ አበባው ያለው በበኩላቸው ግምገማውን ማድረግ ያስፈለገበት ዋና ምክንት በተቋሙ እየተከናወኑ ካሉ ተቋማዊ የለውጥ ሥራዎች ጋር ተያይዞ በኦፕሬሽን ሥራዎች ላይ መዘናጋት እንዳይኖር ያለበትን ደረጃ በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ነው ብለዋል፡፡ የባለሙያዎችን አቅም በማጎልበት በ36 ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የማሻሻያና የአቅም ማሳደግ ሥራዎችን በራስ አቅም እየተከናወኑ መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡ ኃይል ያላገኙ አካባቢዎችን ተደራሽ ለማድረግ እንዲሁም ኃይል ባገኙ አካባቢዎች አቅርቦቱን አስተማማኝ ለማድረግ የዘርፉን አፈፃፀም ማሳደግ ወሳኝ መሆኑን የጠቆሙት አቶ አበባው የኦፕሬሽን ሥራዎችን ለማዘመን እና አሰራሮችን ለማሻሻል እየሰሩ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ ግምገማው በነገው ዕለትም የሚቀጥል ይሆናል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

ዘርፉ የዘጠኝ ወር የሥራ አፈጻጸሙን እየገመገመ ነው .....///..... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን የ2017 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እያካሄደ ነው። ግምገማው የሪጅኖችን የዘጠኝ ወራት ክንውን፣ ያጋጠሙ ችግሮች እና የተወሰዱ የመፍትሄ ርምጃዎች እንዲሁም ቀጣይ የትኩረት አቅጣዎች ላይ ያተኮረ ነው። በግምገማው ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢ/ር አሸብር ባልቻ ተቋሙ እያደረገ ካለው ሪፎርም ጎን ለጎን የኦፕሬሽን ሥራዎችን በአግባቡ በማከናወን የተቋሙን ግቦች ማሳካት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ላይ ለሚደርሱ ጥፋቶች እና ሌሎች አስተዳደራዊ ክፍተቶችን ለማረም ተጠያቂነት ከማስፈን ጎን ለጎን ቀድሞ መከላከል ላይ ያተኮረ አሠራር መዘርጋት አስፈላጊ ነው ብለዋል። ለዚህም ሁሉም ሪጅኖች  ከመስተዳድር አካላት እና ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር ተቀራርቦ በመስራት እና ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት አስተማማኝ ኃይል ለህብረተሰቡ ማድረስ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በዘጠኝ ወራት ውስጥ  የማስተላለፊያ መስመሮች፣ የማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ዘርፉን ለማዘመን የተከናወኑ ተግባራት አፈጻጸም በዝርዝር ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

ጣቢያዉ በዞኑ የተሰማሩ የኢንቨስተሮችን የኃይል ፍላጎት መልሷል ……..///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የወልቂጤ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ በጉራጌ ዞን  ለተሰማሩ ከ315 በላይ የሚሆኑ ኢንቨስተሮችን የኃይል ፍላጎት በተሟላ መልኩ መመለስ መቻሉን የዞኑ አስተዳደር የኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቁ፡፡ የመምሪያው ልዩ አማካሪ አቶ ዳርጌ ተረፈ እንዳስታወቁት የወልቂጤ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በአካባቢው መኖሩ ኢንቬስተሮችን በመሳብ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽዖ እያበረከተ ነው፡፡ በአካባቢው ሰላማዊ እና ምቹ የኢንቨስትመንት አማራጭ ከመኖሩ ባሻገር በቂ የኃይል አቅርቦት መኖሩ ባለሀብቶቹን በመሳብ በኩል ያለውን ዕድል ማስፋቱን ተናግረዋል፡፡ እንደ አቶ ዳርጌ ገለፃ የኢንቨስትመንት ሥራዎች በአግባቡ እንዲከናወኑ ከኃይል አቅርቦት ጋር ለተገናኙ ችግሮች ማከፋፈያ ጣቢያዉ ፈጣን ምላሽ በመስጠት የድርሻዉን እየተወጣ ነው፡፡ በአካባቢዉ እየተነቃቃ የመጣዉን ኢንቨስትመንት አጠናክሮ ለማስቀጠል በቅርቡ የኢንዱስትሪ መንደር ለማቋቋም ዝግጅቶች መጠናቀቃቸዉን አማካሪው ጠቁመዋል፡፡ ባለሀብቶች ዞኑ ባሉት የኢንቨስትመት አማራጮች ላይ ለመሰማራት ሲመጡ በአካባቢው ምንም ዓይነት የኃይል እጥረት እንደማይገጥማቸዉ ልዩ አማካሪው አረጋግጠዋል፡፡ የጉራጌ ዞን አስተዳደር በ10 ወረዳዎች እና በአምስት የከተማ መስዳድሮች የተዋቀረ ሲሆን አካባቢዉን ምቹ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ለማድርግ በርካታ ሥራዎች እየተከናወኑ ስለመሆኑ ተመላክቷል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

ጣቢያው ለአካባቢው ማህበረሰብ የሥራ ዕድል ፈጥሯል  ….....///…..… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአዋሽ ሁለትና ሦስት የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች 50 ለሚሆኑ የአካባቢው ነዋሪዎች ቋሚ የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን የጣቢያዎቹ ሥራ አስኪያጅ ገለጹ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ጌታቸው አበበ እንደገለፁት ጣቢያዎቹ እያንዳንዳቸው 32 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ኖሯቸው  ከ60 ዓመት በፊት በ60 ሚሊዮን ብር ተገንብተው አገልግሎት መስጠት የጀመሩ ናቸው። ጣቢያው በሁለት ማህበራት የተደራጁ 50 የሚሆኑ የአካባቢው ወጣቶችን በጥበቃ ሥራ ላይ በማሰማራት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ ይህም የጣቢያውን ደህንነት በአግባቡ ለማስጠበቅ ከማገዙም ባለፈ የአካባቢው ማህበረሰብ በጣቢያው ላይ ያለውን የባለቤትነት ስሜት የሚያሳድግ መሆኑን ተናግረዋል። የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ከሆኑት መካከል አቶ ወርቁ ቱፋ እንደገለፁት በማህበራቸው የታቀፉት 25 ሰዎች በጣቢያው ሥራ ከመጀመራቸው በፊት አባላቱ በሚያገኙት ገቢ ቤተሰባቸውን ለማስተዳደር ትልቅ ፈተና ነበር። በማህበር ተደራጅተው በጣቢያው በተፈጠረላቸው የሥራ ዕድል ለሁለት ዓመት አካባቢ መስራታቸውን የጠቆሙት አቶ ወርቁ በዚህም ራሳቸውን ጨምሮ አራት ቤተሰቦቻቸውን ለማስተዳደር የሚያስችል ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት እንደረዳቸው ተናግረዋል፡፡ ሌላኛው የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መጋቢ ሃምሳ አለቃ በቀለ ገዳ በበኩላቸው ከሠራዊት ተመላሽና እና የተሰው አባላትን ቤተሰብ ይዞ የፅዳትና ጥበቃ አገልግሎት የሚሰጥ ማህበር እንዳላቸው ጠቁመዋል። በጣቢያው ሥራ ከመጀመራቸው በፊት ቤተሰባቸውን ለማስተዳደር ይቸገሩ የነበሩት መጋቢ ሃምሳ አለቃ በቀለ፤ ጣቢያው በፈጠረላቸው የሥራ ዕድል ከአካባቢያቸው ሳይርቁ ሰባት ቤተሰባቸውን እያስተዳደሩና ልጆቻቸውን እያስተማሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ጣቢያዎቹ ለ25 የማህበሩ አባላት በጥበቃ አገልግሎት የሥራ ዕድል  በመፍጠራቸውም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 25 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ጣቢያው አስተማማኝ ኃይል እያቀረበ ነው ……..///……. የቆቃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ አስተማማኝ ኃይል እያቀረበ መሆኑ አስታወቀ። የማመንጫ ጣቢያው የጥገና ክፍል ኃላፊ አቶ ያፌት ተስፋዬ እንደገለፁት የማከፋፈያ ጣቢያው የምስራቁን የሀገራችን ክፍል ከዋናው ግሪድ ጋር የሚያገናኝ ነው። እንደ አቶ ያፌት ገለጻ ጣቢያው ከመልካ ዋከና፤  ከአዳማ ንፋስ ኃይል ማመንጫ እና ከቃሊቲ ኃይል በመቀበል ለሁርሶ፣ ለአዳማ እና ለቃሊቲ ሁለት ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል የሚሰጥ በመሆኑ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር የማመንጫ ጣቢያው በዕቅድ ላይ የተመሰረተ የጥገናና የፍተሻ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል። ጣቢያው ሲመሰረት ሰው የማይቆጣጠረው የነበረ ቢሆንም ዕድሜው እየገፋ ሲሄድ ግን የሠው ኃይል በመፈለጉ የማመንጫ ጣቢያው ያሉትን የኦፕሬሽን አና የጥገና ሠራተኞች በመመደብ ጭምር የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝ ለማድረግ እየሰራ ነው ብለዋል። ጣቢያው ለረጅም ዓመታት አገልግሎት ከመስጠቱ ጋር ተያይዞ የማዘመንና የማስፉፊያ ሥራ የሚያስፈልገው መሆኑንም ተናግረዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 25 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

በሪጅኑ የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ናቸው ……..///……... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ ሁለት ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እያከናወነ መሆኑን  አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ታዬ እንዳስታወቁት በሪጅኑ የተለያየ የኪሎ ቮልት መጠን ያላቸው ስምንት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና 1 ሺ 180 ኪሎ ሜትር የማስተላለፊያ መስመሮች አሉ። በሪጅኑ የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝ ለማድረግ ከ2016 በጀት ዓመት ጀምሮ በአምስት የማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የማዘመን ሥራዎችን ለማከናወን ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን አብራርተዋል። በዚህም በወላይታ ሶዶ ቁጥር አንድ ማከፋፈያ በ 33 ኪሎ ቮልት መቆጣጠሪያ ወይም ብሬከር  እና በሆሳዕና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ዘመናዊ የጂ አይ ኤስ መቆጣጠሪያ ቅየራ ቅየራ መከናወኑን ተናግረዋል። በወላይታ ሶዶ ቁጥር አንድ የባለ 15 ኪሎ ቮልት እንዲሁም በሀላባና ሳውላ ማከፋፈያ ጣቢያዎች የባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮችን በዘመናዊ መቆጣጠሪያዎች ለመቀየር እየተሰራ መሆኑንም አቶ ምትኩ ጠቁመዋል። ከመቆጣጠሪያ ቅየራው በተጨማሪ በብሔራዊ ኤሌክትሪክ ደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አማካይነት በነባሮቹ የወላይታ ሶዶ ሁለተኛ እና አርባምንጭ ቁጥር አንድ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የማስፋፊያ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ አብራርተዋል። እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ ከማስፋፊያ ሥራው ጎን ለጎን በፕሮጀክቱ አርባ ምንጭ 2ኛን ጨምሮ ሽግዳንና ቲርጋ ላይ የሚገነቡ ሦስት አዳዲስ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ እንዲሁም የ424 ኪሎ ሜትር የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ እየተከናወነ ነው። ይህም በሪጅኑ ያለውን የኃይል ተደራሽነት በዘላቂነት ለማሳደግ እንደሚያስችል ተናግረዋል። ሪጅኑ በሚያስተዳድራቸው ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይም የተጠናከረ የፍተሻ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን አቶ ምትኩ ገልጸዋል። በሪጅኑ የተጠናከረ የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎች እንደሚከናወኑ የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ ለዚህም የባለሙያዎችን አቅም ለመገንባት በማዕከል እንዲሁም በሪጅኑ አቅም የተለያዩ አጫጭርና የሥራ ላይ ሥልጠናዎች እንደሚሰጡ አብራርተዋል። በኃይል መሠረተ ልማቱ ውስጥ የሚተከሉ ዛፎችና የሚገነቡ ቤቶች እንዲሁም የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ስርቆት ለሪጅኑ ፈተና እንደሆኑበትም ጠቅሰዋል። ችግሩን ለመከላከል የሚመለከታቸው የጸጥታና የመስተዳድር አካላት እንዲሁም ህብረተሰቡ የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 25 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

የሁለቱ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች የትውውቅ መርሃግብር አካሄዱ ………///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚዎች እና ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች የተሳተፉበት የተቋማቱ ከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድን የእርስ በእርስ ትውውቅ የትውውቅ መርሃ ግብር አካሄደ፡፡ በተቋማቱ የተደረገውን ሪፎርም ተከትሎ የተመደቡ የሥራ ኃላፊዎችን እርስ በእርስ ለማስተዋወቅ ትናንት ምሽት በተዘጋጀ መርሃግብር ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት በመተጋገዝና ተቀራርቦ በመሥራት በዘርፉ የሚነሳውን ችግር በጋራ መፍታት ይቻላል፡፡ ግንኙነቱ የኃይል ተጠቃሚ ደንበኞችን እርካታ በሚያሳድጉ ጉዳዮች ላይ ጌዜ ሳይጠብቁ ለመነጋገር ዕድል የሚሰጥ ነው ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ጌቱ  ገረመው በበኩላቸው የሁለቱ ተቋማት ግንኙነት ኃይል ከመሸጥና ከመግዛት ያለፈ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ እንደዚህ ዓይነት የግንኙነት መድረኮች የበለጠ የሚያቀራርቡ እና ፈጣን መፍትሔ ለመስጠት የሚያግዙ በመሆናቸው በመደበኛ አሰራሮች ታግዘው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አንስተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 24 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1