en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 540 subscribers, ranking 8 340 in the Technologies & Applications category and 2 161 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 540 subscribers.

According to the latest data from 28 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 1 over the last 30 days and by -4 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 24.98%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.34% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 882 views. Within the first day, a publication typically gains 2 539 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 8.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 29 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 540
Subscribers
-424 hours
-147 days
+130 days
Posts Archive
photo content
+5

በትራንስፎርመር ቃጠሎ ኃይል ተቋርጦባቸው የነበሩ አካባቢዎች ኃይል አግኝተዋል .........///........ በወላይታ ሶዶ ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያ አንድ ትራንስፎርመር ላይ ባጋጠመ የእሳት አደጋ ምክንያት ኃይል ተቋርጦባቸው የነበሩ አካባቢዎች ዳግም ኃይል  እንዲያገኙ መደረጉን የደቡብ 2 ሪጂን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ታዬ እንዳስታወቁት የካቲት 21 ቀን 2016 ዓ.ም ምሽት 5 ሰዓት ላይ በማከፋፈያ ጣቢያው አንድ ትራንስፎርመር ላይ ባጋጠመ  ድንገተኛ የእሳት አደጋ ከጣቢያው ኃይል ሲያገኙ በነበሩ የሶዶ ከተማ እና አካባቢው የኃይል መቋረጥ አጋጥሞ ነበር። የተቋረጠውን ኃይል ለመመለስ በተደረገ አፋጣኝ የጥገና ሥራ ከጣቢያው ኃይል ሲያገኙ የነበሩ ሁሉም አካባቢዎች  ከትላንት ጀምሮ ሙሉ ለሙሉ ዳግም የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያገኙ መደረጉን አቶ ምትኩ ተናግረዋል። አካባቢዎቹ በሶዶ ቁጥር አንድ ከሚገኝ ሌላ ትራንስፎርመር እና ከወላይታ ሶዶ ቁጥር 2 ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል እንዲያገኙ  መደረጉንም ጠቁመዋል። የእሳት አደጋ የደረሰበት ትራንስፎርመር እስኪቀየር ድረስ አካባቢዎች ከወላይታ ሶዶ ቁጥር ሁለት እና በወላይታ ሶዶ ቁጥር አንድ ካለው ትራንስፎርመር ኃይል እንዲያገኙ በመደረጉ በጣቢያዎቹ ላይ የሚፈጥረው ችግር እንደማይኖር ነው የተናገሩት። ከቃጠሎው ጋር በተያያዘ ወደ አርባ ምንጭ፣ ሳውላና ቀይ አፈር ከጣቢያው የሚወጡ መስመሮች ላይ ቃጠሎው ጉዳት ማድረስ አለማድረሱን የመለየት ሥራ ለማከናዎን ሲባል በአካባቢዎቹ ላይ ለተወሰነ ጊዜ ኃይል ተቋርጦባቸው እንደነበርም  አመልክተዋል። ያጋጠመው ችግር እስኪፈታ በትዕግስት ለጠበቁ ደንበኞች ዳይሬክተሩ  ምስጋና አቅርበዋል ።                                                                 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”         የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric    ቴሌግ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     የካቲት 24 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ክለቡ በአቋም መለኪያ ጨዋታ በድጋሚ አሸንፏል ........///......... በሐዋሳ ከተማ ለሚካሄደው ሁለተኛው ዙር የከፍተኛ ሊግ ጨዋታ ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ላይ የሚገኘው የኢትዮ-ኤሌክትሪክ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን በዛሬው ዕለት ባካሔደው የአቋም መለኪያ ጨዋታ የካ ክፍለ ከተማን 2 ለ 1 በመርታት አሸንፏል። ጎፋ መብራት ኃይል ሜዳ በተከናወነው ጨዋታ የኢትዮ-ኤሌክትሪክ የአጥቂ መስመር ተጫዋቾች አቤል ሀብታሙ እና መሳይ ሰለሞን ባስቆጠሯቸው ሁለት ጎሎች የካ ክፍለ ከተማን ሁለት ለአንድ ማሸነፍ ችሏል። ኳስን ይዞ በመጫዎት እና ቶሎ ቶሎ ጎል በመድረስ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በተጋጣሚው ላይ የበላይነት ወስዷል። የካ ክፍለ ከተማዎች በበኩላቸው በመከላከልና በመልሶ ማጥቃት ለመጫወት ሙከራ ቢያደርጉም ከሽንፈት ሳይድኑ ቀርተዋል። የመጀመሪያውን ዙር  በ31 ነጥብ እየመራ የሚገኘው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የሁለተኛውን ዙር ውድድር ለማከናወን በመጪው ሳምንት ወደ ሐዋሳ ከተማ የሚያመራ ይሆናል።                                                                 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”         የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric    ቴሌግ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     የካቲት 23 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

እንኳን ለ128ኛው የአድዋ ድል ቀን አደረሳችሁ! አድዋ የጥቁር ህዝቦች ኩራት! መልካም የድል በዓል! "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን
እንኳን ለ128ኛው የአድዋ ድል ቀን አደረሳችሁ! አድዋ የጥቁር ህዝቦች ኩራት! መልካም የድል በዓል!                                                                 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”         የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric    ቴሌግ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     የካቲት 23 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

ትናንት ማምሻው ላይ ተቋርጦ ያደረው የገፈርሳ ሙገር መስመር ተጠግኗል ……..///…….. ትናንት ማምሻው ላይ ተቋርጦ የነበረው የገፈርሳ ሙገር ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል። የማስተላለፊያ መስመሩ በመበጠሱ ምክንያት የተቋረጠውን መስመር የማገናኘት ሥራ ዛሬ ንጋት 12:00 ሰዓት ላይ ተጀምሮ ከረፋዱ 3:45 ሰዓት ላይ ተጠናቋል። ምሽቱን በሙገር ከተማና አካባቢው እንዲሁም በደርባ፣ ሀበሻ እና ሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካዎች ተቋርጦ ያደረው ኃይል ዳግም ተገናኝቶ አካባቢዎቹና ፋብሪካዎቹ ኃይል አግኝተዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”         የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric    ቴሌግ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     የካቲት 23 ቀን 2016 ዓ.ም

የሚዛን ቦንጋ መስመር ጉዳት ደርሶበታል ……..///…….. የሚዛን ቦንጋ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የባህር ዛፍ በመውደቁ ከትናንት ጀምሮ ኃይል መቋረጡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የደቡብ ምዕራብ ሪጅን ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጌታሁን ሲሳይ እንደገለፁት በመስመር ተሸካሚ ምሰሶው ላይ በደረሰው ጉዳት የምሰሶው ግማሽ አካል ጉዳት ደርሶበታል። በዚህ የተነሳ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች ኃይል ተቋርጦ ማደሩን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። የደረሰውን ጉዳት የመጠገን ሥራ መጀመሩንም አቶ ጌታሁን ገልፀዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”         የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric    ቴሌግ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     የካቲት 23 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

ወደ ሙገር የተዘረጋው መስመር ባልታወቀ ምክንያት ተቋርጧል ……..///…….. ከገፈርሳ ሙገር የተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ባልታወቀ ምክንያት ኃይል ማስተላለፍ ማቋረጡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የማዕከላዊ 1 ሪጅን ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ወንደሰን ወልደማርያም እንደገለፁት ችግሩ የተከሰተው ከገፈርሳ ማከፋፈያ ጣቢያ በ13 ኪሎ ሜትር ርቀት መናገሻ ከተማ አካባቢ ነው። በዚህ የተነሳ በሙገር ከተማና አካባቢው እንዲሁም በደርባ፣ ሀበሻ እና ሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካዎች ኃይል ተቋርጧል። መስመሩ ተደጋጋሚ ስርቆት የሚያጋጥመው ቢሆንም ሰዓቱ በመምሸቱ የተነሳ የችግሩን ትክክለኛ ምክንያት ለማወቅ አለመቻሉን ዳይሬክተሩ ገልፀዋል። ችግሩን ለመለየት ጥረት መጀመሩን የተናገሩት አቶ ወንደሰን መስመሩ ተበጥሶ ከሆነ የማገናኘት ሥራው ነገ ጠዋት ይጀመራል ብለዋል። ይሁንና መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች በስርቆት ምክንያት ወድቀው ከሆነ ግን በሌላ እስኪተካ ተጨማሪ ቀናት እንደሚያስፈልጉና ሌላ መፍትሔ እንደሚታሰብ ጠቁመዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”         የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric    ቴሌግ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     የካቲት 22 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

በእሳት አደጋው ጉዳት የደረሰበትን የትራንስፎርመር ክፍል የመለየት ሥራ እየተከናወነ ነው ………///………. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የወላይታ ሶዶ ቁጥር አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ላይ መነሻ ምክንያቱ ያልታወቀ የእሳት አደጋ ማጋጠሙን የደቡብ ሪጅን 2 የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያ ኦፕሬሽን መምሪያ ገለፀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ታዬ እንደገለጹት በሶዶ ቁጥር አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ላይ ትናንት ምሽት 5፡00 ሰዓት አካባቢ መነሻ ምክንያቱ ያልታወቀ የእሳት አደጋ በመከሰቱ ከፊል የሶዶ ከተማና አካባቢው የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጧል፡፡ ከቃጠሎው ጋር በተያያዘ ወደ አርባ ምንጭ፣ ሳውላና ቀይ አፈር ከጣቢያው የሚወጡ መስመሮች ላይ ቃጠሎው ጉዳት ማድረስ አለማድረሱን የመለየት ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች በጣቢያው ከሚገኝ ሌላ ትራንስፎርመር ኃይል እንዲያገኙ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው የተቃጠለውን ትራንስፎርመር በሌላ በመቀየር በአጭር ጊዜ ችግሩን ለመፍታት እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 22 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

ተቋሙ በራስ ኃይል ባከናወነው የግንባታ ሥራዎች ከ14 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ አድኗል ………///………. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ ባለፉት ስድስት ወራት ባከናወነው የግንባታ ሥራ ተቋሙ ሊያወጣ የነበረውን ከ14 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ማዳኑን አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ሰሎሞን ኃ/ጊዮርጊስ እንዳስታወቁት ባለፉት ስድስት ወራት በመምሪያው ስር ባሉ ሁሉም የሥራ ክፍሎች ከ11 ነጥብ 84 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ለማዳን አቅዶ 14 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ አድኗል፡፡ በበጀት ዓመቱ የተገኘው ውጤት ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ6 ሚሊዮን ብር ብልጫ እንዳለው ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል፡፡ ለፕሮጀክቶች ግንባታ የሚውሉ የግንባታ ግብዓቶችን ግዥ ቀድሞ በመፈፀም፤ ሊከሰት የሚችለውን የዋጋ ግሽበት በመቋቋም፤ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲያልቁ በማድረግ እና ተቋሙ ከጨረታ ግዢ ሊያገኝ የሚችለውን ጥቅም በማስጠበቅ ከዕቅድ ብልጫ ያለው አፈፃፀም ማሳየቱን አቶ ሰሎሞን ተናግረዋል፡፡ መምሪያው ባከናወናቸው ሥራዎች ሀገሪቱ እና ተቋሙ ለውጭ ሥራ ተቋራጮች ሊያወጡት የነበረውን የውጭ ምንዛሪ ማስቀረት መቻሉንም ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡ በራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ የሚገነቡ ፕሮጀክቶች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን የገለፁት ዳይሬክተሩ በበጀት ዓመቱ መጨረሻ ከ23 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ለማዳን ታቅዶ እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ መምሪያው በተቋሙ እየተገነቡ ካሉ ፕሮጀክቶች በተጨማሪ በመንግሰት እየተገነቡ ባሉ ትላልቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ላይ ተሳታፊ እየሆነ መጥቷል፤ በዚህም ተቋሙ በመንግስት በኩል እውቅና እንዲያገኝ ማድረጉን ተናግረዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 22 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

በሪጂኑ ያሉ ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ለማዘመን እየተሰራ ነው ..........///....... በደቡብ ምዕራብ ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽና ጥገና መምሪያ ማከፋፈያ ጣቢያዎችን የኦፕሬሽንና የቁጥጥር ሥራዎችን ለማዘመን እየሰራ መሆኑን አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ጌታሁን ሲሳይ እንዳስታወቁት የማከፋፈያ ጣቢያዎች መቆጣጠሪያ ብሬከሮች ዘመኑን የዋጁ ባለመሆናቸው እና ተጨማሪ ብሬከር የሚያስፈልጋቸው ጣቢያዎች በመኖራቸው በሌላ መቆጣጠሪያ እንዲተኩ ይደረጋል፡፡ በበጀት ዓመቱ የብሬከር ቅየራና ተጨማሪ ብሬከር በሚተከልባቸው የጊቤ፣ በደሌ እና መቱ ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚከናወነው ሥራ ኃይልን በአግባቡ ጥቅም ላይ ለማዋል ያግዛልም ብለዋል። እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ ሥራው በጊቤ ማከፋፈያ ጣቢያ ባለ15 ኪሎ ቮልት እንዲሁም በመቱና በደሌ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ደግሞ በባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮቹ ላይ የሚከናወን ይሆናል፡፡ የመቆጣጠሪያ ብሬከር የማዘመን ሥራው በጣቢያዎቹ ላይ የሚኖረውን የኃይል መቆራረጥ ድግግሞሽ እና የኃይል ብክነትን ለመቀነስ፤ በመለዋወጫ ዕቃ ዕጥረት የተነሳ አገልግሎት ሳይሰጡ የቆዩ መስመሮችን ወደሥራ ለመመለስ እና የብሬከሮችን ኃይል የመጫን አቅም ለማሳደግ እንደሚያግዝ ነው ዳይሬክተሩ የተናገሩት። አቶ ጌታሁን ገለፃ የሚቀየሩ ብሬከሮቹ ለረጅም ዓመታት የሚያገለግሉ እና ከዚህ በፊት በሁለት ብሬከር ሲስተናገድ የነበረውን በአንድ የማስተናገድ አቅም ስላላቸው ለጥገና ሥራ እና ለተጨማሪ ብሬከር ግዥ የሚወጣን ወጪ ይቀንሳሉ፡፡ የብሬከር ቅየራ ሥራው ኃይል ሳይቋረጥ እንደሚከናወን ያነሱት አቶ ጌታሁን በመቱና በደሌ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የሚከናወነው የማዘመን ሥራ እስኪጠናቀቅ ጊዜያዊ አገልግሎት የሚሰጥ የመቆጣጠሪያ ቤይ እንደሚገነባ አስረድተዋል። በጊቤ ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ የሚከናወነው የማዘመን ሥራ ደግሞ ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያ ከተቀመጠ በኋላ እንደሚከናወን ነው የገለፁት። ሪጂኑ የተለያየ የኪሎ ቮልት መጠን ያላቸው 11 ማከፋፈያ ጣቢያዎችን እና 937 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያላቸው የማስተላለፊያ መስመሮችን እያስተዳደረ ይገኛል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 21 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3

ማከፋፈያ ጣቢያዎቹ ተጨማሪ ደንበኞችን የማስተናገድ አቅም አላቸው ………///…….. የአጋሮ፣ የበደሌ እና የመቱ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል የሚፈልጉ ተጨማሪ ደንበኞችን የማስተናገድ አቅም እንዳላቸው የጣቢያዎቹ ኃላፊዎች ገለፁ። የአጋሮ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊ አቶ ዮሴፍ ሞሲሳ እንደገለጹት ጣቢያዉ 50 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የማቅረብ አቅም ቢኖረውም አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው ካለው አቅም በ25 በመቶ ብቻ ነው፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው አንድ ባለ 230 ገቢ መስመር፤ አንድ ባለ 230፣ ሦስት ባለ 33 እና ሁለት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮቸ ሲኖሩት ባሉት አምስት የአነስተኛ ቮልቴጅ ወጪ መስመሮች ለአጋሮ ከተማ እና ከከተማው በ96 ኪሎ ሜትር ርቀት ለሚገኙ ከተሞችና አካባቢዎች ኃይል እያቀረበ ይገኛል፡፡ የበደሌ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊ ተወካይ አቶ ቶፊቅ ሸምሱ በበኩላቸው ጣቢያው 158 ሜጋ ዋት የመሸከም አቅም እንዳለው ገልጸው እያቀረበ ያለው ግን ከ30 ሜጋ ዋት አይበልጥም ብለዋል፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው አገልግሎት መስጠት እንደጀመረ በ15 ኪሎ ቮልት ሦስት ወጪ መስመሮች ለበደሌ ከተማ እና አካባቢው ብቻ ኃይል ሲያቀርብ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ በጣቢያው ላይ የአቅም ማሳደግ ሥራ በማከናወን ተጨማሪ አንድ ባለ 230፣ ሦስት ባለ 33 እና ሦስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮችን በማዘጋጀት ተደራሽነቱን ማስፋት እንደተቻለ ተናግረዋል፡፡ ጣቢያው ባሉት አምስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ለበደሌ ከተማና ቢራ ፋብሪካ እንዲሁም ከከተማዋ እስከ 110 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ለሚገኙ የወረዳ ከተሞችና አካባቢዎች ኃይል እየሰጠ ሲሆን በ33 ኪሎ ቮልት ሁለት ወጪ መስመሮች ደግሞ ጨዋቃ እና ደጋ ለሚባሉ አካባቢዎች ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ ነው የተናገሩት። በተመሳሳይ የመቱ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል የሚፈልጉ ተጨማሪ ደንበኞችን ማስተናገድ የሚያስችል ተጨማሪ አቅም እንዳለው የጣቢያው ኃላፊ ተወካይ አስታውቀዋል። ተወካዩ አቶ ሰይድ አህመድ እንዳስታወቁት የማከፋፈያ ጣቢያው አንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ገቢ መስመር እንዲሁም አንድ ባለ 230፣ አምስት ባለ 33 እና ሦስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች አሉት፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው 40 ሜጋ ዋት የመሸከም አቅም ቢኖረውም ለደንበኞች እየቀረበ ያለው ግን ግማሽ የሚሆነው ብቻ መሆኑን ተወካይ ኃላፊው አንስተዋል፡፡ ጣቢያው ከበደሌ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል ተቀብሎ በ230 ኪሎ ቮልት ለጋምቤላ ማከፋፈያ ጣቢያ እንዲሁም በ33 ኪሎ ቮልት ለማሻ፣ ሌቃና ጎቤ ከተሞችና አካባቢያቸው ኃይል እየሰጠ ይገኛል፡፡ በ15 ኪሎ ቮልት ደግሞ ለመቱ ከተማና አካባቢው፣ ለጎሬ፣ ያዮ፣ ሱጴ ከተሞችና እና ለመቱ ዩኒቨርሲቲ ኃይል እያቀረበ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 21 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2