en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 572 subscribers, ranking 8 356 in the Technologies & Applications category and 2 162 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 572 subscribers.

According to the latest data from 24 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 24 over the last 30 days and by 19 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.91%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.83% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 035 views. Within the first day, a publication typically gains 2 465 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 8.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 25 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 572
Subscribers
+1924 hours
+197 days
+2430 days
Posts Archive
የዞንና የወረዳ መስተዳድሮች የጣቢያውን ጥብቅ ወሰን እንዲያስከብሩ ተጠየቀ ….//…. የገናሌ ዳዋ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ተልዕኮውን በአግባቡ እንዲወጣ የዞንና የወረዳ መስተዳድር አካላት የጣቢያውን ጥብቅ ወሰን የማስከበር ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጥሪ አቀረበ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ ኃላፊዎች፣ የኦሮሚያ ክልል የልማት ተነሺ እና የውሃ ሀብት ቢሮ አመራሮች እንዲሁም የዞንና የወረዳ መስተዳድር አካላት በገናሌ ዳዋ የውሃ ኃይል ማመንጫ የጥብቅ ወሰን ወይም በፈር ዞን የመስክ ምልከታ አድርገዋል፡፡ በተቋሙ የኃይል መሰረተ ልማት ደህንነት፣ ክትትልና ቁጥጥር ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ በመስክ ምልከታው ወቅት እንደገለጹት የጣቢያውንና የማህበረሰቡን ደህንነት ለማስጠበቅ ጥብቅ ወሰን በመከለል ተቋሙ ከቦታው ለተነሱ ሰዎች ካሳ ከፍሏል፡፡ ሆኖም ተቋሙ ካሳ ክፍሏቸው እስከ አሁን ከጥብቅ ወሰኑ ያልተነሱ የልማት ተነሽዎች ከመኖራቸው በተጨማሪ ሌሎች ሰዎችም ወሰኑን አልፈው እርሻ በማረስ በግድቡ ደህንነትና በኦፕሬሽን ሥራው ላይ አደጋ መደቀናቸውን ተናግረዋል፡፡ አቶ ዋለ አክለውም በግድቡ ወሰን ውስጥ የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች በክረምት ወራት ለጎርፍ አደጋ የተጋለጡ መሆናቸውንም አንስተዋል፡፡ ይህም የማህበረሰቡን ደህንነት ለአደጋ በማጋለጥ ተቋሙን ለአላስፈላጊ የካሳ ጥያቄ እንደሚዳርገው ነው የተናገሩት። በጣቢያው ጥብቅ ወሰን ውስጥ ሆነው ካሳ ሳይከፈላቸው የቀሩ ሰዎች ካሉ ተቋሙ በትክክለኛ ማስረጃ ላይ ተመስርቶ ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ዋለ የዞንና የወረዳ የመስተዳድር አካላት ግድቡ ትልቅ አገራዊ ፕሮጀክት መሆኑን ከግምት በማስገባት የጣቢያውን ጥብቅ ወሰን የማስከበር ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል፡፡ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የልማት ተነሺዎች ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ተስፋ በበኩላቸው የግድቡ ውሃ በሚተኛበት ዙሪያ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎች በግድቡና በአካባቢው ማህበረሰብ ደህንነት ላይ ከፍተኛ ሥጋት መደቀናቸውን ተናግረዋል፡፡ የዞንና የወረዳ የመስተዳድር አካላት ከጣቢያው ወሰን ውስጥ የሰፈሩ የልማት ተነሺዎችን አማራጭ ቦታ በማዘጋጀት ወሰኑን ማስጠበቅ እንዳለባቸው ያሳሰቡት አቶ አለማየሁ ከካሳ ጋር ተያይዞ የሚነሱ ችግሮች ካሉም በቀጣይ በትክክለኛ መረጃ ላይ ተመስርተው እንደሚመለሱ ገልጸዋል፡፡ የነገሌ ቦረና ከተማ የውሃ አቅርቦት ፕሮጀክት ከግድቡ ጥብቅ ወሰን ውስጥ በመሰራቱ በክረምት ወራት የግድቡ ወኃ ሲሞላ በፓምፖቹ እና የውኃ መግቢያ (intake) ላይ ጫና እንደሚፈጥር በመስክ ምልከታቸው ማረጋገጣቸውንም አብራርተዋል፡፡ ይህም በአካባቢው የንጹህ የመጠጥ ውኃ አቅርቦት ላይ እንቅፋት መፍጠሩን ገልጸው ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የውኃ ፕሮጀክቱን ከጥብቅ ወሰኑ ውጭ የቦታ ቅያሬ (Relocate) ለማድረግ በቅንጅት እንደሚሰራ ጠቁመዋል፡፡ በተጨማሪም ተቋሙ ካሳ በከፈለበት የጣቢያው ጥብቅ ወሰን የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ለማግኘት ላቀረበው ጥያቄም አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት ከመስተዳድር አካላት ጋር መግባባት ላይ መደረሱን አቶ አለማየሁ ተናግረዋል። ጉጅና ባሌ ዞንን የሚያስተሳስረው የገናሌ ዳዋ የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ጥር 27 ቀን 2012 ዓ.ም ተመርቆ አገልግሎት መስጠት የጀመረ ሲሆን 254 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም አለው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 01 ቀን 2017 ዓ.ም

ማከፋፈያ ጣቢያው በሀገራቱ መካከል ያለውን ኢኮኖሚያዊ ትስስር የሚያጠናክር ነው ……...///……... የአዲጋላ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በኢትዮጵያ እና ጅቡቲ መካከል ያለውን ኢኮኖሚያዊ ትስስር ይበልጥ የሚያጠናክር መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን እንደገለፁት የአዲጋላ ማከፋፈያ ጣቢያ የኤክስፖርት ጣቢያ ከመሆኑ ባለፈ ወደ ጅቡቲ ለተዘረጋው የውሃ መስመር አስተማማኝ ኤሌክትሪክ እያቀረበ ይገኛል። ተቋሙ ለሚያከናውነው የኃይል ሽያጭ እና በሰጥቶ መቀበል መርህ ላይ ለተመሰረተው የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ወደ ተሻለ ደረጃ መድረስ ጣቢያው አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። የአዲጋላ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮናስ ሳሙኤል በበኩላቸው ማከፋፈያ ጣቢያው የተገነባው ኢትዮጵያ በምስራቁ በኩል ከጎረቤት ጅቡቲ ጋር ለሚኖራት የኃይል ኤክስፖርት ማሳለጫ ታስቦ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው 25 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያለው አንድ ትራንስፎርመር እና 74 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው አራት ሪአክተሮች እንዲሁም በ33 ኪሎ ቮልት አምስት ወጪ መስመሮች እንዳሉት አቶ ዮናስ ጠቁመዋል፡፡ ወጪ መስመሮቹም ለአዲጋላ፣ ለአይሻ፣ ለደወሌ እና ለአርዌ ከተሞች እንዲሁም ለኢትዮ- ጅቡቲ የባቡር እና ለጅቡቲ የውሃ መስመሮች አስተማማኝ ኤሌክትሪክ እያቀረበ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በጣቢያው የሚገኙት አራቱ ሪአክተሮች የቮልቴጅ መዋዠቅ ችግር እንዳይፈጠር በማድረግ የተመጠነ እና ያልተቆራረጠ ኃይል እንዲቀርብ ያስችላል። በአካባቢው በኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የሚፈፀም ስርቆት አለመኖሩን የገለፁት አቶ ዮናስ ህብረተሰቡ መሰረተ ልማቶቹን በጋራ ለመጠበቅ የሚያስችል ጠንካራ የመረጃ ልውውጥ ባህል እንዳለውም ተናግረዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 01 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+8

በበዓሉ የነበረው ከፍተኛው የኃይል ጭነት 3 ሺ 884 ሜጋ ዋት ሆኖ ተመዝግቧል ……..///……. በትላንትናው ዕለት በተከበረው የ2017 ዓ.ም የገና በዓል 3 ሺ 884 ሜጋ ዋት ኃይል መመዝገቡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የብሔራዊ ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል አስታወቀ። የማዕከሉ ዳይሬክተር አቶ ሚኪያስ ወንድሙ እንዳስታወቁት ከበዓሉ ዋዜማ ጀምሮ በበዓሉ ዕለት የኃይል መቋረጥ እንዳያጋጥም ከኃይል ማመንጫ እስከ ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያ ድረስ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት ተደርጎ የተለያዩ ሥራዎች ሲከናወኑ ነበር። ለበዓሉ እና ለዋዜማው 4 ሺ 750 ሜጋ ዋት ኃይል ዝግጁ መደረጉንና በዋዜማው 4 ሺ 309 ሜጋ ዋት እንዲሁም በበዓሉ ዕለት 3 ሺ 884 ሜጋ ዋት ኃይል መመዝገቡን ነው ያስታወቁት። ይህም ለማቅረብ ከተዘጋጀው ውስጥ በዋዜማው 441 ሜጋ ዋት እንዲሁም በበዓሉ ዕለት 866 ሜጋ ዋት ትርፍ ኃይል እንደነበር አቶ ሚኪያስ ተናግረዋል። በዋዜማው የተመዘገበው ኃይል ከ2016 ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፃር በ787 ሜጋ ዋት ወይም የ22 በመቶ እንዲሁም የበዓሉ ዕለት በ1 ሺ 196 ሜጋ ዋት ወይም የ44 በመቶ ብልጫ ያለው መሆንኑ ጠቅሰዋል። እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ ከመንዲ- አሶሳ በተዘረጋው መስመር ላይ በበዓሉ ዋዜማ ምሽት ባጋጠመ ችግር ምክንያት ከተቋረጠ ኃይል ውጭ በሌሎች መስመሮች፣ በማመንጫ እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ምንም ዓይነት ችግር ስላልተከሰተ ኃይል አልተቋረጠም። በመስመሩ በተተከሉ ስድስት የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ ምሶሶዎች ላይ ባጋጠመ ስርቆት ምክንያት በበዓሉ ዋዜማ ከምሽት ጀምሮ ኃይል መቋረጡን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ የሪጂኑ የጥገና ባለሙያዎች በበዓሉ ዕለት ጉዳት የደረሰባቸውን የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች በመጠገን ከቀኑ 9 ሠዓት ጀምሮ የተቋረጠውን ኃይል መልሶ ማገናኘት ተችሏል ብለዋል። በበዓሉ ዋዜማና በዕለቱ የኃይል እጥረት ባለማጋጠሙ ከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች እና ጎረቤት ሀገራት ጭምር ኃይል ከዚህ በፊት ይቀርብ በነበረው አግባብ እንደተስተናገዱ አንስተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 30 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

photo content
+7

ለገና በዓል የኃይል እጥረት እንዳያጋጥም ዝግጅት ተደርጓል ........///....... በነገው ዕለት ለሚከበረው የገና በዓል የኃይል አቅርቦት የኃይል እጥረት እንዳያጋጥም አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የብሔራዊ ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል አስታወቀ። የማዕከሉ ዳይሬክተር አቶ ሚኪያስ ወንድሙ እንዳስታወቁት የገና በዓል የኃይል አጠቃቀም ከሌሎች በዓላት የኃይል ጭነቱ ከፍ የማለት አዝማሚያ ስለሚስተዋል ይህን ታሳቢ ያደረገ ዝግጅት ተደርጓል፡፡ በመሆነም በበዓሉ ወቅት የኃይል እጥረት እንዳያጋጥም ካለፉት ዓመታት የበዓል የኃይል አጠቃቀም አዝማሚያ በመነሳት 4 ሺህ 750 ሜጋ ዋት ኃይል ዝግጁ መደረጉን ነው ዳይሬክተሩ የተናገሩት። በ2016 ተመሳሳይ በዓል የነበረው የኃይል አጠቃቀም 3 ሺ 522 ሜጋ ዋት እንደነበር ያስታወሱት አቶ ሚኪያስ ዘንድሮ ግን በዓሉ ሳይደርስ የነበረው የታህሳስ ወር ከፍተኛው የኃይል ጭነት 4 ሺ 630 ሜጋ ዋት ሆኖ መመዝገቡን ነው የተናገሩት። ይህም በበዓሉ ወቅት የኃይል እጥረት እንደማያጋጥም አመላካች እንደሆነና በዓሉ ወቅት ይኖራል ተብሎ ከታሰበው የኃይል ፍላጎት በላይ ከመጣ ፍላጎቱን ማስተናገድ የሚያስችል ተጨማሪ 300 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለመጠባበቂያነት ዝግጁ መደረጉን አስታውቀዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ ለዘንድሮው የገና በዓል ዝግጁ የተደረገው ኃይል አምና በተመሳሳይ ወቅት ከቀረበው ጋር ሲየፃፀር የ34 በመቶ ብልጫ ያለው ነው። በበዓሉ ዕለት የኃይል አቅርቦት ችግር እንዳያጋጥም ለማድረግ በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ሁሉም ዩኒቶች ላይ የፍተሻ ሥራዎችን በማከናወን ዩኒቶቹ ዝግጁ መደረጋቸውን ገልፀዋል። ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለኃይል መቋረጥ ምክንያት እንዳይሆኑ የቅድመ መከላከልና የፍተሻ ሥራዎች መከናወናቸውንም አስረድተዋል። በበዓሉ ምክንያት ለከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች እና ለጎረቤት አገራት በሚቀርበው ኃይል ላይ ተፅዕኖ  እንደማይኖርም ጠቁመዋል፡፡ ለማህበረሰቡ አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ሲባል ከ11 ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል የሚያገኙ የአገልግሎቱ የኢንዱስትሪ ደንበኞች በበዓሉ ወቅት አጠቃቀማቸውን እንዲቀንሱ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር ንግግር መደረጉንም አንስተዋል። በበዓሉ ወቅት ኃይል በተገቢው ሁኔታ ለተጠቃሚው እንዲደርስ ለማድረግ እና ከበዓሉ ጋር በተያያዘ ለሚያጋጥሙ ችግሮች መፍትሔ ለመስጠት ከኃይል ማመንጫና ማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊዎች፣ ከሁሉም ሪጅኖች የጥገና ኃላፊዎችና ሠራተኞች እንዲሁም ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር ውይይት ተካሂዷል ብለዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 28 ቀን 2017 ዓ.ም

እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ! በዓሉ የሠላም እንዲሆን ከልብ እንመኛለን!

ማመንጫ ጣቢያው  ከዕቅድ በላይ ኃይል ማምረት ችሏል ……..///….… በኢትዮዽያ ኤሌክትሪክ ኃይል ግልገል ጊቤ አንድ የውሃ ማመንጫ ጣቢያ  መንፈቀ ዓመት ከዕቅ.ድ በላይ ኃይል ማምረቱን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ  ንጉሳ   ገለፁ። ሥራ አስኪያጁ   እንደገለፁት ጣቢያው  ባለፉት ስድስት ወራት 572,855,721 ጌጋ ዋት ስዓት  ኃይል ለማምረት አቅዶ 587,411,770 ጌጋ ዋት ስዓት በማምረት የዕቅዱን 102.5ነጥ ብ 57 በመቶ ማሳካት ችሏል ፡፡ የጣቢያው የማመንጨት አፈፃፀም ከፍ ሊል የቻለው የቅድመ ጥገና  ስራዎች  በተያዘላቸው ዕቅድ መሰረት በመከናወናቸውና  ለኦፕሬንሽን ስራዎው አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት በመደረጉ ሦስቱም ዩኒቶች በሙሉ አቅማቸው እየሰሩ በመሆኑ እደሆነ  አቶ ደሳለኝ ገልፀዋል። አመታዊ ዕቅዱን ከማሳካት አንፃር ግዱቡ በቂ ወሃ መያዙንም  ሥራአስኪያጁ አክለው ገልፀዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

የሚቀርቡ ቅሬታዎችን በመፍታት የእኔነት ስሜትን ለማሳደግ ይሰራል ........///……... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከገናሌ ዳዋ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ጋር ተያይዞ የሚነሱ የካሳ ክፍያ እና የውሃ አቅርቦት ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ያለመ ውይይት ከባለድርሻ አካላት ጋር በትላንትናው ዕለት አካሂዷል። በውይይቱ ላይ ከካሳ ክፍያ፣ ከጣቢያው የጥብቅ ወሰን (በፈር ዞን)፣ ከግድቡ የውሃ አለቃቀቅ እና የልማት ተነሺዎችን መልሶ ከማቋቋም እንዲሁም በኃይል ማመንጫው የውሃ መግቢያ (intake) አካባቢ ስለተገነባው የነገሌ ቦረና ከተማ የውሃ አቅርቦት ፕሮጀክት ጋር የተያያዙ ጥያቄዎች ተነስተዋል። ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡት በተቋሙ የኃይል መሰረተ ልማት ደህንነት፣ ክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም የአስተዳደራዊ ጉዳዮችና ዶክመንቴሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ  ታምሬ በተደጋጋሚ የሚነሱ የካሳ ጥያቄዎች ለተቋሙና ለጣቢያው የኦፕሬሽን ሥራ ፈተና ሆኖበታል፡፡ ተቋሙ ቅሬታዎችን ለመፍታት የተለያዩ ሥራዎችን ሲያከናውን እንደነበርም ያስታወሱት ሥራ አአስኪያጁ በፕሮጀክቱ ለልማት ተነሽዎቹ 3 ቢሊዮን ብር ካሳ መከፈሉን ገልፀዋል። ይሁንና በዚህ ሂደት ካሳ ያልተከፈለው የልማት ተነሺ ስለመኖሩ በትክክለኛ መረጃ ላይ ተመስርቶ ከቀረበ በህጋዊ አግባብ እንደሚስተናገድ አስታውቀዋል። የነገሌ ቦረና ከተማ የውሃ አቅርቦት ፕሮጀክት ከግድቡ ጥብቅ ወሰን ውስጥ መሰራቱንና ይሄም ትክክል እንዳልነበር የጠቁሙት አቶ ዋለ ችግሩ በዘላቂነት በሚፈታበትና ማህበረሰቡ ንጹህ የመጠጥ ውሃ በሚያገኝበት ዙሪያ ተቋሙ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተባብሮ ለመስራት ዝግጁ መሆኑንም አረጋግጠዋል። ተቋሙ በጣቢያው ዙሪያ ባሉ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚቀርቡ ቅሬታዎችን በመፍታት በጣቢያው ላይ የእኔነት ስሜትን ለማሳደግ የሚያስችሉ የልማት ሥራዎችን እንደሚያከናውንም ተናግረዋል። የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የልማት ተነሲዎች ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ተስፋ በበኩላቸው የማመንጫ ጣቢያው የሀገር ብሔራዊ ኩራት ከሆኑ ግዙፍ ፕሮጀክቶች አንዱ ነው ብለዋል። ከጣቢያው ጋር ተያይዞ የሚነሱ ጥያቄዎች ተገቢነታቸውን ዳግም በመፈተሽና በማረጋገጥ ለቅሬታዎች አፋጣኝ ምላሽ መስጠት ያስፈልጋል ነው ያሉት። የልማት ተነሺዎች ችግር በተጋነነ የካሳ ክፍያ ብቻ የሚፈታ ነው የሚል የተሳሳተ አመለካከት መኖሩን የጠቆሙት አቶ አለማየሁ ካሳ እየተገባቸው ሳያገኙ የቀሩ ካሉ መረጃዎቻቸውን በማሰባሰብና በማረጋገጥ እንደሚፈታ ተናግረዋል። ከውሃ አቅርቦት ጋር ያለው ችግር በአፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጠው ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር እንዲሠራም ጠይቀዋል። በውይይቱ የተነሱ ሀሳቦችን እንደግብዓት በመውሰድ ችግሮቹን በዘላቂነት ለመፍታት አመራሩ በትብብር መንፈስ ማህበረሰቡን ማዕከል አድርጎ መስራት እንዳለበትም አሳስበዋል። በውይይቱ ላይ የክልሉ የልማት ተነሺ እና የውሃ ሀብት ቢሮ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የዞንና የወረዳ መስተዳድር አካላት ተሳትፈዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 24 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

photo content

በጣቢያው ከካሳ ክፍያና ከውኃ አቅርቦት ጋር ተያይዞ የሚነሱ ችግሮችን ለመፍታት ያለመ ውይይት እየተካሄደ ነው ....//.... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የገናሌ ዳዋ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ጋር ተያይዞ የሚነሱ የካሳ ክፍያ እና የውኃ አቅርቦት ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ያለመ ውይይት በነገሌ ቦረና ከተማ መካሄድ ጀምሯል። በተቋሙ የኃይል መሰረተ ልማት ደህንነት፣ ክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም የአስተዳደራዊ ጉዳዮችና ዶክመንቴሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ እንደገለጹት ፕሮጀክቶች በሚገነቡብት አካባቢ ለሚነሱ የማህበረሰብ ክፍሎች ደርጅቱ የካሳ ክፍያዎችን እንደሚፈጽም ተናግረዋል። ሆኖም ከልማት ተነሺዎች የሚቀርብ የተጋነነ የካሳ ክፍያ ጥያቄ ለተቋሙ ፈተና እየሆነ መምጣቱን ያወሱት አቶ ዋለ ችግሩን ለመፍታትም ተቋሙ ከመስተዳድር አካላት ጋር በትብብር እየሰራ ነው ብለዋል። አቶ ዋለ አክለውም በገናሌ ዳዋ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ከካሳ ክፍያ እና ከውኃ አቅርቦት ጋር ያሉ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ተቋሙ ቁርጠኛ መሆኑን አንስተዋል። በውይይቱ ላይ የተቋሙና የጣቢያው ኃላፊዎችን ጨምሮ የኦሮሚያ ውኃ ሥራዎች ድርጅት፣ የልማት ተነሽዎች ኤጀንሲ፣ የዞንና ወረዳ መስተዳድር አካላት እየተሳተፉ ይገኛል። ከዚሁ በተጨማሪም በማመንጫ ጣቢያው አካባቢ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ በሚሆኑበት መንገድ ላይም ውይይት ይካሄዳል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 23 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

የውጤት ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጥቅምት 29 ቀን 2017 ዓ.ም በፋርማሲስት 2ኛ እንዲሁም ህዳር 11 ቀን 2017 ዓ.ም በሞግዚት (Child Care) የስራ መደብ በቋሚነት ለመቅጠር ማስታወቂ
+2
የውጤት ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጥቅምት 29 ቀን 2017 ዓ.ም በፋርማሲስት 2ኛ እንዲሁም ህዳር 11 ቀን 2017 ዓ.ም በሞግዚት (Child Care) የስራ መደብ በቋሚነት ለመቅጠር ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ ስሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል በፋርማሲስት 2ኛ በተ.ቁ 1 የተገለፁት እና በሞግዚት (Child Care) ከተ.ቁ 1 እስከ 4 የተገለጻችሁ በተሰጠው የጽሁፍ ፈተና አብላጫ ውጤት ያመጣችሁ በመሆኑ ከታህሳስ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 5 (አምስት) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ በዋናው መ/ቤት ኮተቤ ብረታብረት በሚገኘው የሰራተኛ ምደባ ቢሮ ማስረጃችሁን ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ፎርም እንድትሞሉ እናሳውቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 23 ቀን 2017 ዓ.ም

ተቋማት ህብረተሰቡ ለሚያነሳቸው ጥያቄዎች ግልፅና ተጨባጭ መልስ ሊሰጡ ይገባል ........///......... የመንግሥት ተቋማት ህብረተሰቡ በየደረጃው ለሚያነሳቸው ጥያቄዎች ግልፅና ተጨባጭ መልስ ሊሰጡ እንደሚገባ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ረዳት ተጠሪ ወ/ሮ መሰረት ኃይሌ ገለፁ። በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከህዝብ የተነሱ ጥያቄዎችን መሰረት በማድረግ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተቋማት ማብራሪያ እንዲሰጡ አድርጓል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ለህዝብ እንደራሴዎች በሰጡት ምላሽ ተቋሙ የኃይል ተደራሽነትን ለማሳደግ እየሰራ ይገኛል። የፌዴሬሽን ምክር ቤት የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን ተደራሽነት ለማረጋገጥ በሚያስቀምጠው ቀመር መሰረት ቅድሚያ የሚሰጣቸውን የመለየት ሥራ መሰራቱን ተናግረዋል። እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ ተቋሙ ተጨማሪ 14 አዳዲስ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን እና የማስተላለፊያ መስመሮች ግንባታ ለማስጀመር በሒደት ላይ ነው። ተቋሙ በአሁኑ ወቅት በነባር የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የአቅም ማሳደግና የማዘመን ሥራዎችን በመስራት የኃይል ተደራሽነትን ለማስፋት በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል። የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ፕሮፌሰር መሐመድ አብዱ እንደገለፁት ሁለቱን ተቋማት በጋራ ምላሽ እንዲሰጡ የተፈለገው ተቋማቱ በቅንጅት በመስራት የጋራ መልስ መስጠት ስላለባቸው ነው። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ወደ ተመረጡበት አካባቢ ሲመለሱ በኃይል መሰረተ ልማት ጥበቃ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች መስራት እንዳለባቸው ተናግረዋል። እንደ ፕሮፌሰር መሐመድ ገለፃ የከፍተኛ የኃይል ማከፋፈያ እና ማስተላለፊያ መስመሮችን መጠበቅ የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት ሊሆን ይገባል። በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ረዳት ተጠሪ ወ/ሮ መሰረት ኃይሌ በበኩላቸው ተቋማቱ ከህዝብ ለተነሱት ጥያቄዎች የሰጧቸው ምላሾች መሻሻል የታየበት ቢሆንም ህዝብ ከሚጠብቀው አንፃር ብዙ መስራት ይጠበቅባቸዋል። በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የኃይል አቅርቦትን ተደራሽ ለማድረግና ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ ዘመናዊ አሰራርን መከተል እንደሚገባም ነው ያስገነዘቡት። በተቋማቱ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች የሚበረታቱ መሆኑን የገለፁት ወ/ሮ መሠረት ቋሚ ኮሚቴውም ሆነ ምክር ቤቱ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 22 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል Change Management Officer III (D4)፣Change Management Officer II (D3) እና Occupational Health
+2
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል Change Management Officer III (D4)፣Change Management Officer II (D3) እና Occupational Health & Safety Officer I የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ነሐሴ 28 ቀን 2016 ዓ.ም እና ጥቅምት 29 ቀን 2017 ዓ.ም የውጭ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ በዚሁ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸ አመልካቾች ጥር 06 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ ብረታ ብረት ፊትለፊት በዋናው መ/ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 22 ቀን 2017 ዓ.ም

የተቋረጠው የጅማ - ቦንጋ መስመር ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል .........///........ በአደጋ የተነሳ ኃይል ማስተላለፍ አቋርጦ የነበረው የጅማ-ቦንጋ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ
የተቋረጠው የጅማ  - ቦንጋ መስመር ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል .........///........ በአደጋ የተነሳ ኃይል ማስተላለፍ አቋርጦ የነበረው የጅማ-ቦንጋ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተጠግኖ ትናንት ምሽት ከ3:00 ጀምሮ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የደቡብ ምዕራብ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ጌታሁን ሲሳይ ኤሌክትሪክ የተቋረጠባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ደንበኞች ችግሩ እስኪቀረፍ ድረስ በትዕግስት ስለጠብቁ አመስግነዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 19 ቀን 2017 ዓ.ም