en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 686 subscribers, ranking 8 039 in the Technologies & Applications category and 2 170 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 686 subscribers.

According to the latest data from 04 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 132 over the last 30 days and by -4 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 26.82%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.99% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 208 views. Within the first day, a publication typically gains 2 509 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 9.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 05 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 686
Subscribers
-424 hours
+57 days
+13230 days
Posts Archive
የሁለቱ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች የትውውቅ መርሃግብር አካሄዱ ………///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚዎች እና ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች የተሳተፉበት የተቋማቱ ከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድን የእርስ በእርስ ትውውቅ የትውውቅ መርሃ ግብር አካሄደ፡፡ በተቋማቱ የተደረገውን ሪፎርም ተከትሎ የተመደቡ የሥራ ኃላፊዎችን እርስ በእርስ ለማስተዋወቅ ትናንት ምሽት በተዘጋጀ መርሃግብር ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት በመተጋገዝና ተቀራርቦ በመሥራት በዘርፉ የሚነሳውን ችግር በጋራ መፍታት ይቻላል፡፡ ግንኙነቱ የኃይል ተጠቃሚ ደንበኞችን እርካታ በሚያሳድጉ ጉዳዮች ላይ ጌዜ ሳይጠብቁ ለመነጋገር ዕድል የሚሰጥ ነው ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ጌቱ  ገረመው በበኩላቸው የሁለቱ ተቋማት ግንኙነት ኃይል ከመሸጥና ከመግዛት ያለፈ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ እንደዚህ ዓይነት የግንኙነት መድረኮች የበለጠ የሚያቀራርቡ እና ፈጣን መፍትሔ ለመስጠት የሚያግዙ በመሆናቸው በመደበኛ አሰራሮች ታግዘው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አንስተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 24 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

የሥራ ቅጥር ማስታወቂያ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.
የሥራ ቅጥር ማስታወቂያ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 23 ቀን 2017 ዓ.ም

ጣቢያው ኃይል የማስተላለፍ ታሪካዊ ሚናውን እየተወጣ ነው ……..///…...... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የቃሊቲ አንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል በማስተላለፍ የነበረውን ታሪካዊ ሚና እየተወጣ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለጹ። ሥራ አስኪያጁ አቶ እጅጉ ማሬ እንደገለጹት ማከፋፈያ ጣቢያው በሁለት ትራንስፎርመሮች በባለ 132 ኪሎ ቮልት ሦስት ገቢ መስመሮች ከቆቃ የመነጨውን ኃይል ተቀብሎ ለአቃቂ፣ ለጎፋ እና በጣቢያው ዙሪያ ለሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎች ኃይል ለማስተላለፍ በ1950 ዎቹ የተገነባ ነው። ጣቢያው የትራንስፎርመሮችን ቁጥር በማሳደግ ከቆቃ በተጨማሪ  በ 230 ኪሎ ቮልት ከመልካ ዋከና የኃይል ማመንጪ ጣቢያ ኃይል ተቀብሎ ለገፈርሳ፣ ለኮተቤ፣ ለአዲስ ሴንተር እና ለሰበታ ማከፋፈያ ጣቢያዎች በባለ 132 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች ኃይል ሲሰጥ እንደነበረም ጠቁመዋል። የኃይል ማመንጫዎች በየጊዜው እያደጉ መምጣታቸውን ተከትሎ የትራንስፎርመሮቹ ቁጥር በመጨመር  የመጫን አቅማቸውን ከ63 ሜጋ ቮልት አምፔር ወደ 125 ሜጋ ቮልት አምፔር ከፍ መድረጉንም ተናግረዋል። እንደ አቶ እጅጉ ገለጻ ጣቢያው አሁን ላይ በ 230 ኪሎ ቮልት አራት ገቢ መስመሮች፣  በ 132 ኪሎ ቮልት አስር፣ በ 45 ኪሎ ቮልት አንድ፣ በ 33 ኪሎ ቮልት አራት እንዲሁም በ 15 ኪሎ ቮልት አምስት ወጪ መስመሮች ሲኖሩት በአዲስ አበባ ዙሪያ ላሉት አብዛኞቹ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል እየሰጠ ይገኛል ብለዋል። የማከፋፈያ ጣቢያው ታሪካዊ ሚናውን መወጣት በሚያስችል መልኩ የኃይል ፍላጎቱን ታሳቢ ያደረገ የአቅም ማሳደግ እና የማዘመን ሥራዎችን ለማከናወን ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ ስለመሆኑም ተናግረዋል። የቃሊቲ አንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ በአሁኑ ወቅት 510 ሜጋ ዋት የመጫን አቅም አለው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 23 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

በጣቢያዎቹ የኃይል ምርቱን አስተማማኝነት የሚጨምሩ የጥገና ሥራዎች ተከናውነዋል ….....///……... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአዋሽ 2 እና 3 የውሃ ኃይል ማመንጫዎችን የኃይል ምርት አስተማማኝነት የሚጨምሩ የጥገና ሥራዎች በራስ አቅም መከናወናቸው ተገለጸ። የጣቢያዎቹ የጥገና ክፍል ኃላፊ አቶ ሮቤል አበበ  እንደገለጹት በማመንጫ ጣቢያዎቹ የቅድመ መከላከል፣ የትንበያ እና የፍተሻ ጥገና ሥራዎችን በራስ አቅም በማከናወን ዩኒቶቹ የአቅማቸውን ከ95 በመቶ በላይ ኃይል እያመረቱ ይገኛል። የአዋሽ ሦስት ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የመቆጣጠሪያ ብሬከርን በመቀየር ቆሞ የነበረው ተርባይን እንዲሰራ በማድረግ የኃይል ምርቱን አስተማማኝነቱን ማስጠበቅ መቻሉን ገልፀዋል። በአዋሽ ሁለት ጣቢያ ከአሁን ቀደም የነበሩ መቆጣጠሪያ ብሬከሮች ረጅም ጊዜ ያገለገሉና የተለያዬ ጉዳት የደረሰባቸው እንደነበሩ የጠቆሙት አቶ ሮቤል ከአዋሽ 7 ኪሎ ዲዝል ጣቢያ የነበረን ብሬከር በማምጣት ተከላ ተጠናቆ የሙከራና የፍተሻ ሥራዎችን እያከናወኑ መሆናቸውን አስታውቀዋል። በተጨማሪም ለአካባቢው ማህበረሰብ አገልግሎት የሚሰጡ ባለ 15 ኪሎ ቮልት መቆጣጠሪያ ብሬከሮችን ሙሉ በሙሉ በአዲስ በመቀየር ወደ አገልግሎት ማስገባት መቻሉንም አብራርተዋል። የጥገና ሥራዎች በራስ አቅም መከናወናቸው ጣቢያዎቹ ለረጅም ዓመት አስተማማኝ ኃይል እንዲያመርቱ ከማስቻሉም በላይ ጊዜንና ወጪን በመቆጠብ የሠራተኞች ቡድናዊ ስሜት እንዲጠነክር እና እርስ በእርስ ልምድ በመለዋወጥ አቅማቸውን የሚያጎለብቱበትን ዕድል መፍጠሩን ተናግረዋል። የአዋሽ 2 እና 3 ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ጌታቸው አበበ በበኩላቸው ጣቢያዎቹ 64 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ኖሯቸው ከ60 ዓመት በፊት ኦፕሬሽን ቢጀምሩም ዛሬም ከ56 ሜጋ ዋት በላይ ኃይል እያመነጩ እንደሚገኙ ገልጸዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለጻ ጣቢያዎቹ የተሰሩት የቆቃ ኃይል ማመንጫ ግድብን ተከትለው በመሆኑ ከቆቃ በሚለቀቀው የውሃ መጠን የበጀት ዓመቱን የኃይል ምረት እቅድ ለማሳካት እየሰራ ነው። ተርባይኖች እንዳይቆሙ ዕቃዎች ላይ ማሻሽያ በመስራት በራስ አቅም በርካታ የጥገና ሥራዎችን እየተሰሩ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ጌታቸው ጣቢያዎቹ ረጅም ዓመት ያገለገሉ ከመሆናቸው ጋር ተያይዞ የመልሶ ግንባታ ሥራ የሚፈልጉ መሆናቸውን አስገንዝበዋል። የጥገና ሥራዎችን በአግባቡ ለማከናወን ባለሙያዎቹ አጫጭር የሥራ ላይ ሥልጠናዎች እንዲያገኙ በማድረግ የእርስ በእርስ መማማሪያ ሥርዓት መዘርጋቱም ጠቁመዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 23 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

የማከፋፈያ ጣቢያው የፍተሻና የሙከራ ሥራ በስኬት ተጠናቋል ……....///…….... የመቱ ማሻ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና የማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት የፍተሻና የሙከራ ሥራ በስኬት መጠናቀቁን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ገለጹ። ሥራ አስኪያጁ አቶ አሸናፊ ሙሉብርሃን እንደተናገሩት የማከፋፈያ ጣቢያው ከዓለም  ባንክ በተገኘ 7 ሚሊዮን ዶላር ብድር  እና ተቋሙ በመደበው አንድ ቢሊየን ብር  ለማሻና ለአካባቢው አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር በማድረጉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያን የኃይል ትስስር ለማሳለጥ ህዳር 2012 ዓ.ም ነበር ግንባታው የተጀመረው። የማከፋፈያ ጣቢያው የፍተሻና የሙከራ ሥራ ትናንት በስኬት ተጠናቆ በዛሬው ዕለት ትራንስፎርመሩን ሥራ የማስጀመር ሥራ መከናወኑን ገልፀዋል። የማከፋፈያ ጣቢያው እያንዳንዳቸው 50 ሜጋ ቮልት አምፔር የመሸከም አቅም ያላቸው ሁለት ትራንስፎርመሮች እንዲሁም ስድስት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች እንዳሉት ተናግረዋል፡፡ አካባቢው በተፈጥሮ ሀብት የታደለ ቢሆንም ለረጅም ጊዜ የመብራት አቅርቦት ባለመኖሩ ነዋሪዎቹ የሀብቱ ተጠቃሚ ሳይሆኑ ቆይቷል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያው ሥራ መጀመር የማሻ ከተማና አካባቢው አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያገኝ በማድረግ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎችን እንደሚያነቃቃ አስረድተዋል። የመቱ ማሻ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታውን ሲኖ ሃይድሮ ኮርፖሬሽን የተባለው የቻይና ኩባኒያ ሲያከናውን በአማካሪነት ደግሞ ኢ. ኤል. ሲ. ELC የተባለ የጣሊያን ኩባንያ ተሳትፎበታል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 22 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+3

ግድቡ በበጀት ዓመቱ ለማመንጨት የታቀደውን ኃይል ለማሳካት የሚያስችል ውሃ ይዟል ……...///......... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የቆቃ የውሃ  ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ግድብ በ2017 በጀት ዓመት ለማመንጨት የያዘውን ዕቅድ ለማሳካት የሚያስችል የውሃ መጠን መያዙን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ሞርካ ኃይሌ እንደገለጹት ከአባ ሳሙኤል ቀጥሎ በ1952 ዓ.ም ሥራ የጀመረው የቆቃ የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላለፉት 65 ዓመታት አስተማማኝ ኃይል እያመረተ ይገኛል። ማመንጫ ጣቢያው በ2017 በጀት ዓመት 134 ነጥብ 9 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ለማምረት አቅዶ በ9 ወራት ውስጥ 119 ጊጋ ዋት ስዓት ኃይል ማምረቱን ጠቁመዋል። ከግድቡ የሚለቀቀው ውሃ በሕብረተሰቡ ላይ የጎርፍ አደጋ እንዳይደርስ እንዲሁም ከማመንጫው በታችኛው ተፋሰስ ለሚገኙ ሰፋፊ የእርሻ ልማቶች የሚያስፈልገውን የውሃ መጠን ለመልቀቅ በግድቡ የሚገኘው ውሃ በውሃና ኢነርጅ ሚኒስቴር እና በአዋሽ ተፋሰስ ክትትልና ቁጥጥር እንደሚደረግበት ገልጸዋል። አሁን ላይ በግድቡ ያለው የውሃ መጠን ከባህር ጠለል በላይ 1586 ነጥብ 68 ሜትር ሲሆን ባለፈው በጀት ዓመት በተመሳሳይ ወቅት ከባህር ጠለል በላይ 1587 ነጥብ 01 ሜትር እንደነበር አውስተዋል። በግድቡ ውስጥ የሚገኘው የውሃ መጠን ጣቢያው በቀሪ ወራት ያለምንም የውሃ እጥረት ኃይል እንዲያመነጭና ዓመታዊ ዕቅዱን እንዲያሳካ የሚያስችለው መሆኑን አቶ ሞርካ ተናግረዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለጻ ዕቅዱን ለማሳካት ከውሃ አስተዳደር ሥራው ጎን ለጎን ሣምንታዊና ወርሃዊ የጥገና ሥራዎች በዕቅድ ተይዘው በመከናወን ላይ ናቸው። ጣቢያው ከ65 ዓመታት በኋላም ሲገነባ ከተቀመጠለት 110 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ አማካይ ዓመታዊ የኃይል ምርት እያመረተ መሆኑን ገልፀው ለዚህም የኦፕሬሽንና የጥገና ክፍሉ ሚና ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዋል። ከ25 ዓመት በፊት በኤሌክትሮ ሜካኒካል ክፍሉ ላይ የመልሶ ግንባታ ሥራ መከናወኑን የጠቆሙት አቶ ሞርካ አሁንም ጣቢያው ረጅም ዓመት ከማገልገሉ ጋር ተያይዞ በተለያዩ ክፍሎች ላይ የመልሶ ግንባታ ሥራ እንደሚያስፈልገው አመልክተዋል። የግድቡን ደህንነት ለመጠበቅና የእምቦጭ አረምን ለመከላከል ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ መልኩ በዕቅድ ተይዞ እየተከናወነ ነው ብለዋል። የቆቃ የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በሦስት ተርባይን 43 ነጥብ 2 ሜጋ ዋት የማምረት አቅም አለው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 22 ቀን 2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1446 ኛው ዓመተ ሂጅራ የዒድ አል ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልፃል:: ኢድ ሙባረክ!
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1446 ኛው ዓመተ ሂጅራ የዒድ አል ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልፃል:: ኢድ ሙባረክ! 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 20 ቀን 2017 ዓ.ም

የአርባ ምንጭ ሁለተኛ ማከፋፈያ ጣቢያ የግንባታ ሥራ 65 በመቶ ደርሷል ……..///………. የደቡባዊ የኤሌክትሪክ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አካል የሆነው የአርባ ምንጭ ሁለተኛ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ የንባታ አጠቃላይ አፈፃፀም 65 በመቶ ላይ መድረሱን በፕሮጀክቱ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች ሱፐርቫይዘር ተናገሩ። ሱፐርቫይዘሩ አቶ ተመስገን ጥላሁን እንደተናገሩት ፕሮጀክቱ ከወላይታ ሶዶ 2ኛ እና በግንባታ ላይ ከሚገኘው የሽግዳን ማከፋፈያ ጣቢያዎች በሁለት ገቢ መስመሮች ኃይል ተቀብሎ በአስር ባለ 33 እና አምስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ለደንበኞች ኃይል ለማቅረብ እየተገነባ ይገኛል። ማከፋፈያ ጣቢያው ሁለት የባለ 125 አውቶ ትራንስፎርመሮች፣ ሁለት ባለ 63 እና ሁለት ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው ትራንስፎርመሮች የተከላና ገጠማ ሥራዎች እንዲሁም ዘይት የመሙላት ሥራዎች መከናወናቸውን ገልፀዋል። የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች መትከያ፣ የፕሮቴክሽንና ሌሎች የኮሙዩኒኬሽኝ ገመዶች የሚዘረጉበት የመሠረት ሥራ እንዲሁም የ230 እና 132 ኪሎ ቮልት የሲዊች ያርድ የስቲል ስትራክቸር ተከላ ሥራዎች ሲጠናቀቁ የ15 እና 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች የስቲል ስትራክቸር ሥራ ደግሞ በመጠናቀቅ ላይ እንደሚኙ አቶ ተመስገን አስታውቀዋል። የመቆጣጠሪያ ቤቱ የግንባታ ሥራ 80 በመቶ የደረሰ  ሲሆን የኦፕሬተሮች የመኖሪያ ቤቶች የግንባታ ሥራ እየተፋጠነ እንደሆነም ተናግረዋል። የመቆጣጠሪያ ክፍሉንና የፕሮቴክሽን ፓናሎች ገጠማና ገመድ ዝርጋታ፣ የውስጥ ለውስጥ መንገዶችን፣ የፍተሻና ሙከራ እንዲሁም ሌሎች የተጀመሩ ቀሪ ሥራዎችን በቀጣዮቹ ስምንት ወራት በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ለማብቃት ታቅዶ እየተሰራ እንደሆነ ሱፐርቫይዘሩ አስረድተዋል። እንደ ሱፐርቫይዘሩ ገለፃ የፕሮጀክቱ  የሲቪል ሥራ 68 በመቶ እንዲሁም የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራ 40 በመቶ ላይ የደረሰ ሲሆን አጠቃላይ አፈፃፀሙ ደግሞ ከ65 በመቶ በላይ ደርሷል። በአካባቢው ያለውን ግሪድ ስርዓት ለማጠናከር የማከፋፈያ ጣቢያውን ከአርባ ምንጭ 1ኛ ማከፋፈያ ጣቢያ ጋር ለማገናኘት የሚያስችል የማስፋፊያ ሥራ በነባሩ ላይ  መጀመሩንም ጠቁመዋል። ከ37 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ በሆነ ወጪ እየተከናወነ የሚገኘው የአርባ ምንጭ 2ኛ  ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ በከተማዋ አካባቢ ሊገነባ ለታሰበው የተቀናጀ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንደስትሪ ፓርክ እና በ120 ኪሎ ሜትር ውስጥ ለሚገኙ አካባቢዎች አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ እንደሚያስችል ከዚህ በፊት መዘገባችን ይታወሳል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 19 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+8

በብልሽት ምክንያት የተቋረጠውን ኃይል መልሶ የማገናኘት ሥራ እየተሰራ ነው   ………..///……… አዲስ ዌስት ተብሎ በሚጠራው የኮልፌ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ትናንት ምሽት ባጋጠመ የቴክኒክ ችግር የተነሳ ኃይል የተቋረጠባቸውን መስመሮች ለማናኘት ርብርብ እተካሄደ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ዘላለም ጌታነህ እንደገለፁት በጣቢያው አንድ ወጪ መስመር ላይ ባጋጠመ ችግር ከጣቢያው ኃይል ሲያገኙ የነበሩት ዘጠኝ መስመሮች በሙሉ ትናንት ለሊቱን አገልግሎት መስጠት አቋርጠው ነበር፡፡ ይሁንና ኃይል ከተቋረጠ ጊዜ ጀምሮ በተሰራው ሥራ ሰባቱ መስመሮች መልሰው ኃይል እንዲያገኙ ማድረግ የተቻለ ሲሆን ቀሪዎቹን ሁለት መስመሮች ለማገናኘት ርብርቡ መቀጠሉን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ ወደ ወይራ፣ ጦር ኃይሎችና ኮካ እንዲሁም ወደ አማኑኤል መሳለሚያ እህል በረንዳ እና መርካቶ የሚሄዱት መስመሮች የሚኖራቸውን ጭነት በማየት ለማገናኘት አልያም በአቅራቢያ ወደሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች መስመሮቹን በጊዜያዊነት የማዛወር ቴክኒካዊ መፍትሔዎች ጎን ለጎን እየታዩ መሆናቸውንም ጠቁመዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 18 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ተቋሙ የኢፍጣር መርሃ ግብር አካሄደ .......////.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል 1446ኛውን የረመዳን ፆምን ምክንያት በማድረግ የእስልምና እምነት ተከታይ ለሆኑ የተቋሙ ሠራተኞች፣ ደንበኞች እና ባለድርሻ አካላት  በራማዳ ሆቴል የኢፍጣር ወይም  የእራት ግብዣ መርሃ ግብር አካሄደ። በተቋሙ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አንዱዓለም ሲዓ በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ ትላቅ ትርጉም ከሚሠጣቸው ሃይማኖታዊ ትዕዛዛት መካከል ታላቁ የረመዳን ፆም አንዱ መሆኑን አንስተዋል። በዚህ የጾም ወር የኢፍጣር መርሃ ግብር ለሙስሊም ሠራተኞች እና ባለድርሻ አካላት መደረጉ በተቋሙ መተሳሰብን እና መተዛዘንን በማዳበር የጋራ ተቋማዊ እሴትን ለመገንባት ያግዛል ብለዋል። የፕሮግራሙ አስተባባሪ አቶ መሐመድ አለው በበኩላቸው የረመዳን ወር በጾምና በስግደት እንዲሁም የተቸገሩትን በመርዳት ከፈጣሪ ምህረት የሚጠየቅበት መሆኑን ገልጸዋል። ስለሆነም የተቋሙ ሙስሊም ሠራተኞች ከኃጢያት በመራቅ፣ የፈጣሪን ፍራቻ በማጽናት እና የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳት ቀሪ ጾሙን እንዲያሳልፉ ጥሪ አቅርበዋል። በተቋሙ የኃይል ማስተላለፍ ዘርፍ የሠው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ተማም አፍደል በበኩላቸው እንደዚህ ዓይነት መርሃ ግብሮች መዘጋጀታቸው የእርስ በርስ ግንኙነትን ከማጠናከር ባሻገር በተቋሙ ላይ የእኔነት ስሜትን ያሳድጋል  ብለዋል። መርሃ ግብሩ እንደ ተቋም ለሁለተኛ ጊዜ መደረጉን ያስታውሱት ዳይሬክተሩ በቀጣይም ሠራተኛውን  በማስተባበር አቅም የሌላቸውን ማገዝ እንደሚገባ አመልክተዋል። ለመርሃ ግብሩ  መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የነበራቸውን የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢ/ር አሸብር ባልቻን ጨምሮ በየደረጃው የሚገኙ የሥራ ኃላፊዎችን፣ሠራተኞችን እና የፕሮግራሙ አስተባባሪዎችን አመስግነዋል።   💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 18 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

የሀገሪቱን ዕድገት የሚመጥን የኃይል መሰረተ ልማት ግንባታ በመከናወን  ላይ ነው ........///......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሀገራዊ የኢኮኖሚ እድገቱን የሚመጥን የኃይል መሰረተ ልማቶችን ግንባታ እያካሄደ መሆኑን የተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ዳይሬክተር ገለጹ። ዳይሬክተሩ አቶ ሞገስ መኮንን እንደገለጹት በአሁኑ ወቅት ያለ ኤሌክትሪክ ኃይል ኢኮኖሚያዊ እድገትንም ሆነ ማህበራዊ ልማት  ፈጽሞ ማሰብ የማይቻልበት ጊዜ ሆኗል። ተቋሙም ይህን ታሳቢ ያደረጉ የኃይል መሰረተ ልማቶችን ግንባታ በመላ ሀገሪቱ በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል። አሁን ላይ ያለውን ሀገራዊ ኃይል የማመንጨት አቅም ከእጥፍ በላይ ለማሳደግ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ አምስት የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ግንባታ በመከናወን ላይ ነው ብለዋል። ተቋሙ ተጨማሪ የኃይል ፍላጎት ባለባቸው አካባቢዎች የማከፋፈያ ጣቢያዎች የማስፋፊያና የማዘመን ሥራ ከማከናወን ጎን ለጎን ተደራሽነቱንና ፍትሐዊነቱን የሚያሰፉ አዳዲስ የማከፋፈያ ጣቢያዎችንና ማስተላለፊያ መስመሮችን እየገነባ እንደሆነም ተናግረዋል። የሚገነቡ የማከፋፈያ ጣቢያዎችና የማስተላለፊያ መስመሮች እስከ አሁን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ያልነበሩትን አካባቢዎች ተደራሽ ማድረግን ትኩረት ያደረጉ መሆናቸውንም ጠቁመዋል። በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት የኃይል ተደራሽነት ሽፋኑን አሁን ካለበት 54 በመቶ ወደ 78 በመቶ ለማድረስ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን አቶ ሞገስ ገልፀዋል። ከዋናው ግሪድ ኃይል የማያገኙ አካባቢዎችም ኦፍ ግሪድ በሆነ ወይም ከግሪድ ጋር ባልተገናኘ መንገድ ኃይል የሚያገኙበትን መንገድ መንግስት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሆነም ጠቁመዋል። የሀገር ውስጥ የኃይል ፍላጎትን ከማሟላት ባሻገርም በቀጣናው የሚገኙ የጎረቤት ሀገራትን በኃይል ለማስተሳሰር በርካታ ተግባራት በመከናወን ላይ እንደሚገኙ አስረድተዋል። በዚህም ለጅቡቲ፣ ለኬኒያና ለሱዳን ኃይል እየቀረበ መሆኑንና በቅርቡም ለታንዛኒያ ማቅረብ እንደሚጀመር ጠቁመዋል። እንደ አቶ ሞገስ ገለጻ ለጎረቤት ሀገራት እየቀረበ ያለው ኃይል ከሚመነጨው ከ10 በመቶ በታች ድርሻ ቢኖረውም የተቋሙን ከ30 በመቶ በላይ ገቢ እየሸፈነና ለቀጣናዊ ትስስር አስተዋጽዖ እያበረከተ መሆኑን አንስተዋል። እየተገነቡ ያሉ የኃይል መሰረተ ልማቶች የአፍሪካ ህብረት በአጀንዳ 2063 የቀረፀውን አህጉሩን በመሰረተ ልማት የማስተሳሰር ዕቅድ ለማሳካት ጉልህ ድርሻ እንደሚያበረክቱ ነው ያብራሩት። ተቋሙ በአሁኑ ወቅት በኦፕሬሽን ላይ ብቻ የሚገኙ 194 የማከፋፈያ ጣቢያዎች፣ 20 ሺ 673 ኪሎ ሜትር የማስተላለፊያ መስመሮች እና 17 የማመንጫ ጣቢያዎችን ያስተዳድራል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 17 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5