Goqa-ጎቃ (Ethio-news)
Open in Telegram
All about Ethiopia!!! ሁሌም ስለ ኢትዮጵያ እንዲሁም አለም-አቀፍ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበረሰባዊ ዜና ከትንተና ጋር።
Show more4 151
Subscribers
No data24 hours
-127 days
-8130 days
Posts Archive
4 151
+1
#Update
እስራኤል በፍልስጤም የሚሰራዉን የተ.መ.ድን እርዳታ ድርጅት የሚያግድ ህግ አወጣች!!
⚡️እስራኤል UNRWA በመባል የሚታወቀውን ድርጅት ያገደው ሰራተኞቹ በጥቅምት 15ቱ ጥቃት ተሳትፈዋል በሚል ምክንያት ነው።
⚡️ተ.መ.ድ ባደረገው ምርመራ ክሱ ከቀረበባቸው 19 ሰዎች መካከል 9ኞቹን ያባረረ ቢሆንም ከእስራኤል የመጣው ውሳኔ አግባብ የሌለው እንዲሁም በሚልየኖች የሚቆጠሩ ፍልስጤማውያንን አደጋ ላይ የሚጥል ነው ብሏል።
UNRWA እ.አ.አ ከ1949 ጀምሮ ተፈናቃይ ፍልስጤማውያንን ሲረዳ የቆየ ድርጅት ሲሆን በተለይም ከጥቅምት 15 ቡኋላ በፍልስጤም የሚንቀሳቀሰው ዋነኛ የእርዳታ ድርጅት ሆኖ ቆይቷል።
@Goqaeth
4 151
Repost from Goqa-ጎቃ (Ethio-news)
+1
#Update
#አረብ ኤምሬትስ ለሊባኖስ 80 ቶን የሰብአዊ እርዳታ ሰጠች
⚡️"አረብ ኢምሬትስ ከሊባኖስ ጋር ነች" በሚል ዘመቻ የተሰጠው እርዳታ "የኢምሬቶች እናት" ተብለው የሚጠሩት እና የሴቶች ህብረት ሊቀመንበር እንዲሁም የሴቶችና ህጻናት ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት በሆኑት ሸኪና ፋጢማ መሪነት የተሰበሰበው ነው።
⚡️እርዳታዉ በሄዝቡላ እና እስራኤል መሀል በቀጠለው ጦርነት ለተጎዱ ንፁሃን ዜጎች እንዲሁም ከ100,000 በላይ ተፈናቃዬች እንዲደርስ የታሰበ ነዉ።
@Goqaeth
4 151
+1
#አረብ ኤምሬትስ ለሊባኖስ 80 ቶን የሰብአዊ እርዳታ ሰጠች
⚡️"አረብ ኢምሬትስ ከሊባኖስ ጋር ነች" በሚል ዘመቻ የተሰበሰበው እርዳታ "የኢምሬቶች እናት" ተብለው የሚጠሩት እና የሴቶች ህብረት ሊቀመንበር እንዲሁም የሴቶችና ህጻናት ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት በሆኑት ሸኪና ፋጢማ መሪነት ነው።
⚡️እርዳታዉ በሄዝቡላ እና እስራኤል መሀል በቀጠለው ጦርነት ለተጎዱ ንፁሃን ዜጎች እንዲሁም ከ100,000 በላይ ተፈናቃዬች እንዲደርስ የታሰበ ነዉ።
@Goqaeth
4 151
+1
#የእስራኤል ካቢኔ መሰብሰቢያ ቦታውን በድንገት ቀየረ።
⚡️የካቢኔው የስብሰባ ቦታ የተቀየረው በተፈጠረ የደህንነት ስጋት ሲሆን ፤ ከአሁን ወዲም ካቢኔው ቋሚ መሰብሰብያ ቦታ እንደማይኖረው ተገልፃል።
⚡️ሄዝቡላ ከጥቂት ቀናት በፊት የእስራኤል ጠቅላይ ሚንስቴር ቢንያም ኔታንያሁን ኢላማ አድርጎ የሰነዘረው ጥቃት በድንገት አፈተልኮ ከወጣው የስብሰባው አድራሻ ጋር ተደምሮ ወደ ዚህ ውሳኔ አምርቷል።
@Goqaeth
4 151
+1
ኢትዬጵያዊው ዮሚፍ ቀጀላ አዲስ ክብረ ወሰን አስመዘገበ!!
⚡️#ቫሌንሽያ በተካሄደዉ የግማሽ ማራቶን ውድድር ድል የቀናው ዮሚፍ ቀጀላ ይህ ያስመዘገበዉ ሁለተኛ ክብረወሰኑ ሆኗል።
⚡️በክረምቱ የፓሪስ ኦሎምፒክ የወንዶች 10,000 ሜትር ሩጫ ላይ 6ተኛ ወጥቶ ያጠናቀቀው ዮሚፍ በዚኛው ውድድር ትክክለኛ አቅሙን አሳይቶናል።
@Goqaeth
4 151
+2
#Update
"የደረሰብንን ጥቃት ማጋነንም ሆነ ማናናቅ አያስፈልግም" -አያቶላ ሆሚኒ
⚡️#የኢራን ከፍተኛ መሪ የሆኑት አያቶላ ሆሚኒ የቅዳሜው ጥቃት ባደረሰዉ ጥፋት መጠን ፤ የሀገሪቷን እና ህዝቦቿን አቅም የሚያንፀባርቅ ምላሽ መሰጠጥ አለበት ብለዋል።
⚡️የሀገሪቷ የዉጭ ጉዳይ ሚንስቴር በበኩላቸዉ የደረሰዉን ጥቃት ነቅፈው #የኢራን ምላሽ የመስጥ ህጋዊ መብት ላይ ለመምከር የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትን (ተ.መ.ድ) የጸጥታ ካዉንስል ስብሰባ ጠርተዋል።
በእውነቱ ከጥቃቱ ቁጥብነት እንዲሁም ከምዕራብ ሀገራት ፍላጎት አንፃር #ኢራን ቀጥተኛ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ እነደ ሄዝቡላና ሀማስ ባሉት ፀረ-አስራኤል ቡድኖች በኩል የማጥቃት ወይም የበለጠ የማስታጠቅ እርምጃ የመውሰድ አዝማምያዋ ያደላል።
@Goqaeth
4 151
+1
ሄዝቡላ ለሰሜን #እስራኤል ነዋሪዎች ማስጠንቀቅያ ሰጠች!!!
⚡️ሄዝቡላ የሰሜን እስራኤል ነዋሪዎች በአስቸኳይ አካባቢዉን ለቀው እነዲወጡ በሰጠዉ መግለጫ አሳዉቋል።
⚡️መግለጫዉ ላይ በተጠቀሱት ቦታዎች ውስጥ #የእስራኤል መከላኪያ ሀይል እስከሰፈረ ድረስ ቦታዎቹ ለታሰቡ ወታደራዊ ጥቃቶች ትክክለኛ ኢላማ እንደሚሆኑ ገልፀዋል።
#በኢራን የሚደገፈዉ ሄዝቡላ ይህንን ማስጠንቀቅያ ያወጣው እስራኤል ኢራን ላይ ካደረሰችው የሚሳይል ጥቃት ጥቂት ሰዐታት ቡኃላ መሆኑ አይዘነጋም።
@Goqaeth
4 151
+2
#የሶማሊያ መንግስት ለተ.መ.ድ የሴቶች ስብሰባ የወንዶች ልዑካን በመላክ በአለም ዙሪያ መነጋገሪያ ሆኖ ቆይቷል።
⚡️ሶማሊያን ወክሎ በስብሰባዉ የተሳተፈው የሶማሊያ የቤተሰብ ሚኒስቴር ጀነራል በሺር በ X ገፃቸዉ የለቀቁትን ፎቶ የሚድያ ገፆች እየተቀባበሉ ተችተዉታል።
⚡️የሶማሊያ ተቃዋሚዎች እና አክቲቪስቶች ክስተቱ የሶማልያ መንግስት በሴቶች ጉዳይ ላይ ያለዉን ቸልተኝነት የሚያንፀባርቅ ነው ብለዋል።
ክስተቱ ከወራት በፊት የሴቶች እና ሰብዐዊ መብቶች ሚኒስቴርን ስያሜ ወደ የቤተሰብ እና ሰብዐዊ መብቶች ሚኒስቴር የቀየረው የመንግስት ዉሳኔ ላይ ትኩረት ከመሳብ ባለፈ በአጠቃላይ ሀገሪቷ ለሴቶች የምትሰጠውን ቦታ ጥያቄ ውስጥ ከቷል።
@Goqaeth
4 151
+2
"ዶናልድ ትራምፕን መደገፍ ፤ ሴቶችን መቃወም ነዉ"
- ሚሼል ኦባማ
⚡️ዘጠኝ ቀናት የቀሩትን #የአሜሪካ ምረጫ በመመለከተ የሀገሪቷ የቀድሞ የክብርት እመቤት ሚሼል ኦባማ ካምላ ሀሪስን በመደገፍ ሚሺጋን ስቴት ዉስጥ ባደረገችዉ ንግግር የትራምፕ መልሶ መመረጥ የሴቶችን መብት የሚነፍግ እንደሆነ ተናገረች።
⚡️የ "Roe vs Wade" መሻር ሴቶች ወሊድ ነክ የህክምና አገልግሎቶችን በቀላሉ እንዳያገኙ ያደረገ መሆኑን ጠቅሳ እያንዳንዱ ወንድ እህቱን፣ እናቱን እና ሴት ልጆቹን እያሰበ እንዲመርጥ አሳስባለች።
ከዚህ በፊትም ሴቶች ላይ ባለው ምልከታ የሚወቀሰዉ ሪኘብሊካኑ ዶናልድ ትራምኘ በዚህ ምርጫ "Roe Vs Wade" ላይ ያለዉ አቋም በተደጋጋሚ እንደ ድክመት ተነስቶበታል።
@Goqaeth
4 151
+2
#Update
"ከአለም አቀፉ ስርዐት ተገላለች፤ የሀገር መሪዎች ሸሽተዋታል" ስትባል የቆየችው #ራሽያ እውነታው ያ እንዳልሆነ አስመሰከረች!!!
⚡️ባሳለፍነው ሃሙስ የተጠናቀቀው የብሪክስ ስብሰባ ላይ ከመሪዎች ጋር በደስታ ሲወያይ የታየው የራሽያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን አሁንም ቢሆን እንዳልተገለለ እና ከበርካታ ሀገራት ጋር ያለዉ ወዳጅነት እንዳቀጠለ አሳይቷል።
⚡️የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተ.መ.ድ) ዋና ፀሐፊዉን አንቶንዬ ጉቴሬዝን ጨምሮ የ36 ሀገራት መሪዎች የታደሙበት የብሪክስ 16ተኛው ስብሰባ የራሽያን ጠንካራ ጥምረቶች አስመስክሯል።
@Goqaeth
4 151
+1
#Update
#የኢራን ቀጣይ እርምጃ ምን ሊሆን ይችላል??!!
⚡️#እስራኤል ማንጊያዉን የኢራንን የጦር ካምፖች እና የአየር ሀይል ኢላማ አድርጋ ማጥቃቷ ይታወሳል።
ሆኖም በጥቃቱ 2 ወታደሮቿን ያጣችዉ #ኢራን የምትሰጠዉ የመልስ ምት ምን ሊሆን እንደሚችል አከራካሪ ሁንዋል።
⚡️አንዳንዶች የጥቃቱን ቁጥብነት ጠቅሰዉ #ኢራን ምላሽ አትሰጥም ሲሉ ሌሎች ደግሞ የወታደሮቹን ሞት አንስተዉ አፅፋዊ ምላሽ አይቀሬ ነው ይላሉ።
⚡️አሁን ላይ ስለ #ኢራን ምላሽ ተጨባች መረጃ ባይኖርም፤ የሀገሪቷ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር በሰጡት መግለጫ "ጥቃቱ የአለም አቀፍ ህግን የጣሰ" እንዲሁም "የኢራንን መልሶ ማጥቃት አስገዳጅ ያደረገ ነዉ" ሲሉ ተናግረዋል።
@Goqaeth
4 151
Repost from F.R.I.E.N.D.S
በጣም ከሚያስቁኝ ግን ከተሸማቀኩባቸው አጋጣሚዎች አንዱ ...
It was longgg ago Ig I was grade 2 እና አንድ ቀን ሠኞ ጠዋት ነው ወደት/ቤት ለመሔድ ጣጣዬን ጨርሼ ዩኒፎርም እየለበስኩ ሱሪዬን አጣሁት። እኔም እናቴም ቤቱን አመሠቃቀልነው ዩኒፎርሜ ሱሪው የለም። ከዛ አማራጭ ስላልነበረ አንደኛ ክፍል እለብሰው የነበረ ከመወልወያ ያመለጠ የተቀደደ ዩኒፎርም ነበረኝ እና እሱን ለበስኩ። ዩኒፎርሙ አቀዳደዱ (ወንዶች ታቁታላችሁ) ከፊት ዚፑ ጀምሮ ሙሉ ስፌቱ እስከኋላ ቀበቶ ማሠሪያው ድረስ ተበታትኗል። ከዛ እሱን ለብሼ ወደት/ቤት ስሔድ ሠዓት ረፍዶ ስለነበር ከብዙ አርፋጆች ጋር በር ላይ አቆሙን (ልንቀጣ መሆኑ ነው)። ከዛ ዳይሬክተራችን መጣ እና ለሁላችንም አቃቂር ማውጣት ጀመረ።
የመጀመሪያውን "አንተ እድሜ ልክ አትለወጥም አይደል ቆይ ወደዛ ወጣ ብለህ ጠብቅ አሳይሃለሁ"
ሁለተኛውን "አይይይይ አንተ ሂድ ወደ ቤት ወላጅ ሳትይዝ ድርሽ እንዳትል የአንተ ነገር በቅቶናል ..."
እያለ እኔ ጋር ደረሰ እና በሱሪዬ መቀደድ እና ጠባብነት ድክምምምምም ብሎ እየሳቀ "አረ ይሄንን ጉድ እዩትማ ሱሪውን እኮ እንደካልሲ የቀኝ እግር ለብቻ የግራ ለብቻ ነው ያደረገው" አለኝ።😂😭😂😭😂😭
@PityTruth
4 151
+1
#update
⚡️የእስራኤል ሃይል የበቀል እርምጃውን በኢራን ላይ እየወሰደ ነው
⚡️በአየር እና በባለስቲክ ሚሳኤል የኢራንን ዋና ከተማ ቴህራንን የደበደበችው እስራኤል ጉዳቱ ምን ያክል እንደሆነ እስካሁን አልታወቀም ቢሆንም የኢራንን አየር ሃይል እና ባለስቲክ ሚሳኤል ማምረቻ ቦታዎችን እንደሆነ ያሉት ማስረጃዎች ያሳያሉ::
⚡️ጥቃቱ ለተወሰነ ሰአታት ተከናውኖ አሁን ላይ ቢያበቃም ቀጣይነት ሊኖራቸው እንደሚችል ፍንጭ የሰጡትየእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ናቸው::
4 151
"የሰሜን ኮሪያን ጦር መጠቀም እና ያለመጠቀም ጉዳይ የእኛ ውሳኔ ነው" - ፕሬዝዳንት ፑቲን
⚡️በዩክሬን ኘሬዝዳንት ዝሌንስኪ በተደጋጋሚ የቀረበው የሰሜን ኮራያ ወታደር ራሽያ ውስጥ የመኖር ክስ የምስል ማስረጃ ከማግኘት ባለፈም ከራሱ ከኙቲን ማረጋገጫ አግኝቷል።
⚡️እስካሁን ባለው መረጃ መሠረት 3000 የሚደርሱ የሰሜን ኮሪያ ልዩ ሀይል ወታደሮች በራሽያ መሬት ላይ ስልጠና እያደረጉ ሲሆን ፤ ሰሜን ኮሪያ በአጠቃላይ 10,000 ወታደሮች ለመላክ እንደተስማማች ይነገራል።
ይህ አስጊ ወታደራዊ ጥምረት #የዪክሬን-ራሽያን ጦርነት አድማስም ሆነ አይነት ሙሉ በመሉ ሊቀይር የሚችል ሲሆን የምዕራብ ሀገራት ቀጣይ እርምጃ ከጦርነቱ ባለፈ የአለም አቀፍ ሀገራት የሀይል አሰላለፍ ላይ ታላቅ ተፅኖ ይኖረዋል።
@Goqaeth
4 151
+2
#የብሪክስ ስብሰባ ትናንት በይፋ መጠናቀቁን ተከትሎ እነዚህን መሰረታዊ ሃሳቦች የስብሰባው አጀንዳዎች ነበሩ
⚡️ህንድ ከኢራን ጠቅላይ ሚኒስተር ጋር በአለም አቀፍ ጉዳዮች ተወያዩ
ይህ የሆነው ህንድ ለእስራኤል ቁጥር የድሮን መስሪያ እና ሌሎችን በማስታጠቅ ላይ እንዳለች
ነው
⚡️ጠቅላላ አባላቱ እስራኤልን አውግዘዋል አክለውም ጦርነቱ በአስቸኳይ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረግ ብለዋል
⚡️የሳውዲው ልኡል በስብሰባው ላይ አልተገኙም ከዛ ይልቅ ከአሜሪካው ስቴት ሴክሪተሪ አንቶኒዮ ብሊንከን ስብስባ አድርገዋል
⚡️አክለውም 13 ሃገራትን እንደ አልያንስ ተቀብለዋቸዋል
እነርሱም
Algeria
Belarus
Cuba
Indonesia
Malaysia
Nigeria
Turkey
Uganda
Uzbekistan. ናቸው
4 151
#እስራኤል ኢራን ላይ ባቀደችው የበቀል እርምጃ አንድ ሺህ የሚጠጉ ባላስቲክ ሚሳይሎችን ልታስወነጭፍ እንደምትችል ተገምቷል!!
⚡️ኢራን በበኩሏ የተታቀደዉ ጥቃት የኒውክሌር እና የነዳጅ ማውጫ ስፍዎቿን ያነጣጠረ ከሆነ አስከፊ መላሽ እንደሚኖረዉ አስጠንቅቃለች።
⚡️ኒውዮርክ ታይምስ ከኢራን ባለስልጣናት ባገኘዉ መረጃ መሰረት ሀገሪቱ ከቴልአቪቭ የሚፈጸመውን ጥቃት ለመመከት እና ከእዚያ በኋላ ስለሚኖሩ ምላሾች ከፍተኛ ዝግጅት በማድረግ ላይ ትገኛለች።
@Goqaeth
