uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 560 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 357-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 160-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 560 obunachiga ega bo‘ldi.

26 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 27 ga, so‘nggi 24 soatda esa -7 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 26.05% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 16.01% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 053 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 491 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 8 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 27 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 560
Obunachilar
-724 soatlar
+147 kunlar
+2730 kunlar
Postlar arxiv
photo content
+5

ለባለሙያዎች በእሳት አደጋ መከላከልና መቆጣጠር ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ ----///--- በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከማዕከላዊ 3 ሪጅን ለተውጣጡ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፍያ ጣቢያዎች ኦፐሬሽን ባለሙያዎች በእሳት አደጋ መከላከልና መቆጣጠር ዙሪያ ለአንድ ሳምንት የተሰጠው ስልጠና መጠናቀቁን የሪጅኑ ጥገናና ኦፕሬሽን ኃላፊ ገለፁ። ኃላፊው አቶ ታደሰ ገብሬ እንደገለጹት ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ጋር በመተባበር ከሪጅኑ ለተውጣጡ ባለሙያዎች መሠረታዊ  የእሳት እና ድንገተኛ  አደጋ  መከላከል ዙሪያ ስልጠና ተሰጥቷል። ሥልጠናው በተግባርና በቴዎሪ ታገዞ መሰጠቱን የጠቆሙት ኃላፊው በሥልጠናው ላይ ከ 20 በላይ ባለሙያዎች መሳተፋቸውንም ተናግረዋል። እንደ አቶ ታደሰ ገለጻ የሥልጠናው ዓላማ በሪጅኑ ውስጥ ባሉ የማስተላለፊያ መስመሮችንና ማከፋፍያ ጣቢያዎች ላይ የሚከሰቱ የእሳት አደጋዎችን አስቀድሞ ለመከላከል ነው። በሪጅኑ ያሉ ባለሙያዎች የእሳት አደጋን አስቀድሞ መከላከል በሚችልባቸውና ሲከሰትም መተግበር ስላለባቸው የደህንነት ሥራዎች ዙሪያ ሥልጠናው በቂ ግንዛቤ እንደፈጠረላቸውም ተናግረዋል። በሥልጠናው ማጠቃልያ ላይ የተገኙት የአዲስ  አበባ  ከተማ  አስተዳደር  የእሳትና  የአደጋ  ስጋት  ስራ  አመራር ኮሚሽን  የስልጠና  ማዕከል ኃላፊ ኮማንደር አለማየሁ ጦፋ ለሰልጣኞች የምስክር ወረቀት ሰጥተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric    ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     መስከረም 25 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

የወላይታ ሶዶ ሁለተኛ የማከፋፈያ ጣቢያ ማስፋፊያ ሥራን በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው …..//….. የወላይታ ሶዶ ሁለተኛ ባለ 400 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ የማስፋፊያ ሥራን በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የብሔራዊ ኤሌክትሪክ ደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ምዕራፍ አንድ ሳይት ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ አንዱዓለም መላኩ እንደገለፁት የብሔራዊ ኤሌክትሪክ ደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አካል የሆነው የወላይታ ሶዶ ሁለተኛ የማከፋፈያ ጣቢያ የማስፋፊያ ሥራ በአሁኑ ወቅት አፈፃፀሙ 40 በመቶ ደርሷል፡፡ በዝናብ ምክንያት የፕሮጀክቱ አፈፃፀም እንዳይጓተት ለማድረግ ክረምቱ ከመግባቱ በፊት ተጨማሪ የሥራ ሰዓቶችን ተግባራዊ በማድረግ የማካካስ ሥራ መከናወኑን የተናገሩት አቶ አንዱዓለም አሁን ላይ ከ140 ሺህ ሜትር ኪዩብ በላይ የአፈር ሙሌትና ከ49 ሺህ ሜትር ኪዩብ በላይ የመሬት ቆረጣ ሥራ መከናወኑን ገልፀዋል። የማስፋፊያ ሥራውን በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ ሊገጥሙ የሚችሉ ስጋቶችን በመከላከል፣ ከዲዛይን ጀምሮ የሥራ ተቋራጩን ዕቅድ ከአማካሪ ድርጅቱ ጋር በቅንጅት በማፅደቅ የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የፕሮጀክቱን አፈፃፀም በየጊዜው በመገምገምና ቀጣይ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ እንዲሁም ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓቶችን በመዘርጋት የክትትልና ቁጥጥር ሥራውን ውጤታማነት ለማሳደግ እየተሰራ እንደሆነም ነው የገለፁት፡፡ የወላይታ ሶዶ ሁለተኛ የማከፋፈያ ጣቢያ የማስፋፊያ ግንባታ በዋናነት አዲስ እየተገነቡ ለሚገኙት ለሽግዳን፣ ቲርጋ እና አርባ ምንጭ ጂ.አይ.ኤስ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል ለማቅረብ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የማስፋፊያ ሥራው የኦሞ ኩራዝ ስኳር ፋብሪካዎች ከሚጠቀሙት የሸንኮራ አገዳ ተረፈ ምርት የሚመነጨውን ከ180 ሜጋ ዋት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል በሽግዳንና ቲርጋ የማከፋፈያ ጣቢያዎች አማካኝነት ወደ ብሔራዊ የኃይል ቋት ለማስገባት ያለመ እንደሆነም ነው ያስረዱት፡፡ ይህም የኢነርጂ ስብጥሩን ከፍ ከማድረጉም በተጨማሪ በሀገሪቱ ያለውን የኃይል አቅርቦት አቅም የሚያሳድግ ነው ብለዋል፡፡ በደቡብ ኢትዮጵያ ኃይል እያቀረቡ የሚገኙት አብዛኞቹ የማስተከላለፊያ መስመሮች ባለ 132 ኪሎ ቮልት ከመሆናቸውም ባሻገር ለበርካታ ዓመታት አገልግሎት ሲሰጡ በመቆየታቸው ሳቢያ አሁን ያለውን የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ለማስተናገድ እንደማይችሉ አቶ አንዱዓለም አስታውሰዋል፡፡ የማስፋፊያ ሥራው ነባሩን የወላይታ ሶዶ ማከፋፈያ ጣቢያ አቅም በ500 ሜጋ ቮልት አምፒር የሚያሳድግና ለኃይል ፍላጎት ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጥ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ የሃዮሰንግ ሄቪይ ኢንደስትሪስ ኮርፖሬሽን የሲቪል ሥራዎች ሥራ አስኪያጅ አቶ አቤኔዘር አለማየሁ በበኩላቸው የወላይታ ሶዶ ሁለተኛ የማከፋፈያ ጣቢያ የማስፋፊያ ሥራ እያንዳንዳቸው 250 ሜጋ ቮልት አምፒር የመጫን አቅም ያላቸው ሁለት ትራንስፎርመሮች ተከላ ሥራን የሚያካትት ነው ብለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የማስፋፊያ ግንባታው የሲቪል ሥራዎች እየተጠናቀቁ መሆናቸውን የገለፁት ሥራ አስኪያጁ ትራንስፎርመሮችን ጨምሮ ለማስፋፊያ ሥራው አስፈላጊ የሆኑ ዕቃዎች ሳይት ሲደርሱ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች እንደሚጀመሩም ተናግረዋል፡፡ የወላይታ ሶዶ ሁለተኛ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የማስፋፊያ ሥራ ከ116 በላይ ለሚሆኑ የአካባቢው ዜጎች ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፍጠሩንም ተናግረዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 24 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ተቋሙ የፕሮጀክቶችን አፈፃፀም ለማሻሻል በትኩረት እየሰራ ነው …..//…. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚያከናውናቸውን የኃይል ማከፋፈያ እና ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክቶችን አፈፃፀም ለማሻሻል በትኩረት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ። በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ክብሮም ካህሳይ እንደገለፁት ተቋሙ በራስ ኃይል እና በውጭ ሥራ ተቋራጮች የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያና የማስተላለፊያ መስመሮችን ግንባታ እያካሄደ ይገኛል። ፕሮጀክቶቹ የኃይል አቅርቦቱን ተደራሽነት በማሳደግ በኩል ሚናቸው የጎላ በመሆኑ በታቀደላቸው ጥራት፣ ጊዜና በጀት እንዲጠናቀቁ ተቋሙ ጠንካራ ክትትልና ቁጥጥር እያደረገ እንደሚገኝ ገልፀዋል። የፕሮጀክቶች የግንባታ ሥራ ሲጀመር በአዋጭነት ጥናቱ ወቅት ያልታዩ ችግሮች እንደሚያጋጥሙ የጠቆሙት አቶ ክብሮም ተቋሙ ከሥራ ተቋራጮችና ከአማካሪዎች ጋር ችግሮችን በጋራ እየገመገመ ቀጣይ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ላይ እንደሚገኝም ነው የተናገሩት። እንደ አቶ ክብሮም ገለፃ የፕሮጀክቶችን አፈፃፀም ለማሳደግ ባለሙያዎች ተገቢውን ዕውቀትና ክህሎት እንዲያገኙ በሀገር ውስጥና በዓለም አቀፍ ተቋማት ጭምር የተለያዩ ሥልጠናዎች እንዲወስዱ እየተደረገ ነው፡፡ ለፕሮጀክት ሥራ አስኪያጆች በፕሮጀክት አስተዳደር ዙሪያ የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎችን በመስጠት ዓለም አቀፍ የብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት እንዲያገኙ መደረጉንም ጠቁመዋል፡፡ በዚህም በአሁኑ ወቅት 40 በመቶ የሚሆኑት የተቋሙ የፕሮጀክት አመራሮች ዓለም አቀፍ የምስክር ወረቀት ማግኘታቸውን የተናገሩት ሥራ አስፈፃሚው ይህም ዓለም አቀፍ ልምዶችንና አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ የፕሮጀክቶችን አፈፃፀም ለማሳደግ ሚናቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃ የፕሮጀክት አስተዳደር ፈተናን ከወሰዱ ተቋማት መካከል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገቡን በመግለፅ ይህም ተቋሙ ተወዳዳሪ የሆኑ የፕሮጀክት አመራሮች እንዳሉት ማሳያ ነውም ብለዋል፡፡ እንደ አቶ ክብሮም ገለፃ ከአቅም ግንባታ ሥራው በተጨማሪ ከውጭ ምንዛሬ፣ ከካሳ ክፍያ፣ ከፅጥታ ችግሮች እና ከስርቆት ጋር የተያያዙ ጉዳዮች በፕሮጀክቶች አፈፃፀም ላይ አሉታዊ ጫና እያሳደሩ ይገኛሉ፡፡ እነዚህን ችግሮች ከሚመለከታቸው የመንግስትና የፀጥታ አካላት እንዲሁም ከማህበረሰቡ ጋር በመተባበር መፍትሔ በመስጠት ፕሮጀክቶች ግንባታቸው ሳይቋረጥ ለመስራት ጥረት እየተደረገ መሆኑንም አብራርተዋል፡፡ ለፕሮጀክቶች የአሰራር መመሪያዎችን በማውጣትና ተግባራዊ በማድረግ፣ የልምድ ልውውጥ መድረኮችን በመፍጠር እንዲሁም ተገንብተው አገልግሎት መስጠት ከጀመሩ የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያ ልምዶችን በመውሰድ ወጥና የተሻለ የፕሮጀክት አፈፃፀም እንዲኖር እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ በዚህም ከጊዜ ወደ ጊዜ የተቋሙ የፕሮጀክት አፈፃፀም እየተሻሻለ በመምጣቱ ሳቢያ ዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ፕሮጀክቶችን የመደገፍ ዝንባሌያቸው እያደገ መምጣቱንም ጠቁመዋል፡፡ ተቋሙ በአሁኑ ወቅት ከ22 በላይ የኃይል ማስተላለፊያ እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ግንባታ በመላው የሃገሪቱ ክፍሎች እያከናወነ ይገኛል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric    ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     መስከረም 23 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

የተቋረጠው ኃይል ሙሉ በሙሉ ተገናኝቷል ......///...... ከቃሊቲ አንድ- መካኒሳ በተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት መስመር አንደኛው ፌዝ ላይ ባጋጠመ ችግር ምክንያት ተቋርጦ የቆየው የኤሌክትሪክ አገልግሎት ሙሉ በሙሉ ተመልሷል። በዚህም ከትላንት ምሽት ጀምሮ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተቋርጦባቸው የቆዩ አካባቢዎች ኃይል ማግኘት ጀምረዋል። ከትላንት ምሽት ጀምሮ ተቋርጦ የቆየውን የኤሌክትሪክ አገልግሎት መልሶ ለማገናኘት የተቋሙ ጥገና ሠራተኞች ርብርብ ሲያደርጉ ቆይተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     መስከረም 23 ቀን 2017 ዓ.ም

#EEP#EBC ፍኖተ ብርሃን የቴሌቪዥንና ሬዲዬ ፕሮግራም በተቋማችን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴዎች ላይ በማተኮር በአዲሱ ዓመት፣ በልዩ አቀራረብ ለዕይታ በሚመች ሰዓት ወደ እናንተ አያደረሰ መሆኑ ይታወቃል። በመሆኑም ዕለተ ሐሙስ መስከረም 23 ቀን ከምሽቱ 3:00 - 3:30 ሰዓት በአማርኛ የቴሌቭዥን ፕሮግራም በዜናዎች ቻናል፣ ዕለተ እሁድ መስከረም  26 ቀን ከምሽቱ 12:10 - 12:40 ሰዓት በኦሮምኛ የቴሌቭዥን ፕሮግራም ቋንቋዎች ቻናል፣ እንዲሁም ዕለተ ዓርብ መስከረም 24 ቀን ከምሽቱ 2:30 - 3:00 ሰዓት በአማርኛ ቋንቋ በብሄራዊ ሬዲዮ በዓይነቱ ልዩ መሰናዶ ይዞላችሁ የሚቀርብ በመሆኑ ዝግጅቱን መከታተል ያስችል ዘንድ የአክብሮት ግብዣውን ከወዲሁ ያቀርባል። የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽ መምሪያ https://youtu.be/urcdDjtWdEg የዩቲዩብ ቻናላችንንም ሰብስክራይብ ያድርጉ! https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric    ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     መስከረም 23 ቀን 2017 ዓ.ም

ከቃሊቲ አንድ - መካኒሳ የተዘረጋው መስመር በመበጠሱ ኃይል ተቋርጧል ……..///…….. ከቃሊቲ አንድ- መካኒሳ የተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር አንደኛው ፌዝ በመበጠሱ ዛሬ ከምሽቱ 2 ሰዓት ሰዓት ጀምሮ ጎፋ ገብርኤል፣ በቄራ፣ በጀርመን አደባባይ፣ በሃና ማሪያም፣ ጀሞ አንድ ኮንዶሚኒየም፣ በለቡ አርሴማ በአካባቢው ኃይል ተቋርጧል፡፡ የደረሰውን ጉዳት በአፋጣኝ በመጠገን አገልግሎቱን ለመመለስ እንቅስቃሴ የተጀመረ ሲሆን ከሰበታ አንድ- መካኒሳ የሚገባውን ተጨማሪ መስመር በመጠቀም ለተወሰኑ አካባቢዎች ኃይል መስጠት ተጀምሯል። በአሁኑ ሰዓት በጎፋ እና መካኒሳ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ከሚወጡት 13 መስመሮች ውስጥ በሰባቱ ኃይል ተቋርጦባቸው ለነበሩ አካባቢዎች ኃይል እየቀረበ ይገኛል። ምሽት ላይ የተበጠሰውን መስመር በመጠገን አገልግሎቱን ለማስቀጠል ጥረቶች ተጀምረዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 22 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ከቆቃ- ሁርሶ በተዘረጋው መስመር ላይ በደረሰ ጉዳት በአካባቢው ኃይል ተቋርጧል ………///………. ከቆቃ-ሁርሶ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥምር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ በተፈፀመ ስርቆት ኃይል መቋረጡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሁለት ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያዎችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ዘበርጋ እንደገለፁት ኃይል የተቋረጠው በአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ ወረዳ በንቲ ቀበሌ ልዩ ስሙ አዋሽ ፓርክ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በአንድ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ላይ በተፈፀመ ስርቆት ምክንያት ነው። የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ በምስራቅ የሃገሪቱ ክፍል ለሚገኙ ከተሞችና አካባቢዎች፣ ለአዲስ አበባ- ጅቡቲ የባቡር መስመር እንዲሁም ለጅቡቲ የኤሌክትሪክ ኃይል እያቀረበ እንደነበረ የገለፁት ዳይሬክተሩ በደረሰው ጉዳት ምክንያት በተጠቀሱት ቦታዎች የኃይል አቅርቦት መቋረጡን ጠቅሰዋል። እንደ አቶ አለማየሁ ገለፃ በስርቆት ምክንያት ከወደቀው አንድ ምሰሶ በተጨማሪ ሰባት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች በአስጊ ሁኔታ ላይ ይገኛሉ። ጉዳት የደረሰበትን የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ለመቀየር የቴክኒክ ባለሙያዎች ቡድን ተዋቅሮ ወደ ሥራ መግባቱን ያነሱት አቶ አለማየሁ ጥገናውን ለማከናወን ተመሳሳይ የመለዋወጫ ዕቃዎችን የመለየትና የማጓጓዝ ሥራዎች እንደሚሰሩ ተናግረዋል። ስርቆት የተፈፀመበት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ጥምር የኤሌክትሪክ መስመሮችን የያዘ በመሆኑ የጥገና ሥራው ከ20 ቀን ያላነሰ ጊዜ ሊወስድ እንደሚችል ገልፀዋል። የጥገና ሥራው ሙሉ በሙሉ እስከሚጠናቀቅ ድረስም ከመስመሩ ኃይል ሲያገኙ ለነበሩ ከተሞችና አካባቢዎች በፈረቃ ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ለማድረግ ጥረቶች ይደረጋሉ ያሉት ዳይሬክተሩ ህብረተሰቡ የተፈጠረውን ችግር ተረድቶ በትዕግስት እንዲጠብቅም ነው መልዕክት ያስተላለፉት። ይህ በእንዲህ እንዳለ ከመተሃራ - አዋሽ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የባቡር መስመር ላይ በሚገኙ ዘጠኝ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ ጉዳት በመድረሱ የጥገና ሥራዎችን ለማከናወን ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ እንደሚገኝም ነው የጠቆሙት። በአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ በኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ ምሰሶ አካላት ላይ እየተፈፀሙ የሚገኙ የስርቆት ወንጀሎች መበራከታቸውን የገለፁት አቶ አለማየሁ የአካባቢው ማህበረሰብ፣ የመስተዳድር እና የፀጥታ አካላት ለኃይል መሰረተ ልማቶቹ ተገቢውን ጥበቃና ትኩረት እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 22 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

#EEP#EBC ፍኖተ ብርሃን የቴሌቪዥንና ሬዲዬ ፕሮግራም በተቋማችን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴዎች ላይ በማተኮር በአዲሱ ዓመት፣ በልዩ አቀራረብ ለዕይታ በሚመች ሰዓት ወደ እናንተ አያደረሰ መሆኑ ይታወቃል። በመሆኑም ዕለተ ሐሙስ መስከረም 23 ቀን ከምሽቱ 3:00 - 3:30 ሰዓት በአማርኛ የቴሌቭዥን ፕሮግራም በዜናዎች ቻናል፣ ዕለተ እሁድ መስከረም  26 ቀን ከምሽቱ 12:10 - 12:40 ሰዓት በኦሮምኛ የቴሌቭዥን ፕሮግራም ቋንቋዎች ቻናል፣ እንዲሁም ዕለተ ዓርብ መስከረም 24 ቀን ከምሽቱ 2:30 - 3:00 ሰዓት በአማርኛ ቋንቋ በብሄራዊ ሬዲዮ በዓይነቱ ልዩ መሰናዶ ይዞላችሁ የሚቀርብ በመሆኑ ዝግጅቱን መከታተል ያስችል ዘንድ የአክብሮት ግብዣውን ከወዲሁ ያቀርባል። የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽ መምሪያ https://youtu.be/urcdDjtWdEg የዩቲዩብ ቻናላችንንም ሰብስክራይብ ያድርጉ! https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric    ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     መስከረም 22 ቀን 2017 ዓ.ም

በሪጅኑ በሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት ጥረት ይደረጋል በሰሜን ሪጅን በሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የሚስተዋሉ የሲቪል፣ የኤሌክትሮ ሜካኒካል እና ሌሎች መሰል ችግሮችን ለመፍታት ጥረት እንደሚደረግ በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ የሥራ ኃላፊዎች በጣቢያዎች የአሰራር ስርዓት፣ በጣቢያዎች ላይ ስለሚስተዋሉ ተግዳሮቶች እና መፍትሄዎች ዙሪያ በሪጅኑ ከሚገኙ የማከፋፈያ ጣቢያ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አካሂደዋል። የጣቢያዎች የአቅም ማነስ፣ የተበላሹ ትራንስፎርመሮች እና ብሬከሮች በወቅቱ ያለመቀየር፣ የተሽከርካሪ፣ የኢንተርኔት፣ የሥራ ላይ መሳሪያዎች አቅርቦት እና የስታፍ ፕላን ያለመሟላት ዋና ዋና ችግሮች እንደሆኑ ተሳታፊወች አንስተዋል፡፡ ፡ ጣቢያዎች የተጣለባቸውን ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ ምቹ የሥራ ከባቢ ከመፍጠር አኳያ የጣቢያ ሠራተኞች የመኖሪያ ቤት ችግርና ጥራት፣ የውስጥ ለውስጥና ከከተማ ወደ ጣቢያ የሚያስገቡ መንገዶች፣ ችግር እልባት ሊሰጥ እንደሚገባም በውይይቱ ተነስቷል። የሰሜን ሪጅን የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሮቤል ገ/ እግዚአብሔር በበኩላቸው በሪጅኑ በሚገኙ ጣቢያዎች ላይ ከሲቪል፣ ከኤሌክትሮ ሜካኒካል፣ ከአደረጃጀትና ከመሳሪያ አቅርቦት ጋር የተያያዙ ችግሮች ለጣቢያ ሠራተኞች የቅሬታ ምንጭ እየሆነም ተናግረዋል። በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፉ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ እንደተናገሩት ውይይቱ ከጣቢያ ኃላፊዎች ግብዓት በመሰብሰብ ለሚነሱ ጉዳዮች በተደራጀ መልኩ መፍትሔ ለመስጠትና ድጋፍ ለሚደረግ ያግዛል። የሥራ ላይ መሳሪያዎች ለማሟላት፣ ምቹ የሥራ ከባቢ ለመፍጠር እና ለተነሱ ችግሮች መፍትሄ ለመስጠት ከሪጅኑ ጋር በመተባበር በአስቸኳይ መፍትሔ አቅጣጫ ተቀምጧል። የተቋሙን ውሳኔ እና የሌሎች የሥራ ክፍሎችን ተሳትፎ የሚጠይቁ ጉዳዮችን ለመፍታት ዘርፉ ጥረት እንደሚያደርግ ያረጋገጡት አቶ ጋሻው በጣቢያዎቹ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮቹን ለመፍታት አንዲሁም የጣቢያዎቹን ደህንነት ለማስጠበቅ ሁሉም የጣቢያ ሠራተኛ የአሰራር ስርዓቱን ተከትሎ ሥራውን ማከናወን እና ሁሉም የራሱን ኃላፊነት መወጣት እንዳለበትም አስገንዝበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 22 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+8

ህፃናትን ሀገር ተረካቢ ለማድረግ የተያዘው ዓላማና ዕቅዳችን ተጠናክሮ ይቀጥላል-ወ/ሮ ሌንሴ ---///--- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የህፃናት ማቆያ ማዕከል የተቋሙን ሴት ሠራተኞች ከስራቸው በተጨማሪ ልጆቻቸውን ማሳደግ ጫናን ከማቃለል ባሻገር የነገውንሀገር ተረካቢ ለማድረግ የተያዘው ዓላማና ዕቅዳችን ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የሴቶች ህጻናትና ወጣቶች መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሲ ኢደኤ እንደተናገሩት ማዕከሉ የተቋሙን ሴት ሰራተኞች ህፃናት ልጆች ተቀብሎ ከሰኞ እስከ አርብ ከጠዋቱ 2፡00 ስዓት እስከ ቀኑ 11፡00 ስዓት ድረስ በመንከባከብ ላይ እንደሚገኝ ገልፀው ህፃናትን በመንከባከብ ረገድ አሁን የሚታየው ወጤት የሚያበረታታና ወላጆቻቸውን ብቻ ሳይሆን የተቋሙን አሰራር ያገዘ ነው፡፡ የህፃናት ማቆያ ማዕከሉ ከ4 ወር እስከ 4 ኣመት ድረስ ላሉ የተቋሙ ሴት ሰራተኞች ልጆች የመኝታ፣ የመጫወቻ፣ የምግብና ሌሎች ተጨማሪ አገልግሎቶችን የሚሰጥ መሆኑ ደረጃውን የጠበቀ ማቆያ ብቻ ሳይሆን እየተደረገ ያለው እንክብካቤ ሀገር ተረካቢ ትውልድን ለመፍጠር መሰረት እየጣለ ያለ ማዕከል ነው ብለዋል፡፡ አሁን ያለውና የሚታየው የህፃናት እንክብካቤና ሀገር ተረካቢ ትውልድን ለመፍጠር የሚደረገው የተቋማችን ትልቅ ዓላማ የሚመሰገንና ሌሎች ሃገራዊና ህዝባዊ ተቋማት ይህን ትልቅ ዓላማ ተረድተው በየቦታቸው እንዲከፍቱትና ሀገር ተረካቢ ትውለድን እንዲያፈልቁ አሳስበዋል፡፡ በህፃናት ማሳደጊያ ማዕከሉ ተጠቃሚ ከሆኑት የተቋሙ ሰራተኞች መካከል ወ/ሮ ቤተልሔም ሽዋንግዛው እንደተናገሩት የማዕከሉ ተጠቃሚ በመሆኔ ስራዬን ተረጋግቼ እንድሰራና ልጄ ጤናማ ሆኖ እንዲያድግልኝ ያደረገልኝ በመሆኑ ደስተኛ ነኝ ብለዋል፡፡ ሌላዋ ተጠቃሚ የተቋሙ ሰራተኛ ወ/ሮ ፍቅርተ ከበደም የልጃቸው እዘህ መሆን በጤና እንዲያድግልኝና ስራዬን ተረጋግቼ እንድሰራ ስላስቻለኝ ተቋሜን አመሰግናለሁ ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የህፃናት ማቆያ ማዕከል አሁን 49 ህፃናትን ከተቋሙ ሴት ሰራተኞች ተቀብሎ በመንከባከብ ላይ ይገኛል ፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 22 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+8

ሪጅኑ በሚያከናውናቸው ሥራዎች ላይ እያጋጠሙ የሚገኙ ችግሮችን ለመፍታት እየተሰራ ነው ....//.... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ሪጅን በሚያከናውናቸው የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎች ላይ እያጋጠሙ የሚገኙ ችግሮችን ለመፍታት እየተሰራ መሆኑን በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ የሥራ ኃላፊዎች ከሰሜን ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና የሥራ መሪዎች እና ሠራተኞች ጋር በሪጅኑ እያጋጠሙ በሚገኙ ችግሮች እና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ውይይት አካሒደዋል፡፡ የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ሮቤል ገ/ እግዚአብሔር በሰሜኑ የሃገሪቱ ክፍል ተከስቶ በነበረው የፀጥታ ችግር ሳቢያ ጉዳት ደርሶባቸው ለነበሩ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ዘላቂ መፍትሔ መስጠት ባለመቻሉ፣ የጣቢያዎችን አቅም ለማሳደግና በዕቅድ ተይዘው የቆዩ ፕሮጀክቶች ትግበራ በመዘግየቱ እና የመልሶ ግንባታ ሥራዎች በአፋጣኝ ባለመከናወናቸው በሪጅኑ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ተግዳሮት አንደሆነ በውይይቱ ወቅት አንስተዋል፡፡ የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ከምዘና ሥርዓት፣ ከዕድገትና ዝውውር፣ ከጥቅማ ጥቅም እና ከሠራተኞች አቅም ግንባታ እንዲሁም ከመለዋወጫ ዕቃዎች እጥረት፣ ከሥራ ላይ ደህንነትና ከሥራ መሳሪያዎች አቅርቦት ጋር የተያያዙ ችግሮች እንደሚስተዋሉ አንስተዋል:: በሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ የማስተላለፊያ መስመሮች ማስተባባሪያ አንድ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ተስፋዬ መንግሥቱ የመለዋወጫ ዕቃዎች አቅርቦት እጥረት እንደ ተቋም የሚስተዋል ችግር መሆኑን ገልፀው ችግሩን ለመቅረፍም ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል። በዚህም ተቋሙ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ አካላት የመለዋወጫ ዕቃዎችን ከሀገር በቀል አምራቾች ግዥ ለመፈፀም በሂደት ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። የሥራ ላይ መሳሪያዎች ችግርን ለመቅረፍ በ1 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዶላር ግዥ በመፈፀም ለሁሉም ሪጅኖች መከፋፈሉን ያስታወሱት አቶ ተስፋዬ በሪጅኑ ያለውን የሥራ ላይ ደህንነትና የሥራ መሳሪያዎች ዕጥረት በዘላቂነት ለመፍታት በትኩረት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። በሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ የማስተላለፊያ መስመሮች ማስተባባሪያ ሁለት ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ፀሐይነህ አበበ በበኩላቸው ጉዳት የደረሰባቸውን የማስተላለፊያ መስመሮች መልሶ ለመጠገን 1 ሺ 700 ኪሎ ሜትር የኮንዳክተር ግዥ መፈፀሙን ተናግረዋል። የኮንዳክተር ገመዶቹ ጥቅም ላይ ከመዋላቸው በፊት ጉዳት የደረሰባቸውን የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች በጥናት በመለየት ወደ ሥራ ለማስገባት ጥረት እንደሚደረግም አብራርተዋል፡፡ በሪጅኑ የሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን አቅም ለማሳደግ እንደሚሰራ የተናገሩት የማከፋፈያ ጣቢያዎች የሪጅን ማስተባበሪያ ሁለት ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘውዱ አስማረ ዘርፉ የፓወር ትራንስፎርመር፣ የብሬከር እና ሌሎች የመለዋወጫ ዕቃ አቅርቦት ችግሮችን ለመፍታት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። በውይይቱ ላይ የማጠቃለያ ሃሳብ ያነሱት በዘርፉ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ ሁሉም ሠራተኛ ተቋማዊ አስተሳሰብ እንዲኖረው በማድረግ ችግሮችን በዘላቂነት መፍታት እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 21 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9