617
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ከላይ የተዘረዘሩት ት/ቤቶች ተማሪዎች በመደበኛው የስልጠና ሰዓት የተመደቡ ቢሆንም በማታው እንዲሁም በቅዳሜና እሁድ የስልጠና መርሃግብር የየትኛውም ት/ቤት ተማሪዎች በኮሌጃችን ተመዝግበው መሠልጠን የሚችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
እንዴት አመሻችሁ ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ት/ቤቶች ተማሪዎች በኮሌጃችን ጎፋ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የተመደቡ ስለሆነና ምዝገባ በኦንላይን ዛሬ የተጀመረ መሆኑን እንዲያውቁት ብታደርጉልን
1. ሰዲል
2. ላፍቶ
3. ለቡ
4. ቡርቃ ዋዮ
Repost from Addis Ababa Education Bureau
#ማስታወቂያ
(ህዳር 5/2016 ዓ.ም) የRemedial ፕሮግራም የዩኒቨርሲቲ ምርጫን በተመለከተ
በ 2015 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች የተቋም ምርጫችሁን በየትምህርት ቤታችሁ በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ ህዳር 12/2016 ዓ.ም ድረስ ማስተካከል የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ማሳሰቢያ፡ -
ከታች የተዘረዘሩ ዩኒቨርሲቲዎች የ Remedial ፕሮግራም የማያስተናግዱ መሆኑን እንገልጻለን።
1. አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
2. አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
3. አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
4. ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
5. አርሲ ዩኒቨርሲቲ
6. ኮተቤ የትምህርት ዪኒቨርሲቲ
ትምህርት ሚኒስቴር
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!
You Tube: https://www.youtube.com/@addisababaeducationbureau9728
TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/
Website: - aaceb.gov.et
Email;- aacaebc@gmail.com
Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
ቀን 3/03/2016ዓ.ም
የሀዘን መግለጫ
ተማሪ ሲፋን ለሜቻ የሰዲል ለኢትዮጲያ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የ9C ክፍል ተማሪ ስትሆን በደረሰባት ድንገተኛ ህልፈተ ሕይወት የት/ቤቱ ማህበረሰብ የተሰማውን መሪር ሀዘን እየገለፀ ለቤተሰባ ና ለጓደኞቿ መፅናናትን እንመኛለን፡፡
ት/ቤቱ
Repost from Kolfe education official channel🇪🇹
አዲስ የተማሪዎች ዝውውር መመሪያ ረቂቅ 2016ዓም
አዲስ የተማሪዎች ዝውውር መመሪያ ረቂቅ 2016ዓም
ዋና ዋና ነጥቦች
ከዚህ በፊት በተለያዩ ክልሎች ወጥነት ያልነበረው የተከታታይ ምዘና አያያዝ ማለትም 60% ተከታታይ ምዘና 40% ማጠቃለያ ፈተና አሁን ወደ 40% ተከታታይ ምዘና 60% ማጠቃለያ ፈተና ተሰጥቶ ከ100% ይያዛል
ከ9-11ኛ ክፍል Maths and English ከ50% በታች ያመጣ ተማሪ እንዲሁም 1-7ኛ ክፍል 6ኛን ሳይጨምር Maths እና የማስተማሪያ ቋንቋውን ከ50% በታች ካመጣ ወደቀጣይ ክፍል መዛወር አይችልም
አንድ ክፍል ደረጃ ከአንዴ በላይ ከደገመ ከትምህርት ይሰናበታል
