es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 572 suscriptores, ocupando la posición 8 356 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 162 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 572 suscriptores.

Según los últimos datos del 24 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 24, y en las últimas 24 horas de 19, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 25.91%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 15.83% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 4 035 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 465 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 8.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 25 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 572
Suscriptores
+1924 horas
+197 días
+2430 días
Archivo de publicaciones
ክልሉ ለተቋሙ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገለጸ፤ ...//... የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሚያከናውናቸው የኃይል መሰረተ ልማት ሥራዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገለጸ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ ኃላፊዎች ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አመራሮች ጋር የአሶሳ ማከፋፈያ ጣቢያ የመሬት ይዞታ ለውጥን በተመለከተ ውይይት አድርገዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ እና የንብረት አስተዳደር መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ከሊል ሽፋ ከማከፋፋያ ጣቢያው የመሬት ይዞታ ለውጥ ጋር ተያይዞ በተቋሙ በኩል የሚነሱ ቅሬታዎችንና የማከፋፈያ ጣቢያው የኃይል አቅርቦት በተመለከተ ገለፃ አድርገዋል። የሥራ ኃላፊዎቹ በገለጻቸው የመሬት ይዞታ ለውጡ በአሶሳ ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ በሚከናወነው የማስፋፊያ ሥራ፣ በጣቢያው ደህንነት እና በኃይል አቅርቦቱ ላይ ችግሮችን የሚያስከትል መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የአሶሳ ከተማ ከንቲባ አቶ አብዱልካሪም አብዱራሂም የመሬት ይዞታው ለውጥ በከተማው እየተካሄደ ካለው የኮሪደር ልማት ጋር ተያይዞ የተከሰተ መሆኑንና ለማከፋፈያ ጣቢያውም ምትክ መሬት እንደሚሰጥ ተናግረዋል፡፡ የርዕሰ መስተዳድሩ የመሠረተ ልማት ዘርፍ አማካሪ አቶ አበራ ባያታ በበኩላቸው ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ - አሶሳ ለሚዘረጋው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ እና በነባሩ የአሶሳ ማከፋፈያ ጣቢያ ውስጥ ተቋሙ ለሚያከናውናቸው የማስፋፊያ ሥራዎች የክልሉ መንግስት ተገቢውን ክትትልና ድጋፍ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ በውይይቱ ወቅት እንደተናገሩት ከማከፋፈያ ጣቢያው የመሬት ይዞታ ለውጥ ጋር ተያይዞ እየተነሱ ያሉ ቅሬታዎች በግንኙነትና በመረጃ ክፍተት የተፈጠሩ ናቸው፡፡ ለክልሉ ሁሉን አቀፍ እድገት የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ወሳኝ መሆኑን የገለጹት አቶ ጌታሁን ከተቋሙ ጋር በትብብርና በቅንጅት ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ክልሉ ከተቋሙ ጋር በቅርበት ተባብሮ ለመስራት አሶሳ ከተማ ውስጥ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ቢሮ እንዲያደራጅ ምክትል ፕሬዝዳንቱ ጥሪ አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 14 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

photo content

ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቱን ጎበኙ .........///......... የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ እና የደሴ ከተማ  የንግዱ ማኅበረሰብ አባላት በከተማዋ የተጀመረውን ባለ 230/33/15 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ጎበኙ፡፡ ፕሮጀክቱ ከማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ በተጨማሪ 5 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታን ያካትታል፡፡ 1 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በጀት የተመደበለትን የማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ እና የማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ በሁለት ዓመት ተኩል ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተይዞለታል፡፡ የፕሮጀክቱ ግንባታ በኢትዮጵያ አሌክትሪክ ኃይል የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ የሚከናወን ሲሆን በአሁኑ ወቅት የማከፋፈያ ጣቢያው አጥር እና የትራንስፎርመር ማስቀመጫ መሰረቶች ግንባታ በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡ የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው ሳሙኤል ሞላልኝ ከጉብኝቱ በኋላ እንደተናገሩት የማከፋፈያ ጣቢያው የከተማውን ህዝብ የረጅም ጊዜ ጥያቄ የሚመልስ ነው፡፡ ግንባታው ሲጠናቀቅ የከተማዋን የኃይል መቆራረጥ ከማስቀረት ባለፈ ለከተማዋ አጎራባች ለሆኑ የአማራና የአፋር ክልሎች ወረዳዎች ተጨማሪ ኃይል ለማቅረብ ያስችላል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 09 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

ሪጅኑ ባለፉት ስድስት ወራት በስምንት ማከፋፍያ ጣቢያዎች ላይ አስቸኳይ የጥገና ሥራዎችን አከናውኗል ……..///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ ምዕራብ ሪጅን ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፍያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ባለፉት ስድስት ወራት በስምንት ማከፋፈያ ጣቢያዎች አስቸኳይ የጥገና ሥራዎችን ማከናወኑን ገለጸ፡፡ የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ጌታሁን ሲሳይ እንደገለጹት ሪጅኑ የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝነት የሚያሳድጉ በዕቅድ ላይ የተመሰረቱ የጥገና ሥራዎች በማከፋፈያ ጣቢያዎችና በማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ያከናውናል፡፡ በዚህም በ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት በስምንት ማከፋፍያ ጣቢያዎች ላይ አስቸኳይ የጥገና ሥራዎችን መስራቱን ተናግረዋል፡፡ በሚዛን፣ በጅማ አንድና ሁለት፣ በመቱ፣ በበደሌ እና ሌሎች ማከፋፍያ ጣቢያዎች ላይ ከፓወር ኬብል፣ ከትራንስፎርመር፣ ከብሬከርና ከባትሪ ጋር በተገናኘ የተከሰቱ የአስቸኳይ ጥገናዎችን ማከናወኑን ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም ከግልገል ጊቤ 1 ኃይል ማመንጫ - ሰኮሩ ማከፋፈያ ጣቢያ በተዘረጋው ባለ 400 ኬሎ ቮልት ማስተላለፊያ መስመር ላይ በስድስት ቦታዎች የኮንዳክተር የጥገና ስራ ተከናውኗል፡፡ የጥገና ሥራው በማከፋፈያ ጣቢያዎቹና ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ በተደጋጋሚ ያጋጥም የነበረውን የኃይል መቆራረጥና በየጊዜው የሚከሰቱ የአስቸኳይ ጥገና ሥራዎችን መቀነሱን ጠቁመዋል። በሪጅኑ የሚገኙ የማከፋፈያ ጣቢያዎችን ለማዘመን በርካታ ተግባራት መከናወናቸውንና በደሌ 33 ኬሎ ቮልት ስዊች ጊር በጂአይኤስ የመቀየር ሥራ መሸራጹን ጸናግሯል፡፡ በመቱ፣ በጅማ እና ግልገል ጊቤ 1 ማከፋፈያ ጣቢያዎች ደግሞ ለማስፋፊያ ሥራው የሲቪል ሥራዎች እየተከናወኑ ናቸው ብለዋል፡፡ የደቡብ ምዕራብ ሪጅን አስራ አንድ የማከፋፈያ ጣቢያዎችን እና 1900 ኪሎ ሜትር ሴርኪዩት የማስተላለፊያ መስመሮች እና ያስተዳድራል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 09 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

የብድርና ቁጠባ ማህበሩ የምስጋና ፕሮግራም አካሄደ .........///......... የኢትዮ ኤሌክትሪክ ገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ህብረት ሥራ ማህበር በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እየተደረገለት ላለዉ ቁሳዊና ቴክኒካል ድጋፍ ምስጋና አቀረበ፡፡ ማኅበሩ ባዘጋጀዉ የምስጋና ፕሮግራም አስተዋጽኦ ላደረጉለት ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዲሁም በሁለቱ ተቋማት ለሚገኙ ለተለያዩ የሥራ ክፍሎች የእዉቅና ምስክር ወረቀት አበርክቷል፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የማህበሩ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ አንበስ ግዛቸዉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለማህበሩ እያደረገ ስላለዉ ሁሉን አቀፍ ድጋፍ አመስግነዉ ስለማህበሩ ቀጣይ ዕቅዶች ይፋ አድርገዋል፡፡ የማህበሩ የብድር ጣሪያ አንድ ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ብር እንዲሆን መወሰኑን፣ የማህበሩን አሰራር የሚያዘመንና የሚያሳልጥ አሰራር ለመዘርጋት የተለያዩ ጥረቶች መጀመራቸውን የቦርድ ሰብሳቢዉ አስታዉቀዋል፡፡ በማህበሩ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ የሚሳተፉ የማህበሩ አባለትን ተቋማቱ ከሚገኙባቸው የሥራ ቦታዎች በተመረጡ ተወካዮቻቸዉ እንዲሳተፉ የሚያስችል አሰራር እንደሚተገበር ጠቁመዋል፡፡ እንደ አቶ አንበስ ገለፃ የማህሩ አባል ለመሆን የሚፈልግ ሠራተኛ ቢያንስ የደመወዙን ስድስት በመቶ በመቆጠብ ማህበሩን የሚቀላቀልበት አሰራር ተዘርግቷል። ማህበሩ ጽ/ቤቱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና መስሪያ ቤት መክፈቱ የአገልግሎት ፋላጊ ሠራተኞችን የሥራ ጊዜ በመቆጠብ እርካታቸውን የሚያሳድግ በመሆኑ ማህበሩን ይበልጥ እንደሚያጠናክር በመድረኩ ላይ ተነስቷል። ማህበሩ እንደሌሎች የቁጠባ እና ብድር ማህበራት ወደ ባንክ በሚያድግበትን እና የሠራተኛውን የመኖሪያ ቤት ችግር በሚቀርፍበት አግባብ ላይ ትኩረት አድርጎ እንዲሰራም ተጠይቋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና ተወካዮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 08 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

የውጤት ማስታወቂያ ነሐሴ 15 ቀን 2016 ዓ.ም በሹፌር 2ኛ-(ሲ3) የስራ መደብ በቋሚነት ለመቅጠር ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መ
የውጤት ማስታወቂያ ነሐሴ 15 ቀን 2016 ዓ.ም በሹፌር 2ኛ-(ሲ3) የስራ መደብ በቋሚነት ለመቅጠር ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል ከተ.ቁ 1 እስከ 3 ያላችሁ በመንገድ ትራንስፖርት ህግና ደንብ በሚፈቅደው አግባብ መሠረት በተሰጠው የተግባር ፈተና አብላጫ ውጤት ያመጣችሁ በመሆኑ ከጥር 08 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 5 (አምስት) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ ብረታብረት በሚገኘው ዋና መ/ቤት የሰራተኛ ምደባ ቢሮ የትምህርት ማስረጃችሁን እና የስራ ልምድ ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ፎርም እንድትሞሉ እናሳውቃለን፡፡  💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 07 ቀን 2017 ዓ.ም

ጣቢያው ባለፉት ስድስት ወራት ከ226 ጊጋ ዋት ስዓት በላይ ኃይል አምርቷል ......//...... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመልካ ዋከና የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ2017 በጀት ዓመት ያለፉት 6 ወራት 226 ነጥብ 75 ጊጋ ዋት ሠዓት ማምረቱን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለጹ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ቴዎድሮስ በቀለ እንደገለጹት ጣቢያው ባለፉት 6 ወራት 246 ነጥብ 41 ጊጋ ዋት ስዓት ኃይል ለማምረት አቅዶ 226 ነጥብ 75 ጊጋ ዋት ሠዓት ኃይል በማምረት የዕቅዱን 92 በመቶ አሳክቷል። በ2016 በጀት ዓመት የመጨረሻ ወራት በጣቢያው ግድብ ላይ የነበረው ውሃ በከፍተኛ ደረጃ በመቀነሱ በግድቡ የተሻለ ውሃ ለመያዝ ሲባል በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ወራት በአንድ እና ሁለት ዩኒት ብቻ እንዲሰራ በመደረጉ አፈፃፀሙ ዝቅ ማለቱን ተናግረዋል። በጣቢያው ላይ የቅድመ መከላከል፤ የትንበያና የሁኔታ አመላካች ጥገና ሥራዎች በእቅድ ተይዘው እየተከናወኑ በመሆኑና በግድቡ በቂ ውሃ በመኖሩ በቀጣይ በጀት ዓመት የተሻለ ኃይል ለማምረት እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ጣቢያው ያለምንም መልሶ ግንባታ ከ37 ዓመት በላይ በማገልገሉ በየጊዜው የተለያዩ ችግሮች እየተከሰቱ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ቴዎድሮስ  ካሉት አራት ተርባይኖች አንዱ ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት እየሰጠ አለመሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የመልሶ ግንባታ ሥራ ለመስራት ከሩሲያ ከመጡ ባለሙያዎች ጋር ውይይት መደረጉን ገልጸው ስምምምቱ ተፈርሞ በአፋጣኝ ወደ ሥራ እንዲገባ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ በአራት ተርባይን 153 ሜጋ ዋት የማምረት አቅም ያለው የመልካ ዋከና የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ከ1980 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 06 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

የተሽከርካሪ ጥገና አሰራርን ለማዘመን እየተሰራ ነው .........///......... የተሽከርካሪ ጥገናን በዘመናዊ አሰራር በመታገዝ ለማከናወን የሚያስችል ዝግጅት እያደረገ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተሽከርካሪ አስተዳደር መምሪያ ገለፀ። መምሪያው የተሽከርካሪ ጥገናን በሳፕ ቴክኖሎጅ በመታገዝ ለማከናወን የሚያስችል ስልጠና ለተሽከርካሪ ጥገና አስተዳደር ባለሙያዎችና የሥራ ኃላፊዎች እየሠጠ ይገኛል። ስልጠናውን በንግግር ያስጀመሩት በተቋሙ የተሽከርካሪ አስተዳደር መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ኃይላይ ተስፋይ እንደገለፁት የሁለተኛው ምዕራፍ የሳፕ ትግበራ አካል የሆነውን የተሽከርካሪና ማሽነሪ ጥገናና አስተዳደር ማኑዋልን በአግባቡ ለመተግበር ለባለሙያዎች ሥልጠና መስጠት ያስፈልጋል፡፡ ስልጠናው ከዚህ በፊት በማኑዋል ሲከናወን የነበረውን የተሽከርካሪ የጥገና ሥራ በዘመናዊ የአሰራር ስርዓት በመታገዝ ለማከናወን እንደሚያስችል ተናግረዋል:: እንደ አቶ ኃይላይ ገለፃ ሞጁሉ ተግባራዊ ሲደረግ የቅድመ መከላከል ጥገና እና በአጋጣሚ የሚከሰቱ የሥራ ላይ ብልሽት ጥገና ሥራዎችን በቀላሉ ለማከናወን ይረዳል። የአሰራር ስርዓቱ ለተሸከርካሪዎች በወቅቱ የጥገና አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ የአገልግሎት ጊዜያቸውን ለማራዘም፣ የአደጋ ተጋላጭነትን ለመቀነስ፣ የመረጃ አያያዝን ለማሳደግ እና በየጊዜው የሚስተዋሉ ብልሽቶችን በማስቀረት ለተሽከርካሪ ጥገና የሚወጣውን ወጭ ለመቀነስ እንደሚያግዝ አቶ ኃይላይ አስረድተዋል። ሞጁሉ ሥራዎችን በቀላሉ ለማከናወን እንደሚያግዝ በመገንዘብ ሰልጣኞች ስልጠናውን በአግባቡ በመከታተል ለተግባራዊነቱ የበኩላቸውን ሚና መወጣት እንደሚጠበቅባቸውም ዳይሬክተሩ አሳስበዋል፡፡ ሥልጠናውን እየሰጡ የሚገኙት በተቋሙ የተሸከርካሪ ጥገና አስተዳደር ባለሙያ የሆኑት አቶ ብርሃኑ ታፈሰ በበኩላቸው ስልጠናው ከተሸከርካሪ ጥገና ጋር በተያያዘ የሚያገለግሉ መረጃዎችን በአሰራር ስርዓቱ እንዴት ማስገባት እንደሚቻል እና በጥገና ሂደቶቹ ላይ ትኩረት ያደርጋል ብለዋል፡፡ የአሰራር ስርዓቱ የተሸከርካሪዎችን አጠቃላይ መረጃዎች፣ በጥገና ሥራዉ ላይ ምን ሥራዎች እንደሚከናወኑ፣ ተሸከርካሪው በማን ሥር እንደሚገኝና ጥገና የት እንደሚደረግለት እንዲሁም የሚከናወኑ የጥገና አይነቶችንና ጥገናው የሚካሄድበትን ጊዜ እንደሚያሳውቅ አቶ ብርሃኑ አስረድተዋል፡፡ ለአምስት ቀናት በሚቆየው ስልጠና ላይ አስራ ስድስት የተሽከርካሪ ጥገና አስተዳደር ባለሙያዎች እና የሥራ ኃላፊዎች እየተሳተፉ ሲሆን በቀጣይ ለኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እና ለሪጅን የተሸከርካሪ ጥገና ባለሙያዎች ተመሳሳይ ስልጠና ለመስጠት መታቀዱ ተገልጿል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአሁኑ ወቅት ከ1 ሺ 200 በላይ ተሽከርካሪዎችና ማሽነሪዎች ያስተዳድራል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 05 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

ተቋማቱ የኃይል አቅርቦትን ለማሻሻል በጋራ ተስማሙ ........///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ለህብረተሰቡ አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ በሚያስችሉ የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ተወያዩ። የሁለቱን ተቋማት የጋራ ውይይት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ሽፈራው ተሊላ መርተውታል። በሁለቱ ተቋማት የተለዩና መፍትሄ የተበጀላቸው ጉዳዮች በዝርዝር ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል። በአዲስ አበባና በሌሎችም ከተሞች የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝ ለማድረግ በተሰሩና መሰራት ባለባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ማብራሪያ ቀርቧል። ከኃይል አቅርቦት ጋር በተያያዘ ለቅድመ መከላከል ጥገናም ሆነ ለማሻሻያና መልሶ ግንባታ ሥራ የሚቋረጥ ኃይል ላይ ሁለቱ ተቋማት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡ ተቋማቱ የሚሰጡት አገልግሎት ለሀገር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ያለው ፋይዳ የጎላ መሆኑ በሠራተኞች ዘንድ ተመሳሳይ ግንዛቤ መያዝ እንዳለበት አቅጣጫ አስቀምጠዋል። በውይይቱ ላይ የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 02 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

ዘርፉ የግማሽ ዓመቱን አፈፃፀም ገመገመ .........///........ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የንብረት አስተዳደርና ጠቅላላ አገልግሎት ዘርፍ የተሽከርካሪ ስምሪትና አስተዳደርን የግማሽ ዓመት የሥራ አፈጻጸም በመገምገም በመገምገም ከአሽከርካሪዎች ጋር ተወያየ። ውይይቱን የመሩት የዘርፉ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ስመኝ አያሌው እንደገለጹት  መድረኩ የተቋሙን ስትራቴጂክ ግቦች መሰረት የተዘጋጀው በሥራ ክፍሉ የተከናወኑ ተግባራትን፣ ያጋጠሙ ችግሮችን እና የተወሰዱ የመፍትሄ እርምጃዎችን እንዲሁም የሥራ ላይ ምክክር ለማድረግ ታስቦ ነው፡፡  ሥራ አስፈፃሚዋ ባቀረቡት የአፈጻጸም ሪፖርት የሥራ ክፍሉ በግማሽ ዓመቱ 396 የተሸከርካሪ አገልግሎት ጥያቄ ቀርቦለት ለ241 ጥያቄዎች ምላሽ መስጠቱን እና ለ104 ተሸከርካሪዎች የቴክኒክ ምርመራ ለማድረግ አቅዶ ለ108 ተሽከርካሪዎች ምርመራ ማድረጉን ገልፀዋል። ወጪን ከመቀነስ አኳያ በሥራ ክፍሉ በሚገኙ የፑል ተሸከርካሪዎች ላይ በተደረገው የነዳጅ ቁጥጥር 1274 ሊትር ነዳጅ በመቀነስ ከ109,974 ብር በላይ ማዳን መቻሉን ጠቅሰዋል፡፡ በግምገማው ላይ ከጂ.ፒ.ኤስ. አጠቃቀም፣ ከተሽከርካሪ ጥገና፣  ከጋራዥ አገልግሎት አሰጣጥ እና ከሥራ ክፍሉ ጋር የተያያዙ የተለያዩ ጥያቄዎች ከሠራተኞች ቀርበው ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል። ከጂ.ፒ.ኤስ. አጠቃቀም ጋር ተያይዞ ለተነሳው ጥያቄ ምላሽ የሰጡት ሥራ አስፈፃሚዋ ጂ.ፒ.ኤስ. በተሸከርካሪዎች ላይ መገጠሙ የተሽከርካሪ አስተዳደር አሰራር ን ማዘመኑን ገልፀዋል። ቴክኖሎጂው ተሽከርካሪዎች የት እንዳሉ ለማወቅ፤ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ አዘዋውሮ ለማሰራት፣ የነዳጅና ጎማ አጠቃቀምን ወጪ ቆጣቢ በሆነ መንገድ ለማስተዳደር እንዳስቻለ አስረድተዋል። እንደ ወ/ሮ ስመኝ ገለፃ የቴክኖሎጂው መተግበር የተቋሙ ተሽከርካሪዎችን የፍጥነት ገደብን በመወሰን አደጋን ለመቀነስ፣ ተሸከርካሪዎች የሄዱበትን አቅጣጫና ምን ያህል ኪሎ ሜትር እንደተጓዙ በማሳየት የተቋሙን ሀብት ለታለመለት ዓላማ ለማዋል አስችሏል። የዘርፉ የሥራ ኃላፊዎች ከሠራተኞች ለተነሱት ጥያቄዎቹ ተጨማሪ ማብራሪያና አስተያየት ሰጥተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 01 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

photo content
+9