en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 692 subscribers, ranking 8 036 in the Technologies & Applications category and 2 171 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 692 subscribers.

According to the latest data from 03 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 143 over the last 30 days and by -1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 27.84%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.00% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 369 views. Within the first day, a publication typically gains 2 511 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 04 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 692
Subscribers
-124 hours
+47 days
+14330 days
Posts Archive
photo content
+4

ፕሮጀክቱ በጥናት ውጤቱ መሰረት እየተከናወነ ነው ……..///……… የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በአካባቢያዊና ማህበረሰባዊ ጉዳዮች ተፅዕኖ ግምገማ ጥናት ውጤት መሰረት መከናወኑን በፕሮጀክቱ የማህበራዊ ሳይንስ ባለሙያ አስታወቁ፡፡ ባለሙያው አቶ አዲሱ እጅጉ እንዳስታወቁት ፕሮጀክቱ በሚከናወንበት ወቅትና ወደ ኦፕሬሽን ሲገባ በአካባቢና በማህበረሰቡ ላይ ሊኖር የሚችለውን አሉታዊና አዎንታዊ ተፅእኖ ለመለየትና መፍትሔ ለማስቀመጥ የአካባቢያዊና ማህበረሰባዊ ጉዳዮች ተፅዕኖ ግምገማ ጥናት ተካሂዷል፡፡ ጥናቱ ፕሮጀክቱ በአካባቢው መልከዓ ምድር፣ በአየር ንብረት፣ በውሃ አካላት፣ በእፅዋት፣ በእንስሳትና ማህበረሰቡ ላይ ጉዳት ማድረሱንና አለማድረሱን ለማወቅ ትኩረት ያደረገ እንደነበርም አስታውሰዋል፡፡ በጥናቱ ላይ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት መሳተፋቸው እና ጥናቱ በትክክለኛመረጃ ላይ ተመስርቶ መከናወኑ ፕሮጀክቱ ወደ ትግበራ ሲገባ በማህበረሰቡ ተቀባይነት እንዲኖረው ከማድረግ ባለፈ ከማህበረሰቡ ለሚነሱ ጥያቄዎች በጥናቱ መሰረት ምላሽ መሰጠቱን ጠቅሰዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም መሬታቸው በፕሮጀክቱ ለተወሰደባቸው አካላት አስፈላጊውን የካሳ ክፍያ ለመፈፀም፣ ማህበረሰቡ በፕሮጀክቱ ላይ የባለቤትነት ስሜት እንዲኖረው እና ፕሮጀክቱን በተያዘለት ጊዜ እንዲከናወን ለማድረግ ማገዙንም አስረድተዋል፡፡ ፕሮጀክቱ አሁን ለደረሰበት አፈፃፀም የአካባቢያዊና ማህበረሰባዊ ጉዳዮች ተፅዕኖ ግምገማ ጥናት ከፍተኛ ሚና መጫወቱን ባለሙያው አመልክተዋል፡፡                                                                                                                     የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በአርሲ ዞን ሂጦሳ ወረዳ ከሚገኙ ቀበሌዎች አራቱን  ያካልላል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር↠ https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠  https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 6 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

በኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ስርቆት የተነሳ በአማራ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች ኃይል ተቋርጧል .........///....... ከኮምቦልቻ 2 ወደ ኮምቦልቻ 1 ማከፋፈያ ጣቢያ በተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ በተፈፀመ ዝርፊያ ዛሬ ከረፋዱ 5:30 ሰዓት አካባቢ በአንዳንድ አካባቢዎች ኃይል ተቋርጧል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምስራቅ አንድ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ በድሩ አህመድ እንደገለፁት በኮምቦልቻ ከተማ አቅራቢያ በተፈፀመው ዝርፊያ አንድ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ሲወድቅ ሌላኛው ተፈታቶ ከመውደቁ በፊት ተደርሶበታል። በዚህ የተነሳ በኮምቦልቻ ከተማና አካባቢው፣ በደሴ ከተማና አካባቢው፣ በአቀስታ ከተማና አካባቢው እንዲሁም በዓለም ከተማና አካባቢው ኃይል መቋረጡን ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል። የኮምቦልቻ ቁጥር አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ ወደ ደሴ በ66 ኪሎ ቮልት፣ ወደ አቀስታ እና ዓለም ከተማ ማከፋፈያ ጣቢያዎች በ132  ኪሎ ቮልት እንዲሁም ለኮምቦልቻ ከተማ በ15 ኪሎ ቮልት ኃይል ሲሰጥ ነበር። የወደቀውን የብረት ምሰሶ መልሶ ለማቆምና የመውደቅ ስጋት ያጠላበት ሁለተኛውን ምሰሶ በሌሎች ድጋፎች መልሶ ለማቆም ጊዜ የሚፈልግ በመሆኑ ህብረተሰቡ ችግሩን ተገንዝቦ በትዕግስት እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 5 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በታንዛኒያ የኤሌክትሪክ ከባንያ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ሚስተር ጋሲማ ኒያሞ ሀንጋ ድንገተኛ ህልፈት የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀዋል። ኒያሞ ሀንጋ የታንዛኒያን ብሎም የቀጣናውን ኢነርጂ ዘርፍ በምስራቅ አፍሪካ የኃይል ቋት በኩል ለማላቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ባለራዕይና ቁርጠኛ መሪ ሲሉ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገልፀዋቸዋል። በተሽከርካሪ ድንገተኛ አደጋ በደረሰባቸው ህልፈት በእጅጉ ማዘናቸውን ያስታወቁት ኢንጂነር አሸብር ለቤተሰቦቻቸው፣ ለሥራ ባልደረቦቻቸውና ለታንዛኒያ ኤሌክትሪክ ኩባንያ መጸናናትን ተመኝተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 5 ቀን 2017 ዓ.ም

Condolence Message from the CEO of Ethiopian Electric Power (EEP) It is with profound sorrow that I extend my heartfelt condolences on the sudden and tragic passing of Mr. Gissima Nyamo-Hanga, Managing Director of TANESCO, who lost his life in a road accident. Mr. Nyamo-Hanga was a committed and visionary leader whose efforts significantly contributed to advancing the power sector in Tanzania and the regional power trade through the Eastern Africa Power Pool (EAPP). His passing is a significant loss to TANESCO and the broader energy community in EAPP. I express our deepest sympathies to his family, colleagues, and the TANESCO family on behalf of EEP and myself. May you find strength during this difficult time, and may his soul rest in eternal peace. Eng. Ashebir Balcha Chief Executive Officer, EEP 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 5 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

የማከፋፈያ ጣቢያውን አቅም የማሳደግ ሥራ እየተከናወነ ነው …….///………. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምስራቅ 2 ሪጂን ሥር የሚገኘውን የሠመራ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን አቅም ለማሳደግ የሚያስችል ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የጣቢያው ኃላፊ አስታወቁ። ኃላፊው አቶ እንድሪስ አህመድ እንደገለፁት የጣቢያውን የኦፕሬሽን አቅም ለማሳደግ በባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች የዘመናዊ መቆጣጠሪያ ብሬከር ቅየራ ሥራ እየተከናወነ ነው። በማከፋፈያ ጣቢያው ለረጅም ጊዜ አገልግሎት ሲሰጥ  የቆየውን ኤር ኢንሱሌትድ ስዊች ጊር ወደ  ጋዝ ኢንሱሌትድ ስዊችጊር ብሬከር  የመቀየር ሥራ መሰራቱ የጣቢያውን የኦፕሬሽን አቅም ለማሳደግ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። የብሬከር ቅየራው አሁን ላይ 70 በመቶ መድረሱንና ሲጠናቀቅ የጣቢያውን ኃይል የማቅረብ አቅም አስተማማኝና የተቀላጠፈ እንደሚያደርገው ጠቅሰዋል። የሪጂኑ ጥገና ክፍል ኃላፊ አቶ ሙሀመድ አብዱ በበኩላቸው የሠመራ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የዘመናዊ መቆጣጠሪያ ብሬከር ቅየራ ለሠመራ፣ ለሎጊያ፣ ለሚሌ፣ ለአሳይታ፣ ለዱብቲ ከተሞችና ለኢንዱስትሪ ፓርኮች አስተማማኝ ኃይል ማቅረብ ያስችላል ብለዋል። የሰመራ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ከኮምቦልቻ በ 230 ኪሎ ቮልት የተቀበለውን ኃይል ወደ አፍዴራና ዲቾቶ ማከፋፈያ ጣቢያዎች በማስተላለፍ ከ80 በመቶ በላይ የሆነውን የአፋር ክልል ተደራሽ ያደርጋል። አንድ ገቢ መስመርና ሁለት ወጪ መስመሮች ያሉት የሰመራ ማከፋፈያ ጣቢያ በ2003 ዓ.ም  ተገንብቶ ለክልሉ በዋነኛነት ኃይል በማቅረብ እያገለገለ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 5 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

የተቀየረው ትራንስፎርመር ሥራው ጀምሯል ………..///……… በአዲስ ዌስት ወይም ኮልፌ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ብልሽት ገጥሞት በሌላ የተተካው ትራንስፎርመር ሥራ መጀመሩን የማዕከላዊ ሦስ
የተቀየረው ትራንስፎርመር ሥራው ጀምሯል   ………..///……… በአዲስ ዌስት ወይም ኮልፌ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ብልሽት ገጥሞት በሌላ የተተካው ትራንስፎርመር ሥራ መጀመሩን የማዕከላዊ ሦስት ሪጅን አስታወቀ፡፡ የሪጅኑ የጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ  ታደሰ  ገብሬ እንዳስታወቁት የትራንስፎርመር ፍተሻና ሙከራ ሥራ በሥኬት በመጠናቀቁ ትራንስፎርመሩ ሥራ እንዲጀምር ተደርጓል፡፡ የትራንስፎርመሩ ሥራ መጀመር ከጣቢያው ኃይልሲያገኙ በነበሩ አካባቢዎች ለሳምንታት በፈረቃ ሲሰጥ የቆየውን አገልግሎት እንደሚያስቀር ተናግረዋል፡፡ ይሁንና ትራንስፎርመሩ በሙሉ አቅሙ መሥራት ሲጀምር የሚፈጠረውን የኃይል ጭነት ለማቃለል በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል አንድ ወይም ሁለት የሥርጭት መስመሮችን በቅርብ ወደሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች  የማዛወር ሥራ ሊሰራ እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ4 ቀን 2017 ዓ.ም

በጣቢያው የትራንስፎርመር ቅየራ ሥራው ተጠናቋል   ………..///……… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አዲስ ዌስት የኮልፌ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ብልሽት ያጋጠመውን ትራንስፎርመር የመቀየር ሥራ መጠናቀቁን የማዕከላዊ ሦስት ሪጅን አስታወቀ፡፡ በሪጅኑ የጥገና ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ  ታደሰ  ገብሬ እንዳስታወቁት የማከፋፈያ ጣቢያው ካሉት ሁለት ትራንስፎርመሮች በአንዱ ላይ ብልሽት በማጋጠሙ ምክንያት ከጣቢያው ኃይል ሲያገኙ የነበሩት የተወሰኑ አካባቢዎች ላይ ከመጋቢት 18 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ኃይል በፈረቃ ሲሰጥ ቆይቷል፡፡ ችግሩ እስኪፈታ ድረስም ኃይል ለተቋረጠባቸው የምዕራብ አዲስ አበባ አካባቢዎች በቀሪው አንድ ትራንስፎርመር ኃይል በፈረቃ ሲቀርብ መቆየቱን ጠቁመዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ብልሽት ያጋጠመው ትራንስፎርመር የቅየራ ሥራ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ የፍተቫና የሙከራ ሥራ መጀመሩን ተናግረዋል፡፡ የፍተሻና ሙከራ ሥራው በስኬት ከተጠናቀቀ ዛሬ ማምሻውን አልያም ነገ ጠዋት በፈረቃ ኃይል ሲያገኙ የነበሩ አካባቢዎች ወደ መደበኛ የኃይል ሥርጭት እንደሚመለሱ ተናግረዋል፡፡ አቶ ታደሰ ያጋጠመው ችግር እስኪፈታ በትዕግስት ለጠበቁ ነዋሪዎችም ምስጋና አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠  https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 3 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

የጣቢያው የፍተሻና የሙከራ ሥራው በስኬት ተጠናቋል ……..///…….. የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ የፍተሻና የሙከራ ሥራ በስኬት መጠናቀቁን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ጌቱ ያደታ እንዳስታወቁት ማከፋፈያ ጣቢያው ከሦስት አቅጣጫ በአራት የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች እንዲገናኝ በማድረግ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል። ጣቢያው ከቆቃ፣ ከመልካዋከና እና ከበቆጂ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ጋር ለማገናኘት የሁለት የኤሌክትሪክ ተሸካሚ ምሰሶዎችና የሽቦ ዝርጋታ ሥራ በተቋሙ የራስ ኃይል መምሪያ መከናወኑንም ነው አቶ ጌቱ የጠቆሙት። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው የኮሙዩኒኬሽን፣ የስካዳ እና የመቆጣጠሪያ ሥርዓቶች በተቋሙ ባለሙያዎች ተሰርተው ትራንስፎርመሮቹ ወደ ሥራ እንዲገቡ መደረጉን ሥራ አስኪያጁ አስረድተዋል። የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ ሁለት ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሮችና 4 ገቢ መስመሮች እንዳሉትም ነው የጠቀሱት። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በቀጣይ 40 በመቶ የቅድመ ፍተሻ ሥራ የተከናወነላቸውን የንፋስ ተርባይኖች ከኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ጋር በማገናኘት ኃይል እንዲያመነጩ ይደረጋል። በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ በየሳምንቱ 10 ሜጋ ዋት በድምሩ 80 ሜጋ ዋት ወደ ብሔራዊ የኃይል ቋት ለማስገባት ታቅዶ እየተሰራ እንደሆነም ነው አቶ ጌቱ የገለፁት። የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ እንደ ሀገር ከንፋስ የሚመነጨውን ኃይል ከ404 ሜጋ ዋት ወደ 504 ሜጋ ዋት ከፍ በማድረግ የኃይል ስብጥሩን ለማሳደግና አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ያስችላል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠  https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 2 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ የሚፈጸመውን ስርቆት መከላከል ይገባል .....///...... በኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር መስመር የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ የሚፈጸመው ተደጋጋሚ ስርቆት ለመከላከል የሚያስችል ውይይት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በአፋር ክልል አዋሽ ሰባት ከተማ ተካሄደ። በውይይቱ ላይ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትሩ ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ፣ የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ታከለ ኡማን ጨምሮ የአካባቢው የሃይማኖት አባቶች፣ የጎሳ መሪዎች እና የፀጥታ አካላት ተሳትፈዋል። መስመሩ የኢትዮጵያ የወጪ እና ገቢ ዕቃዎች የሚጓጓዙበት መሆኑን በውል መረዳት እንደሚያስፈልግ ኃላፊዎቹ አስረድተዋል። በባቡር መስመሩ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ላይ በሚፈጸም ተደጋጋሚ ስርቆት የተነሳ የባቡር መስመሩን ሙሉ አቅም ለመጠቀም እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን ገልፀዋል። ይህም ገቢ እና ወጪ ዕቃዎች እንዲዘገዩ በማድረግ በዓለምአቀፍ ገበያ ላይ ተወዳዳሪነትን በመቀነስ እና የዋጋ ንረትን በማስከተል በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንደሚያስከትል ተናግረዋል። በመሆኑም ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍ የክልሉ መንግስት፣ ማህበረሰቡ እና ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በባቡር መስመሩ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ የሚፈፀመውን ስርቆት ለመከላከል ከመንግሥት ጎን በመሆን የማጋለጥ ስራ እየሰሩ መሆኑን እና ይሄን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልፀዋል። በአዋሽ-ወልዲያ-ሃራ ገቢያ የባቡር የኃይል አቅርቦት ፕሮጀክት ላይ በአስር ቀናት ውስጥ ብቻ ከ80 ኪሎ ሜትር በላይ የኮንዳክተር ሽቦ ገመድ እና 25 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር የኦፕቲካል ፋይበር መስመር ለስርቆት መዳረጉን መዘገባችን ይታወሳል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 2 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ማከፋፈያ ጣቢያው አቅሙን ለማሳደግ እየሰራ ነው ........///......... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰበታ ሁለት ባለ 400 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ አቅሙን ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን ገለጸ። የጣቢያው ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ አየልኝ እንደገለጹት በባለ 400 ኪሎ ቮልት በሀገሪቱ የመጀመሪያው የነበረው ማከፋፈያ ጣቢያው በ2002 ዓ.ም ወደ ሥራ ሲጀምር በዋናነት የግልገል ጊቤ 2 ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ኃይል ተቀብሎ ለማስተላለፍ ነው። ጣቢያው ከግልገል ጊቤ 2 በገላን ማከፋፈያ ጣቢያ በኩል እንዲሁም ከጊቤ 3 ኃይል ማመንጫ ጣቢያ እና ከሆለታ ማከፋፈያ ጣቢያ በ 400 ኪሎ ቮልት አራት ገቢ መስመሮች ሲኖሩት ካራ ቆሬ አካባቢ ለሚገኘው ሰበታ አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ  እንዲሁም ለኢትዮ ጅቡቲ የባቡር መስመር በ230 ኪሎ ቮልት ጥምር መስመር ኃይል እንደሚሰጥ ተናግረዋል። በማከፋፈያ ጣቢያው ዙሪያ ለሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎችና ለፋብሪካዎች በ33 ኪሎ ቮልት ኃይል የሚሰጥ ሲሆን ከ34 በላይ ወጪ መስመሮች እንዳሉት ገልጸዋል፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው እያንዳንዳቸው 250 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው ሁለት አውቶ ትራንስፎርመሮች እንዳሉት የጠቆሙት አቶ ሙሉጌታ በሦስት መስመር ወደ 60 ሜጋ ዋት አካባቢ ኃይል ለዳታ ማይኒንግ ድርጅት እያቀረበ ይገኛል ብለዋል፡፡ የሰበታ ሁለት ማከፋፈያ ጣቢያ በ 400 ኪሎ ቮልት ጥምር መስመር ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመነጨውን ኃይል ከሆለታ ማከፋፈያ ጣቢያ ተቀብሎ ወደ ብሔራዊ የኃይል ቋት እያስገባ እንደሚገኝ አብራርተዋል። በቀጣይም የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝነት ለመጨመር አንድ ተጨማሪ አውቶ ትራንስፎርመር እና ለአካባቢው ማሕበረሰብ አገልግሎት የሚሰጥ አንድ ፓወር ትራንስፎርመር ከውጪ ለማስገባት በሂደት ላይ መሆኑን ገልጸዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 29 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

በማመንጫ ጣቢያው የዕቃ ግምጃ ቤት የካይዘን አሰራር ተግባራዊ ተደርጓል ……..///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጊቤ ሦስት የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የዕቃ ግምጃ ቤቶች የካይዘን አሰራር ሥርዓት ተግባራዊ መደረጉን ጣቢያው አስታወቀ። የጣቢያው የጥገና ባለሙያ አቶ እሸቱ አበራ እንደተናገሩት የኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎችን ለማቀላጠፍ የሚያግዝ የካይዘን የአሰራር ሥርዓትን በዕቃ ግምጃ ቤቶች ተግባራዊ በማድረግ ውጤታማ ሥራ ተከናውኗል። የካይዘን የአሰራር ሥርዓት ከመተግበሩ በፊት የዕቃ ግምጃ ቤቶቹ ደረጃቸውን ያልጠበቁና ዕቃዎቹም በተለያዩ ቦታ በዘፈቀደ የተቀመጡ እንደነበረ አስታውሰዋል። በዚህም ዕቃዎቹ በሙቀትና በተለያዬ ምክንያቶች በአጭር ጊዜ ከመበላሸታቸውም በተጨማሪ ለሥራ ሲፈለጉ በቀላሉ የማይገኙ በመሆኑ ውጤታማ የኦፕሬሽን እና የጥገና ሥራዎችን ለማከናወን አዳጋች ነበር ብለዋል። ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት በካይዘን የአሰራር ሥርዓት ግንዛቤ ያላቸው ባለሙያዎች ተመድበው ወደ ሥራ መገባቱን ጠቁመዋል። እንደ ባለሙያው ገለጻ በጣቢያው በሚገኙ ሦስት የዕቃ ግምጃ ቤቶች ላይ የሚሰሩና የሚወገዱ የመለዋወጫ ዕቃዎችና መሣሪያዎችን በመለየት በዓይነታቸውና በአገልግሎት ዘመናቸው መሰረት ከሦስት ወር በላይ ጊዜ በመውሰድ የማደራጀት ሥራ ተሰርቷል። ይህም ጣቢያው ያሉትንና የሌሉትን የመለዋወጫ ዕቃዎች ለይቶ እንዲያውቅ በማስቻሉ ቀደም ሲል ዕቃዎቹን ለመፈለግ ይወስድ የነበረውን ጊዜና በብልሽት ምክንያት ያጋጥም የነበረውን አላስፈላጊ ወጭ ማስቀረት መቻሉን ተናግረዋል። የጣቢያው የዕቃ ግምጃ ቤት ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ  ማርታ ጉንቴ በበኩላቸው ከሦስት ወር በላይ ጊዜ በመውሰድ የተደራጁት ዕቃዎች ዓይነትና ዝርዝር መረጃዎች መለያ ተሰጥቷቸው ተመዝግበው መቀመጣቸውን ገልጸዋል። ይህም በግምጃ ቤቱ ውስጥ ያሉ ዕቃዎችን ለማወቅ፣ ያለቁ ዕቃዎችን ለማሟላት እና የሚገቡ ዕቃዎችን በዓይነታቸው አደራጅቶ በማስቀመጥ ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት ማስቻሉን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከአራት ዓመት በፊት ከኢትዮጵያ ካይዘን ኢንስቲትዩት ጋር የካይዘን ትግበራ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሞ ወደ ሥራ መግባቱ ይታወሳል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 29 ቀን 2017 ዓ.ም