en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 680 subscribers, ranking 8 053 in the Technologies & Applications category and 2 173 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 680 subscribers.

According to the latest data from 05 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 112 over the last 30 days and by -12 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.83%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.95% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 050 views. Within the first day, a publication typically gains 2 501 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 06 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 680
Subscribers
-1224 hours
-127 days
+11230 days
Posts Archive
የተቋሙ ሠራተኞች በመንግስት ውሳኔዎች እና አቅጣጫዎች ዙሪያ ተወያዩ ........///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች "ከቃል ወደ ባህል" በሚል መሪ ሀሳብ የብልፅግና ፓርቲ ባካሄደው ሁለተኛ መደበኛ ጉባዔ በተቀመጡ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ዙሪያ ውይይት አካሂደዋል። በውይይቱ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለፁት ውይይቱ ሠራተኛው በጉባዔው በተቀመጡ ውሳኔዎችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ግንዛቤ በመጨበጥ ለተግባራዊነቱ እንዲሰራ ለማድረግ ነው። ፓርቲው መንግስትን የሚመራ እንደመሆኑ መጠን ሠራተኞችም የፓርቲውን ውሳኔዎችና ያስቀመጣቸውን የትኩረት አቅጣጫዎች በመረዳት  ሥራቸውን በዚሁ አግባብ ማከናወን እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። በመድረኩ ላይ በፓርቲው ሁለተኛ ጉባዔ በተቀመጡ ውሳኔዎችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ የተዘጋጀ ሰነድ በንባብ ቀርቧል። ጠንካራ የፓርቲ ግንባታ፣ የብሔራዊነት ገዥ ትርክት ግንባታን ማጠናከር፣ ውጤታማ የሰላም ግንባታ ሥራ መስራት፣ የፍትህ ዘርፍ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የሀገር ግንባታን ማጠናከር እና የኢኮኖሚ ልማትን ማፋጠን የሚሉት በጉባዔው ከተቀመጡ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች መካከል መሆናቸው በሰነዱ ላይ ተመልክቷል። በተጨማሪም ማህበራዊ ብልፅግናን የሚያረጋግጡ ሥራዎችን በውጤታማነት ማስቀጠል፣ ውጤታማ የዲፕሎማሲ ሥራዎች መስራት፣ የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ውጤታማነትን ማረጋገጥ እና ጠንካራ የሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ሥራዎችን መስራት የሚሉ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች በፓርቲው መቀመጣቸውም ተገልጿል። በውይይቱ ላይ ከሠላም፣ ከተቋም ግንባታና አገልግሎት አሰጣጥ፣ ከልማትና መልካም አስተዳደር እንዲሁም ከፍትህ ሥርዓቱ ጋር የተያያዙ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች በተሳታፊዎች ቀርበዋል። በተቋሙ የኮርፖሬት ፋይናንስ እና ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ በሰጡት ምላሽ የመንግስት የልማት ድርጅቶች በመንግስት ፖሊሲና የፖለቲካ አቅጣጫዎች የሚመሩ መሆናቸውን ገልፀዋል። መንግስት የግጭት መንስዔዎችን ከምንጩ ለማድረቅና የሀገሪቱን ሀብት በፍትሐዊነት ለመጠቀም በትኩረት እየሰራ መሆኑን አቶ ደመረ ጠቅሰዋል። የሰላም ጉዳይ ለመንግስት ብቻ የተተወ ባለመሆኑ ሁላችንም ሰላምን ለማጽናት የድርሻችንን ልንወጣ ይገባል ነው ያሉት። በተቋሙ የትራንስሚሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አንዱዓለም ሲዓ በበኩላቸው ገዢ ሀገራዊ ትርክት ለመገንባት የጋራ መግባባት መፍጠር ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። መንግስት ከሰላም እጦት ጋር የተያያዙ ችግሮችን አካታች በሆነ መልኩ ለመፍታት ሥር ነቀል ለውጥ ለማምጣት እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል። የኢንጂነሪንግ እና ግንባታ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ውድነህ የማነ በበኩላቸው ውይይት የተደረገበት ሰነድ የፓርቲ ብቻ ሳይሆን የመንግስት ሰነድ በመሆኑ፣ እንደዜጋ ማወቅና  በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት መፈፀም ስለሚጠበቅብን ነው ብለዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 18  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

photo content
+9

በውሃ ኃይል ማመንጫ ዘርፍ  የሠለጠነ ባለሙያ ለማፍራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ ………///……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በውሃ ኃይል ማመንጫ ዘርፍ የሰለጠነ ባለሙያ ለማፍራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ቮይት ሀይድሮ ከተሰኘ የጀርመን ኩባንያ ጋር ተፈራርሟል። ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እና በቮይት ሀይድሮ ኩባንያ የሀይድሮ ሰርቪስ እና አውቶሜሽን ኃላፊ ሚስተር አሎይስ ታግሊበር ተፈራርመዋል፡፡ ኢንጂነር አሸብር በፊርማ ሥነስርዓቱ ላይ እንደተናገሩት ተቋሙ በአሁኑ ወቅት እያመነጨ ካለው የኤሌክትሪክ ኃይል 92 በመቶ የሚሆነው ከውሃ የሚገኝ በመሆኑ ስምምነቱ በዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል ለማፍራት ያግዛል፡፡ ኩባንያው ያለውን የካበተ ልምድ ለተቋሙ ለማካፈል እያደረገ ያለውን ጥረት አመስግነው ስምምነቱ ከኩባንያው ጋር ያለውን ግንኙነት እንደሚያጠናክረውም አስታውቀዋል፡፡ የአቅም ግንባታ ሥራው ውጤታማ እንዲሆን ኩባንያው አቅም ያላቸው ባለሙያዎች በመመድብ እንዲሰራ አሳስበዋል፡፡ በቮይት ሀይድሮ ኩባንያ የሀይድሮ ሰርቪስ እና አውቶሜሽን ኃላፊ ሚስተር አሎይስ ታግሊበር በበኩላቸው ኩባንያቸው ከተቋሙ ጋር በተለያዩ ዘርፎች በጋራ ሲሰራ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ በውሃ ኃይል ማመንጫዎች ላይ ለተቋሙ ባለሙያዎች የአቅም ግንባት ለመስጠት የተደረሰው ስምምነት በአቅም ግንባታ ጉዳዮች ላይ ከተቋሙ ጋር ለመስራት አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ኩባንያቸውው በውሃ ኃይል ማመንጫዎች ላይ ያለውን ልምድ እና እውቀት ለተቋሙ ለማከፈል ዝግጁ መሆኑን አንስተው ለዚህም ብቃት ያላቸው ባለሙያዎችን በመመደብ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል፡፡ በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የቴክኒካል ድጋፍ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ አብዱ ይማም እንደተናገሩት ስምምነቱ በውኃ ኃይል ማመንጫዎች ላይ ከዲዛይን ጀምሮ ማመንጫዎች አገልግሎት መስጠት እስከሚያቆሙበት (decommissioning) ባለው የአሰራር ሂደት ላይ የአቅም ግንባታ ስልጠና ለመስጠት ያለመ ነው፡፡ በስልጠናው ላይ ከጀነሬሽን ኦፕሬሽን ዘርፍ እና ከኢንጂነሪንግ ዘርፍ የጀነሬሽን ዲዛይን የሥራ ክፍል የተውጣጡ 80 ባለሙያዎችና የሥራ ኃላፊዎች እንደሚሳተፉበት ጠቁመዋል፡፡ የአቅም ግንባታ ለመስጠት የተካሄደው ስምምነት ለዘጠኝ ወራት የሚቆይ ሲሆን ለዚህም  የአራት ሚሊዮን ዶላር ስምምነት ተደርጓል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 17  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

የተቋሙን የሥራ አፈፃፀም መለኪያ መስኮች ለማሻሻል ይሰራል …....///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚያከናውናቸውን የኃይል መሠረተ ልማቶች ግንባታና የኦፕሬሽን ሥራዎች እንዲሁም አስተዳደራዊ ጉዳዮች የሥራ አፈፃፀም መለኪያዎችን ለማሻሻል እንደሚሰራ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ አስታወቀ። የተቋሙን የ6 ወራት አፈፃፀም ሪፖርት ለኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ  ያቀረቡት የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ  ሥራ አስፈፃሚ አቶ ህይወት እሸቱ ተቋሙ በፕሮጀክት ግንባታ፣ በኦፕሬሽን፣ በፋይናንስ፣ በለውጥ ሥራዎች እንዲሁም በሰው ኃይል አስተዳደርና አቅም ግንባታ ሥራዎች የነበረውን አፈፃፀም አቅርበዋል። ተቋሙ በኦፕሬሽን ዘርፍ ከ13 ሺህ ጌጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል በማምረት የዕቅዱን 115 ነጥብ 6 በመቶ ማሳካቱን የገለፁት አቶ ህይወት ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ40 ነጥብ 2 በመቶ ዕድገት አሳይቷል ብለዋል። ባለፉት 6 ወራት ለሀገር ውስጥ ደንበኞች 11 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር፣ በዶላር ለሚከፍሉ ደንበኞች 70 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዶላር እና ለጎረቤት ሀገራት 61 ሚሊዮን ዶላር  ሽያጭ መከናወኑን ጠቅሰው 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በታሪፍ ለውጥ ምክንያት የተገኘ መሆኑን በሪፖርቱ አመልክተዋል። እንደ አቶ ህይወት ገለፃ የ2016 በጀት ዓመት የኦዲት ሪፖርት ንፁህ ሆኖ መገምገሙ፤ ለመጀመሪያ ጊዜ የስድስት ወራት የተቋም ፋይናንስ መዝጋት መቻሉ እና በውጭ ምንዛሬ የሚደረግ ግብይት መጨመሩ ባለፉት 6 ወራት ከተመዘገቡ መሻሻሎች መካከል ይጠቀሳሉ። በተቋሙ የኮርፖሬት ፋይናንስና ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ እንደተናገሩት ተቋሙ 87 በመቶ የሚሆነው የፋይናንስ ገቢውን ወደፊት ሀብት ያመጣሉ ተብለው በሚታሰቡ ፕሮጀክቶች ላይ እያዋለ ይገኛል። ባለፉት 6 ወራት የታየው የፋይናንስ ገቢ ዕድገት ከውጭ ምንዛሪ መሻሻል ጋር ተያይዞ የመጣ መሆኑንም ነው ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ያብራሩት። በተቋሙ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አንዱዓለም ሲዓ በበኩላቸው ተቋሙን በዲጂታላይዜሽን መስኮች የማዘመንና የአሰራር ሥርዓቶችን የመዘርጋት ሥራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል። የተቋሙን ድረ-ገፅ ጨምሮ ሦስት የአሰራር ሥርዓቶችን የሚያዘምኑ ሶፍትዌሮች በራስ አቅም መዘጋጀታቸውንም ነው የገለፁት። በኢትዮጵያ ኢንቨስትመት ሆልዲንግስ የኢነርጂና ኮኔክቲቪቲ ዘርፍ ፖርቲፎሊዮ ዳይሬክተር አቶ ቴዎድርስ ተገኘ እንደተናገሩት የኃይል ምርት ዕድገትና የአቅርቦት መሻሻሎች፣ ተቋሙን ለማዘመን እየተሠሩ ያሉ የለውጥ ሥራዎች፣ ወቅታዊ የሂሳብ መግለጫ ዝግጅት እንዲሁም ፕሮጀክቶችን በራስ አቅም የማከናወን ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን የአፈፃፀም መለኪያ መስኮች ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ መለኪያዎች ጋር የማጣጣምና የማሻሻል ሥራዎች እንደሚሰሩም ነው የጠቆሙት። ተቋሙ የገቢ አሰባሰብ ሥርዓቱ ላይ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባው የጠቀሱት አቶ ቴዎድሮስ ከሱዳን ጋር ተያይዞ ያልተከፈሉ ውዝፍ የኃይል ሽያጭ ገቢዎችን ለመሰብሰብ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በጋራ እንደሚሰራ ተናግረዋል። በግምገማው ላይ የማጠቃለያ ሃሳብ የሰጡት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በበኩላቸው በተቋሙ ተተኪ አመራሮችን ከማፍራት አንፃር መመሪያ ተዘጋጅቶ ወደ ሥራ ተገብቷል ብለዋል። እንደ ኢንጂነር አሸብር ገለፃ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ጋር በትብብር በመስራት በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆነ ተቋም ለመፍጠር በትኩረት ይሰራል። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን ማስተዳደር ከጀመረ ወዲህ ይህ የአፈፃፀም ግምገማ የመጀመሪያው ነው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 17  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

የማከፋፈያ ጣቢያውን አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች ለውጥ አምጥተዋል …….///………. የጅግጅጋ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች  እየተከናወኑ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ደምለው ተሾመ እንደገለፁት እየተከናወነ የሚገኘው የጂ.አይ.ኤስ ስዊችጊር ቅየራ ሥራ የማከፋፈያ ጣቢያውን የኦፕሬሽን አቅም ለማዘመን የሚያግዝ ነው። በአሁኑ ወቅት በማከፋፈያ ጣቢያው ለረጅም ዓመታት አገልግሎት ሲሰጡ የቆዩትን የ15 እና 33 ኪሎ ቮልት ስዊችጊሮች በሌላ ዘመናዊ መቆጣጠሪያዎች የመቀየር ሥራ መሰራቱንም ነው የተናገሩት። የጅግጅጋ ማከፋፈያ ጣቢያ ከዓመት በፊት ከ17 ሜጋ ዋት ያልበለጠ ኃይል የመጫን አቅም እንደነበረው የገለፁት ሥራ አስኪያጁ በ15 እና 33 ኪሎ ቮልት ስዊችጊሮች ላይ በተከናወነው የአቅም ማሳደግ ሥራ ሳቢያ ኃይል የማቅረብ አቅሙ ከ24 ሜጋ ዋት በላይ ከፍ ማለቱን ጠቅሰዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በተደረገው የአቅም ማሳደግ ሥራ ቀደም ሲል በ15 ኪሎ ቮልት አራት የነበሩ ወጪ መስመሮችን ወደ አምስት እንዲሁም በ33 ኪሎ ቮልት አራት የነበሩ ወጪ መስመሮችን ወደ ስድስት ማሳደግ ተችሏል። በአየር ሲሰራ የቆየው መቆጣጠሪያ (vacume switchgear ) በዘመናዊ መቆጣጠሪያ በመቀየሩ የኃይል መቆራረጥንና በጥገና ሥራዎች ላይ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮችን በመቅረፍ የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎችን በቀላሉ ለማከናወን እንደሚረዳ ነው ሥራ አስኪያጁ የጠቆሙት። በ2016 በጀት ዓመት በጣቢያው 31 ነጥብ 5 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያለው ተጨማሪ ትራንስፎርመር ማስቀመጥ ቢቻልም በ15 እና 33 ኪሎ ቮልት ስዊችጊሮች የአቅም ውስንነት የተነሳ የሚፈለገውን ኃይል ለተጠቃሚው ህብረተሰብ ማድረስ እንዳልተቻለ አስታውሰዋል። በ1997 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት የጀመረው የጅግጅጋ ማከፋፈያ ጣቢያ በ132 ኪሎ ቮልት ከሐረር ቁጥር ሦስት ኃይል ተቀብሎ በባለ 33 ኪሎ ቮልት  ለቀብሪበያህ፣ ቶጎ ውጫሌ፣ ጭናክሰን፣ ፋፈን እና በጅግጅጋ ዙሪያ ለሚገኙ ከተሞችና አካባቢዎች እንዲሁም በባለ 15 ኪሎ ቮልት አራት ለጅግጅጋ ከተማ ኃይል እያቀረበ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 17  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ የጡረተኞች ማህበር ተመሰረተ .....///..... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለረጅም ዓመታት አገልግለው በጡረታ የተሸኙ የቀድሞ ሠራተኞች የጋራ ማህበር ዛሬ በይፋ ተመሠረተ። "የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ የጡረተኞች ማህበር" በሚል ሥያሜ የተመሠረተው ማህበሩ በዋናነት በጡረታ የሚገኙ ጥቅሞችን ለማስከበር ታስቦ መቋሙ በምሥረታ ጉባዔው ላይ ተገልጿል። የማህበሩ ሊቀመንበር አቶ ተሾመ መርዕድ በመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለፁት ከወጣትነት ዕድሜ ጀምሮ በጡረታ በክብር እስከ ተሸኙበት ድረስ ዕውቀታቸውን፣ ልምዳቸውንና ጉልበታቸውን ሳይቆጥቡ በቅንነት በማገልገላቸው ለማህበረሰባዊ ለውጥ እና ለሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገት አሻራቸውን አሳርፈዋል፡፡ ይሁን እንጂ  በሀዘንና ደስታ ጊዜ ከሚተጋገዙበት የመረዳጃ ዕድር በዘለለ ጡረተኞችን የሚወክል ማህበር ባለመኖሩ ከቀድሞ ተቋማቸው ማግኘት የሚገባቸውን ድጋፍ ለማግኘት እንዲሁም ለብዙ ዓመታት ያገኙትን ልምድ ለማካፈልና አብሮ ለመሥራት የሚያስችል ምቹ ሁኔታ አልነበረም ብለዋል። በመሆኑም ለረጅም ዓመት አገልግለው የተሠናበቱ ሠራተኞች በጡረታ የሚገኙ ጥቅሞችን ለማስከበር እና መብታቸውን ለመጠየቅ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ የጡረተኞች ማህበር መመስረቱን ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ በበኩላቸው ሀገሪቱ የምትጠቀምባቸው የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች  ላይ "የእናንተ አሻራ ስላረፈበት ልትኮሩ ይገባል" ብለዋል። በጡረታ የተሰናበቱ ሠራተኞች የሚያነሷቸውን ጥያቄ በህግ አግባብ ለመመለስ ተቋሙ ቁርጠኛ መሆኑን ያረጋገጡት ኃላፊው የቀድሞ አንጋፋ ሠራተኞችም የነበራቸውን እውቅትና ልምድ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የሁለቱ የኤሌክትሪክ ተቋማት መሰረታዊ የሠራተኛ ማህበር ኃላፊዎች በበኩላቸው በጡረታ ለሚሰናበቱ ሠራተኞች ከአሁን በፊት ሲደረጉ ከነበሩ ድጋፎች በተጨማሪ የሚቀርቡ የመብት ጥያቄዎችን በጋራ እንድሚፍቱ ቃል ግብተዋል፡፡ ጉባዔው የማህበሩን ሊቀመንበር ጨምሮ አምስት አባላት ያሉት የሥራ አሥፈጻሚ ኮሚቴ አባላትን በመምረጥ በይፋ ተመስርቷል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተብለው የሚጠሩት ሁለቱ ተቋማት ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ መብራትና ኃይል ባለስልጣን በኋላም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ተብለው በአንድ ሥም ይጠሩ እንደነበር ይታወሳል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 15  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

በተቋማችን የሚገኙ የኃይል ማመንጫዎች፣ ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የግንባታና ኦፕሬሽን እንዲሁም ሌሎች ሥራዎችን የሚመለከቱ የተለያዩ የቪዲዮ ፕሮዳክሽኖችን በተቋማችን ስም በተከፈተ የዩቱዩብ ቻናል ላይ ሲጫኑ ቆይተዋል። በመሆኑም ተቋማችን ሲያከናውናቸው የነበሩትንና እያከናወናቸው የሚገኙ ሥራዎችን በአግባቡ ለመረዳት እና ለብዙኃኑ ተደራሽ ለማድረግ ከዚህ በታች በተቀመጠው https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ማስፈንጠሪያ ወይም ሊንክ በመግባት መረጃዎቹን ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን መረጃውን ለብዙኃኑ ለማድረስ እንዲቻል ቻናሉን ሰብስክራይብ በማድረግ ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲጋብዙ በአክብሮት እንጠይቃለን። ተቋማችን የሚያከናውናቸውን ስራዎች በምስልና ድምፅ ከሚዘጋጁት መረጃዎች በተጨማሪ የፅሁፍ መረጃዎችን ከፈለጉም በተለያዩ የዲጂታል አማራጮች መረጃዎች የሚያገኙ መሆኑን እንገልፃለን። 📡📲💡። 📖 በዲጂታል መጽሔቶቻችንን 👉 https://www.eep.com.et/?page_id=17536 ላይ ያንብቡ። የኢ.ኤ.ኃ. ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 14  ቀን 2017 ዓ.ም

ሪጅኑ አስተማማኝ ኃይል ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችሉ ሥራዎች ማከናወኑን ገለፀ ……..///……. የምስራቅ ሁለት ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ ባለፉት ስድስት ወራት አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችሉ ሥራዎች ማከናወኑን አስታወቀ። የመምሪያው ተወካይ ዳይሬክተር አቶ ወርቁ ሙሉ እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት በጅግጅጋ፣ ፊቅ፣ ጎዴ፣ ደገሃቡር እና ቀብሪደሃር  የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የአስቸኳይ ጥገና እና የፍተሻ ሥራዎች ተሰርተዋል። ሪጅኑ የኃይል አቅርቦቱን ይበልጥ አስተማማኝ ለማድረግ በጅግጅጋ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ የአቅም ማሳደግ ሥራዎች ማከናወኑን ጠቁመዋል። በአሁኑ ወቅት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ለጅግጅጋ ከተማና አካባቢው አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ የጠቀሱት ተወካይ ዳይሬክተሩ በጣቢያው ከተሰራው የ15 እና 33 ኪሎ ቮልት ስዊችጊር የማዘመን ሥራ ባሻገር የትራንስፎርመር አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ ጥያቄዎች ለተቋሙ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ መቅረቡን ተናግረዋል። በቀጣይም በጎዴ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ የዘመናዊ ስዊችጊር ቅየራ ሥራ ለማከናወን ታቅዶ እንቅስቃሴዎች መጀመራቸውንም ነው አቶ ወርቁ የገለፁት። እንደ ተወካይ ዳይሬክተሩ ገለፃ ሪጅኑ በስሩ በሚያስተዳድራቸው አምስት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና የማስተላለፊያ መስመሮች በዕቅድ ላይ የተመሰረቱ የጥገና እና የፍተሻ ሥራዎች እያከናወነ ይገኛል። በዚህም በግማሽ በጀት ዓመቱ በአምስቱ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ 85 ቤዮችን የመጠገን እና የመፈተሽ ሥራ መስራቱን ተናግረዋል፡፡ ሪጅኑ በሚያስተዳድራቸው የማስተላለፊያ መስመሮች ላይ 1 ሺ 643 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ብረቶች ላይ እንዲሁም 719 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የፍተሻና ጥገና ሥራዎች መከናወናቸውንም ነው አቶ ወርቁ ያብራሩት። እንደ ተወካይ ዳይሬክተሩ ገለፃ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት በተከናወኑ የጥገና እና የፍተሻ ሥራዎች በተደጋጋሚ ይከሰት የነበረውን የኃይል መቆራረጥ እንዲቀንስ አስችሏል። በጎዴ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ደረጃውን የጠበቀ የአጥር ግንባታ ሥራ በመከናወን ላይ እንደሚገኝ የተናገሩት አቶ ወርቁ የአጥር ግንባታው በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ ግመሎች ወደ ጣቢያው እንዳይገቡ ለመከላከል ያለመ መሆኑንም ነው የገለፁት። ባለፉት ስድስት ወራት የጅግጅጋ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የኦፕሬሽን ሠራተኞች መኖሪያ ቤት ዕድሳት መከናወኑን ጠቅሰው በቀጣይም የቀብሪድሃር እና ደጋሃቡር የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የኦፕሬሽን ሠራተኞች የመኖሪያ ቤት ዕድሳት ለማከናወን የግዥ ሂደቱ መጠናቀቁን አብራርተዋል። ሪጅኑ በጅግጅጋ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ውስጥ በተቋሙ የራስ ኃይል የግንባታ መምሪያ በኩል ጊዜያዊ ተገጣጣሚ የቢሮ ግንባታ ለማከናወን አቅዶ በስፋት እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝም ነው የተናገሩት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 14  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

በመንግስትና ግል አጋርነት የሚለሙ ስምንት የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ተለይተዋል ……..///…….… በመንግስት እና በግል አጋርነት የሚለሙ ስምንት የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች መለየታቸውን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመንግሥት እና የግል አጋርነት መመሪያ ገለፀ። በመምሪያው የፀሐይና ንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ሥራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ ዘውዴ እንደገለጹት የኃይል ስብጥሩን በማሳደግ የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማስፋት በኃይል ማመንጨት ዘርፍ የግል አልሚዎች እንዲሳተፉ የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ ተዘጋጅቷል፡፡ የግል ዘርፉ ኃይል ማመንጫ ገንብቶና ኃይል አመንጭቶ ለተቋሙ መሸጥ አዲስ አሰራር በመሆኑ የፕሮጀክቶችን አዋጭነት በተመለከተ ተቋሙ የግል ዘርፉን ለማሳተፍና ለማበረታታት ብሎም ፕሮጀክቶቹን ሥራ ላይ ለማዋል የሚያስችል ጥናት በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን መሰራቱን ተናግረዋል፡፡ በዚህም በመንግስትና በግል አጋርነት የሚለሙ ስምንት የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች መለየታቸውንና ከእነዚህ ውስጥ የአራቱ ማለትም ጋድ 1 እና 2፣ ዲቼቶ እና ወራንሶ ጥናታቸው መጠናቀቁንም አብራርተዋል፡፡ በጥናት የተለዩትን የፀሐይ ኃይል ማመንጫዎች ለማልማት እ.ኤ.አ በ2019 ግንቦት ወር ጨረታ መውጣቱን  አቶ አሸናፊ አስታወሰዋል፡፡ ይሁንና በወቅቱ የውጭ ምንዛሪ አቅርቦት ዋስትና በመጠየቁ፣ በውጭ ሀገር ፕሮጀክቱን የተመለከተ የገንዘብ ዝውውር ለማከናወን አካውንት የመክፈት ፈቃድ በመጠየቁ እና ይህንን ለማስፈጸም የሚያስችል አዲስ መመሪያ በማስፈለጉ የግል አልሚዎቹ ወደ ተግባር አለመግባታቸውን ጠቁመዋል፡፡ አሁን ላይ ግን በሀገሪቱ እየተተገበረ በሚገኘው የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ ላይ መንግስት ለፕሮጀክቶቹ ትኩረት በመስጠቱ፣ የውጭ ምንዛሬ አቅርቦት ዋስትና በመተግበሩ እና የውጭ ምንዛሬ አካውንት ለመክፈት አስቻይ ሁኔታ በመኖሩ ፕሮጀክቶቹን ወደ ትግበር እንዲገቡ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በዚህም ጋድ 2 እና ወራንሶ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን በመንግስት እና በግል አጋርነት ለማልማት ጨረታ ወጥቷል ብለዋል፡፡ ሁለቱ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች 225 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም እንዳላቸውና ፕሮጀክቶቹን ለማጠናቀቅ 200 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል፡፡ ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ የኃይል ስብጥሩን በማሳደግ የኤሌክትሪክ ተደራሽነቱን ከማስፋትም ባሻገር መንግስት ፕሮጀክቱን በራሱ የፋይናንስ አቅም ቢሰራ ሊያወጣ የሚችለውን ፋይናንስ በግል አልሚው በመሸፈን ፕሮጀክቶቹን መተግበር የሚያስችለው መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ፕሮጀክቶቹ በመንግስትና ግል አጋርነት ሲለሙ በተሻለ ጥራትና ጊዜ ለማጠናቀቅ ዕድል ይፈጥራል ያሉት ሥራ አስኪያጁ ከአዋጭነት ጥናቱ ጀምሮ እስከ ፕሮጀክቱ ትግበራ የእውቀት ሽግግር እንዲኖር ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ከስምንቱ የፀሐይ ኃይል ማመንጫዎች እስከ 750 ሜጋ ዋት ለማመንጨት ዕቅድ ተይዟል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 14  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

በራስ ኃይል የሚከናወኑ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አሳሰቡ …….///…… በራስ ኃይል የሚከናወኑ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜና በጀት ማጠናቀቅ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሳሰቡ፡፡ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ከተቋሙ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በራስ ኃይል የሚከናወኑ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ያሉበትን ደረጃ ገምግመዋል፡፡ ኢንጂነር አሸብር በዚሁ ወቅት እንዳሉት በተቋሙ የራስ ኃይል የሚከናወኑ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የተቋሙ የመፈጸም አቅም የሚገነባባቸው ከመሆናቸውም በተጨማሪ በጥራትና በጊዜ በማጠናቀቅ በዘርፉ ተወዳዳሪ ለመሆን ዕድል የሚሰጥ ነው ፡፡ የተቋሙ አብዛኛው በጀት በፕሮጀክቶች ላይ እንደሚውል የጠቆሙት ኢንጂነር አሸብር በሥራ ሂደት እያጋጠሙ ያሉ ችግሮች ላይ ተወያይቶ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ እና አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ውይይቱ ማስፈለጉን ተናግረዋል፡፡ በራስ ኃይል በግንባታ ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜና በጀት እንዲሁም በተቀመጡ ዝርዝር መስፈርቶች መሰረት እንዲጠናቀቁ ለማድረግ በሥራው ላይ የሚሳተፉ አካላት ተቀናጅተው መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡ የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ውድነህ የማነ በበኩላቸው በተቋሙ በራስ ኃይል መምሪያ አስር የሚሆኑ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፍያ ጣቢያዎች ግንባታ በመካሄድ ላይ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ ውይይቱ በራስ ኃይል የሚሰሩ ፕሮጀክቶችን አፈጻጸም በመገምገም ከአስተሳሰብ ጀምሮ አሰራሮችን በመለወጥ እንዲሁም ፕሮጀክቶችን አቅዶ ከመፈፀም፣ ከፋይናንስ እና ከዕቃ አቅርቦት በተያያዘ እያጋጠሙ ያሉ ችግሮች በመቅረፍ አፈጻጸማቸውን ለማሻሻል እንደሚያግዝ ገልጸዋል፡፡ ቀደም ሲል የራስ ኃይል ግንባታና ማማከር የሥራ ክፍሎች ለየብቻ የነበሩ መሆኑን ያስታወሱት አቶ ውድነህ በመዋቅሩ ሁለቱ ክፍሎች በአንድ ላይ መሆናቸው ከዲዛይን ጀምሮ የግንባታ ሥራዎች በተቀናጀ መልኩ እንዲከናወኑ ያስችላል ብለዋል፡፡ እንደ ሥራ አስፈጻሚው ገለጻ የኢንጂነሪንግ ክፍሉ እንደ ተቆጣጣሪ ሳይሆን የኮንስትራክሽን ኃይሉ የሚፈልገውን ቴክኒካዊ ድጋፍ ለመስጠት ዕድል የሚሰጥ በመሆኑ ፕሮጀክቶች በጥራት፣ በጊዜና በተያዘላቸው በጀት ለማጠናቀቅ ይረዳል፡፡ በውይይቱ የፕሮጀክቶችን አፈፃፀም በመገምገም የሚስተዋሉ ችግሮች ተለይተው የሚፈቱበት ቀጣይ አቅጣጫ እንደሚቀመጥም ጠቁመዋል፡፡ ፕሮጀክቶችን በጊዜ ማጠናቀቅ ለተቋም ብሎም ለሀገር የሚኖረውን ሚና ከግምት በማስገባት ሁሉም ተቀናጅቶ መስራት እንደሚኖርበትም አሳስበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 13  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ጣቢያው የአካባቢውን የኃይል ፍላጎት ለመመለስ ችሏል ………///………. በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሆለታ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ወደስራ ያስገባቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች የተሟላ ኃይል  ለማቅረብ ምቹ ሁኔታ መፍጠራቸውን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለፁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ጥላሁን አዘዘው እንደተናገሩት የሆለታ ማከፋፈያ ጣቢያ ለአቃቂ፣ ሰበታ እና ሱሉልታ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እንዲሁም ለአካባቢው ነዋሪዎችና በኢንቨስትመንት ዘርፍ ለተሰማሩ አምራቾች በተሟላ መልኩ ኃይል በማቅረብ ላይ ይገኛል፡፡ ጣቢያው የተገጠመለት ጂ አይ ኤስ መቆጣጠሪያ፣ የስካዳ ሲስተም እና ሌሎች የቴክኖሎጂ ውጤቶች ጣቢያው ኃይል ሳይቆራረጥ ደንበኞች ጋር ለማድረስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳበረከቱ የጣቢያው የጥገና ባለሙያ ተዳቻ ገናሌ ተናግረዋል። የጣቢያው መሳሪያዎች የኃይል መቋረጥ ሲኖር ችግሩ የደረሰበት መስመር እና የችግሩን ዓይነት እንዲሁም የችግሩን መጠን በመለየት መረጃን በቀላሉ መልሶ ለመጠገን እንደሚያግዝ አስረድተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 13  ቀን 2017 ዓ.ም