ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 572 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 356,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 162

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 572 名订阅者。

根据 24 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 24,过去 24 小时变化为 19,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.91%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.83% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 035 次浏览,首日通常累积 2 465 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 8

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 25 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 572
订阅者
+1924 小时
+197
+2430
帖子存档
ማከፋፈያ ጣቢያው ከ48 ሰዓታት በኋላ ለደንበኞች አገልግሎት መስጠት ይጀመራል ..…..///..…. የደብረ ታቦር ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ከ48 ሰዓታት በኋላ ለደንበኞች አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የራስ ኃይል መምሪያ የፕሮጀክት አስተዳደር አንድ ሥራ አስኪያጅ አቶ ተድላ ሰይፉ እንደገለጹት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታው በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ በተቋሙ የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ ላለፉት አስራ አራት ወራት ሲከናወን ቆይቷል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያው የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች ሙሉ በሙሉ ተጠናቀው ላለፉት ሁለት ወራት የሙከራና የፍተሻ ሥራ ሲከናወን መቆየቱንም ነው የተናገሩት፡፡ በትላንትናው ዕለት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያውን ከአላማጣ ወደ ባህርዳር ከሚሄደው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር ጋር የማገናኘት እንዲሁም በዛሬው ዕለት ደግሞ የትራንስፎርመር ፍተሻና የሙከራ ሥራ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን ገልጸዋል፡፡ እንደ አቶ ተድላ ገለፃ የማከፋፈያ ጣቢያው የፍተሻና የሙከራ ሥራ መጠናቀቁን ተከትሎ አስር ባለ 15 እና አስር ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ከ48 ስዓታት በኋላ ለደንበኞች አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ ይደረጋሉ፡፡ የፕሮጀክቱ በስኬት መጠናቀቅ ሌሎች መሰል ፕሮጀክቶችን በራስ አቅም ማከናወን እንደሚቻል የታየበት ነው ያሉት አቶ ተድላ የማከፋፈያ ጣቢያው ለአገልግሎት ዝግጁ መሆን ለደብረ ታቦርና አካባቢው አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲያገኝ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰት እንደሚያነቃቃ አስረድተዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የበቆጂ ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የሙከራና ፍተሻ ሥራ በማከናወን ለህብረተሰቡ ኃይል ለመስጠት የሚያስችሉ የመጨረሻ ሥራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 23 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ሚሽን 300 ኢትዮጵያን ጨምሮ 300 ሚሊዮን አፍሪካውያንን  ተጠቃሚ ያደርጋል ……..///…….. የአፍሪካ የኃይል ጉባዔ ሚሽን 300 በሚል መሪ ሀሳብ በመጪዎቹ አምስት ዓመታት ኢትዮጵያን ጨምሮ 300 ሚሊዮን አፍሪካውያንን የኤሌትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮጀክት ማቀዱን ይፋ አድርጓል፡፡ ለፕሮጀክቱ ማስፈፀሚያ ከዓለም ባንክ፣ ከአፍሪካ ልማት ባንክ፣ ከኢስላሚክ ልማት ባንክ፣ ከእሲያ የመሰረተ ልማት እና ኢንቨስትመንት ባንክ፣ ከፈረንሳይ ልማት ኤጄንሲ እና ከኦፔክ ፈንድ አጋሮች 53 ነጥብ 95 ቢሊዩን ዶላር መገኘቱን የአፍሪካ ልማት ባንክ ይፋ አድርጓል፡፡ የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት አጃይ ባንጋ እንደተናገሩት በአፍሪካ ከሚገኙ 600 ሚሊዮን ኤሌክትሪክ ኃይል ከማያገኙ ዜጎች ለግማሹ የኤሌትሪክ ኃይል ለማቅረብ ታቅዶ እየተሰራ ነው። ዕቅዱን ለማሳካት ከመንግስታት፣ ከንግድ ተቋማት፣ ከበጎ አድራጎት ድርጅቶች እና ከልማት ባንኮች ጋር በትብብር እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡ ባሳለፈነው ሰኞ እና ማክሰኞ በታንዛኒያ ዳሬሠላም በተደረገው ጉባዔ ላይ 30 የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች ተመጣጣኝ እና አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2030 እንዲስፋፋ ያላቸውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል። በጉባዔው ኃይልን ተደራሽ ለማድረግ ሀገራቱ አስፈላጊ የሆነ ለውጦች ላይ በመስራት 600 ሚሊዮን ሰዎችን ኤሌትሪክ አልባ ያደረገውን ችግር ለመታገል ቆርጠው እንደሚነሱ ቃል ገብተዋል፡፡ ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን አሁን ካለበት 54 በመቶ ወደ 78 በመቶ ለማሳደግ እና በየዓመቱ ለ3 ነጥብ 4 ሚሊዮን ቤተሰብ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ያለመ የኢነርጂ ፖሊሲ ቀርፃ እየሰራች ትገኛለች፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 23 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

የማከፋፈያ ጣቢያው የፍተሻና የሙከራ ሥራ በስኬት ተጠናቋል ……....///…….... የደብረ ታቦር ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና የማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት የፍተሻና የሙከራ ሥራ በስኬት መጠናቀቁን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ገለጹ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ቴዎድሮስ ከፈለኝ  እንደተናገሩት የማከፋፈያ ጣቢያው ለደብረ ታቦርና አካባቢው አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ሰኔ 2015 ዓ.ም ነበር ግንባታው የተጀመረው። የማከፋፈያ ጣቢያው የፍተሻና የሙከራ ሥራ ትናንት በስኬት መከናወኑን እና በዛሬው ዕለትም ትራንስፎርመሩን ሥራ የማስጀመር ሥራ እንደሚከናወን ጠቁመዋል። የማከፋፈያ ጣቢያው 100 ነጥብ 8  ሜጋ ዋት ኃይል የመሸከም አቅም ያላቸው ሁለት ባለ 63 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሮች እንዲሁም አስር ባለ 15 እና አስር ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች እንዳሉት አቶ ቴዎድሮስ ገልፀዋል፡፡ በፕሮጀክቱ የግንባታ ሂደት የፀጥታ ስጋት እንዲሁም የዕቃ አቅርቦት ችግሮች አጋጥመውት የነበረ ቢሆንም ግንባታው በተያዘለት መርሀግብር መጠናቀቁ እንደ ታላቅ ስኬት እንደሚነሳ ተናግረዋል። የደብረ ታቦር ማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ መጀመር  ደብረ ታቦር ከተማ እና አካባቢው አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያገኙ በማድረግ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎችን እንደሚያነቃቃ አስረድተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 23 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

የጎረቤት ሀገራትን በኤሌክትሪክ ኃይል ለማስተሳሰር እየተሰራ ነው …....///…..... ኢትዮጵያ የጎረቤት ሀገራትን በኤሌክትሪክ ኃይል ለማስተሳሰር እየሰራች መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ገለጹ። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀስላሴ በታንዛኒያ በተካሄደው የአፍሪካ ታዳሽ ኃይል ጉባዔ ላይ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ በፓን አፍሪካኒዝም ፍኖተ ካርታ 13 ሀገራትን በኤሌክትሪክ ኃይል ለማስተሳሰር እየሰራች ነው። ሀገሪቱ በአሁኑ ወቅት ለጅቡቲ፣ ለኬኒያና ለሱዳን ኃይል እያቀረበች መሆኑንና በቅርቡም ለታንዛኒያ ማቅረብ እንደምትጀምር ተናግረዋል። በቀጣይም ያላትን እምቅ የታዳሽ ኃይል ሀብት በአግባቡ በመጠቀም ሌሎች የአፍሪካ ሀገራትን በኃይል ለማስተሳሰር የኢነርጂ ፖሊሲ ቀርፃ እየሰራች መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ፕሮጀክቶች ግንባታ ላይ ህዝቡ ንቁ ተሳታፊ መሆኑን የገለፁት ፕሬዝዳንቱ ለዚህም ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ለአብነት አንስተዋል። በሀገር ውስጥ ከኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ጋር የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታትም መንግሥት በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል። በዚህም በየዓመቱ ለ3 ነጥብ 4 ሚሊዮን ቤተሰብ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ እየተደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል። እንደ ሀገር ተቋማዊ ሪፎርም በማድረግ፣ የግል ዘርፉን በማሳተፍና ከልማት አጋሮች ጋር በትብብር በመስራት በዘርፉ ውጤት መገኘቱንም ገልፀዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 21 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

ጣቢያው ባለፉት ስድስት ወራት ከዕቅዱ በላይ ኃይል አመንጭቷል ........///....... የፊንጫ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ለማመንጨት ካቀደው የ17 በመቶ ብልጫ ያለው ኃይል ማምረቱን የጣቢያው ኃላፊ ገለፁ። ኃላፊው አቶ ታደስ ፍቃዱ እንደገለፁት በግማሽ ዓመቱ 348 ጊጋ ዋት ሠዓት ኃይል ለማመንጨት አቅዶ 409 ነጥብ 3 ጊጋ ዋት ሠዓት ኃይል በማምረት የዕቅዱን 117 ነጥብ 62 በመቶ አሳክቷል። ቀደም ሲል በጣቢያው የማቀዝቀዣ ሥርዓት ተፈጥሮ የነበረው ችግር በኃይል ማመንጨት ሥራው ላይ ተፅዕኖ አሳድሮ እንደነበር ኃላፊው አስታውሰዋል። ይሁንና የማቀዝቀዣ ሥርዓቱ በግማሽ ዓመቱ በራስ ኃይል በመጠገኑ ለኃይል ማመንጨት አፈፃፀሙ ከፍ ማለት አስተዋጽዖ ማበርከቱን አመልክተዋል። በራስ ኃይል የተከናወነው የጥገና ሥራ ተቋሙን ከተጨማሪ ወጪ እንዳዳነው የጠቆሙት አቶ ታደሰ ይህ ሥራ በውጭ ተቋማት ቢከናወን ኖሮ የባለሙያ እና የዕቃ ግዥን ጨምሮ 22 ሚሊዮን ብር ያስወጣ እንደነበር አስታውቀዋል። እንደ ኃላፊው ገለፃ የጣቢያውን ዩኒቶች ደህንነት ለማረጋገጥ የፍተሻና ጥገና ሥራዎች በተያዘላቸው መርሃ ግብር መሠረት በአግባቡ ተከናውነዋል። በአሁኑ ወቅት በግድቡ ላይ ያለው የውሃ መጠን በቀሪ ወራት ለማመንጨት የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት የሚያስችል መሆኑንም ተናግረዋል። በ1967 ዓ. ም ኃይል ማመንጨት የጀመረው የፊንጫ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ 134 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም አለው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 20 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ተቋሙ ባለፉት ስድስት ወራት በስርቆት ከ126 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት ደርሶበታል .........///…...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት በኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶ ብረቶችና ሽቦዎች ስርቆት ምክንያት ከ126 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት እንደደረሰበት በተቋሙ የኃይል መሰረተ ልማት ደህንነት፣ ክትትልና ቁጥጥር ቢሮ ገለጸ። የቢሮው  ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ እንደገለጹት በኃይል ማስተላለፊያ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀሙ የስርቆት ወንጀሎች የተቋሙ ብቻ ሳይሆን የብሔራዊ ደህንነት ስጋት ሆነዋል። ባለፉት ስድስት ወራት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች 16 የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ ምሰሶዎች በስርቆት ምክንያት መውደቃቸውን እና በስርቆቱ ከ92 ነጥብ 32 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው 43 ሺ 671 ብረቶች መሰረቃቸውንም ተናግረዋል። የወደቁ የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ ምሰሶዎችንና የተሰረቁ የኮንደክተር ሽቦዎችን መልሶ ለመተካት ከ34 ነጥብ 35 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ መደረጉን የጠቆሙት አቶ ዋለ ባለፉት በስድስት ወራት ብቻ በስርቆቱ ምክንያት ሳይሸጥ የባከነውን ኃይል ሳይጨምር ተቋሙ በአጠቃላይ ከ126 ነጥብ 81 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት እንደደረሰበት ተናግረዋል። እንደ አቶ ዋለ ገለፃ በበጀት ዓመቱ ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር ሠፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች በመከናወናቸው ምክንያት በኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ ይፈፀሙ የነበሩ የስርቆት ወንጀሎች ካለፉት ዓመታት ተመሳሳይ ወቅቶች ጋር ሲነጻጸር መቀነስ አሳይቷል፡፡ የችግሩን አሳሳቢነት በመረዳት ይበልጥ ተደራሽ ለመሆን ተቋሙ በ2017 በጀት ዓመት የኃይል መሰረተ ልማት ደህንነት፣ ክትትልና ቁጥጥር የሥራ ክፍልን አቋቁሞ ወደ ሥራ መግባቱንም ሥራ አስኪያጁ አስታውሰዋል። የሥራ ክፍሉን በቁሳቁስና በሰው ኃይል ለማደራጀት እየተሰራ እንደሆነና በክልል ከተሞች ጭምር መዋቅሩን ለመዘርጋት በቅጥር ሂደት ላይ እንደሚገኝም ነው የተናገሩት፡፡ የክፍሉ መደራጀት በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎችን በባለቤትነት ስሜት እንዲጠብቁ የሚያስችል ሠፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን ለመስራት እንደሚያግዝ  ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት በግንባታ ላይ የሚገኙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክቶችን ሳይጨምር በተቋሙ 41 ሺ 747 የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ ምሰሶዎች በኦፕሬሽን ላይ ይገኛሉ፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 19 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ምርታማነትን ለማሳደግ ምቹ የሥራ ከባቢ መፍጠር ያስፈልጋል ....//.... ለኃይል ምርታማነት ምቹ የስራ ከባቢን መፍጠር ላይ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጫ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት ዕቅድ አፈጻጸሙን በአዳማ ከተማ ገምግሟል። በግምገማው ወቅትም የተሽከርካሪ፣ የመለዋወጫ ዕቃዎችና የሥራ ላይ መሣሪያዎች እጥረት፣ የደመወዝና ጥቅማ ጥቅም፣ የሠራተኞች ደህንነትን ከማረጋገጥ፣ የመኖሪያ ቤት ካለመሟላት እንዲሁም ከትምህርት ቤትና የህፃናት ማቆያ በበቂ ሁኔታ አለመኖር ጋር በተያያዘ የተነሱ ችግሮች እልባት እንዲሰጣቸው በጣቢያዎቹ የሥራ ኃላፊዎችና በሠራተኛ ማህበር የዘርፉ ተወካዮች በኩል ተጠይቋል። በተጨማሪም በተቋሙ እየተከናወነ ስላለው የመዋቅር ማሻሻያ ሥራ፣ ከደረጃ ዕድገትና ዝውውር፣ ከጣቢያዎች የሠው ኃይል አደረጃጀትና  የሠራተኛ እጥረት፣  ከመሬት ይዞታ ማረጋገጫ፣ ከመድኃኒትና ከሠራተኞች የደንብ ልብስ አቅርቦት እንዲሁም ከ"ፒቲ ካሽ" በጀት አመዳደብ ጋር በተያያዘም ጥያቄዎች ተነስተዋል፡፡ ለተነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያ የሰጡት የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አቶ እያየሁ ሁንደሳ ተቋሙ የተጣለበትን ተልዕኮ በአግባቡ እንዲወጣ ለሠራተኞች ምቹ የሥራ ከባቢ መፍጠር ያስፈልጋል ብለዋል። በዚህም የማመንጫ ጣቢያ ሠራተኞችን ደረጃ ከማሻሻል ጀምሮ የመለዋወጫ ዕቃዎችን፣ የደንብ ልብስ፣ የደመወዝና የጥቅማ ጥቅም ጥያቄዎችን ለመመለሰ እየተሰራ እንደሆነም አስረድተዋል። በቀጣይ በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች  ለሚስተዋሉ ችግሮች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር መፍትሔ በመስጠት ሠራተኛው ተረጋግቶ ሥራውን የሚያከናውንበትን ምቹ የሥራ ከባቢ ለመፍጠር ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም ነው ሥራ አስፈፃሚው የተናገሩት። በተቋሙ ተግባራዊ እየተደረገ ያለው የመዋቅር ማሻሻያ ሥራ ተቋማዊ ለውጥ ለማምጣትና ስትራቴጅክ ዕቅዱን ለማሳካት እንደሚያስችል የገለፁት አቶ እያየሁ ሠራተኛው በመዋቅር ማሻሻያው ሳይረበሽ ሥራው ለይ ትኩረት በማድረግ ኃላፊነቱን በአግባቡ መወጣት እንደሚኖርበትም አሳስበዋል። የአሠራር ሥርዓትን ለማዘመን እየተተገበረ ያለውን ሳፕን ጨምሮ በበጀት አጠቃቀም፣ በዕቅድና ሪፖርት አዘገጃጀት፣ በሠራተኞች አቅም ግንባታ እና እውቀት ሽግግር ላይ በትኩረት እንዲሰራ ሥራ አስፈፃሚው  አቅጣጫ አስቀምጠዋል። በዕለቱ የተቋሙን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወክለው መልዕክት ያስተላለፉት በዋና ስራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት የዶክመንቴሽንና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ በበኩላቸው ሠራተኛው ዘርፉ ለተቋሙ የጀርባ አጥንት መሆኑን ተገንዝቦ የተሰጠውን ሥራ በአግባቡ ማከናወን እንደሚጠበቅበት አስታውቀዋል። ከደመወዝ፣ ከተሽከርካሪ እጥረት፣ ከደረጃ እድገትና ዝውውር እንዲሁም ከአደረጃጀት ጋር በተያያዘ የሚነሱ ጥያቄዎች እየተከናወነ ባለው የመዋቅር ማሻሻያ መፍትሔ እንደሚሰጣቸው የጠቆሙት አቶ ዋለ ማሻሻያው በሠራተኛው ኽልውና ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንደማያሳድርም አረጋግጠዋል። በቀጣይ በወጭ ቅነሳ፣ ምቹ የሥራ ከባቢ ፈጠራ፣ ክፍት ቦታዎችን በጓሮ አትክልት ማልማት እንዲሁም ሥራን በአግባቡ ለመፈፀም ራስን ማዘጋጀትና ማብቃት ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ማሳሰባቸውን አቶ ዋለ ተናግረዋል። ተቋሙ ባለፉት ስድስት ወራት 13 ሺ 517 ነጥብ 6 ጊጋ ዋት ሠዓት ኃይል በማምረት የዕቅዱን 115 ነጥብ 6 በመቶ አፈፃፀም ማስመዝገቡን በግምገማው ወቅት ተገልጿል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 17 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

የሦስትዮሽ የኃይል ሽያጭ ሥምምነት ተፈረመ .......///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ  ኃይል፣ የታንዛኒያ የኤሌክትሪክ አቅራቢ ኩባንያ እና የኬንያ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ኩባንያ ሲያካሂዱት የቆዩትን የሦስትዮሽ የኃይል ሽያጭ ድርድር አጠናቀው ስምምነት ላይ ደረሱ። ስምምነቱ በኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ላይ ያተኮሩ የህግ፣ የኮሜርሻል እና የቴክኒክ ጉዳዮች ላይ  መሠረት ያደረገ እንደሆነ በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ወቅት ተገልጿል። የሦስትዮሽ ድርድሩን መጠናቀቅ ይፋ ለማድረግ በተዘጋጀው የፊርማ ሥነ-ሥርዓት ላይ ኢትዮጵያ ከታንዛኒያ ጋር የኃይል ሽያጭ እንዲሁም ኬንያ ከታንዛንያ ጋር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የኪራይ ውል ሥምምነት ተፈራርመዋል። የኃይል ሽያጭ ሥምምነቱ በሀገራቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ፀድቆ ከሚያዝያ 2017 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ የተገለፀ ሲሆን በሥምምነቱ መሠረት ኢትዮጵያ ለታንዛኒያ 100 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ታከናውናለች። ሥምምነቱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የህግ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ መርክነህ ይገዙ፣ የኬንያ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ኩባንያ (KETRACO) ስትራቴጂ ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ጎድፍሬይ ካሪዩኪ እና የታንዛኒያ የኤሌክትሪክ አቅራቢ ኩባንያ (TANSCO) የዕቅድ፣ ምርምር እና ኢንቨስትመንት ምክትል ዳይሬክተር ሚስስ ሬንታ ንድጌ ተፈራርመዋል። በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ወቅት ንግግር ያደረጉት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የህግ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ መርክነህ ይገዙ ሀገራቱ የሦስትዮሽ ድርድሩን ለማሳካት ላደረጉት ጥረት ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የሦስትዮሽ ሥምምነቱ ከኃይል ሽያጭ ባለፈ ለቀጣናዊ የንግድና ኢኮኖሚ ትስስር ፋይዳው የጎላ እንደሆነም ነው የገለፁት። ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያና ኬንያ መካከል የኃይል ሽያጭ ውል ሥምምነት ተፈርሞ ተግባራዊ እየተደረገ እንደሚገኝ ያወሱት ዳይሬክተሩ ከኃይል ሽያጩም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ማግኘት መቻሉን ተናግረዋል። እንደ አቶ መርክነህ ገለፃ ሦስቱ ተቋማት የህግ፣ ኮሜርሻልና ቴክኒክ ጉዳዮች እንዲሁም በጋራ ተባብረው በሚሰሩበት ዙሪያ በጥልቀት ገምግመው የኃይል ሽያጭ ሥምምነቱን አፅድቀዋል። የሦስትዮሽ ሥምምነቱ ኢትዮጵያ በኬንያ በኩል ለታንዛኒያ የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ለማከናወን የሚያስችላትን መብት የሚሰጣት መሆኑንም ነው ዳይሬክተሩ ያብራሩት። የታንዛኒያ የኤሌክትሪክ አቅራቢ ኩባንያ የዕቅድ፣ ምርምር እና ኢንቨስትመንት ምክትል ዳይሬክተር ሚስስ ሬንታ ንድጌ ድርድሩ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ እንዳስደሰታቸው ገልፀው ተቋማቱ ለተግባራዊነቱ በቁርጠኝነት እንዲሰሩ ጠይቀዋል። የኬንያ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ኩባንያ ስትራቴጂ ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ጎድፍሬይ ካሪዩኪ በበኩላቸው የሦስትዮሽ የኃይል ሽያጭ ድርድሩ በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ላደረጉ የሦስቱ ተቋማት ባለሙያዎችም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 16 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

ዘርፉ የስድስት ወሩን የሥራ አፈፃፀም እየገመገመ ይገኛል ...//... የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀምን በአዳማ ከተማ እየገመገመ ይገኛል። በግምገማው ላይ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም፣ የተስተዋሉ ጠንካራ ጎኖች፣ ያጋጠሙ ችግሮች እና ለችግሮቹ የተወሰዱ የመፍትሔ ሃሳቦች እየቀረቡ ውይይት እየተደረገባቸው ይገኛል። ውይይቱ በማመንጫ ጣቢያዎች የሚስተዋሉ የመለዋወጫ ዕቃዎች፣ የሥራ ላይ መሳሪያዎች አቅርቦት እና ሌሎች ችግሮች እልባት ለመስጠት ያግዛል። ከዚህ በተጨማሪም የስድስት ወሩን የሥራ አፈፃፀም በመገምገም በቀጣይ ቀሪ ወራት የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት የሚያስችል አቅጣጫ ለማስቀመጥና በጣቢያዎች መካከል ልምድ ለመለዋወጥ እንደሚያስችል ተገልጿል። ከጥር 15 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለሁለት ቀናት እየተካሄደ ባለው ውይይት የዘርፉን ሥራ አስፈፃሚ አቶ እያየሁ ሁንዴሳን ጨምሮ ሌሎች የዘርፉ እና የሁሉም ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የየማመንጫ ጣቢያ የመሠረታዊ ሠራተኞች ማህበር ተወካዮች እየተሳተፉበት ይገኛል። ውይይቱን የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አቶ እያየሁ ሁንዴሳ እና በዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ ቤት የዶክመንቴሽንና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ እየመሩት ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 16 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ክልሉ ለተቋሙ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገለጸ፤ ...//... የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሚያከናውናቸው የኃይል መሰረተ ልማት ሥራዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገለጸ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ ኃላፊዎች ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አመራሮች ጋር የአሶሳ ማከፋፈያ ጣቢያ የመሬት ይዞታ ለውጥን በተመለከተ ውይይት አድርገዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ እና የንብረት አስተዳደር መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ከሊል ሽፋ ከማከፋፋያ ጣቢያው የመሬት ይዞታ ለውጥ ጋር ተያይዞ በተቋሙ በኩል የሚነሱ ቅሬታዎችንና የማከፋፈያ ጣቢያው የኃይል አቅርቦት በተመለከተ ገለፃ አድርገዋል። የሥራ ኃላፊዎቹ በገለጻቸው የመሬት ይዞታ ለውጡ በአሶሳ ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ በሚከናወነው የማስፋፊያ ሥራ፣ በጣቢያው ደህንነት እና በኃይል አቅርቦቱ ላይ ችግሮችን የሚያስከትል መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የአሶሳ ከተማ ከንቲባ አቶ አብዱልካሪም አብዱራሂም የመሬት ይዞታው ለውጥ በከተማው እየተካሄደ ካለው የኮሪደር ልማት ጋር ተያይዞ የተከሰተ መሆኑንና ለማከፋፈያ ጣቢያውም ምትክ መሬት እንደሚሰጥ ተናግረዋል፡፡ የርዕሰ መስተዳድሩ የመሠረተ ልማት ዘርፍ አማካሪ አቶ አበራ ባያታ በበኩላቸው ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ - አሶሳ ለሚዘረጋው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ እና በነባሩ የአሶሳ ማከፋፈያ ጣቢያ ውስጥ ተቋሙ ለሚያከናውናቸው የማስፋፊያ ሥራዎች የክልሉ መንግስት ተገቢውን ክትትልና ድጋፍ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ በውይይቱ ወቅት እንደተናገሩት ከማከፋፈያ ጣቢያው የመሬት ይዞታ ለውጥ ጋር ተያይዞ እየተነሱ ያሉ ቅሬታዎች በግንኙነትና በመረጃ ክፍተት የተፈጠሩ ናቸው፡፡ ለክልሉ ሁሉን አቀፍ እድገት የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ወሳኝ መሆኑን የገለጹት አቶ ጌታሁን ከተቋሙ ጋር በትብብርና በቅንጅት ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ክልሉ ከተቋሙ ጋር በቅርበት ተባብሮ ለመስራት አሶሳ ከተማ ውስጥ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ቢሮ እንዲያደራጅ ምክትል ፕሬዝዳንቱ ጥሪ አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 14 ቀን 2017 ዓ.ም