ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ
Open in Telegram
ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።
Show more638
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-1130 days
Posts Archive
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ እንኳን #ለሰሞነ_ሕማማት ለመጨረሻ ቀን #ለቀዳም_ሥዑር እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
❤ #ዕለተ_ቅዳሜ።
❤ በዚች ቀን አባታችን አዳምም ከፈጣሪው ጋር ታረቀልን በማለት "ገብረ ሰላመ በመስቀሉ ትንሣኤሁ አግሃዶ፤ በመስቀሉ ሰላም አደረገ ትንሣኤውን ገለጠ" ሊቁ ቅዱስ ያሬድ። እያልን የተድላ፣ የደስታ ምልክት ወይም መገለጫ የሆነ ልምላሜ ያለውን ቆጽለ ሆሣዕና ወይም ቄጤማ ግጫ ይዘን የምሥራች እንባባላለን፡፡ ኤፌ. 2፥14-15 "ወዘእንበለ ምሳሌሰ ኢተናግሮሙ፣ ያለ ምሳሌ አልተናገረምና እንዳለ" ማቴ 13፥34-35 በኖኅ ጊዜም ርግብ "ሐጸ ማየ አይኅ፣ ነትገ ማየ አይኅ፣ የጥፋት ውኃ ጎደለ፣ አለቀ" እያለች ቈጽለ ዕፀ ዘይት ይዛ ለኖኅ አብስራዋለች፡፡ ዘፍ. 8፥8-11 ርግብ የካህናት፣ ኖኅ የምእመናን፣ ኖኅ እጁን ዘርግቶ ርግብን እንደተቀበላት ካህናትም በየመንደሩ እየዞሩ ክርስቶስ ተመረመረ ዲያብሎስ ታሰረ በማለት ቄጤማ ሲያድሉ ምእመናንም እጃቸውን ዘርግተው መቀበላቸው የዚህ ምሳሌ ነው፡፡ ስለዚህ አሁንም ቢገኝ የወይራ ልምላሜ ቢታጣ ግጫን እየታደልን የምሥራች መባባላችን ነፍሳት ከሲኦል ለመውጣቸው መታሰቢያ ነው፡፡ ይህን ቈጽለ ልምላሜ ይዞ ተድላ፣ ደስታ መግለጽ ከጥንት ጀምሮ ሲያያዝ የመጣ ነው እንጂ እንግዳ ነገር አይደለም፡፡ ለዚህ በመጀመሪያዪቱ ቀን ከበጎ እንጨት ፍሬን የሰሌንና የተምር ዛፍ ልምላሜ ይዛችሁ በየዓመቱ ሰባት ቀን ተድላ፣ ደስታ ታደርጋላችሁ ብሏል፡፡ ዘሌ. 23፤40-44
❤ #አክፍሎት።
❤ አክፍሎት ማለት ማካፈል፣ ማጠፍ፣ መደረብ፣ ሁለቱን ቀን አንድ አድርጎ መጾም፣ ጌታ ከተያዘበት እስከተነሣበት ድረስ ይህ ሥርዓት የመጣው በቤተ ክርስቲያናችን ትምህርት እመቤታችን፣ ያዕቆብና ዮሐንስ የጌታን ትንሣኤ ሳናይ እህልና ውኃ አንቀምስም ብለው እስከ ትንሣኤ በመቆየታቸው ምክንያት ነው፡፡ በሀገራችን ብዙ ሰዎች ሐሙስ ማታ የቀመሱ እሑድ የትንሣኤ ዕለት ብቻ እህልና ውኃ የሚቀምሱት፤ ያልተቻላቸው ግን ዓርብ ማታ የቀመሱ እስከ ትንሣኤ ይሰነብታሉ፡፡ የሁለት ቀን ማክፈሉ እንኳ ቢከብድ ቅዳሜን ማክፈል ሥርዓት ነው፡፡ ቅዳሴው በመንፈቀ ሌሊት ስለሆነ በልቶ ማስቀደስና መቁረብ እንዳይሆን፡፡
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "አንሰ ሰከብኩ ወኖምኩ። ወተንሣእኩ እስመ እግዚአብሔር አንሥአኒ። ኢይፈርህ እምአእላፍ አሕዛብ"። መዝ 3፥5-6 ወይም መዝ 125፥2። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 5፥6-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 3፥15-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 3፥12-15። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 27፥62-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ቅዳሴ ነው።
❤ እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ፃዕማ ወድካም አመ ከመዮም ያብጽኀነ ያብጽዕክሙ እግዚአብሔር በፍስሃ ወበሰላም።
❤ መልካም በዓልና የአፍሎት ጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ የሚጽፍለትም ጸሐፊ መረጡለት ስለ ምዕመናን አጠባበቅና ስለማስተማር ወደ አገሮች ሁሉና ወደ ኤጲስቆጶሳቱ መልእክት ይልክ ነበር።
❤ እርሱም ከኃጢአታቸው ተመልሰው ንስሐ እንዲገቡ ሕዝቡን ይመራቸውና ይገስጻቸው ነበር እግዚአብሔርን ይፈሩት ዘንድ። ንጽሐ ነፍስ ንጽሐ ልቡና ያለው ሆነ የዚህን ዓለም ጣዕም ያለውን ምግብ አይሻም አይመኝም ክብሩንም ቢሆን ወይም ጥሪቱን ለድኆችንና ችግረኞችን አስቦ ይመጸውታቸው ነበር እንጂ። ከእነርሱ የሚተርፈውን ለቤተ ክርስቲያን ማሠሪያ ያደርገው ነበር።
❤ ይህ አባት ሙሉ ዓመት አልኖረም በዚያ የሚያንስ ነው እንጂ። በሰላም በፍቅርም ሚያዝያ3 ዐረፈ። ከአባ ሚካኤል በረከቱ ከእኛ ጋር ለዘላለሙ ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የሚያዝያ3 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለመርቄ_ክርስቲያናዊ_ክቡር። እንተ መጠወ ወርቆ ለእግዚአብሔር። ሶበ ፈነወ ፵ በመድሎተ ልጥር። ወሰላም በፍቁሩ መምለኬ ጣዖት ጉዝፋር። ምስለ ሰብአ ቤቱ ዘአምነ እምዝንቱ መንክር"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሚያዝያ_3።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ሚያዝያ ፫ (3) ቀን።
❤ እንኳን #ለክርቲያናዊ_ነጋዴ ሲያርፋ ሁለት አንበሶች የቀበሩትና የላከው አርባ ልጥረ ወርቅ መብዓ ከሰማይ በክብር ወርዶ ራሱ ጌታችን በእጁ ለተቀበለው #ለቅዱስ_መርቄ ለዕረፍት በዓል፣ ለኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ #ለአባ_ዮሐንስ ለዕረፍት በዓልና #ለእስክንድርያ_ሰባ_አንደኛ_ሊቀ_ጳጳሳት_ለአባ_ሚካኤል ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #ለቅዱስ_መርቄ፦ ይህም ቅዱስ ከአንጾኪያ ሰዎች ወገን ነው ጉዝፋር የሚባልም ወዳጅ ነበረው ይህም ጉዝፋርም ጣዖት የሚያመልክ ከሀዲ ነው ከሃይማኖት በቀር በምንም በምን አይለያዩም።
❤ ከዕለታትም በአንዲቱ መርቄና ጉዝፋር ግዱድ ወደሚባል አገር ለንግድ ሒደው ሰው በሌለበት በበረሀ ውስጥ አምስት ቀን ተጓዙ ክርስቲያናዊ መርቄም ባለጸጋ ነው ከእርሱ ጋራም አርባ ልጥረ ወርቅ ነበር።
❤ በጎዳና በጉዞ ላይም እያሉ ለሞት የሚያደርስ ደዌን ታመመ ከዚያም ራሱን አጽናንቶ እንዲህ ብሎ ጻፈ "ከባሪያህ ልጅ ከባሪያህ መርቄ ከእኔ ያለ በጥቁር በቅሎ የተጫነ አርባ ልጥረ ወርቅ ለአንተ ይሁን ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ የክብር ባለቤት ሆይ ስለ በደሌ ይቅር ብለኸኝ መንግሥተ ሰማያትን ትሰጠኝ ዘንድ ለልጆቼ ለሚስቴም ወይም ለዘመዶቼ አይሁን ብዬአለሁ"። ይቺን ደብዳቤ ጠቅልሎ ወዳጁ ጉዝፋርን ጠራው የሚለውን ሁሉ ያደርግለት ዘንድ አማለው። ከዚያም በምሞትበት ጊዜ አትንካኝ ግን ይህን አርባ ልጥረ ወርቅ እንደተጫነ ከበቅሎው ጋራ ወስደህ የክብር ባለቤት ለሆነ ለሕያው እግዚአብሔር ልጅ ለጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ በእጁ ስጠው። ለልጆቼ እንዳትሰጥ ከእርሱ በቀር ለማንም ቢሆን አትስጥ" አለው። ጉዝፋርም እንዲህ ብሎ መለሰለት "አንተ ራስህ ሞቶ ተነስቶ ወደ ሰማይ ወጣ የምትል አይደለምን እኔ ወደ ሰማይ ወጥቼ ልሰጠው እችላለሁን?"።መርቄም እንዲህ አለው "ወደ ቤተ ክርስቲያን ሒድ ራሱ ወደ አንተ ይመጣል እጅ በእጅ ስጠው" አለው።
❤ ከዚህ በኋላ መርቄ ለመሞት ሲቃረብ ራቅ ብሎ በመቀመጥ ጉዝፋር መሞቱን ይጠብቅ ነበር። ወደርሱም መላእክት የብርሃን ልብስ ይዘው ሲወርዱ አየ ከእርሳቸውም ጋራ ጻድቃን ሰማዕታት አሉ ዳዊትም በመሰንቆ ያመሰግን ነበር መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል ወርዶ በሥጋው ላይ ሦስት ጊዜ ዞረ ያንጊዜም የመርቄ ነፍስ ከሥጋዋ ተለይታ ወደ ሰማይ እንዲህ ባለ ሁኔታ ዐረገች። ሁለት አንበሶችም መጡ ምድሩንም ቆፍረው ቀበሩት።
❤ ጉዝፋርም ተነሣ የመርቄንም ወርቅ ጭኖ ስለአየው ሁሉ እያደነቀ ሔደ። አንጾኪያም በደረሰ ጊዜ የቤተ ክርሰቲያንኑን አስተዳዳሪ ቀሲስ ታዴዎስን አግኝቶ መርቄ እንዳለው ነገረው። ቀሲስ ታዴዎስም ሊረከበው ወደ ጉዝፋር ሔደ። ግን "የክብር ባለቤት ከሆነ ከጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ለማንም አልሰጥም ወዳጄ መርቄ እንዳማለኝ እጅ በእጅ እሰጠዋለሁ እንጂ" ብሎ ከለከለው።
❤ ከዚያም ሒዶ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ቅጽር ግቢ ገባ። ቀሲስ ታዴዎስም ደጁን ከፈተለት የተጫነውንም ወርቅ አውርዶ በፊቱ አኑሮ በዚያ ቆመ። ከሌሊቱ እኩሌታ ላይ እንደ ነጐድጓድ ድምጽ ያለ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሰማ። ታላቅ ብርሃንም ወጣ ጌታችንም ከሰማይ ወርዶ በመሠዊያው ላይ ተቀመጠ መላእክትም ከእርሱ ጋር አሉ። ከመላእክትም አንዱ "ከሀዲ ጉዝፋር ከዚህ ለምን ቆምክ" አለው። እርሱም "ወዳጄ መርቄ ለክብር ባለቤት ለጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እንጂ ለሌላ እንዳይሰጥ ብሎ እንደማለው" ነገረው። መልአኩም "የክብር ባለቤት የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ጌታ ኢየሱስ ክርሰቶስ ይህ ነውና ና ስገድ" አለው። ጉዝፋርም ሰገደ ደብዳቤውንም ሰጠው እየተንቀጠቀጠም "የክብር ባለቤት ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ አመንኩብህ" አለ።
❤ ጌታም ያንን ወርቅ ይመዝኑት ዘንድ አዘዘ። አርባ ልጥርም ሆነ ጉዝፋርንም ከቀሲስ ታዴዎስ ዘንድ እንዲጠመቅ አዘዘው። ከቤተሰቡ ሁሉ ጋር ተጠመቀ የተጠመቁትም ሰባ አምስት ነፍስ ሆኑ። ኃጢአተኛውን በንስሐ ተመልሶ መዳኑን እንጂ መሞቱን ለማይወድ ቸር ይቅር ባይና ሰውን ለሚወድ እግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #ለኢየሩሳሌም_ኤጲስቆጶስ_አባ_ዮሐንስ፦ የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ የኦሪት ምሁራን የሆኑ አዋቂዎች ነበሩ የኦሪትን ሕግ ትምህርቶችንም እያስተማሩት አሳደጉት። ክርስቲያኖችን በጸና ልቡና የሚከራከራቸውና የሚጣላቸው ነበር መጻሕፍትን አዘውትሮ ከመመርመሩ የተነሣ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ዓለም እንደመጣና ሰውም እንደሆነ በሞቱም ዓለምን እንደአዳነ አመነ። እርሱም የባሕርይ አምላክ እንደሆነ አምኖ በኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስነት ለመሾም እስቲገባው ድረስ በበጎ ሥራው በዕውቀት አደገ።
❤ ኤልያስ የሚባለው እንድርያኖስም በነገሠ ጊዜ ከኢየሩሳሌም አገር የፈረሰውን ሕንፃ ሁሉ እንዲያንፁና በስሙ ኤልያስ ተብሎ እንዲጠራ አዘዘ። ከዚህም አይሁድ ምኵራብ ደጃፍ ላይ ታላቅ ግምብ ሠሩ ከከበረ ደንጊያም ሠሌዳ ሠርቶ በላዩም ስሙን ኤልያስን ጽፎ በመግቢያው አኖረው በዘመኑም ኢየሩሳሌም አሕዛብንና አይሁድን ተመላች ሠለጠኑባትም።
❤ ክርስቲያኖችም ሊጸልዩ ወደ ጎልጎታ ሲመጡ በአዩአቸው ጊዜ አሕዛብ ይከለክሉአቸው ነበር በዚያ ዝሁራ በሚባል ኮከብ ስም መስጊድ ሠርተው ነበርና። ስለዚህም ክርስቲያኖችን በዚያ እንዳያልፉ ይከለክሏቸው ነበር። በዚህም አባት ላይ አሕዛብ ታላቅ መከራና ኀዘን ደረሰበት ብዙ ጊዜ ደብድበውታልና በምድር ላይም ጐትተውታልና አጐሳቁለውታልና እርሱም ነፍሱን ወደርሱ ይቀበል ዘንድ የክብር ባለቤት ጌታችን ልመናውን ሰምቶ ሚያዝያ3 በሰላም ዐረፈ። የአባ ዮሐንስ በረከቱ ከእኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ሚካኤል፦ ይህ የከበረ አባት በእስክድርያ ለተሾሙ አባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሰባ አንደኛ ነው። ይህ አባት ከታነሽነቱ ጀምሮ የምንኵስና ልብስ ሊለብስ ወደደ በአስቄጥስ ገዳም በአባ መቃርስ ቤተ ክርስቲያን መንኵሶ እስከ ሸመገለ ድረስ በዚያ ኖረ። በብዙ መነኰሳትም ላይ አበ ምኔት ሁኖ ተሾመ በዘመኑ ሁሉ መልካም ተጋድሎ በመጋደል እግዚአብሔርን ደስ አሰኘው። በወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ ወንበር ላይ ሊቀ ጵጵስና ለመሾም እስቲገባው ድረስ ፍጹም ተጋድሎ በመጋደል ደከመ።
❤ ከእርሱ በፊት የነበረ ሊቀ ጳጳሳት አባ ገብርኤል በዐረፈ ጊዜ ወንጌላዊ ቅዱስ ማርቆስ ወንበር ያለ ሊቀ ጳጳሳት አራት ወር ኖረ በዚች ሹመት የሚሻል ሲመረምሩና ሲመርጡ ብዙ ደከሙ። ከብዙ ድካምም በኋላ ሦስት የገዳም ሰዎችን መርጠው ስማቸውን በሦስት ክርታስ ጻፉ የክብር ባለቤት የጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስንም ስም በአንዲት ክርታስ ጽፈው እየአንዳንዳቸውን አሽገው በመሠዊያው ውስጥ አኖሯቸው። ቸር ጠባቂ ይሾምላቸው ዘንድ ኤጲስቆጶሳቱና ካህናቱ እስከ ሦስት ቀን እየጸለዩና እየቀደሱ እግዚአብሔርን በመማለድ ኖሩ። ከሦስት ቀኖችም በኋላ አንድ ታናሽ ብላቴና ጠርተው "ከእነዚህ ከሦስቱ ስሞች አንዱን አንሥተህ ስጠን" አሉት። ያም ብላቴና የዚህን አባት አባ ሚካኤል ስም ያለበትን ያንን ክርታስ አወጣ። ሁሉም እግዚአብሔር እንመረጠው አውቀው ይገባዋል ይገባዋል ይገባዋል እያሉ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት እርሱም በሹመቱ ላይ ሁኖ እንደሚገባ በመልካም አመራር ሥራውን መራ።
❤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።❤
❤ እንኳን ለክብር ባለቤት #ለጌታችን_ለአምላካችን_ለመድኃኒታችን_ለኢየሱስ_ክርስቶስ ለዐበይት በዓል ለአንዱ ለሰሞነ ሕማማት አምስተኛ ቀን #ለስቅለት_መታሰቢያ_በዐል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
❤ #ዕለተ_ዓርብ።
❤ የስቅለት ቀን ስቅለት ማለት መስቀል፣ መሰቀል፣ አሰቃቀል ማለት ነው፡፡ መስቀል በቁሙ መስቀያ፣ መመዘኛ፣ መሰቀያ፣ መንጠልጠያ፣ ለሞት የሚያበቃ መከራ በማር 8፥34 "ወጸውዖሙ ለሕዝብ ምስለ አርዳኢሁ ወይቤሎሙ ዘይፈቅድ ይፀመደኒ ይጽልአ ለነፍሱ ወያጥብዕ ወይፁር መስቀል ሞቱ ወይትልወኒ፤ ከደቀ መዛሙርቱም ጋር ሕዝቡን ጠርቶ እንዲህ አላቸው፡፡ ሊከተለኝ የሚወድ ሰው ራሱን ይካድ፤ ጨክኖም የሞቱን መስቀል ተሸክሞ ይከተለኝ" ይላል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም በ1ኛ ቆሮ. 1፤17 ላይ "ወኢኮነ በጥበበ ነገር ከመ ኢንስዐር መስቀሎ ለክርስቶስ የክርስቶስን መስቀሉን ከንቱ እንዳናደርግ ነገርን በማራቀቅ አይደለም" ይላል፡፡
❤ ጌታችን በተሰቀለ ዕለት ከሰድስት ሰዓት ጀምሮ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ በምድር ሁሉ ላይ ጨለማ ሆነ፡፡ ፀሐይ ጨለመ፣ እነሆም የቤተ መቅደስ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ከሁለት ተቀደደ፤ ምድርም ተናወጠች፤ ዓለቶችም ተሰነጠቁ፤ መቃብሮችም ተከፈቱ፤ ተኝተውም ከነበሩት ቅዱሳን ብዙዎች ተነሱ፤ ከትንሣኤውም በኋላ ከመቃብሮች ወጥተው ወደ ቅድስት ከተማ ለብዙዎች ታዩ፡፡ ማቴ. 27፤51
❤ ጌታችን ለዓለሙ ያሰበውን ቤዛነት ሊፈጽም በመስቀል ላይ መሰቀሉ የሚታሰብበት ነውና ለስቀለቱ መታሰቢያ የሚሆን አጎበር ተዘጋጅቶ ከርቤ እየታጠነ ስቅለቱ የሚመለከቱ ምንባባት ሲነበብና ሲሰገድ ይዋላል፡፡ የሰው ልጅ በሙሉ በእግረ አጋንንት ረግጦ ከፈጣሪው ተጣልቶ ለ5500 ዘመን በጨለማ መኖሩን ለማስታወስም መንበሩ ታቦቱ በዚህ ቀን በጥቁር ልብስ ይሸፈናሉ፡፡ ዲያቆኑም በቤተ ክርስቲያን በመዞር የሚያሰማው የቃጭል ድምፅ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለቅሶ አንድም ዋይ ዋይ እያሉ የተከተሉት የኢየሩሳሌም ሴቶችን ሙሾም ምሳሌ ነው፡፡ ሉቃ. 23፤31 በዕለተ ዓርብ ነፍሳት ከሲኦል ወጡ፡፡ አንቀጸ ገነት ተከፈተልን፣ ርስተ መንግስተ ሰማያት ተመለሰችልን።
✝ ✝ ✝
❤ #የጠዋት_የ12_ሰዓት_ምስባክ፦ "እስመ ቆሙ ላዕሌየ ሰማዕተ ዐመፃ። ወሐሰት ርዕሰ ዐመፃ። እስመ ቆሙ ላዕሌየ ሰማዕተ ዐመፃ"። መዝ26፥12 ወይም መዝ34፥11። የሚነበቡት ወንጌላት ማቴ 27፥1-14፣ ማር 15፥1-5፣ ሉቃ 22፥66-71 እና ዮሐ18፥28-40 ናቸው።
✝ ✝ ✝
❤ #የሦስት_ሰዓት_ምስባክ፦ "ዐገቱኒ ከለባት ብዙኃን። ወአኃዙኒ ማኅበሮሙ ለእኩያን። ዐገቱኒ ከለባት ብዙኃን"። መዝ 21፥16። የሚነበቡት ወንጌላት ማቴ 27፥15-16፣ ማር15፥6-15፣ ሉቃ 23፥13-25 እና ዮሐ 19፥1-12 ናቸው።
✝ ✝ ✝
❤ #የስድስት_ሰዓት_ምስባክ፦ "ቀነውኒ እደውየ ወእገርየ። ወኈለቁ ኲሎ አዕፅምትየ። ቀነዉኒ እደውየ ወእገርየ"። መዝ 21፥16። የሚነበቡት ወንጌላት ማቴ 27፥27-45፣ ማር 15፥16-33፣ ሉቃ 23፥27-44 እና ዮሐ 19፥13-27 ናቸው።
✝ ✝ ✝
❤ #የዘጠኝ_ሰዓት_ምስባክ፦ "ወወደዩ ሐሞተ ውስተ መብልየ። ወአስተዩኒ ብሒዐ ለጽምዕየ። ወወደዩ ሐሞተ ውስተ መብልየ"። መዝ 68፥21። የሚነበቡት ወንጌላት ማቴ 27፥46-50፣ ማር 15፥34-37፣ሉቃ 23፥45-46 እና ዮሐ 19-28-30 ናቸው።
❤ እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ፃዕማ ወድካም አመ ከመ ዮም ያብጽኀነ ያብጽዕክሙ እግዚአብሔር በፍስሃ ወበ ሰላም።
❤ መልካም የስቅለት በዓልና የስግደት ቀን ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ❤
❤ #ሚያዝያ ፪ (2) ቀን።
❤ እንኳን #ለቅዱስ_ቃይናን_ልጅ_ለቅዱስ_መላልኤል ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓል፣ ፊት እንደ ውሻ የሚመስል የሆነ በጸሎቱ ታላላቅ ተዓራትን አድርጎ አስተምሮ ሊይዞት የመጡትን ወታደሮችና ሊያስቱት የመጡ ሁለት አመንዝራ ሴቶችን #በእግዚአብሔር_አምነው ሰማዕትነት እንዲቀበሉ ላደረገ #ለቅዱስ_ክርስትፎሮስ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓልና ከሐሊባ አገር ሰው ለሆነ #ለከበረ_አባት_ለቅዱስ_ስምዖን ለዕረፍቱ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ከሚታሰቡት፦ #በቅዱስ_ክርስትፎሮስ በትምህርቱና በሚታደርገው ተዓምራት አምነው ሰማዕትነት ከተቀበሉ #ከሁለት_ሴቶች_ከሁለት_መቶ_ወታደሮችና ከሌሎች ብዙ ሰዎች እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱስ_መላልኤል፦ መቶ ስልሳ አምስት ዓመት ኖረ ቅዱስ ያሬድን ወለደው። ቅዱስ መላልኤልም ያሬድ ከወለደው በኋላ ሰባት መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ ወንዶችና ሴቶች ልጆችን ወለደ።
❤ የቅዱስ መላልኤል መላ ዘመኑ ሁሉ ስምንት መቶ ዘጠና አምስት ዓመት ነው። ይኸውም ሚያዝያ ሁለት ቀን በእሑድ ዕለት ሞተ በማከማቻም ውስጥ ቀበሩት። የፈጣሪው በረከት በላያችን ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱስ_ክርስትፎሮስ፦ ይህም ቅዱስ ሰውን ይበሉ ከነበሩ ሰዎች አገር ነው በጦርነትም ማረኩት አባቱም በሐዋርያ ቅዱስ ማትያስ እጅ ያመነ ነው።
❤ በማረኩትም ጊዜ ቋንቋቸውን አያውቅም ነበር የክብር ባለቤት ወደሆነ እግዚአብሔርም ማለደ ቋንቋቸውንም ገልጦለት እንደርሳቸው ተናገረ የክርስቲያን ወገኖችን የሚያሠቃዩአቸውንም ገሠጻቸው የጦር ሠራዊቱንም የሚመራ መኰንን ጽኑዕ ግርፋትን ገረፈው። ቅዱስ ክርትፎሮስም
መኰንኑን "የጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ትእዛዙ ኃይሉን ባትይዘኝና ባታስታግሠኝ አንተና ሠራዊትህ ከእኔ እጅ ባልዳናችሁ ነበር" አለው። መኰንኑም ስለ ርሱ ወደ ንጉሥ ላከ ከእርሱ የሆነውንም ነገረው።
❤ ንጉሡም ወደ ርሱ እንዲያመጡት ሁለኀት መቶ ወታደሮች ላከለት እርሱም ያለ መፍራት ያለ ማፈግፈግ አብሮቸው ሔደ። በእጁ በትር ነበረች በላይዋ በጸለየ ጊዜ በቀለችና አበበች። እነዚያ ወታደሮች ተርበው የሚበሉት እንጀራ በአጡ ጊዜ ቅዱስ ክርስትፎሮስ ጸለየ በእነርሱ ዘንድ እንጀራ በዝቶ ተትረፈረፈ እጅግም አድንቀው በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ። ወደ አንጾኪያም ደርሰው በሊቀ ጳጳሳት አባ ጳውሎስ እጅ የክርስትና ጥምቀትን ተጠመቁ።
❤ ወደ ንጉሡም ፊት በደረሱ ጊዜ ንጉሥ ዳኬዎስ ሊያስፈራውና ሊሸነግለው ጀመረ ደግሞ እጅግ መልከ መልካም የሆኑ ሁለት አመንዝራ ሴቶችን ወደርሱ ሰደደ እነርሳቸው እንደሚያስቱትና በኃጢአት እንደሚጥሉት አስቧልና። እርሱ ግን ገሠጻቸው አስተማራቸውም በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምነው በደማቸው ምስክር ሆኑ። እንዲሁም እነዚያ ሁለት መቶ ወታደሮች በንጉሡ ፊት በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመኑ ራሶቻቸውንም በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ የሰማዕትነትንም አክሊል በመንግሥት ሰማያት ተቀበሉ።
❤ ቅዱስ ክርስትፎሮስም ንጉሡን "አንተ የሰይጣንን ሥራ የምትቀበል ማደሪያው የሆንክ" ብሎ ዘለፈው ንጉሡም ተቆጥቶ በትልቅ ብረት ምጣድ ውስጥ እንዲጨምሩትና ከበታቹ እሳትን እንዲያነዱ አዘዘ። እንዲሁም አደረጉበት ነገር ግን ከጉዳት እንዳሰቡት ምንም የደረሰበት የለም። ጤነኛ ሁኖ ሰዎችን አስተማራቸው እንጂ። እጅግም አድንቀው በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ። ቅዱሱንም ከእርሷ ሊአወጡት ወደዚያች ብረት ምጣድ ቀረቡ ንጉሡም አንገታቸውን በሰይፍ እንዲቆርጧቸው አዘዘ የሕይወት አክሊልንም ተቀበሉ።
❤ ከዚያም በኋላ ታላቅ ደንጊያ በአንገቱ አንጠልጥለው ከጥልቅ ጒድጓድ እንዲጨምሩት ንጉሡ አዘዘ በጨመሩትም ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ በጤንነት አወጣው። ማሠቃየቱንም በሰለቸ ጊዜ አንገቱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ ንጉሡ አዘዘ። ቅዱሱም በእግዚአብሔር መንግሥት የድል አክሊል ተቀዳጀ። ጸሎቱ በረከቱ ከእኛ ጋር ለዘላለም ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የሚያዝያ2 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለክርስትፎሮስ_ዘተፄወወ_በጸብእ። በውስተ ሀገሩ ዘእምነ በትምእምርተ ማትያስ ረድእ። በህየ ተቀትለ በእንተ ክርስቶስ እግዚእ። ወሰላም ለእለ ሞቱ ምስሌሁ በስንዕ። ክልኤቱ አንስት ወአምዓት ሰብእ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ(አርኬ) #የሚያዝያ_2።
❤ እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ፃዕማ ወድካም አመ ከመዮም ያብጽኀነ ያብጽዕክሙ እግዚአብሔር በፍስሃ ወበሰላም።
❤ መልካም የሰሞነ ሕማማት የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።❤
❤ እንኳን #ለሰሞነ_ሕማማት_አራተኛ_ለሕጽበተ እግር፣ #ለጸሎተ ሐሙስ_ለምስጢር ቀን_ለሐዲስ #ኪዳን_ሐሙስ_ለነጻነት_ሐሙስና_ለአረንጓዴው_ሐሙስ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
❤ #ዕለተ_ሐሙስ።
❤ ከስቅለትና ከትንሣኤ በፊት ያለው ሐሙስ በቤተ ክርስቲያናችን የተለያዩ ስያሜዎች አሉት፡፡
1) #ሕጽበተ_እግር_ይባላል።
❤ ይህ ስያሜ የተሰጠው ጌታችን በዚህ ዕለት የደቀ መዛሙርቱን እግር በማጠቡ ምክንያት ነው፡፡ ይህም የሚያሳየው የዓለምን ኃጢአት ለማጠብ የመጣ መሆኑን ነው፡፡ ይህንን ለማስታወስ ዛሬ ካህናት ጳሳሳት በመካከላችን ተገኝተህ የእኛንና የሕዝቡን ኃጢአት እጠብ ሲሉ በቤተ ክርስቲያናችን የተገኙትን ምእመናን እግር በወይንና በወይራ ቅጠል ሲያጥቡ ያረፍዳሉ፡፡ ዮሐ 13፤4-15።
2) የትእዛዝ ሐሙስ ይባላል ምክንያቱም፦
2.1. ከኅጽበተ እግር በኋላ ጌታችን ደቀመዛሙርቱን እናንተም እንዲሁ አድርጉ ብሎ ስላዘዘ።
2.2. በጌቴሴማኒ "ወደፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ ብሎ ያዘዘት ዕለት በመሆኑ"።
2.3. ሥርዓተ ቁርባንን ከሠራ በኋላ ‹‹ከመዝ ግበሩ›› መታሰብያን አድርጉ በማለት በዚህ ዕለት ያዘዘበት በመሆኑ ነው፡፡
3) #የጸሎት_ሐሙስ_ይባላል፡፡
❤ የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ የሚደክም ሥጋን የተዋሐደ አምላክ ፍጹም ሰው መሆኑን ለመግለጽና ለአርአያነት ጠላቶቹ መጥተው እስኪይዙት ድረስ በጌቴ ሴማኒ ሲጸልይ በማደሩ ምክንያት ነው፡፡ ማቴ 26፤36፣ ዮሐ. 17፤1
4) #የምስጢር_ቀንም_ይባላል፡፡
❤ ከአምስቱ አዕማደ ምሥጢር አንዱ በዚህ ዕለት ተመሥርቷል፡፡ ይኸውም ይህ ስለ እናንተ በመስቀል ላይ የሚቆረሰው ሥጋዬ ነው፤ እንካችሁ ብሉ፡፡ ጽዋውንም አንሥቶ አመሰገነ ይህ ስለ እናንተ ነገ በመስቀል የሚፈስ ደሜ ነው፤ ከእርሱም ጠጡ፡፡በማለት እኛ ከእርሱ ጋር አንድ የምንሆንበትን መንገድ ከጠላት ዲያብሎስ ሰውሮ ለደቀ መዛሙርቱ የገለጠበት ቀን በመሆኑ የተሰጠ ስያሜ ነው፡፡ በዚህ ዕለት ቅዳሴ ይቀደሳል፡፡ የሚቀደሰውም በለሆሳስ ሲሆን እንደ ቃጭል በመሆን የሚያገለግለውም ጽናጽል ነው፡፡ ይህም አይሁድ ጌታችንን ለመያዝ ሲመጡ ድምፃቸውን ዝግ አድርገው በለሆሳስ እየተነጋገሩ መምጣታቸውን ለማሰብ ነው፡፡
አንድም፦ በዘመነ ብሉይ ጸሎት ዋጋው ምድራዊ እንደነበር ለማጠየቅ ነው፡፡
በቅዳሴውም ኑዛዜ አይደረግም፡፡ ሥርዓተ ቁርባን ግን ይፈጸምበታል፡፡ ይህም ጌታችን የሰጠውን ዘለዓለማዊ ቃል ኪዳን ለማሰብ ነው፡፡ በዚህ ዕለት ክርስቲያን የሆነ ሁሉ በንስሐ ታጥቦ ተዘጋጅቶ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን መቀበል ይኖርበታል፡፡
5) #የሐዲስ_ኪዳን_ሐሙስ_ይባላል፡፡
❤ ምክንያቱም መሥዋዕተ ኦሪት ማለትም በእንስሳ ደም የሚቀርበው መሥዋዕት ማብቃቱን ገልጦ፣ ለድኅነተ ዓለም ራሱን የተወደደ መሥዋዕት አድርጎ ያቀረበበት ዕለት በመሆኑ ነው፡፡ ሉቃ 22፤18-20 ይህ ጽዋ ስለ እናንተ በሚፈሰው ደሜ የሚሆን የአዲስ ኪዳን ነው፡፡ ከእርሱም ጠጡ በማለቱ ይታወቃል፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአዳምና ለልጆቹ ሁሉ ዘለዓማዊ ቃል ኪዳን በራሱ ደም የፈጸመበት ዕለት መሆኑን በማሰብ የቃል ኪዳኑ ፈጻሚዎች ጠባቂዎች መሆን እንደሚገባን እንማራለን፡፡
6) #የነጻነት_ሐሙስ_ይባላል፡፡
❤ ለኃጢአትና ለዲያብሎስ ባሪያ ሆኖ መኖር ማብቃቱ የሰው ልጅ ያጣውን ክብር መልሶ ማግኘቱ የተረጋገጠበት ቀን ስለሆነ ነው፡፡ ራሱም ጌታችን መድኃታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ሰው ልጅ ነጻነት ሲናገር ከእንግዲህ ወዲህ ባሮች አይደላችሁም፤ ባሪያ ጌታው የሚደርገውን አያውቅምና፤ ወዳጆቼ ግን ብያችኋለሁ በማለቱ ዮሐ.15፤15 ከባርነት ነጻ የወጣንበት ቀን መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ያስረዳል፡፡ ስለዚህ እያንዳንዱ ክርስቲያን ከኃጢአት ባርነት በመራቅ ከእግዚአብሔር ጋር የሚያወዳጀውን መልካም ሥራ በመሥራት ሕይወቱን በቅድስና መምራት ይኖርበታል፡፡ እርሱ ጠላቶቹ ስንሆን ወዳጆቹ አድርጎናል፡፡ ማቴ 26፤17-19።
7) #አረንጓዴው_ሐሙስ_ይባላል፡፡
❤ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአትክልት ቦታ ስለ ጸለየ፡፡
8) #ፋሲካ_በአልዓዛር_ቤት_ይባላል፦
❤ ጌታችን የአይሁድን የፋሲካ በዓል ያከበረበት ታላላቅ ምሥጢራትን የፈጸመበት በአልዓዛር ቤት በመሆኑ ነው፡፡
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_ሕጽበተ_እግር_ምስባክ፦ "ትነዝኀኒ በአዛብ ወእነጽሕ። ተሐፅበኒ ወእምበረድ እጸዓዱ(ወእጻዓዱ)። ታሰምዓኒ ትፍሥሕተ ወኃሤተ። "። መዝ50፥7-8። የሚነበበው ወንጌል13፥1-20።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ወሠራዕከ ማእደ በቅድሜየ። በአንፃሪሆሙ ለእለ ይሣቅዩኒ። ወአጽሐድከ በቅብዕ ርእስየ"። መዝ 22፥5 ወይም መዝ 40፥9። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 11፥23-34፣ 1ኛ ጴጥ 2፥11-25፣ የሐዋ ሥራ 10፥34-43። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 26፥20-31። የሚቀደሰው ቅዳሴ ኤጲፋንዮስ ነው። መልካም የጸሎተ ሐሙስ በዓልና የሰሞነ ሕማማት ጊዜ ለሁላችን ይሁንልን።
❤ እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ፃዕማ ወድካም አመ ከመዮም ያብጽኀነ ያብጽዕክሙ እግዚአብሔር በፍስሃ ወበሰላም።
❤ መልካም የሰሞነ ሕማማት የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ❤
❤ "#የተባረከ_የሚያዝያ_ወር_ቀኑ_ዐሥራ_ሦስት ሰዓት ሲሆን ከዚያም ይጨምራል" ።
❤ #ሚያዝያ ፩ (1) ቀን።
❤ እንኳን #ለካህኑ_ለቅዱስ_አሮን (ለሊቀ ነቢያት #ለቅዱስ_ሙሴ_ወንድሙ) ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓል፣ ለከበረ አባት የሲዖል ሥቃይ አይቶ "ወደዘላለም ጨለማ ሊወስዱኝ ዛሬ የዚህን የኃላፊውን ዓለም ብርሃን ማየት አልሻም" እያለ ፊቱን በቆብ ሽፍኖ ዕድሜው ሙሉ ሲያለቅስ ለነበረ #ለአባ_ስልዋኖስ ለዕረፍት በዓልና #ለቅድስት_መጥሮንያ_ለዕረፍቱ_በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከቅዱስ_አበከረዙንም ጋር በሰማዕትነት ከዐረፉ #ከቅዱስ_ዮስጦስና_ከሚስቱ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ በዚች ቀን በእስክንድርያ ከተማ በሚገኝ በግብጻውያን መጽሐፍ እንደ ተጻፈ በላዕላይ ግብጽ ያለ ግብጻዊውም እንደተጻፈ ለእንበረም ልጅ #ለቅዱስ_ሙሴ_ወንድሙ_ለሆነ_የካህኑ_ቅዱስ_አሮን የዕረፍቱ መታሰቢያ ሆነ ይላሉ።
❤ በኦሪቱ መጽሐፍ የተጻፈው ግን እስራኤል ከግብጽ ከወጡ በሁለተኛው ወር በሦስተኛው ቀን ዐረፈ ይላል። ይኸውም ግንቦት ስምንት ነበር የእስራኤል ወሮች በጨረቃ እየተቈጠሩ ዓመቱን ስለሚዞሩ በዚያች ዓመት ሚያዝያ አንድ ቀን ሁኖ ስለተገኘ።
❤ በእኛ(በኢ.ኦ.ተ) ዘንድ ግን የኦሪት ዘኊልቊ መጽሐፍ በአምስተኛው ወር መባቻ ስለሚል መታሰቢያውን ነሐሴ አንድ ቀን እናደርጋለን።
+ + +
❤ ካህኑ ቅዱስ አሮን፦ ይህም ሰው የነቢያት አለቃ ለኦሪት ሕግ መምህር ለሆነ ለሙሴ ለነቢዪት ማርያምም ወንድም ነው እርሱም ከሌዊ ነገድ ነው።
❤ እግዚአብሔርም በግብጽ ምድር ብዙ አስደናቂ ተአምራትን በእጆቹ አደረገ። እግዚአብሔርም እርሱንና ልጆቹን መርጦ ካህናቶቹ አድርጎ ከእስራኤል ልጆች ከገንዘባቸውና ከመሥዋዕታቸውም ዓሥራትን ሰጣቸው። የቆሬም ልጆች በጠላትነት በተነሡበት ጊዜ እግዚአብሔር ፈርዶ አጠፋቸው ምድርንም አዘዛት አፍዋንም ከፍታ ዋጠቻቸው።
❤ በበጎ ተጋድሎውና የኦሪትንም ሕግ በመጠበቅ እግዚአብሔርን ከአገለገለ በኋላ የክብር ባለቤት ወደሆነ እግዚአብሔር ሔደ። የካህኑ የቅዱስ አሮን ጸሎቱ በረከቱ ከእኛ ጋር ለዘላለም ትኑር አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ስልዋኖስ፦ ይህም አባት በአስቄጥስ ገዳም ከከበረ አባ መቃርስ ዘንድ በታናሽነቱ መነኰሰ በጠባብ መንገድ ሁሉ ተጋደለ በብዙ ጾምና ጸሎት በመትጋት በትሕትና በፍቅር ተወስኖ ኖረ ታላቅ አባትም ሆነ።
❤ የክብር ባለቤት ጌታችንም አምላካዊ ራእይን ይገልጽልት ነበር ድንቅ የሆኑ ነገሮችንም ይነግረዋል። ይህም እንዲህ ነው በአንዲት ዕለት ልቡ ተመስጦ በምድር ላይ በግምባሩ ተደፍቶ ብዙ ጊዜ ቆየ በዚያም በኋላ ነቅቶ ራሱን ቀና አደረገ። ከእርሱ ዘንድ ያሉ ወንድሞች መነኰሳትም በእርሱ ላይ የደረሰበትን ይነግራቸው ዘንድ ለመኑት ዝም ብሎ መሪር ልቅሶ ያለቅሳል እንጂ ሊነግራቸው አልወደደም። ከእርሱ የሆነውን ያስረዳቸው ዘንድ ግድ ባሉት ጊዜ እንዲህ አላቸው "ተድላ ወዳለበት ገነት አውጥተውኝ በዚያ የጻድቃንን መኖሪያ አየሁ ደግሞ የሥቃይ ቦታዎችንም። ሁለተኛም ብዙዎች መነኰሳትን ወደ ገሀነም ብዙዎች ምዕመናን ወደ መንግሥተ ሰማያት ሲወስዷቸው አየሁ እንግዲህ እኔ ለነፍሴ የማላለቅስ ለምድንድነው" አላቸው። ከዚያች ቀንም ጀምሮ "በኋላ ወደዘላለም ጨለማ ሊወስዱኝ ዛሬ የዚህን የኃላፊውን ዓለም ብርሃን ማየት አልሻም" እያለ ፊቱን በቆብ ሽፍኖ የሚያለቅስ ሆነ።
❤ ይህም አባት በመንፈሳዊ ሥራ የተጠመደ ሆነ ደቀ መዛሙርቱንም ለምግባቸው የሚሆን ሥራን ከመሥራት እንዳያቋርጡ ከዕለት ምግባቸው የሚተርፈውንም እንዲመጸውቱ ያዛቸዋል።
❤ በአንዲት ቀንም አንድ ታካች የሆነ መነኰስ ወደርሱ መጣ ሽማግሌውን አባትና ደቀ መዛሙርቱን ሲሠሩ አይቷቸው "ለኃላፊ ምግብ ትሠራላችሁ ትደክማላችሁ የዘላለም ሕይወት ለሚሆን ምግብ ሥሩ ድከሙ እንጂ ይህ በከበረ ወንጌል የተጻፈ አይደለምን "ማርያምም የማይቀሟትን በጎ ዕድል ትምህርትን አንደመረጠች" ብሎ ጠቀሰ። ሽማግሎው አባ ስልዋኖስም እንዲህ ሲናገር በሰማው ጊዜ ደቀ መዝሙሩን እንዲህ ሲል አዘዘው "ይህን መነኰስ ከእንግዳ ማሳረፊያ ቤት አስገብተህ የሚያነበው መጽሐፍ ስጠው በሩንም በላዩ ዝጋ በእርሱ ዘንድም ለመብል የሚሆን ምንም ምን አትተው "። ረድኡም ሽማግሌው መምህሩ እንዳዘዘው አደረገ። ዘጠኝ ሰዓትም ሲሆን መነኰሳቱ ተሰበሰቡ ከሽማግሌው አባትም ጋር ጸሎት አድርገው ምግባቸውን ተመገቡ። ያን እንግዳ መነኰስ ግን አልጠሩትም እርሱም ቢጠሩኝ ብሎ ወደ ደጃፍ እየተመለከተ ይጠብቅ ነበር። በረኃብም በተቃጠለ ጊዜ ከበዓቱ ወጥቶ ወደ አባ ስልዋኖስ ሒዶ "አባቴ ሆይ መነኰሳቱ ራታቸውን በሉን" አለው ሽግሌውም "አዎን በሉ" ብሎ መለሰለት። ሁለተኛ ደግሞ "እኔ እንግዳ ስሆን ለምን አልጠራችሁኝም" አለ የከበረ አባት ስልዋኖስም "አንተማ ሥጋዊ መብል የማትሻ መንፈሳዊ ሰው ነህ በጎ ዕድልን ስለመረጥክ እኛ ግን ሥጋዊያን ሰዎች ለሥጋዊ መብል የምንሠራ የምንደክም ነን ስለዚህም ለምግባች የሚሆነውን በእጃችን እንሠራለን" ብሎ መለሰለት። ያ መነኰስም በንግግሩ እንደበደለ አወቀ። አባ ስልዋኖስንም "አባቴ ሆይ እኔ በድያለሁና ይቅር በለኝ" ብሎ ሰገደለት።
❤ አባ ስልዋኖስም " ማርታ በመሥራት እንደ ደከመች እንድከም እንሥራ ከማርያም ይልቅ ማርታ የተዘጋጀች ሁናለችና" ብሎ መለሰለት። ያ ታካች የነበረ መነኰስም በዚህ አባት ትምህርት ተመክሮና ተገሥጾ ሁልጊዜ የሚሠራና ከእርሱ የሚተርፈውንም ለድኆች የሚመጸውት ሆነ።
❤ ይህም አባት ስለ መንፈሳዊ ተጋድሎ ጥቅም ያላቸው ብዙ ድርሳናትንና ተግሣጻትን ደረሰ።
❤ ዕድሜውም በመልካም ሽምግልና በተፈጸመ ጊዜ የሚያርፍባትን ሰዓት እግዚአብሔር ነገሮት በእርሱ አቅራቢያ ያሉ መነኰሳትን ጠርቶ ከእርሳቸው በረከትን ተቀበለ። በጸሎታቸውም እንዲያስቡት ለመናቸው እርሱም በእግዚአብሔር ዘንድ እንዲያስባቸው ለመኑት እርስበርሳቸውም ተሰነባበተው በፍቅር በሰላም ሚያዝያ1 ዐረፈ። የአባ ስልዋኖስ ጸሎቱ በረከቱ ከእኛ ጋር ለዘላለሙ ትኑር አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ በዚች ቀን ደግሞ በላይኛው ግብጽ ያሉ ዐረቦች ተሰብሰበው በአስቄጥስ ያሉ አድባራትናንና ገዳማትን የአባ መቃርስንም ቤተ ክርስቲያን ከበቡ በአድባራቱና በገዳማቱ ያለውንም ዕቃ ሁሉ ማረኩ። መነኰሳትም ተሰበሰቡ በከበረ አባቶችም ስም ወደ እግዚአብሔር በጸሎት ማለዱ።
❤ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እነዚያን ዓረቦች አስደግጦ አሳደዳቸው ያንጊዜም ማንም የተከተላቸው ሳይኖር ድል ሁነው ሸሹ። ከክብር ባለቤት ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል በቀር ማንም የተከተላቸው ሳይኖር ነው። ይቅር ብሏቸዋልና ጌታችንን አመሰገኑት ለእርሱም ክብር ምስጋና ገንዘቡ ይሁን ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሚያዝያ1 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለስልዋኖስ_ቢጸ_መላእክት_ዘኮነ። ፍትወተ ዓለም እምልቡ እስመ ተመነነ። እምአመ ርዕየ ጽልመተ ኃጥአን ደይነ። በቆብዐ ርእሱ ገጾ ከደነ። ህየንተ በዘምድር ይርአይ በሰማይ ብርሃን"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሚያዝያ_1
❤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ❤
❤ እንኳን #ለሰሞነ_ሕማማት_ሦስተኛ_ቀን_ለምክር፣ #ለመልካም_መዓዛ_ላለውና_ለዕንባ ቀን እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
❤ #ዕለተ_ረቡዕ።
❤ ይህ ዕለት የምክር ቀን ይባላል፡፡ ምክንያቱም የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሓፍት ጌታን እንዴት መያዝ እንደሚገባቸው ምክር የጀመሩበት ወይም የያዙበት ቀን ስለሆነ ነው፡፡ በዚህ ምክራቸው ላይ በጣም ትልቅ ጭንቀት ነበር፡፡ ምክንያቱም ወቅቱ የፋሲካ በዓላቸውን የሚያከብሩበት በመሆኑ ብዙውን ሕዝብም በጌታችን ትምህርት የተማረኩ፣ ተአምራቱን የሚያደንቁ ስለነበር ሁከት እንዳይፈጥር ነው፡፡ በዚህ ጭንቀት ሳሉ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ የአስቆሮቱ ይሁዳ በመካከላቸው በመገኘት የምክራቸው ተባባሪ ሆኖ ጭንቀታቸውን አስወግዶላቸዋል፡፡ ማቴ. 26፤1-5፣ ማር. 14፤1-2 የሐዲስ ኪዳን ካህናት ምእመናን በዚህ ዕለት በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ተሰብስበው ከእህልና ውኃ ተለይተው፣ መላ ሰውነታቸውን ለእግዚአብሔር አስገዝተው፣ የሞት ፍርዱን በማሰብና በማልቀስ፣ ስለዚህ ታሪክ የሚያወሳውንም በማንበብ እስከ ኮከብ መውጫ በጾም፣ በጸሎትና በስግደት ተወስነው ይቆዩና ወደ ቤታቸው ይሄዳሉ፡፡ ይሁዳ ማለት ታማኝ ማለት ቢሆንም እንደ ስሙ ግብሩ ሆኖ አልተገኘም፡፡ ስምና ግብሩ አልተባበረለትም፡፡ እኛ እንደ ስማችን ይሆን ግብራችን?
❤ መልካም መዓዛ ያለው ቀንም ይባላል፡፡ ምክንያቱም ጌታችን በዚህ ዕለት በቤተ ስምዖን ዘለምጽ ተቀምጦ ሳለ መላ ሕይወቷን ለዝሙት አስገዝታ ትኖር የነበረችው ማርያም እንተ እፍረት ከእንግዲህ በኃጢአት ተጎድቶ የኖር የነበረውን ሕይወቴን እንደዚሁ መልካም ሽቶ ዋጋው እጅግ በጣም ውድ የሆነ ከሦስት መቶ ዲናር በላይ የሚያወጣ በአልባስጥሮስ ብልቃጥ የሞላ ሽቱ ይዛ በመሄድ በጠጉሩ (በራሱ) ላይ በማርከፍከፍ ስላቀረበች ነው፡፡
❤ የእንባ ቀንም ይባላል፡፡ ይህም ይህችው ሴት በጌታችን እግር ላይ ተደፍታ መላ ኃጢአቷን ይቅር እንዲላት በእንባዋ እግሩን አጥባዋለችና፡፡ ማቴ. 26፤6-13፣ ማር. 14፤3-9፣ ዮሐ. 12፤1 ከዚህም እያንዳንዳችን ልንማር የሚገባን ነገር አለ፡፡ ይኸውም የራሱን ኃጢአት በማሰብ ማልቀስና የተወደደ መሥዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር ማቅረብን ነው፡፡
❤ እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ፃዕማ ወድካም አመ ከመዮም ያብጽኀነ ያብጽዕክሙ እግዚአብሔር በፍስሃ ወበ ሰላም።
❤ መልካም የሰሞነ ሕማማት የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ ከዚህ በኋላ "በልተው ጠጥተው ደስ ባላቸው ጊዜ በፊታችን ይጫወት ዘንድ ሶምሶንን ከግዞት ቤት ጥሩት" አሉ። ጠርተው አምጥተውም ተዘባበቱበት በሁለት ምሰሶዎች መካከልም አቆሙት። ሶምሶንም የሚሚመራውን ብላቴና "አሳርፈኝ ይህ ቤት የቆመባቸው ምሰሶዎችንም አስጨብጠኝ ወደነርሳቸውም አስጠጋኝ" አለው ያም የሚመራው ብላቴና እንዳለው አደረገለት። በዚያ ቤት ወንዶችም ሴቶችም መልተው ነበር የኢሎፍሊ ሹማምንትም ሁሉ በዚያ በሰገነት ነበሩ ሶምሶን ሲጫወት ያዩት ዘንድ የተሰባሰቡ ወንዶችም ሴቶችም ሦስት ሽህ ይሆኑ ነበር።
❤ ሶምሶን ወደ እግዚአብሔር ጮኸ "አቤቱ አስበኝ አንዲት ነገርንም አድምጠኝ እንግዲህ ስለ ሁለት ዐይኖቼ ፈንታ ከኢሎፍላውያን አንዲት በቀልን ልመልስ" አለ። ሶምሶን ያ ቤት በላያቸው የተደገፈባቸው በመካከል ያሉ እነዚያን ሁለት ምሰሶዎች ያዛቸው አንዲቱን በቀኙ አንዲቱንም በግራው ይዞ ገፋቸው። ሶምሶንም ሰውነቴ ከኢሎፍሊ ሰዎች ጋራ ትሙት ብሎ በኃይሉ ነቀነቃቸው ያም ቤት በውስጡ ባሉ በሕዝቡ ላይና በኢሎፍሊ ሹማምንት ላይ ወደቀባቸው የሞቱትም እንዲህ ሆኑ ሶምሶን በሕይወቱ ሳለ ከገደላቸው ሲሞት የገደላቸው በዙ። ያባቱ ወገኖች ሁሉና ወንድሞቹ ወርደው በድኑን አነሡ ወስደውም በአባቱ በማኑሔ መቃብር ቀበሩት። የመስፍኑ የቅዱስ ሶምሶን የፈጣሪው ቸርነት ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት30 ስንክሳር።
❤ እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ፃዕማ ወድካም አመ ከመዮም ያብጽኀነ ያብጽዕክሙ እግዚአብሔር በፍስሃ ወበሰላም አሜን።
❤ መልካም የሰሞነ ሕማማት የጾምና የስግደት ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #መጋቢት ፴ (30) ቀን።
❤ እንኳን #ለከበረ_መልአክ_ለቅዱስ_ገብርኤል መታሰቢያ በዓል፣ ለእስራኤል ልጆች መሳፍንት ለአንዱ #ለቅዱስ_ሶምሶን ለመታሰቢያ በዓልና ለቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድ ለሥጋው ፍልሰት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ በዚች ቀን #ከእግዚአብሔር ዘንድ ስለተሰጠው ስለ ክብሩ ልዕልና #ለከበረ_መልአክ_ለቅዱስ_ገብርኤል የወልደ እግዚአብሔርን ሰው የመሆኑን ዜና ለምትወልደው ለድንግል ማርያም እንዲያበሥራት የተገባው ስለሆነ በዓሉን ልናከብር ይገባል።
❤ ስለዚህ በዚች በከበረች ታላቅ ጸጋ በዚህ መልአክ እጅ እግዚአብሔር ይቅር ብሎናልና ፈጽሞ ልናከብረው ይገባናል።
❤ እርሱም ደግሞ ስለ ክርስቶስ መምጣትና በዓለም ድኅነት መገደሉን ለኢየሩሳሌምም መዳኛዋ መሆኑን ስለ ወገኖቹ ከምርኮ መመለስ ሲጸልይ ለቅዱስ ዳንኤል የነገረው ሱባዔዎችንም የወሰነለትና በሱባዔዎቹም መጨረሻ ንጹሐን የሚነጹበት የክብር ባለቤት ክርስቶስ ይመጣል ይገድሉታልም ለኢየሩሳሌምም መደኛዋ ይሆናታል ያለው ይህ መልአክ ነው።
❤ ከዚያ በኋላም ለእስራኤል ልጆች የሚደረጉ መሥዋዕቶችና ቊርባኖች ይሻራሉ። የክብር ባለቤት ጌታችን ስለ ዓለሙ ሁሉ ድኅነት ለእመቤታችን ማርያም ከእርስዋ መወለዱን ይነግራት ዘንድ የተገባው አድርጎታልና ስለዚህ ሁል ጊዜ የበዓሉን መታሰቢያ ልናደርግ ይገባል።
❤ ጌታ ከጠላታችን ሠይጣን እጅ ያድነን ዘንድ ስለ እኛ እንዲማልድ በበጎ ሥራ ሁሉ እንዲረዳን እንለምነው። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #መስፍኑ_ቅዱስ_ሶምሶን፦ የዚህም ጻድቅ የአባቱ ስም ማኑሔ ይባላል ከነገደ ዳን ነው። እናቱም መካን ነበረች የእግዚአብሔር መልአክ ወደርስዋ መጥቶ ከርስዋ ልጅ መወለዱን ነገራት "የወይን ጠጅ የማር ጠጅ ከመጠጣት ለመሥዋዕት የማይሆን ርኵስ የሆነውን ሁሉ ከመብላት እንድትጠነቀቅ አዘዛት። ያም ሕፃን ከእናቱ ማሕፀን ከተወለደ ጀምሮ ለእግዚአብሔር የተለየ ገንዘቡ ነውና በራሱ ላይ ምላጭ አይድረስበት እርሱም እስራኤልን ከኢሎፍላውያን እጅ ሊያድናቸው ይጀምራል" አላት።
❤ የእግዚአብሔር መልአክም ያላትን ለባሏ በነገረችው ጊዜ ያንን መልአክ ያሳየው ዘንድ እርሱም ወደ እግዚአብሔር ለመነ ልመናውንም ሰማው። የእግዚአብሔርም መልአክ ተገልጦለት "ለሚስትህ ያዘዝኳትን እንድትጠነቀቅ እዘዛት" አለው።
❤ ከዚህም በኋላ ፀንሳ ይህን ጻድቅ ሰው ወለደችው እግዚአብሔርም ባረከው የእግዚአብሔርም መንፈሰ ረድኤት አድሮበት ከኃይል ጋር ተወለደ። ሕፃኑም አድጎ ጐለመሰ በአንዲት ዕለትም አንበሳ ሊበላው በእርሱ ላይ ተነሣ እግዚአብሔርም መንፈስ አደረበትና የፍየል ጠቦትን አንሥተው እንዲጥሉ አንሥቶ ጣለው በእጁም ውስጥ እንደኢምንት ሁኖ ገደለው።
❤ ሁለተኛም ስለ ሚስቱ በተቆጣ ጊዜ ሶምሶን ሒዶ በሩጫ ሦስት መቶ ቀበሮዎችን ያዘ። ችቦ አምጥቶ በጅራታቸው አሠረ በሁለቱም ጅራቶቻቸው መካከል አንድ አንድ ችቦ አደረገ። በዚያች ችቦ እሳትን አቀጣጥሎ ወደ ኢሎፍላውያን አዝመራ ሰደዳቸው። የታጨደውን ክምርና እሸቱን ነዶውንም የዘይቱንና የወይኑንም ቦታዎች አቃጠሉ። ሊጣሉትም በተነሱበት ጊዜ ጭንጭናቸውን ሰበራቸው ብርቱ ሰልፍም ተደርጎ ብዙ ሰዎችን ገደለ ወርዶም በዋሻ ውስጥ ተቀመጠ። ስለዚህም ኢሎፍላውያን ወደ ይሁዳ ዘምቶው የአህያ መንጋጋ በአለበት ሰፈሩ። የይሁዳም ሰዎች ሁሉ "ወደ እኛ ለምን ዘመታችሁ" አሏቸው ኢሎፍላውያንም "ሶምሶንን እናሥረው ዘንድ እንዳደረገብንም እናደርግበት ዘንድ መጣን" አሉ።
❤ ከይሁዳም ሦስት ሺህ ሰዎች በኤጣም ወዳለች ዋሻ ወርደው ሶምሶንን "ኢሎፍላውያን እንዲገዙን አታውቅምን በእኛ ለምን እንዲህ አደረግህ" አሉት። ሶምሶንም "በእናንተ እንዳደረጉባችሁ እኔም በእነርሳቸው እኔም እንደዚያው አደረግሁባቸው" አላቸው። እሥረን "ለኢሎፍላውያን ልንሰጥህ መጣን" አሉት ሶምሶንም "እናንተ እንዳትገድሉኝ ማሉልኝ ለእነሱ አሳልፋችሁ ስጡኝ እናንተ ግን እኔን በጠብ አትገናኙኝ" አላቸው እርሱም ማሉለት። በሁለት አዲስ ገመዶች አሥረው ከዚያች ዋሻ አወጡት አሳልፈውም ሰጡት ኢሎፍላውያንም ደነፉ ሊቀበሉትም ሮጡ የእግዚአብሔር መንፈስ ረድኤት አደረበት በክንዱ ያሉ ገመዶች ገለባ እሳት በበላው ጊዜ እንዲያር እርር ኩምትር አሉ እሥራቱም ከክንዱ ተፈታ። የአህያ መንጋጋ አጥንት በጎዳና ወድቆ አገኘ እጁን ዝቅ አድርጎ አነሣት በዚያችም ሺህ ሰዎችን ገደለባት።
❤ ከዚህም በኋላ ውኃን እጅግ ተጠማ ወደ እግዚአብሔር ጮኸ "ይህን ታላቅ ድኅነት በእኔ በባሪያው እጅ አደረግህ አሁን ግን በውኃ ጥም እሞታለሁ በእነዚህም በቈላፋን እጅ እወድቃለሁ" አለ። እግዚአብሔር ከዚያች የአህያ መንጋጋ ውኃ አፈለቀለት ያንንም ጠጥቶ ነፍሱ ተመለሰችለት።
❤ እስራኤልንም ሃያ ዓመት አስተዳደራቸው። ከዚህም በኋላ ሶምሶን ከዚያ ተነሥቶ ወደ ጋዛ ሔደ በዚያም ሚስት አግብቶ ተቀመጠ። ለጋዛም ሰዎች "ሶምሶን ወደዚህ መጣ" ብለው ነገሯቸው በከተማውም በር መላ ሌሊቱን ሁሉ ከበው ሲጠብቁት አደሩ ሌሊትን ሁሉ ከበው ሲጠብቀው አድረን "ጠዋት እንግደለው" አሉ። ሶምሶን እስከ ሌሊቱ እኩሌታ ተኛ ከዚያም በኋላ ተነሥቶ በከተማው በር ያሉ የመጠበቂያውን በደጃፍ ሁለቱን የመቃን መድረኮች ያዘ ከሰዎቹ ሁሉ ጋራ በትከሻው ተሸክመ በኬብሮን አንጻር ወዳለ ተራራ አውጥቶ በዚያ ጣላቸው።
❤ ከዚህም በኋላ በሦራህ ወንዝ አጠገብ የምትኖር ሴትን ወደደ ስምዋም ደሊላ ነው። እርሷም አግብቶ በዚያ ተቀመጠ። የኢሎፍሊ ሹማምንትም ወደርሱዋ ወጥተው "አታሊልን ኃይሉ በምን እንደ ሆነ በምንም እንድናሥረው ዕወቂ እኛ ሺው ሰዎች ሽህ ብር እንሰጥሻለን" አሏት።
❤ ደሊላም ሶምሶንን "ኃይልህ ጽኑ መሆኑ በምን እንደሆነ ንገረኝ በምንስ ቢያሥሩህ ትደክማለህ" አለችው። ሶምሶንም ሦስት ጊዜ ሸነገላት ደሊላም "እወድሻለሁ ልቤም ከአንቺ ጋራ ነው ለምን ትለኛለህ እንሆ ስትሸነግለኝ ይህ ሦስተኛህ ነው ኃይልህ ጽኑ መሆኑ በምን እንደሆነ አልነገርከኝም" አለችው።
❤ ከዚህ በኋላ መላ ሌሊቱን በነገር ባደከመችው ጊዜ ልሙት ብሎ እስቲበሳጭ ድረስ ዘበዘበችው። በልቡ ያለውን ሁሉ ነገራት "እኔ ለእግዚአብሔር የስለት ልጅ ነኝና ከእናቴ ማኅፀን ከተወለድኩ ጀምሮ ምላጭ ራሴን አልነካኝም ጠጉሬን ከተላጨሁ ኃይሌ ተለይቶኝ እደክማለሁ ከሰውም እንዳንዱ እሆናለሁ" አላት። የልቡን ሁሉ እንደገለጠላት በአወቀች ጊዜ በጭኖቿ መካከል አስተኝታ ሲያንቀላፋ ጠጉር ቆራጭ ጠቀሰችው ሰባት የራሱንብርጉዎች ቆርጣ ጠጉሩን ላጨች እርሱም ይደክም ጀመር ኃይልም ተነሣው።
❤ ኢሎፍላውያንም ይዘው ሁለት ዐይኖቹን አወጧቸው ወደ ጋዛንም አውርደው በእግር ብረት አሠሩት በግዞትም ሁኖ እህልን ይፈጭ ነበር። ከዚህም በኋላ የኢሎፍሊ አለቆች ለጣዖታቸው መሥዋዕት ሊሠዉ ተሰበሰቡ። ሕዝቡም በአዩት ጊዜ ጣዖታቸውን አመሰገኑት "አገራችንን ያጠፋት ሬሳዎቻችንን ያበዛ ጠላታችንን በእጃችን ጣለው" አሉ።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #መጋቢት ፴ (30) ቀን።
❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ ድርሳነ ቅዱስ ሚካኤልንና ድርሳነ ቅዱስ ገብርኤልን ለደረሱት ለታላቁ አባት #ለአባ_ዮሐንስ_አፈቅራዊ_ዘአክሱም ለዕረፍታቸው መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላም በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #አቡነ_ዮሐንስ_አፈቅራዊ_ዘአክሱም፦ የተባሉት ኢትዮጵያዊው ጻድቅ የአክሱም ሊቀ ጳጳስ የነበሩ ሲሆን በድርሰታቸው የታወቁ ስለሆኑ ዳግማዊ ዮሐንስ አፈወርቅ የሚል ስያሜ የተሰጣቸውና ግብፃዊያንም በጣም የሚያከብሯቸው ታላቅ አባት ናቸው፡፡ ድርሳነ ቅዱስ ሚካኤልንና ድርሳነ ቅዱስ ገብርኤልን የደረሱ አባት ናቸው፡፡ ድርሳኑንም ሲጽፉ ቅዱስ ሚካኤል ይመራቸው ነበር፡፡ በደብረ ዳሞ ተቀምጠው ዘጠኙ ቅዱሳን ያመጧቸውን ከ300 በላይ የሚሆኑ ቅዱሳት መጻሕፍትን ሰብስበው እንደገና በልዩ አምስት ዓምድ አድርገው አዘጋጅተው ያስቀመጡ ታላቅ አባት ናቸው፡፡ አባታችን ተደግፈው ይጸልዩባት የነበረችው ዛፍ እርሳቸው ከማረፋቸው በፊት ለመነኮሳቱ "አባታችን ዛሬ ያርፋልና ተጠንቀቁ" ብላ አስቀድማ የተናገረችላቸው ጻድቅ ናቸው፡፡ ገድላቸው በደብረ ዳሞ፣ በደብረ ጽሞና፣ በገዳመ ሞጊና፣ በአክሱም፣ በጣና፣ በደብረ በንኮል ይገኛል፡፡ ከአባታች አቡነ ዮሐንስ አፈቅራዊ ዘአክሱም ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን።
❤ እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ፃዕማ ወድካም አመ ከመዮም ያብጽኀነ ያብጽዕክሙ እግዚአብሔር በፍስሃ ወበሰላም አሜን።
❤ መልካም የሰሞነ ሕማማት የጾምና የስግደት ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።
ሙታን በሚነሱባት ዕለት ዕድላቸው ከአንተ ጋር ይሆናል ባሕሩም ቃልህን ሰምቶ ይታዘዝልሃል" አለችኝ።
❤ ምሕረትንና ርኅራኄን የተመላች እመቤቴ የብርሃን እናት ድንግል ማርያም ይህን ስትናገረኝ እንሆ በእጃቸው የጦር መሣሪያ የያዙ ኃይለኖች ሰዎችን የተመሉ መርከቦችን በቅርብ አየኋቸው እጅግም ፈራሁ እመቤቴ ማርያምም ተሠወረችኝ። ነገር ግን ከደመና ውስጥ "ማጥመቅንም አታቋርጥ" የሚለኝን ቃል እሰማ ነበር። እኔም በታላቅ ቃል "ፈጣሪዬ ሆይ ይህን የባሕር ውኃ ለእሊህ ለተጣሉ በጎች ሰይጣንም ለማረካቸው ጥምቀትን አድርገው ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ በዚህ ባሕር ጥምቀት እሊህን ሰዎች በሦስትነትህ ስሞች የልጅነትን ክብር የሚቀበሉ አድርጋቸው" በማለት አሰምቼ ተናገርኩ። እንዲህም ይህን እያልኩ ከባሕሩ ውኃ ዘግኜ ሰዎች በአሉባቸው መርኮቦች በላያቸው ረጨሁት የሰዎቹም ቁጥራቸው አንድ መቶ ሃምሳ ሺህ ነው።
❤ እኔ ወደአለሁበት የባሕር ዳር በደረሱ ጊዜ ከመርከባቸው ወጥተው ፈለጉኝ እኔም እመቤቴ የብርሃን እናት እንዳዘችኝ በፊታቸው ቆምኩ በረድኤቷ ተማምኛለሁና አልፈራሁም። በአዩኝም ጊዜ ሁሉም በፊቴ ሰገዱ በአንድ ቃልም "ቅዱስ ጳውሎስ ሆይ ፍቅር አንድነት ለአንተ ይሁን ወደአንተ ከመድረሳችን በፊት በመርከቦች ውስጥ እያለን እኛ ያየነውን አየህን?" አሉኝ። እኔም "አዲስ የተወለዳችሁ ልጆች ሆይ ምን አያችሁ?" አልኋቸው "የሰማይ ደጆች ተከፍተው የቀኝ እጅ እንደ እሳት ነበልባል ተዘርግታ አየን ደግሞ የፊቷ ብርሃን ከፀሐይ ሰባት እጅ የሚበራ ሴት አየን። እርሷም ከደመና በታች የምትረጨውን ውኃ ተቀብላ በላያችን ትረጨዋለች ትስመናለች ታቅፈናለችም። በራሶቻችንም ላይ የብርሃን አክሊሎችን ታደርጋለች" አሉኝ። ይህንንም በሰማሁ ጊዜ ፈጽሞ ደስ አለኝ በስሙ በምንሠራው ሥራ ሁሉ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር እንዳለ ተረዳሁ።
❤ ከዚህም በኋላ ሌሎች መርከቦች መጡ ኃይለኞች ሰዎችን ከጦር መሣሪያ ጋር የተመሉ ናቸው እንዲህም እያሉ ዛቱብኝ "አንተ ሥራየኛ ጥበበኞች ሕርምስና በለንዮስ ታምራት የሚያደርጉባቸው የጠልሰም መጻሕፍቶች ከእኛ ጋራ እንዳሉ ዕወቅ" በማለት እኔም "ቸር ፈጣሪዬ ሆይ የቀደሙትን በጎች ይቅር እንዳልካቸውና በውስጣቸው ኃይልህን እንደገለጥክ ለእነዚህም እንዲሁ ኃይልህን ግለጥ ይቅር በላቸው" አልኩ። ከዚያም በኋላ ከባሕሩ ውኃ ዘግኜ በላያቸው ረጨሁ "ይህ ውኃ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥምቀትን ይሁናችሁ" አልኩ ወዲያውኑ መርኮቦች ከባሕሩ ዳር ደረሱ። ሁሉም ሰዎች ከመርከብ ወጥተው በፊቴ ሰገዱ "የቸር አምላክ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ሆይ እናመሰግንሃለን" አሉኝ። ይህንንም ድንቅ ተአምር ከቀደሙት ባልንጀሮቻቸው ጋራ ተነጋገሩ ዜናዬም በዚያች አገር ንጉሥ ዘንድ ተሰማ እርሱም ከሠራዊቱ ጋራ ተነሣ በመርከቦችም ተጭነው ወደእኔ መጡ። እኔም ዓይኖቼን ወደ ሰማይ አቅንቼ የፈጣሪዬን ስም ጠራሁ ባሕርዋንም በመስቀል ምልክት አማተቡኩባት። እንዲህም አልኳት "አንቺ ባሕር በእግዚአብሔር ልጅ በጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ትከፈዪ ዘንድ አዝሻለሁ ምድሩም ይገለጥ መርከቦችም በየብስ ውስጥ ይቁሙ"። ነገሬም ሳልጨርስ ባሕርዋ ተከፈለች በውስጥዋም ዐሥራ ሦስት ጎዳናዎች ተገለጡ መርከቦችም ውኃ በሌለው ምድር ላይ ቆሙ ይህንንም አይተው ሰይፎቻቸውን መዘዙ ዕንጨቶችም ሁነው አገኟቸው እኔም ከባሕሩ ውኃ ዘግኜ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ እያልኩ በላያቸው ረጨው። በዚያን ጊዜ እሊያ መርከቦች ነፋስ ተሸክሟቸው ያለ ውኃ ከምድር ከፍ ከፍ ብለው ተጓዙ ሰዎችም ከውስጣቸው ወጥተው ወደእኔ መጥተው ሰገዱ። ከእርሳቸው የቀደሙ ሰዎች ሰላምታ እንዳቀረቡልኝ ንጉሡም ከአገር ሰዎች ሁሉ ጋር በፊቴ ሰገደ።
❤ ከዚያም በኋላ ከእርሳቸው ጋር ወሰዱኝ ወደ ከተማውም በደረቅ ያለ መርከብ ገባን በምኵራባቸውም ተከልለው የሥንዴ እሸትም እንደ መሥዋዕት ሁኖ ተጥሎ አየሁ ይህንንም አይቼ እጅግ አዘንኩ። የአገር ሰዎችም "ክቡር መምህር ሆይ በዚች ዕለት ለአማልክት በዓል የምናደርግባት እንደ ነበረ ዕወቅ አሁን አንተ ለማን ታዘናለህ ለአብ እናድርገውን ወይም በወልድ ስም ወይም በመንፈስ ቅዱስ ስም በስማቸው ያጠመቅከን ስለሆነ" አሉኝ።
❤ እኔም "እግዚአብሔርን ያመልኩት ዘንድ የሚገባቸውን ሃይማኖትን አስተማርኳቸው መጻሕፍትንም በእጄ ጻፍኩላቸው። በአማላጅነቷ ከርኵስ ሰይጣን ተገዥነት ስለዳኑ ያንን በዓል የብርሃን እናት በሆች በእመቤታችን በድንግል ማርያም ስም እንዲያደርጉት አዘዝኋቸው ዕለቱም የእግዚአብሔርን ልጅ እንደምትፀንሰውና በሥጋ እንደምትወልደው የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ያበሠረበት ስለሆነ።
❤ እኔም አምላካዊ ትምህርት አስተማርኳቸው በቀናች ሃይማኖትም እንዲጸኑ አደረግኋቸው ውኃው በተከፈለበትም ላይ በእመቤታችን ድንግል ማርያም ስም ታላቅ ቤተ ክርስቲያን እንዲሠሩ አዘዝኳቸው። በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ድንቆች የሆኑ ብዙ ተአምራቶችንም አደረኩላቸው። ከዚያ በኋላ ከእርሱ ዘንድ ወጥቼ መጣሁ"። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን የአባታችን የሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስ በረከቱም በላያችን ይደር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት29 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለፅንሰትከ_በከርሠ_ማርያም_ፅሌ። መጽሐፈ ሐሤት ክርስቶስ ዘኢኮንከ መጽሐፈ ወይሌ። ሶበ ርእዩከ በታሕቱ እንዘ ኢተዓርቀ እምሉዔሌ። አእኰቱከ ቃለ አኰቴት በሃሌ። ሰላም በምድር ወበሰማይ ሃሌ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የመጋቢት_27።
❤ እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ፃዕማ ወድካም አመ ከመዮም ያብጽኀነ ያብጽዕክሙ እግዚአብሔር በፍስሃ ወበ ሰላም አሜን።
❤ መልካም የሰሞነ ሕማማት የጾምና የስግደት ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።
ተአምኆ ቅዱሳን ወግጻዌ (የቅዱሳን ሰላምታ) Teamho Kidusan Wegtsawe (Yekidusa Selamta) Saints Of The Orthodox Tewahedo Church.:
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #መጋቢት ፳፱ (29) ቀን።
❤ እንኳን #ለክብር_ባለቤት_ለጌታችን_ለአምላካችን #ለመድኃኒታችን_ለኢየሱስ_ክርስቶስ ለበኵረ በዓላት ለሆነ #ለጽንሰት በዓልና፣ #ለጥንት_ትንሣኤ_በዓል፣ ዓለም ለተፈጠረበት ቀንና #ለሐዋርያው_ቅዱስ_ጳውሎስ እልዋሪቆን በምትባል አገር ገብቶ #በእመቤታችን_በቅድስት_ድንግል_ማርያም ረዳትነት (አማላጅነት) ላስተማረበትና ብዙ ሺህ ሰዎች በጌታችን ስም ላጠመቀበት በሰላም አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ በዚች ቀን #ለእመቤታችን_ለቅድስት_ድንግል_ማርያም_የከበረ_መልአክ_ቅዱስ_ገብርኤል_የምሥራች የነገረበት ድኅነትን የተመላች ታላቅ በዓል ናት።
❤ በዚህም የከበረ ወንጌል ምስክር ሁኗል እንዲህ ሲል፦ "ቅድስት ኤልሳቤጥ ከፀነሰች በኋላ በስድስተኛው ወር ቅዱስ ገብርኤል የገሊላ ክፍል የሆነች ናዝሬት ወደምትባል አገር ከዳዊት ወገን ለሆነ ዮሴፍ ለሚባል ሰው ወደታጨች ወደ አንዲት ድንግል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተላከ። የድንግሊቱም ስም ማርያም ነው። መልአኩም ወደርሷ ገብቶ "ደስተኛ የሆንሽ ደስ ይበልሽ ጸጋን የተመላሽ ሆይ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋራ ነው አንቺ ከሴቶች ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ" አላት።
❤ እርስዋም አይታ ከንግግሩ የተነሣ ደንግጣ "እንዲህ ያለ ሰላምታ ይቀበሏል" ብላ አሰበች። መልአኩም እንዲህ አላት "ማርያም ሆይ በእግዚአብሔር ዘንድ ባለሟልነትን አግኝተሻልና አትፍሪ። እንሆ ትፀንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ ስሙንም ኢየሱስ ትዪዋለሽ እርሱ ታላቅ ነው የልዑል እግዚአብሔር ልጅም ይባላል። እግዚአብሔር አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል ለያዕቆብ ወገንም ለዘላለም ነግሦ ይኖራል ለመግሥቱም ፍጻሜ የለውም" አላት።ማርያምም መልአኩን "ወንድ ሳላውቅ ይህ እንደምን ይሆናል" አለችው። መልአኩም መልሶ እንዲህ አላት "መንፈስ ቅዱስ መጥቶ ያድርብሻል የልዑል ኃይልም ያጸናሻል ከአንቺ የሚወለደው ከሦስቱ አካል አንዱ የልዑል እግዚአብሔር ልጅ ይባላል። እንሆም ዘመድሽ ኤልሳቤጥም እርስዋ ደግሞ በእርጅናዋ ፀንሳለች ወንድ ልጅም አገኘች ለእርስዋም መካን ትባል ለነበረችው ይህ ስድስተኛ ወር ነው ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና። ማርምም "እንሆኝ የእግዚአብሔር አገልጋይ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ" አለችው።
❤ ያን ጊዜም ድንግል ስትሆን ረቂቅ ፅንስን ተቀበለች የእግዚአብሔር አካላዊ ቃል ወልድ ዋህድ ለኩነተ ሥጋ ወርዶአልና ይህም አንድ ባሕርይ አንድ ህልውና ሲሆን ከሦስቱ አካል አንዱ ነው ከዓለም መፈጠር አስቀድሞ የነበረ በማይመረመር ድንቅ በሆነ ተዋሕዶ እንዴትም እንደሆነ በማይታወቅ በቅድስት ድንግል ማርያም ማሕፀን አደረ ፅንስ ሁኖ ኖረ። በዚያን ጊዜም የኋላ ኋላ መለየት ከቶ የሌለው ፍጹም ሰውነት ነሥቶ ተዋሐደ መለኮቱ ከትስብእቱ ጋራ ያለ መለያየት አንድ ሁኖአልና።
❤ ይቺም ዕለት የበዓላት ሁሉ በኵር ናት በእርሷም የዓለም ድኅነት ተጀምሮዋልና። ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቸር አባቱና ይቅር ባይ ከሆነ መንፈስ ቅዱስ ጋር ክብር ምስጋና ለዘላለሙ ይሁን አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ በዚችም ዕለት ደግሞ #በመድኃኒታችን_በከበረች_ልዩ_በሆነች_ትንሣኤው የዓለም ድኅነት ሆነ በረቀቀ ጥበቡ ሠላሳ ሦስት ዓመት ያህል በምድር ላይ ሥራውን ሠርቶ በፈጸመ ጊዜ በፈቃዱ ሕማማተ መስቀል ተቀብሎ ሙቶ ከተቀበረ በኋላ በሦስተኛው በዚች ቀን በሃያ ዘጠኝ ከሙታን ተለይቶ ተነሥቷልና።
❤ በዚች ቀን አስቀድሞ ደጅ ለሚጠኑት በዓለም ላሉ ሰዎች ሰው በመሆኑ ድኅነታቸውን አበሠራቸው እንዲሁም ደግሞ በዚች ዕለት ከሲኦል በመዳን ሙታንና ሕያውን ደስ አላቸው በዚች በጌታችንና በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ መነሣት መነሣታቸውን አረጋገጡ የከበረ ቅዱስ ጳውሎስ በመነሣቱ ክርስቶስ የሙታን በኵር ሆነ እንዳለ እርሱ ለሙታን በኵራቸው ነውና። ለእርሱም ክብር ምስጋና ለዘላለሙ ይሁን አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #የከበረ_ሐዋርያ_ቅዱስ_ጳውሎስ፦ እልዋሪቆን ከምትባል አገር ደርሶ አስተማረ ይቺም ምድር ዳርቻ ናት። ራሱ ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ አለ "ከዚያም በእግዚአብሔር መልአክ ትዕዛዝ ወደዚያች አገር ሔድኩ አገሪቱም እንደ ሮሜ አምሳል ታላቅ የሆነች እጅግ ውብ ናት ፍሬዋም የበዛ ነው። በውስጡ የሚታለፍበት ስሙ ገርጋ የሚባል ባሕር ግን አግድመቱ ሦስት መቶ ምዕራፍ ነው።
❤ መጋቢት ሃያ ሰባት ቀንም በመጀመሪያ ከዚያ ከባሕሩ ዳርቻ ደረስኩ ለአገሩም ሰዎች በዓላቸው ነበር የጽጌ ረዳ አክሊልም እየታቱ በጣዖቶቻቸው ራስ ላይ ያኖራሉ ከስንዴአቸውም አዲስ እሸትን ለጣዖቶቻቸው ያቀርባሉ። የአገር ጠባቂ የሚሉትም በጠልሰም የተቀረጸ ሥዕል በአገሩ ቅጽር ላይ ተደርጓል ወደዚያች አገር የሚመጣ እንግዳ ሰው ሲያይ በላዩ ያደረ ርኵስ መንፈስ በታላቅ ድምጽ ይጮኻል። የአገር ሰዎችም የዚያን ጠልሰም ጩኸቱን በሚሰሙ ጊዜ ወደ አገራቸው የመጣውን እንግዳ ወጥተው ይገድሉታል ሕጋቸው እንዲሁ ነውና ወደ አገራቸው ይገባ ዘንድ ማንንም አይተዉም አያሰናብቱም።
❤ እኔም ወደዚያች አገር ደርሼ ወደ ባሕሩ በቀረብኩ ጊዜ ያ ጠለሰም እንሆ እንግዳ ወደ እናንተ ደረሰ ብሎ በአገራቸው ቋንቋ ጮኸ። የአገር ሰዎችም ድምፁን ሰምተው ከንጉሣቸው ጋራ ብዙ ሠራዊት መጡ በዚያን ጊዜ ስለ በዓላቸው ተሰብስበው ነበርና ፈለጉኝ እኔ ግን የአሽኮኮዎች መሸሻ ወደ ሆነ ዋሻ ገባሁ። ከዚያም ገብቼ በረሀብና በጥም ስለተሠቃየሁ አለቀስኩ። በዚያን ቀን የፀሐይ ትኩሳት ከመጽናቱ የተነሣ ሐሩር ሆኖ ነበርና በዚያም እስከ ሌሊት ቆይቼ ከዚያ ወጥቼ ከባሕሩ ውኃ ጠጣሁ ቁሜም ወደ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ጸለይኩ።
❤ ንጋትም በሆነ ጊዜ ከዚያ ዋሻ ወጥቼ ወደ አገር ለመግባት ፈለግሁ። ያ ጠለሰም አሁንም መምጣቴን እየገለጠ ሁለተኛ እንደ ታላቅ ነጐድጓድ ጮኸ ለባሕሩም ልማድ አለው ጠለሰሙ በሚጮኸ ጊዜ ይታወካል ማዕበሉም ይነሣል ያን ጊዜም ያገር ሰዎች ሊገድሉኝ መጡ። ከሩቅ በአየኋቸውም ጊዜ ፈራሁ እንደቀድሞውም በዚያ ዋሻ ደግሜ ተሸሸግሁ ጌታ ክርስቶስንም እለምነው ዘንድ ጀመርኩ በአባት በቅዱስ ጴጥሮስ ጸሎት ተማፀንኩ በወንድሞቼ በሐዋርያትም ጸሎት። ይልቁንም ንጽሕት ድንግል በሆነች በብርሃን እናት በእመቤታችን ማርያም በአማላጅነቷ ተማፀንኩ በሌሊቱ ርዝመት ሁሉ ስጸልይ አደርኩ።
❤ በነጋም ጊዜ ወደ ባሕሩ ዳር ወጣሁ ያም ጠልሰም እንደ ልማዱ ጮኸ ተራራዎችም እስቲናወጹ ጨኸቱን አበዛ የባሕሩም ማዕበል ታወከ። ውኃውም እንደ ደም ሆነ የአገሩም ሰዎች ከሠራዊቶቻቸው ጋራ እንደ ቀድሞው ወጡ ባሕሩም መርከቦችን ተመላ እኔም ልሠወር ሮጥኩ። በዚያን ጊዜም የብርሃን እናት እመቤታችን ድንግል ማርያም ቁማ አየኋት "ጳውሎስ ሆይ ወዴት ትሸሻለህ አምላክህ ክርስቶስ እንዲህ እንድትሸሽ አዘዘህን? እርሱ ራሱ ሥጋችሁን የሚገድሉትን አትፍሯቸው ነፍሳችሁን ግን መግደል አይችሉምና ያለ አይደለምን። አንተም በቦታህ ጸንተህ ቁም እኔም ከአንተ ጋራ አለሁ እጄንም ከአንተ አላርቅም በርታ ጠንክርም የዚችን አገር ሰዎች ሁሉንም በዚህ የባሕር ውኃ እንደምታጠምቃቸው ዕወቅ በእጅህም አምነው
