en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 540 subscribers, ranking 8 340 in the Technologies & Applications category and 2 161 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 540 subscribers.

According to the latest data from 28 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 1 over the last 30 days and by -4 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 24.98%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.34% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 882 views. Within the first day, a publication typically gains 2 539 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 8.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 29 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 540
Subscribers
-424 hours
-147 days
+130 days
Posts Archive
photo content
+4

የተበጠሰው የባህር ዳር - ጋሸና - አላማጣ መስመር በእልህ አስጨራሽ ርብርብ ተጠግኗል ……..///…….. ትናንት ጉዳት ደርሶበት የተበጠሰው የባህር ዳር - ደብረታቦር - ንፋስ መውጫ - ጋሸና - አላማጣ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር በከፍተኛ ርብርብ መጠገኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የሰሜን ምዕራብ ሪጅን የኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ውበት አቤ እንዳስታወቁት ዛሬ ከማለዳ ጀምሮ በተከናወነው የጥገና ሥራ የተበጠሰውን መስመር መልሶ የማገናኘቱ ሥራ ማምሻውን ተጠናቋል። የባህር ዳር ወልዲያ ኮምቦልቻ የኃይል ማስተላለፊያ ፕሮጀክትን በመገንባት ላይ የሚገኘው ታታ ሊሚትድ ማሽነሪ ከማቅረብ ባለፈ ባለሙያዎቹ ከሪጅኑ የጥገና ባለሙያዎች ጋር እንዲሳተፉ ማድረጉን ተናግረዋል። ጥገናውን ተከትሎ የክልሉ መዲና ባህርዳር፣ ጎንደር እና ሌሎች ከተሞች እንዲሁም የትግራይ መዲና መቀሌና ሌሎች ከተሞች ዳግም ኃይል ማግኘታቸውን ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡ ወልዲያ፣ ኮምቦልቻና በአካባቢው ያሉ ከተሞች እንዲሁም በኮምቦልቻ በኩል ኃይል ሲያገኙ የነበሩት የአፋር መዲና ሠመራ እና ሌሎች ከተሞችን ለማገናኘት ጥረቱ ቀጥሏል። በጥገና ሥራው ላይ ለተሳተፉ የሪጅኑ ባለሙያዎችና ለታታ ሊሚትድ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 27 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

photo content

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቻይልድ ኬር አድሚኒስትሬቲቭ አሲስታንት 1ኛ የሥራ መደብ ሠራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ታህሳስ 15 ቀን 2016 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁ ተወዳዳሪዎች መካከል ወ/ሮ ስንታየሁ ብርሁኑ ፋንታሁን በተሰጠው የጽሁፍ እና የቃል ፈተና ብልጫ ያመጡ በመሆኑ ከየካቲት 26 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የሥራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ በሚገኘው በተቋሙ ዋና መ/ቤት የሰው ኃይል ምደባ ቢሮ በመገኘት የትምህርት ማስረጃ ዋናውን በመያዝ ቀርበው የቅጥር ሂደት እንዲፈፅሙ እናሳውቃለን፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 27 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ተቋሙን ከሳይበር ጥቃት ለመከላከል እየተሰራ ነው- ወንድወሰን ሽፈራው ……..///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ተግባራዊ ማድረግ የጀመረውን የዲጂታል አሰራር ተከትሎ ሊሰነዘሩበት ከሚችሉ የሳይበር ጥቃቶች ራሱን ለመከላከል እየሰራ መሆኑን በተቋሙ የሳይበር ደህንነት ሞኒተሪንግ እና ሪሶርስ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ወንደወሰን ሽፈራው እንዳስታወቁት በተቋሙ የለሙና ተግባራዊ የተደረጉ የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂና የሲስተም መሰረተ ልማቶች እየጨመሩ መምጣታቸውና የተቋሙ አሰራር ዲጂታላይዝ መደረጉ ተቋሙ ለሳይበር ጥቃት ተጋላጭ እንዲሆን ያደርገዋል፡፡ በመሆኑም ተቋሙን ከሳይበር ጥቃት ለመከላከል በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ እና በኦፕሬሽን ዘርፎች የሚተገበሩ ቴክኖሎጂዎች ላይ ትኩረት በማድረግ እየተሠራ ይገኛል ብለዋል፡፡ ተቋሙን ከሳይበር ጥቃት ለመከላከል የሳይበር ደህንነት የሚመራባቸው የተለያዩ ፖሊሲዎችና ማኑዋሎች ተቀርፀው ተግባራዊ መደረጋቸውን ነው አቶ ወንድወሰን የተናገሩት፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በራስ አቅም የሚበለጽጉም ሆነ ከውጪ የሚገዙ ሶፍትዌሮች የሚተገበሩት የሳይበር ጥቃት ተጋላጭነት ደረጃቸው ተፈትሾ ነው፡፡ በኃይል መሰረተ ልማቱ ዘርፍ እየተስፋፋ የመጣውን የሳይበር ጥቃት ስጋት ለማስወገድ የግሪድ መሰረተ ልማቱን ደህንነት ለማስጠበቅ የሚያስችሉ የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ ስለመሆናቸውም አቶ ወንድወሰን አንስተዋል፡፡ የሳይበር ደህንነት ቅድመ ሁኔታዎች ባልተካተቱባቸው የማከፋፈያ እና ማመንጫ ጣቢያዎች ላይ የጥቃት ተጋላጭነት ዳሰሳ በማከናወን እንዲካተቱ እየተደረገ እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡ አዲስ የሚገነቡ የኃይል መሰረተ ልማቶችን ከሳይበር ጥቃት ለመከላከል የሚያስችሉ ሶፍትዌሮችና ሌሎች ቅድመ ሁኔታዎች ተካተውባቸው እንዲገነቡ እየተደረገ ስለመሆኑም አስረድተዋል፡፡ እስከ አሁን ባለው ሁኔታ በተቋሙ ላይ የሳይበር ጥቃት አጋጥሞ እንደማያውቅ አቶ ወንድወሰን አረጋግጠዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 27 ቀን 2016 ዓ.ም

ከባህር ዳር - ጋሸና - አላማጣ የተዘረጋው መስመር በመበጠሱ ኃይል ተቋርጣል ……..///…….. ከባህር ዳር - በደብረታቦር - ንፋስ መውጫ - ጋሸና - አላማጣ የተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር በመበጠሱ በአካባቢዎቹ ኃይል መቋረጡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የሰሜን ምዕራብ ሪጅን የኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ውበት አቤ እንዳስታወቁት ዛሬ ከረፋዱ 4፡30 ሰዓት ጀምሮ በንፋስ መውጫ አካባቢ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ አንደኛው ፌዝ በመበጠሱ ከንፋስ መስጫ - ጋሸና- አላማጣ - መሆኒ - መቀሌ የሚሄደው መስመር ኃይል ተቋርጣል፡፡ የደረሰውን ጉዳት በአፋጣኝ በመጠገን አገልግሎቱን ለመመለስ እንቅስቃሴ መጀመሩን ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ከደብረ ብርሃን - ሸዋሮቢት - ኮምቦልቻ የተዘረጋው መስመር በሸዋ ሮቢት ከተማ አቅራቢያ በመበጠሱ ከሸዋ ሮቢትና ከሚሴ ከተሞች በስተቀር አብዛኛዎቹ የሰሜን ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎች ኃይል መቋረጡን የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ በድሩ አህመድ አስታውቀዋል፡፡ ከኮምቦልቻ በባቲ ኃይል ሲያገኙ የነበሩት የአፋር ክልል መዲና ሰመራና የተለያዩ የክልሉ ዞኖችና ወረዳዎች እንዲሁም በወልዲያ አላማጣ መስመር ኃይል ሲያገኙ የነበሩት የትግራይ ክልል መዲና መቀሌን ጨምሮ አብዛኛዎቹ ከተሞች ኃይል እንደተቋረጠባቸው ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ እንደ አቶ በድሩ ገለፃ ከትናንት በስቲያ ከሰዓት በኋላ የተበጠሰውን መስመር በመጠገን አገልግሎቱን ለማስቀጠል ጥረቶች ተጀምረዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 26 ቀን 2016 ዓ.ም

ምስል ከአርካይቭ
ምስል ከአርካይቭ

photo content
+2

በፕሮጀክቱ ለደህንነት ቅድሚያ ሰጥቶ እየተሠራ ነው ………///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በፕሮጀክቶች ትግበራ ወቅት ለደህንነት ቅድሚያ ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን የበቆጂ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት አስታወቀ። በፕሮጀክቱ የሥራ ደህንነት ባለሙያ የሆኑት ዮዲት ታምሩ እንደገለፁት በፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ የሠራተኞችን የሥራ ላይ ደህንነት ለማስጠበቅ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ይገኛል፡፡ በፕሮጀክቶች ላይ የሚሳተፉ ሠራተኞች ለተለያዩ አደጋዎች ተጋላጭ በመሆናቸው ሠራተኛው ደህንነቱ ተጠብቆ እንዲሰራ ለማድረግ የተለያዩ የሥራ ላይ አደጋ መከላከል ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ እንደ ባለሙያዋ ገለፃ የሠራተኛውን ደህንነት ለማረጋገጥ በሥራ ላይ ስለሚያጋጥሙ አደጋዎች፣ በአደጋ መከላከያ መንገዶች፣ ሠራተኞች በስራ ቦታቸው ላይ ስለሚኖራቸው እንቅስቃሴ እና ከደህንነት መሳሪያዎች አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የግንዛቤ ማስጨበዎች ተሰጥተዋል፡፡ ከግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራው በተጨማሪ ተቋሙ የሥራ ላይ ደህንነት መጠበቂያ መሳሪያዎችን እያቀረበ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ሠራተኛው የተሠጠውን የግንዛቤ ማስጨበጫ በተግባር ላይ ማዋሉን እና በሥራ ቦታው ላይ የደህንነት መሳሪያዎቹን በአግባቡ እየተጠቀመ ስለመሆኑ የክትትል ሥራዎች እንደሚከናወኑም ባለሙያዋ ገልፀዋል፡፡ በፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ ላይ በአናፂነት እየሠሩ የሚገኙት አቶ ደጀኔ ጣፋ እና ሙሐመድ ጉደታ በበኩላቸው ተቋሙ የአደጋ መከላከያ መሳሪያዎችን ከማቅረብ ጀምሮ የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫዎችን እየሠጣቸው እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ የሚሰጣቸውን የግንዛቤ ማስጨበጫ ተግባር ላይ በማዋል ደህንነታቸው ተጠብቆ እየሠሩ እንደሚገኙም አረጋግጠዋል፡፡ በበቆጂ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የግንባታ ሥራ ላይ ከ150 በላይ የሚሆኑ ሰዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 26 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

የማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ የሰረቁ ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ ……..///……. ከጌዶ - ገፈርሳ በተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥምር መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ ስርቆት የፈፀሙ ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ፡፡ ሰለሞን ድሪባ እና ሰኚ ደረጀ የተባሉት ግለሰቦች ጥቅምት 7 ቀን 2016 ዓ.ም. የስርቆት ድርጊቱን የፈጸሙት በሸገር ከተማ አስተዳደር ገፈርሳ ጉጄ ክፍለ ከተማ ልዩ ስሙ መገልቱ በተባለ አካባቢ ነበር፡፡ ወንጀለኞቹ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ብረቶቹን ሰርቀው በመቆራረጥ በማዳበሪያ ይዘው ሲሄዱ እጅ ከፍንጅ የተያዙት በአካባቢው በጥበቃ ስራ ላይ በተሰማሩ ሚሊሻዎች ነው፡፡ ጉዳዩ የቀረበለት የሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ ተከሳሽ ሰለሞን ድሪባ በአራት ዓመት ከአምስት ወር፤ 2ኛ ተከሳሽ ሰኚ ደረጄ በአምስት ዓመት እንዲቀጡ ውሳኔ ማስተላለፉን የማዕከላዊ ሪጅን 1 የማስተላለፊያ መስመር እና ኦፕቲካል ፋይበር ጥገና ሥራ አስኪያጅ ገልፀዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 25 ቀን 2016 ዓ.ም

የፕሮጀክቱን የግንባታ ሥራ እስከ ግንቦት ወር ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው ………///……… የበቆጂ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ግንባታን እስከ መጪው ግንቦት ወር ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን የፕሮጀክቱ የሳይት አስተባባሪ ተናገሩ፡፡ አስተባባሪው አቶ እንዳልካቸው ጃንቦ እንደተናገሩት ትራንስፎርመር የማስቀመጥ፣ የመቆጣጠሪያ ክፍል ጣሪያ የኮንክሪት ሙሊት፣ የውስጥ ለውስጥና መጋቢ መንገዶች ጠረጋ፣ የጣቢያው የግቢ አጥር እና የመኖሪያ ቤቶች የመሰረት ሥራ እና 90 በመቶ የሚሆነው የሲዊችያርድ ቁፋሮ፣ የመሰረትና የብረት ተከላ ሥራዎች ተጠናቀዋል። የሲዊችያርድ የብረት ተከላ፣ የመኖሪያ ቤቶች ኮለን የማቆም እና የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ሥራዎችን ለማጠናቀቅ እየተሰሩ መሆኑን አቶ እንዳልካቸው ገልጸዋል፡፡ እንደ አስተባባሪው ገለፃ የኤሌክትሪክ ዕቃዎችን የመገጣጠም፣ የመሬት ውስጥ መስመሮችን የመዘርጋት፣ የፍሳሽ ማስወገጃ፣ የመኖሪያ ቤቶችና የመቆጣጠሪያ ክፍል የግድግዳ ግንባታና የማጠናቀቂያ እንዲሁም የማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ በቀጣይ የሚከናወኑ ይሆናል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያው የሲቪል ሥራ ከ45 በመቶ እንዲሁም የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች ከ5 በመቶ በላይ መከናወናቸውን የጠቆሙት አቶ እንዳልካቸው ቀሪ የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራዎችን እስከ ግንቦት 2016 ዓ.ም ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡ የበቆጂ ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የሳይት ሥራ አስኪያጅ ተወካይ አቶ ተኮላ ተሾመ በበኩላቸው በአሁኑ ወቅት የማከፋፈያ ጣቢያው አብዛኛዎቹ ሥራዎች መከናወናቸውንና የማስተላለፊያ መስመሩ የምሶሶ መትከያ የመሰረት ቁፋሮ መጀመሩን ተናግረዋል፡፡ ፕሮጀክቱን በተያዘው የበጀት ዓመት መጨረሻ ሥራ ለማስጀመር እየተሰራ እንደሆነ የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ በአሁኑ ወቅት የዕቃ አቅርቦትና የዲዛይን ሥራውን ጨምሮ አፈፃፀሙ 63 ነጥብ 8 በመቶ ደርሷል ብለዋል። እንደ አቶ ተኮላ ገለጻ ለፕሮጀክቱ የሚያስፈልጉ ሁሉም ዕቃዎች ሳይት በመድረሳቸው እና ከካሳ ክፍያ ጋር በተያያዘ ችግሮች ባለመኖራቸው ፕሮጀክቱን በተያዘለት ጊዜ ማጠናቀቅ ይቻላል፡፡ የፕሮጀክቱ አማካሪና ተቆጣጣሪ መሀንዲስ አቶ ሲሳይ አዱኛ እንደተናገሩት የፕሮጀክቱ ሥራዎች በስምምነቱ ላይ በተቀመጠው መስፈርት መሠረት እንዲከናወን ቁጥጥር እየተደረገ ነው፡፡ እስከ አሁን ባለው ሁኔታ ከዕቃዎች ጥራት ጀምሮ የግንባታ ሥራዉ ጥራቱን በጠበቀ እየተከናወነ እንደሚገኝም አረጋግጠዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 25 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

photo content
+9

photo content

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር 4ኛ የሥራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ጥር 17 ቀን 2016 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡ በዚሁ መሰረት የካቲት 19 ቀን 2016 ዓ.ም የጽሁፍ ፈተና ተፈትኛችሁ ያለፋችሁ በመንገድ ትራንስፖርት በሚፈቅደው ህግ እና ደንብ መሰረት ከ74 በላይ ውጤት ያመጣችሁ ለተግባር ፈተና ያለፋችሁ ሲሆን ከተራ ቁጥር 1 እስከ 4 ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች የካቲት 27 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ በሚገኘው ዋናው መ/ቤት ተሽከርካሪ ጥገና አስተዳደር ቢሮ የተግባር ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እሳውቃለን፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 25 ቀን 2016 ዓ.ም

የቦንጋ ሚዛን የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በጊዜያዊነት ተጠግኗል ……..///…….. በባህር ዛፍ መውደቅ የተነሳ ለሶስት ቀናት ተቋርጦ የነበረው የቦንጋ ሚዛን ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር በጊዜያዊነት በእንጨት ምሰሶ ተተክቶ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የደቡብ ምዕራብ ሪጅን ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጌታሁን ሲሳይ እንደገለፁት መስመር ተሸካሚ ምሰሶው በጊዜያዊነት በመጠገኑ ኃይል ተቋርጦባቸው የነበሩት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች ዳግም ኃይል ማግኘት ጀምረዋል። የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን የሚሸከሙ የብረት ምሰሶዎችን በእንጨት ምሰሶዎች መተካት የማይመከር ቢሆንም በጊዜያዊነት የተወሰደ መፍትሔ በመሆኑ ህብረተሰቡና የመስተዳድር አካላት ትልልቅ ዛፎችን በመስመሩ ሥር እንዳይተከሉ በማድረግ እና ለኤሌክትሪክ መሰረተልማቶች ጥበቃ በማድረግ እንዲተባበሩ ዳይሬክተሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 24 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5