en
Feedback
ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

Open in Telegram

ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።

Show more
637
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-1230 days
Posts Archive
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤           ❤ #ኅዳር ፲፯ (17) ቀን። ❤ እንኳን #ለዓለም_ሁሉ_መምህር ለቊስጥንጥንያው ሊቀ ጳጳስ #ለቅዱስ_ዮሐንስ_አፈ_ወርቅ_ለሥጋው_ለፈለሰበት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከቡሩክ #አብርሃምና_ከሚስቱ_ሐሪክ_ከወጺፍ_ጻድቃን ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                           ✝ ✝ ✝ ❤ #የቅዱስ_ዮሐንስ_አፈ_ወርቅ_የሥጋው_ፍልሰት፦ ይህም እንዲህ ነው መበለቲቱን ቦታዋን በግፍ ነጥቃታለችና እርሱም እንድትመስላት ቢያዛት ስለአልሰማችው ስለ መበለቲቱ ቦታ ቅዱስ ዮሐንስ ንግሥት አውዶክስያን በአወገዛት ጊዜ በእርሱ ላይ ተቆጣች ሰይጣንም በልቧ አደረና ስለ ክፉ ሥራቸውና ስለ በደላቸው አውግዞ የለያቸውን ኤጲስቆጶሳት በእርሱ ላይ ሰበሰበች። እርሱንም ስለ መሰደዱ ከእርሷ ጋር ተስማምተው አድራኮስ ወደምትባል ደሴት አጋዘችው በዚያም ጥቂት ዓመታት ኑሮ ወደ መንበረ ሢመቱ ተመለሰ። ❤ ከዚህም በኋላ ዳግመኛ መናፍቃን የሆነ ኤጲስ ቆጶሳትን ሰበሰበችና ወደ አርማንያ አጋዙት ከዚያም በረሀ ወደሆነ ሩቅ አገር ሰደዱትና በዚያ ዐረፈ። የአርቃዴዎስም ልጅ ታናሹ ቴዎዶስዮስ በነገሠ ጊዜ መልክተኞችን ልኮ የቅዱስ ዮሐንስን ሥጋ ብዙ በመዘመርና በማመስገን በታላቅ ክብር ወደ ቊስጥንጥንያ አፍልሶ አስመጣው ይህም ከዕረፍቱ በኋላበሠላሳ አምስት ዓመት ነው። ❤ በሌላ በቅብጢ መጽሐፍ በግንቦት ወር ሃያ ሁለት ቀን እንደ ደረሰ ይነገራል በሮሜውያን መጽሐፍ ግን በየካቲት ወር ሃያ ሁለት ቀን ተባለ የዕንቊ ፈርጾች ባሉት የዕብነ በረድ ሳጥን ውስጥ አድርገው ወደ ቤተ መቅደስ አስገቡት ከሥጋውም ታላላቅ የሆነ ድንቆች ተአምራት ተገለጡ። ❤ ሁለተኛም የእስክንድርያ ግጻዌና የአገረ ቅብጥ ኤጲስቆጶስ አባ ዮሐንስ የጻፈው ግጻዌ የመለካውያንም ግጻዌ በዚች በኅዳር ዐሥራ ሰባት ቀን ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ እንዳረፈባት ተባበሩ። ሁለተኛም ደግሞ የመለካውያን ግጻዌ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ዐይሉል በሚባል ወር በዐሥራ አራት እንዳረፈ ይናገራል ይህም በመድኃኒታችን በመስቀል በዓል መስከረም ዐሥራ ሰባት ቀን ነው። ስለዚህም ራሱን ለማሰሰቻል ወደ ኅዳር ዐሥራ ሰባት ቀን ለወጡት። ❤ የቀደሙ መጻሕፍት ግን ዕረፍቱን ግንቦት ዐሥራ ሁለት ቀን እንደሆነ ያወሳሉ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ቅዱስ በከበረ አባት በዮሐንስ አወ ወርቅ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦የኅዳር 17 ስንክሳር።                        ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "እስመ መምህረ ሕግ ይሁብ በረከተ። ወየሐውር እምኀይል ውስተ ኃይል። ወያስተርኢ አምላከ አማልክት በጽዮን"። መዝ 83፥6-7። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 10፥1-22።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "እግዚአብሔር ያፈቅሮሙ ለጻድቃን። እግዚአብሔር የዐቅቦሙ ለፈላስያን። ወይትዌከፎሙ ለዕቤራት ወለእጓለ ማውታ"። መዝ 145፥8-9። የሚነበቡት መልዕክታት ፊሊ 1፥12-19፣ 1ኛ ጴጥ 2፥10-18 እና የሐዋ ሥራ 16፥14-25 የሚነበበው ወንጌል ማቴ10፥16- ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅድስት ወለተ ጴጥሮስና የአቡነ ሲኖዳ የዕረፍታቸው በዓልና የነቢያት (የገና) ጾም ጊዜና ለሁላችንም ይሁንልን።             

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ #ኅዳር ፲፯ (17) ቀን። ❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊቷ_ሰማዕት_ወጻድቅ ለሆነችው በጣና ባሕር ላይ ቆማ ስትጸልይ ልብሷ ለገዳሙ ያበራ ለነበረችው ለታላቋ እናት #ለቅድስት_ወለተ_ጴጥሮስ ለዕረፍት በዓልና ለኢትዮጵያዊው ጻድቅ ዐፅማቸውን የተሸከች በቅሎም ለወለደችና ለመካኖች ልዩ ቃል ኪዳን ለተሰጣቸው ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ሲኖዳ ለዕረፍታቸው በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #ሰማዕት_ወጻድቅ_ቅድስት_ወለተ_ጴጥሮስ፦ የትውልድ ሀገሯ ጎንደር ደዋሮና ፈጠጋር ነው፡፡ አባቷ ቅዱስ ባሕር ሰገድ እናቷ ቅድስት ክርስቶስ ዕበያ ይባላሉ፡፡ በሕግ በሥርዓት በሊቀ ጳጳሱ ትእዛዝ የንጉሥ ሱስንዮስን የአማካሪዎች አለቃ የሆነውን መልክአ ክርስቶስን አግብታ ሦስት ልጆችን ወልዳለች፡፡ ባሏም ታላቅና እጅግ ባለጸጋ ነበርና ከልጆቿ ጋር በተድላ በደስታ መኖር እንደ ጀመረች "አቤቱ ፈጣሪዬ ሆይ እነዚህ ሦስት ልጆቼ አንተን የማያስደስቱ ከሆነ በሞት ውሰዳቸው" ብላ ከጸለየች በኋላ እንደፍላጎቷ ሦስቱም ልጆቿ በሞት ተወስደውላታል፡፡ ❤ ባለቤቷም እጅግ እየወደዳት እርሷ ግን"ይህ ዓለም እንደ ጤዛ ያልፋል" ብላ ከሞላ ሀብቷ ከሞቀ ቤቷ ተለይታ ወጥታ በመመነን ጣና ገባች በዚያም በተጋድሎ ስትኖር ባሏ ሄዶ አበምኔቱን "ለምን ገዳም አስገባሃት?" ብሎ ከሰሳቸውና ከገዳሙ አስወጣት፡፡ እርሷ ግን ተደብቃ አክሱም ሄዳ ደብረ በንኰል ገዳም ገባች፡፡ ተመልሳም መጥታ በጣና ባሕር ላይ ቆማ መጸለይ ጀመረች፡፡ ❤ በዘመኗም የነበረው ገዢ ጨካኝና ለጣዖት የሚሰግድ ስለነበር በትልቅ ገደል ወርውረው እንዲጥሏት አደረጋት፡፡ ነገር ግን መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ከእግዚአብሔር ተልኮ መጥቶ በክንፉ ተቀብሏት ወስዶ ብሔረ ብፁዓንን አሳይቶ መልሶ አምጥቶ ዋልድባ አደረሳት፡፡ ❤ ቅድስት እናታችን ወደ ጉምዝ አገርም ተሰዳ ሳለ በነደደ እሳት ውስጥ ቢጨምሯት እሳቱ ምንም ሳያቃጥላት ወጥታለች፡፡ ተመልሳም በጣና ባሕር ላይ ቆማ ስትጸልይ ልብሷ ለገዳሙ ያበራ ነበር፡፡ ባሏም እምነቱን ቀይሮ ከካቶሊኮች ጋር ስለተዛመደ ቅድስት እናታችን ካቶሊኮችንና ባሏን አጥብቃ ስለተቃወመች በገመድ አስረዋት በጎንደር ከተማ ጎዳና ላይ ጎትተው አሠቃይተዋታል፡፡ ❤ ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ ሰባት ገዳማትን ያቀናች ሲሆን ከ700 በላይ በሚሆኑ ወንዶች መነኰሳትና ሴቶች መነኰሳይት ላይ እመ ምኔት ሆና ተሹማ አገልግላለች፡፡ ከመነነችበትም ጊዜ ጀምሮ ምግቧም የመረረ ቅጠል፣ ኮሶና አመድ ነበር፡፡ ❤ ቅድስት እናታችን ታላቁን የሬማ መድኃኔዓለምን ቤተ ክርስቲያን ሠርታ ሙታንን እያስነሣች፣ ድውያንን እየፈወሰች በታላቅ ተጋድሎ እያገለገለች ሳለ ኅዳር 17 ቀን በታላቅ ክብር ዐርፋለች፡፡ ጌታችንም ድንቅ የሆነ ቃልኪዳን ገብቶላታል፡፡ በዕረፍቷም ጊዜ የብርሃን ምሰሶ ከምድር እስከ ሰማይ ተተክሎ ታይቷል፡፡ ❤ የእናታችን የቅድስት ወለተ ጴጥሮስ መላ ዕድሜዋ ሃምሳ ዓመት ነው። ከመመነኗ አስቀድሞ ሃያ አራት ዓመት ከመነነች በኋላ ሃያ ስድስት ዓመት ኖራለች። ከእናታችን ከቅድስት ወለተ ጴጥሮስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎቷም ይማረን!። ምንጭ፦ ገድለ ወለተ ጴጥሮስና መዝገበ ቅዱሳን።                              ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #አቡነ_ሲኖዳ፦ ሲኖዳ ማለት "ታማኝ" ማለት ነው፡፡ ትውልድ አገራቸው ጎጃም ሲሆኑ የሸዋ ባላባት ልጅ ናቸው፡፡ በጎጃም ደብረ ዲማህ አጠገብ ደብረ ፅሞና በተባለው ቦታ ይኖሩ የነበሩ ሰዎች ያመልኩት የነበረውን ትልቅ ዘንዶ አቡነ ሲኖዳ በመስቀል ባርከው ከሁለት ሰንጥቀውታል፡፡ ሰዎቹንም አስተምረው አሳምነው አጥምቀው የእመቤታችንን ቤተ ክርስቲያን ሠርተውላቸዋል፡፡ ጻድቁ የሊቀ ሰማዕታት የቅዱስ ጊዮርጊስ ዓይነት ገድል አላቸው፡፡ ለዘንዶ ምግብ እንዲትሆን ግብር ሆና የተሰጠችውን ሴት ልጅ ከጫካ አግኝተው ዘንዶውን በመስቀላቸው አማትበው ገድለው ልጅቷን አድነዋታል፡፡ ❤ በዘመናቸው ነግሦ የነበረው "ሕዝበ ናኝ" የተባለው ንጉሥ በሰዎች ወሬ "ንግሥናዬ ለሌላ ይሰጣል ትላለህሳ" በማለት ጻድቁን እጅና እግራቸውን አስሮ ካሠቃያቸው በኋላ እጃቸውን አስቆረጣቸው፡፡ ነገር ግን ለአቡነ ሲኖዳ እመ ብርሃን የብርሃን እጅ ተከለችላቸው፡፡ በጌቴሴማኒ ያለችው ሉቃስ የሳላትና ስርጉት የተባለችው የእመቤታችን ሥዕል በየጊዜው እየተገለጠች ታነጋግራቸው ነበር፡፡ ንጉሡ በስደትና በግዞት ብዙ እያሠቃያቸው ሳለ መልአክ መጥቶ ዕለተ ዕረፍታቸውን ነግሯቸው እሳቸውም ደቀ መዛሙርቶቻቸውን ጠርተው ከተሰናበቷቸው በኋላ ነው ንጉሡ በኅዳር 17 ቀን አንገታቸውን ያሰየፋቸው፡፡ ከአንገታቸው ውኃ፣ ደምና ወተት ፈሷል፡፡ ❤ ጻድቁ በሐይቅ ደሴት የተቀበሩ ቢሆንም ቀድሞ በሚያገለግሉበት በድፍን ምስራቅ ጎጃም ድርቅና ርኃብ ስለሆነ በደብረ ፅሞና ገዳም ይኖሩ የነበሩት አባ መቃርስ ዐፅማቸውን አፍልሰው በማምጣት በደብረ ዲማህ አጠገብ በስማቸው በተሰራው በደብረ ፅሞና ቤተ ክርስቲያን በክብር ሲያሳርፉት ወዲያው ዝናብ ጥሎ ድርቁም ጠፍቷል፡፡ ዐፅማቸውን ተሸክማ ያመጣችው በቅሎም ወልዳለች፡፡ ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ ሲኖዳ ለማይወልዱ መካኖች እጅግ ልዩ ቃልኪዳን ነው የተሰጣቸው፡፡ መቃብራቸውን እየዞሩ እምነታቸውን እየተቀቡ ገድላቸውን እየታሹ የማይወልዱ መካኖች የሉም፡፡ ከሩቅም ሆነው በስማቸው ተስለው እምነታቸውን ተቀብተው የሚወልዱ በጣም ብዙዎች ናቸው፣ እንኳንስ ሰው ይቅርና ዐፅማቸውን የተሸከች በቅሎም ወልዳለችና!። ❤ የጻድቁ ሌላኛው በስማቸው የተሰየመውና እጅግ ተአምረኛው ታቦታቸው ዛሬም አቡነ ሲኖዳ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከአ.አ 180 ኪ.ሜ ርቆ ከጣርማ በር አልፎ ሞላሌ ከተማ ውስጥ ይገኛል፡፡ በሰሜን ሸዋ በሚገኘው በዚህ ቤተ ክርስቲያናቸው ውስጥ በዘመናችንም በጣም በርካታ ተአምራት ይደረጋሉ፡፡ ለጻድቁ የተሰጠችውን የስዕለት በግ ጅብ ቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ ገብቶ ሊበላ ሲል ቀንዱን ነክሶ ደርቆ ሞቶ ሲገኝ በጉ ግን ምንም አልሆነም፡፡ አቃቢቷም እንዲሁ ከትልቁ ተራራ ሥር በትልቅ ቅል ውኃ ቀድተው ሲመለሱ ገመዱ ተበጥሶ ቅሉ ከነውኃው ከትልቁ ገደል ገብቶ ድንጋይ ላይ ቢያርፍም ቅሉ ሳይሆን ድንጋዩ ነው የተሰበረው፡፡ የአካባቢው ነዋሪም "በጉ ጅብ ገደለ፣ ቅሉ ድንጋይ ሰበረ" እያሉ ጻድቁን ያወድሷቸዋል፡፡ ከአባታች ከአቡነ ሲኖዳ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸውም ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን ከሚለው መጽሐፍ።               

242513398 Arsema Solomon Abysinya 🔴የመኪና አደጋ ለደረሰባት እህታችን በዚ አካውንት አስገቡልን ነገ ረቡዕ 17/03/18 ማታ 12:00 ባለው ብር ይኬዳል።

❤ አባ ዳንኤልም በሰማ ጊዜ ከእግሩ በታች ሰገደለት አኗኗሩን ሁሉ ይነግረው ዘንድ ክብር ይግባውና በጌታችን ስም አማጸነው ንጉሥ አኖሬዎስ በእጅ ሥራው ደክሞ ከሚያገኘው በቀር ይህም ሰሌን መታታት ነው ሳይበላ፣ ሳይለብስ አርባ ዓመት እንደሆነው የሚተርፈውን ለድኆች እንደሚሰጥ ምግቡም እንጀራና ጨው ቅጠል መጻጻ እንደሆነ የማንንም ገንዘብ ለመቀማት እንዳልደፈረ ድንግልናው እንደጠበቀ ነገረው። አባ ዳንኤል ከእግሩ በታች ወድቆ "በአንተ ላይ ስለተመካው ይቅር በለኝ" አለው። ከዚህ በኋላ አባ ዳንኤል ፈጽሞ እያዘነ ወደ ቦታው ተመለሰ። ❤ ከሁለት ወሮችም በኋላ መምህሩ አውሎጊስን ተሰጋብቶ አኖሬዎስ ከቤተ መንግሥቱ ውስጥ ወጣ እግዚአብሔርም መልአኩን ላከለትና ተሸክሞ ወደ አባ ዳንኤል አደረሰው በተጋድሎ በመጠመድ ኑረው ገድላቸውን ፈጽመው በአንዲት ዕለት ዐረፉ እንዲሁም አውሎጊስና ረዳቱ በዛች ዕለት በአንድነት ዐረፉ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእሊህ ቅዱሳን ፀሎት ይማረ በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #ቅዱስ_ኪስጦስ፦ ይህንንም ቅዱስ ኪስጦስን መኰንኑ በያዘው ጊዜ ጽዕኑ ስቃይ ሳሰቃየው ከዚህም በኋላ ራሱን በሰይፋ ቆረጠ የሰማዕትነት አክሊልን በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ። የቅዱስ ኪስጦስ በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የኅዳር 16 ስንክሳር።                            ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "እግዚኦ በኃይልከ ይትፌሣሕ  ንጉሥ። ወብዙኀ ይትኀሠይ በአድኅኖትከ። ፍትወተ ነፍሱ ወሀብኮ"። መዝ 20፥1-2። የሚነበቡት መልዕክታት የሚነበበው 2ኛ ቆሮ 9፥5-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 5፥2-12 እና የሐዋ ሥራ 14፥23-ፍ.ም። ወንጌል ሉቃ 14፥7-16። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ቄርሎስ ቅዳሴ ነው። መልካም የነቢያት (የገና) የጾም ጊዜና በዓል ለሁላችን ይሁንልን።              

❤ "በስመ አብ ወወልደ  ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ❤            ❤ #ኅዳር ፲፮ (16) ቀን። ❤ እንኳን #በሮሜ_አገር በከሀዲ መኰንን በእስክድሮስ እጅ ሰማዕትነት ለተቀበለች #ለቅድስት_ጣጡስ_ለዕረፍት በዓል፣ ለመነኰስ #አባ_ዳንኤልና #ለንጉሥ_አኖርዮስ_ለዕረፍታቸው በዓል፣ ለእስክድርያ አገር አርባ ስምንተኛ ሊቀ ጳጳስ #ለአባ_ዮሐንስ ለዕረፍት በዓል፣ ለከበረና ለተመሰገነ #ለገዳማዊ_አባ_አቡናፍር ከምስር ከተማ ውጭ ለተሰራች ቤተ ክርስቲያኑ ለከበረችበት፣ #ለቅዱስ ኪስጦስ በመኰንኑ በመክሲሞስ እጅ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡት፦ በሐይቅ ዳር እንዳለ ጽጌ ረዳ መዐዛው ከሚጥም #ከቅዱስ_ፊቅጦር_ከመታሰቢያው፣ #ከንጉሥ_አኖሬዎስ_መምህር_ከአባ_አውሎጊስና #ከንጉሥ_አኖሬዎስ_ረድኡ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                    ✝ ✝ ✝ ❤ #ቅድስት_ጣጡሳ፦ ወደርሱም በቀረቧት ጊዜ እለስክድሮስ "ለአማልክት ሠዊ" አላት እርሷም "ከፈጠረኝ ከጌታዬ ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር አልሠዋም" ብላ መለሰች። መኰንኑም የፊቷን መሸፈን እንዲገልጡ አዘዘ ውበቷንም አይቶ አደነቀ ዐይኖቿ እንደ አጥቢያ ኮከብ ናቸውና ቁመቷም እንደ ዘንበባ ደም ግባቷም እንደ ጽጌ ረዳ ነው በዚያም ወራት የሚመሳሰላትየለም ነበር። ❤ ንጉሡም በአያት ጊዜ እርሷም በመውደዱ ልቡ ተነጠቀ እንዲህም አላት "እሺ በይኝና ለታላቅ አምላክ ለአጵሎን ሠዊ እኔም ለቤተ መንግሥቴ እመቤት አደርግሻለሁ" አላት። ቅድስት ጣጡስም "እኔ ክብር ይግባውና ከክርስቶስ ከመንጋዎቹ ውስጥ ነኝ ከእርሱ በቀር ለሌላ አልሠዋም ነገር ግን ወደ አማልክቶችህ መሠዊያ ቤት ገብቼ ኃይላቸውን እንዳይ ፍቀድልኝ" አለችው። በዚያንም ጊዜ ወሰዷት በገባች ጊዜ ጣዖታቱ ይጠፉ ዘንድ ክብር ይግባውና የኃይል ባለቤት ወደ ሆነ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጸለየች ወዲያውኑ ንውጽውጽታ ሁኖ ጣዖታቱ ከመቀመጫቸው ወድቀው ተሰባበሩ ታላቁ አምላካቸው አጵሎንም ቊልቊል ወድቆ ተቀጠቀጠ ከጣዖቱ አገልጋዮችም ብዙዎች ሞቱ በአጵሎን ላይ አድሮ የሚኖር ርኩስ መንፈስ እዲህ ብሎ ጮኸ "ጣጡስ ሆይ እኔ ካንቺ ምን አለኝ አንቺስ ከእኔ ምን አለሽ እነሆ ማደርያዬን ቀጥቅጠሽ ከእርሱ አውጥተሽኛልና" ንጉሡም ይህ አይቶ ተቆጣ በግንባሯ ደፍተው በበትሮች እንዲደበድቧት በአለጋዎችም ንዲገርፏት አዘዘ ከሥጋዋም በወተት አምሳል ነጭ ደም ፈሰሰ ወደ እግዚአብሔርም በለመነች ጊዜ የሚደበድቧትን የእግዚአብሔር መላእክት የሚያሰቃዪቸው ሆኑ ቅድስት ጣጡስን ግን ሥቃያቸው የማይነካት ሆነ። ❤ ሁለተኛም ለተራበ አንበሳ እንዲሰጧት ንጉሡ አዘዘ አንበሳውም በደረሰ ጊዜ በፊቷ ሰገደ የእሮቿንም ትቢያ ላሰ ከሰማይም "እኔ ከአንቺ ጋራ ነኝና ንጽሕት ጣጡስ ሆይ ደስ ይበልሽ" የሚል ቃል መጣ። ንጉሡም ከክፉ ነገር የደረሰባት እደሌለ አይቶ እራሷን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ ተጋድሎዋንም ፈጸመች በሌሊትም የሮሜ ጳጳስ መጥቶ በከበሩ ልብሶ ገነዛት በወርቅና በብር ከተለበጠ የእብረ በረድ ሳጥን ውስጥ ጨመራትና በአማረ ቦታ አሮራት ከስጋዋም ብዙዎች ተአምራቶች ተገለጡ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቷ ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋራ ይኑር ለዘላለሙ አሜን።                                                         ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_ዳንኤልና_ንጉሥ_ቅዱስ_አኖሬዎስ፦ ይህ አባ ዳንኤል ታላቅ ገድለኛ ነው። እንጀራን፣ ዓሳንም ቢሆን ማርንም ዛይትን ቢሆን ከብቻው ቅጠል በቀር ሳይቀምስ አርባ ዓመት ተኩል በአስቄጥስ ገዳም ኖረ። ❤ ከብዙ ዘመንም በኋላ የመመካት ኀሳብ መጣበት በልቡም "እንደኔ ትርሕምት መቆምን የታገሰ በገዳም በውኑ አለን?" አለ ሰውን የሚወድ እግዚአብሔርም ብርሃናዊ መልአኩን ላከለት መልአኩም "ዳንኤል ሆይ በጎ ያልሆ እንዲህ ያላ ትምክትን ለምን ትመካለህ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከትሕትና በቀር ትምክህትን አይሻምና" አለው። ❤ አባ ዳንኤልም መልአኩን "ጌታዬ ከእኔ የሚሻል ከአለ ንገረኝ ወደርሱ ሆጄ አየው ዘንድ በመመካቴም ወደ ፈጣርዬ እለማመጥ ዘንድ" አለው። መልአኩም "ንጹሕ ቅዱስ እግዚአብሔርን ሚፈራ ሰው የሮሜና የቊስጥንጥንያ ንጉሥ አኖሬዎስ በመንግሥተ ሰማያት ባልጀራህ ነው" አለው። አባ ዳንኤል በሰማ ጊዜ በምድር ላይ ተደፋ በራሱም ላይ አመድ ነስንሶ ክብር ይግባውና በአምላካዊ ጥበቡ ወደ ሮሜ አገር አድርሷ እርሱን አኖሬዎስ ያሳየሆን ዘንድ ጌታችንን ለመነው። ❤ እንዲህ ሲጸልይም ደመና መጣች ተሸከመችውና ከሮሜ ንጉሥ ከአኖሬዎስ ቤተ መንግሥት ደጅ አደረሰችው የንጉሥ አኖሬዎስም ረዳት አገኘው ረድኡም እጅ ነስቶ ከርሱ ቡራኬ ተቀበለና "አባቴ ሆይ ወደዚህ የመጣህበት ጉዳይህ ምንድነው?" አለው። አባ ዳንኤል "ልጄ ሆይ የሚቻልህ ከሆነ ከአገር መኳንንት ወደ አንዱ አድርሰኝና ወደ ንጉሡ እንዲያስገባኝ" አለው። ረዳቱም "እኔ ባስገባህ መግባትን አትሻምን?" አለው። "ልጄ ሆይ እሻለው አስገባኝ እግዚአብሔር ይባርክህ" አለው። ዳግመኛም ረድኡ "አባቴ ሆይ ማች የሆነ ንጉሥን በማየት ምን ታገኛለህ" አለው። አባ ዳንኤል "ፈጣሪ ባያዘኝ ወደዚህ ባልጣው ነበር" አለው። ረዳቱም "ለጌታዬ የሚያሻው እስከምገዛ ጥቂት ታገሰኝ" አለው። ❤ በዚያንም ጊዜ አንባሻ ጨውና መጻጻ የጎመን ቅጠልም ገሽቶ ወደ ጌታው ወደ ንጉሥ ወደ መምህሩ አውሎጊስ ወደሰ አባ ዳንኤልን በውጪ ተወው ንጉሡም ረዳቱን "አንተ አላዋቂ ነህን አባ ዳንኤል በውጪ የሚታቆመው" አለው። ይህንንም ብሎ ንጉሡ ከመምህሩ ከአውሎጊስ ጋር ወጣ ለአባ ዳንኤል ሰገዱለት ሰላምታም ተሰጣጥተው ወደ ቤተ መንግሥት አስገቡትና በአንድነት ተቀመጡ። ዘጠኝ ሰዓትም በሆነ ጊዜ ረዳቱ የሚበሉት አቀረበላቸው በአንድነትም ተነስተው ጸለዩ አባ ዳንኤል እንዳይታመም እጀራ መብላት ፈርቶ "ጌቶቼ እንጀራ ባለብላቴ በእኔ ላይ አታጉረምርሙ እንዳልታመም ፈርቼ ነው እንጂ በትዕቢት አይደለም" አላቸው። ቅጠልንም ሰጡት ማዕዳቸውም በጽመው ጸሎትን ጸለዩ ከዚህ በኋላ ንጉሥ አኖሬዎስ አባ ዳንኤልን ስላመጣጡ መረመረው አባ ዳንኤልም "ወንድሜ ሆይ የሚቻልህስ ከሆ ወደ ንጉሡ አስገባኝ በጌታ ክርስቶስ ትዕዛዝ መጥቻለሁና" አለው። ንጉሡ ነገ አስገባኀለው አለው። ❤ በማግስቱም አኖሬዎስ አይን የሚበዘብዝ ልብሰ መንግሥቱን ለብሶ በዙፋኑ ላይ ተቀመጠ በአባ ዳንኤልንም አስገቡት በአየው ጊዜ ፈርቶ ተንቀጠቀጠ ረዳቱም መፍራቱ አይቶ ወደ ማደርያው መለሰው ንሡም ችሎቱ ሲጨርስ ልብስ ለብሶ አባ ዳንኤል ወደ አለበት ገባ አባ ዳንኤልንም ባየው ጊዜ "ወንድሜ ሆይ በልቤ ያለው ነግሬው ወደ ቦታዬ እመለስ ዘንድ ወደ ንጉሡ ለምን አላስገባኝ" አለው። አኖሬዎስ "አባቴ ሆይ አልገባህም? ለዝች ምድር ንጉሥ ብለው የሰየሙኝ በኀላፊ ዙፋንም ላይ ተቀምጨ ያየኸኝ እኔ አኖሬዎስ ነኝ" አለው።

❤ "በስመ አብ ወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ #ኅዳር ፲፭ 15 ቀን። ❤ እንኳን #ለነቢያት_ለስብከተ ጌና_ጾም እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ "#ጾም_ትፌውስ_ቁስለ_ነፍስ ወታጸምም ኲሎ ፍትወታተ ዘሥጋ ትሜህሮሙ #ለወራዙት_ጽሙና እስመ #ሙሴኒ_ጾመ በደብረ ሲና"። ትርጉም፦ #ጾም_የነፍስን_ቁስል ታድናለች የሥጋ ፍትወትንም ታስወግዳለች #ለጎልማሶችም°ደህንነትን (መታገስን) ታስተምራለች #ሙሴም_በሲና_ተራራ_ጾሟልና፡፡ #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በጾመ_ድጓው_ላይ።                              ✝ ✝ ✝ ❤ በዚችም ቀን #የስብከት_ጌና (የነቢያት) #ጾም_መጀመሪያ_ነው ይህም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለተወለደበት በግብጽ የሚኖሩ ያቆባውያን ክርስቲያኖች የሠሩት ነው። ይቅርታው ቸርነቱ ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ❤ እግዚአብሔር አምላክ ጾሙን ለአገራችን ኢትዮጵያ ሰላም፣ ፍቅር፣ አንድንትና መታሳሰብን የሚያመጣ ያድርግል፣ ከኦርቶዶክስ ተዋሕዶም ሃይማኖት አማኞቿ ምዕመናንና ምዕመናት መከራውን፣ እንግልቱን፣ ስደቱንና ሞቱን የሚያስወግድ ያድርግልን። አምላከ ቅዱሳን ልዑል እግዚአብሔር ጾሙን በሰላም ጀምረን በሰላም እንድጨርስ ረድቶን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም ያድርሰን።               

❤ መድኃኒታችንም "የለመንከኝ ሁሉ አስጥሃለሁ አንተም በቀኜ ትኖራለህ ሥጋህንም ኤልያስ በዐረገበት ሠረገላ ውስጥ አኖራለሁ" አለው ሕፃን ቂርቆስ በሰማ ጊዜ እጅግ ደስ ብሎት ጌታችንን አመሰገነው። ከዚህም በኋላ በሌሊቱ እኩሌታም ከእናቱ ጋር አንገቱን ተቆረጠ መድኃኒታችንም በማይጠፋ አክሊል ጋረደው ነፍሶቻቸውንም በታላቅ ክብር ከእርሱ ጋር አሳረገ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ቂርቂቆስና በእናቱ ቅድስት ኢየሉጣ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር 15 ስንክሳር።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ብዑላንሰ ነድዩ ወርኅቡ። ወእለሰ የኀሥሥዎ ለእግዚአብሔር። ኢተፀነሱ እምኲሉ ሠናያት። መዝ 33፥10። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 6፥24-27።                                                    ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ወይርአዩ አሕዛብ በቅድመ አዕይንቲነ። በ­ቀለ ደሞሙ ለአግብርቲከ ዘተክዕወ። ይባዕ ቅድሜከ ገዐሮሙ ለሙቁሓን"። መዝ 78፥10-11። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 14፥12-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 2፥21-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 13፥1-13።  የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 5፥1-5። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ወልደ ነጐድጓድ። መልካም የቅዱስ ሚናስ የዕረፍት በዓል፣ የቅዱስ ቂርቆስ የልደት በዓልና የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።             

አለችው መኰንኑም "ስምሽን ስጪ ተናገሪ" አላት እርሷም "የኔ ስም ክርስቲያን መባል ነው" አለችው። መኰንኑም "ይህስ ስንፍና ነው የሚጠቅምሽ አይደለም እንዳትሞቺ ስምሽን ስጪ ተናገሪ" አላት። የከበረች ኢየሉጣም "የኔ ስም ክርስቲያን መባል እንደሆነ ነገርኩህ ሞት የሚሽረው በሰዎች ዘንድ የምጠራበትን ከፈለግህ ስሜ ኢየሉጣ ነው" ብላ መለሰችለት። መኰንኑም "ጽኑ የሆኑ ሥቃዮችን በላይሽ ሳያመጡ ተነሥተሽ መሥዋዕትን ለአማልክት አቅርቢ" አላት። የከበረች ኢየሉጣም "ዕውነት ነገርን ለመሥራት የምትሻ ከሆነ ዕድሜው ሦስት ዓመት የሆነ ሕፃን ልጅ ይፈልጉ ዘንድ ወደ አገሩ መንደር ላክ ወዳንተም ያምጡትና የምንገዛለትንና የምናመልከውን እርሱ ይነገረን" አለችው። ❤ ያን ጊዜም የሦስት ዓመት ልጅ ይፈልጉ ዘንድ መኰንኑ ወታደሮችን ላከ የአገር ሰዎችም ልጆቻቸውን ሠውረዋልና አላገኙም ከዚያም ከከተማው ቅጽር ውጭ በፀሐይ መውጫ ወዳለው በረሀ በኩል ወጡ የቅድስት ኢየሉጣንም ልጅ አገኙት ይህ ሕፃን "የስንት ዓመት ልጅ ነው" ብለው ስለርሱ ጠየቁ ሰዎችም "ይህ ሕፃን የሦስት ዓመት ሲሆን የክርስቲያናዊት መበለት ልጅ ነው" አሏቸው። ያንንም ሕፃን ይዘው ወደ መኰንኑ ወሰዱት መኰንኑም መልኩ የሚያምርና ደም ግባት ያለው እንደሆነ በአየ ጊዜ "ደስ የምትል ደስተኛ ሕፃን ሰላምታ ይገባሃል" አለው። ሕፃኑም "እኔን ደስተኛ ማለትህ መልካም ተናገርክ ላንተ ግን ደስታ የለህም እግዚአብሔር ለዝንጉዎች ደስታ የላቸውም ብሏልና ብሎ መለሰለት መኰንኑም ሕፃኑን "ሳልጠይቅህ ይህን ያህል ትመልስልኛለህን" አለው። ሕፃኑም "ገና ከዚህ የሚበዛ ነገርን እመልስልሃለሁ" አለው። ❤ መኰንኑም "ስምኽ ማነው” ብሎ በጠየቀው ጊዜ "ከንጹሕ ዐዘቅትና ከማይለወጥ ከማይጠፋ ውኃ የተገኘ ሕፃን ስሜ ክርስቲያን መባል ነው" ብሎ መለሰለት። መኰንኑም "ዳግመኛ እንዳትሞት ስምህን ንገረኝ" አለው የከበረ ሕፃንም "ስሜ ክርስቲያን መባል እንደሆነ ነገርኩህ ሞክሼ ስም የምትሻ ከሆነ  እናቴ የሰየመችኝ ቂርቆስ ነው" በማለት መለሰለት፡፡ መኰንኑም ሕፃን ቂርቆስን "እሺ በለኝና እሾምሃለሁ በብዙ ወርቅና ብርም አከብርሃለሁ" አለው። ሕፃኑም "የሰይጣ መልእክተኛ ለዕውነትም ጠላቷ የሆንክ ከእኔ ራቅ" አለው። መኰንኑም ሰምቶ ተቆጣ ደሙ እንደ ውኃ እስከሚፈስ ቆዳውን እንዲጨምቁትና እንዲግፉት አዘዘ። የከበረች ኢየሉጣሜ የልጅዋን ትዕግሥት በአየች ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰገነችው። ❤ ከዚህም በኋላ መኰንኑ "ጨውና ሰናፍጭ አምጡ አለ። የሁለቱንም አፍንጮቻቸውን ከፍተው ያንን ጨውና ሰናፍጭ እንዲጨምሩባቸው አዘዘ ያን ጊዜ ሕፃኑ "ትእዛዝህ ለጒረሮዬ ጣፋጭ ሆነ ከማርና ከስኳርም ለአፌ ጣመኝ" ብሎ ጮኸ። ሁለተኛም መኰንኑ እንዲህ ብሎ አዘዘ የረዘሙና የተሳሉ በእሳትም እንደ ፍም የጋሉ ዐሥራ አራት የብረት ችንካሮች አምጡ ሰባቱን በእናቱ አካላት ውስጥ ጨምሩ በሕፃኑም ሁለት ጆሮዎቹ ሁለት በዐይኖቹ ሁለት በአፉና በአፍንጫው አንድ በልቡ ጨምሩ እንዲህ ሲጨመርበት ጆሮዎቹ እንዲአሩ ዐይኖቹም ይጠፋ ዘንድ አንደበቱም ይቃጠል ዘንድ ወደ ልቡም ጽኑ ሕማም ገብቶ እርሱ ከዚህ ዓለም በሞት እንዲለይ ለእናቱም እንዲሁ አድርጉ ችንካሮችም በቅዱሳኑ በሥጋቸው ሁሉ ተጨመሩ። የክብር ባለቤት በሆነ በጌታችን ትእዛዝ የብረቶቹ ግለት ጠፍቶ እንደ በረዶ ቀዘቀዘ ጤነኞችም ሆኑ መኰንኑም "ወደ ወህኒ ወስዳችሁ በዚያ አሥራችሁ ዝጉባቸው" አለ። ❤ ከዚህም በኋላ መኰንኑ "የሥቃይ መሣሪያን ይሠራ ዘንድ እንዳዝዘው ብረትን የሚያቀልጥ ሰው አምጡልኝ" አለ። በአመጡለትም ጊዜ ሰይጣን ወደ መኰንኑ ልብ ገብቶ አንደበቱን ዘጋውና መናገር ተሳነው ሕፃኑ ፈጥኖ አክሊልን ለመቀበል እንደሚተጋ ሰይጣን ስለ አወቀ ስለዚህ ዘጋው። ❤ ከዚህም በኋላ ሕፃኑ ሠራተኛውን ጠርቶ "እኔንና እናቴን የሚያሠቃዩ በትን የሥቃይ መሣሪያ መሥራት ትችላለህ ይህ መኰንን ግን ምንም የሚያውቀው ነገር የለም" አለው። ሠራተኛውም እንደምትሻው በል ንገረኝ እምታዝዘኝ እኔ መሥራት እችላለሁ" አለው። ሕፃኑም ቅዱስ ቂርቆስ እያዘዘው...። ብረት ሠሪውም ሰምቶ እጅግ አደነቀ የሚረዱትንም ከአገር ውስጥ መቶ ሠራተኞችን ሰብስቦ መሥራት ጀምረ በአርባ ቀንም ጨረሰ። ❤ ከዚህም በኋላ መኰንኑ እለእሰሰክድሮስ ቂርቆስንና እናቱን ወደ አደባባይ ያመጡአቸው ዘንድ አዘዘ ያን ጊዜ አንደበቱ ተፈትቶ ነበርና እንዲህ አለ "ሕፃኑንና እናቱን ከቆዳቸው ጋር ራሳቸውን ላጩአቸውና በላያቸው የእሳት ፍሞችን ጨምሩ እርር ብለው እንዲቃጠሉ ዳግመኛም አራት ችንካሮችን ከትከሻዎቹ እስከ ተረከዙ ድረስ እንዲተክሉበት አዘዘ የእግዚአብሔርም መልአክ መጥቶ ሥቃዩን ከርሱ አራቀ። ዳግመኛም ከጥዋት እስከ ማታ ከሥቃይ መሣሪያዎች ውስጥ ጨምረው አዋሏቸው ግን ማሠቃየት ተሳናቸው። ❤ ከዚህም በኋላ ከማምጠቂያው ውስጥ ጨምረው መገዙአቸውና አመድ እስከሆኑ ከቅባትና ከጨው ጋር በብረት ምጣድ ውስጥ ቆሉአቸው ጌታችንም አስነሥቶ አዳናቸው። ወደ መኰንኑም በገቡ ጊዜ እንዲህ አላቸው "በእውነት ከሙታን ተለይታችሁ የተነሣችሁ ከሆነ ይህ ጫማዬ በእግሬ ወጥቶ እንደ ቀድሞው ሕያው እንዲሆን አድርጉ ሕፃን ቂርቆስም በጸለየ ጊዜ ያ ጫማ ታላቅ በሬ ሆነ ከአንገቱም ፍየል ወጣ። በዚያንም ሰዓት ለዐሥራ አንድ ሽህ አራት ሰዎች በሬውንና ፍየሉን አርደው ምሳ እንዲአደርጉላቸው መኰንኑ አዘዘ እንዲህም አለ ይህ "በቅቷቸው ከጠገቡ ከዚህም ሌላ ምግብ ካልፈለጉ የተሠራው ሁሉ ዕውነተኛ ነዋሪ ነው"። ❤ ከዚህም በኋላ አርደው ምሳ አደረጉላቸውና ከፍየሉ ሥጋ ስድስት እንቅብ ከበሬው ሥጋ አራት እንቅብ አተረፉ መኰንኑም የተረፈውን ሥጋ አይቶ ወደ ባሕር እንዲጥሉት አዘዘ። መኰንኑም ቢያፍር የሕፃኑን ምላስ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ ጌታችንም ምላሱን መለሰለት ዳግመኛም በታላቅ ጋን ውኃ አፍልተው ሕፃን ቂርቆስንና እናቱን ኢየሉጣን ይጨምሩአቸው ዘንድ አዘዘ እናቱም አይታ ፈራች። ልጅዋም ወደ እግዚአብሔር በጸለየላት ጊዜ አምላካዊ ኃይልን አሳደረባትና ከልጅዋ ጋር ወደ ጋኑ ገባች። እንደ ውርጭም ቀዝቃዛ ሆነ ደግሞም በውስጡ መንኲራኵር ወዳለበት የብረት ምጣድ እንዲጨምሩአቸውና ሥጋቸው እስከሚቦጫጨቅ እንዲስቡአቸው አዘዘ የእግዚአብሔርም መልአክ ቅዱስ ገብርኤልም በሕይወት አወጣቸው። ❤ መኰንኑም እነርሱን ማሸነፍ በተሳነው ጊዜ ቸብቸቧቸውን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ በዚያን ጊዜ ለስም አጠራሩ ስግደት የሚገባው የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወረደ ሕፃን ቅዱስ ቂርቆስንም "የምትሻውን ለምነኝ" አለው። ሕፃኑም "ሥጋዬ በምድር አይቀበር ስሜን ለሚጠራ መታሰቢያዬን ለሚያደርግ ቤተ ክርስቲያኔን ለሚሠራ የተጋድሎዬን መጽሐፍ ለሚጽፍና ለሚያጽፍ ወይም ለሚያነበው ለቤተ ክርስቲያኔ መባ ለሚያገባ በውስጧም ለሚጸልይ ለሁሉም ፍላጎታቸውን ስጣቸው ኃጢአታቸውንም ይቅር በል ስሜም በሚጠራበት በዚያች ቦታ የከብት ዕልቂት አይምጣ በሰውም ላይ አባር ቸነፈር በእህልም ላይ ድርቅ የውኃም ማነስ አይሁን"።

❤ "በስመ አብ ወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤          ❤ #ኅዳር ፲፭ 15 ቀን። ❤ እንኳን #ለታላቁ_ሰማዕት የስሙ ትርጓሜ ቡሩክና የታመነ ለሆነ #ለቅዱስ_ሚናስ_ለዕረፍት_በዓል፣ #ለታላቁ_ሰማዕት_ለሕፃኑ_ቅዱስ_ቂርቆስ_ለልደት መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰ። በተጨማሪ በዚችን ቀን ከሚታሰበው፦ ከአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ስልሳ አንደኛ ከእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ከቅዱስ አባት ከሁለተኛው #አባ_ሚናስ ዕረፍት ረድኤትና በረከትን ያሳፈን።                                                   ✝ ✝ ✝ ❤ #ታላቁ_ሰማዕት_ቅዱስ_ሚናስ፦ የዚህም ቅዱስ አባቱ አናቅዮስ ከሚባል አገር ነው ስሙም አውዶክስዮስ ነው እርሱም አገረ ገዥነት ተሹሞ ሳለ ወንድሙ ቀንቶበት በንጉሥ ዘንድ ነገር ሠራበት ንጉሡም ወደ አፍራቅያ አገር ሰደደውና በዚያም አገረ ገዢ አድርጎ ሾመው የአገር ሰዎችም ሁሉ ደስ አላቸው እርሱ ለሰው የሚራራ እግዚአብሔርም የሚፈራ ደግ ሰው ነውና። ❤ እናቱም ልጅ አልነበራትም በአንዲት ዕለት ወደ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን በበዓልዋ ቀን ገብታ የክርስቲያንን ወገኖች ያማሩ ልብሶችን ለብሰው ከልጆቻቸው ጋር ደስ እያላቸው ሲገቡ አየቻቸው። በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ሥዕል ፊት አለቀሰች ልጅን ይሰጣት ዘንድ ወደ ልጅዋ ወደ እግዚአብሔር እንድትለምንላትም ለመነቻት በዚያን ጊዜ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ሥዕል አሜን የሚል ቃል ወጣ። ❤ ከዚህም በኋላ ወደ ቤቷ ገብታ ይህን ቃል ለባሏ ነገረችው እርሱም "የእግዚአብሔር ፈቃዱ ይሁን" አለ። ከጥቂት ቀኖችም በኋላ እግዚአብሔር ይህን የተባረከና የከበረ ልጅን ሰጣት የእመቤታችንም ሥዕል "ሚናስ" ብላ እንደሰየመችው ስሙን ሚናስ ብለው ሰየሙት። ጥቂት በአደገ ጊዜም የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት አስተማሩት። ዐሥራ ሁለት ዓመትም ሲሆነው በመልካም ሽምግልና አባቱ ዐረፈ ከእርሱም በኋላ በሦስተኛ ዓመት እናቱ ዐረፈች ቅዱስ ሚናስም ብቻውን ቀረ። መኳንንቱም አባቱን አብዝተው ከመውደዳቸው የተነሣ ሚናስን በአባቱ ፈንታ ምስፍናን ሾሙት እርሱም የክርስቶስን አምልኮት አልተወም። ❤ ዲዮቅልጥያኖስም በካደ ጊዜ ሁሉንም ሰዎች ጣዖታትን እንዲአመልኩ አዘዛቸው ብዙዎችም ክብር ይግባውና በክርስቶስ ስም በሰማዕትነት ሞቱ። በዚያንም ጊዜ ቅዱስ ሚናስ ሹመቱን ትቶ ወደ ገዳም ገባ ታላቅ ተጋድሎን እየተጋደለ ብዙ ዘመናት ኖረ። በአንዲትም ዕለት ሰማይ ተከፍቶ ሰማዕታትን የብርሃን እክሊሎችን ሲአቀዳጁአቸው አየ "ስለ ክርስቶስ ስም በመከራ የደከመ ይህን አክሊል ይቀበላል" የሚል ቃልን ሰማ። በዚያንም ጊዜ ወደ ከተማ ተመለሰና ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ታመነ ሰዎችም አብዝተው አባበሉት በወገን የከበረ እንደሆነ እነርሱ ያውቁ ነበርና። መኰንኑም ብዙ ቃል ኪዳን ገባለት ባልሰማውም ጊዜ ጽኑዕ በሆነ ሥቃይ እንዲአሠቃዩት አዘዘ። ማሠቃየቱንም በሰለቸ ጊዜ በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ። በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ኅዳር 15 ቀን ተቀበለ ብዙዎችም በእርሱ ምክንያት ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም በሰማዕትነት ሞቱ። ❤ የቅዱስ ሚናስንም ሥጋ ወደ እሳት እንዲጥሉት መኰንኑ አዘዘ እሳትም አልነካውም ምእመናን ሰዎችም የቅዱስ ሚናስን ሥጋ ወስደው በአማሩ ልብሶች ገነዙት የስደቱ ወራትም እስከሚፈጸም በአማረ ቦታ ውስጥ አኖሩት። ❤ በዚያንም ወራት የመርዩጥ አገር ሰዎች ከአምስቱ አገሮች ሠራዊትን ሊአከማቹ ወደዱ የቅዱስ ሚናስንም ሥጋ ረዳት ይሆናቸው ዘዘንድ በመንገድም እንዲጠብቃቸው ከእርሳቸው ጋር ወሰዱት። እነርሱም በባሕር ላይ መርከብ ውስጥ ሳሉ ፈታቸው እንደ ከይሲ አንገታቸው እንደ ግመል አንገት ያለ አውሬዎች ከባሕር ወጡ ይልሱትም ዘንድ ወደ ቅዱስ ሚናስ ሥጋ አንገታቸውን ዘረጉ ከቅዱ ሚናስም ሥጋ እሳት ወጥታ እነዚያነሰ አራዊት አቃጠላቻቸው ሰዎችም አይተው አደነቁ ደስታም አደረጉ ፈርተው ነበርና። ❤ ወደ እስክንድርያ አገርም ደርሰው ሥራቸውን ፈጽመው ወደ አገራቸው በሚመለሱ ጊዜ የቅዱስ ሚናስን ሥጋ ከእርሳቸው ጋር ሊወስዱ ወደው በገመል ላይ በጫኑት ጊዜ ገመሉ ከቦታው የማይነሣ ሆነ። ሁለተኛም በሌላ ገመል ጫኑት እርሱም መነሣትን እመቢ አለ አብዝተውም ደበደቡት ገመሉም ከቶ አልተንቀሳቀሰም እነርሱም ያቦታ እግዚአብሔር የፈቀደለት መሆኑን አወቁ ቦታውንም አዘጋጅተው ቀበሩት። ❤ ጌታችንም በበግ እስከገለጠው ድረስ ብዙ ዘመናትን በዚያ ቦታ ኖረ ይህም ቤተ ክርስቲያኑ በከበረችበት በሰኔ ዐሥራ አምስት ቀን ተጽፎአል። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ሚናስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                          ✝ ✝ ✝ ❤ #የእስክንድርያ_ስልሳ_አንደኛ_ሊቀ_ጳጳሳት #ሁለተኛ_አባ_ሚናስ፦ ይህም ቅዱስ ሚናስንም ከታናሽነቱጨያለ ፍላጎቱ ወላጆቹ ሚስት አጋቡት ትእዛዛቸውን መተላለፍ ስለአልፈለገ የጋብቻውን ሥርዓት ሁሉ በቤተ ክርስቲያን ፈጸመ። ለርሱ ይህ ሁሉ ሕልም ይመስለው ነበር ወደ ሙሽሪትም ወደ አዳራሽ በአስገቡት ጊዜ ተቀምጦ እንዲህ ብሎ ተናገራት "እኅቴ ሆይ ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱን ካጠፋ ምን ይጠቅመዋል እንደ ተጻፈ ሁሉ ያልፋልና ግን የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ለዘላለሙ ይኖራል አሁንም ድንግልናችንን እንድንጠብቅ ነይ ቃል ኪዳን እናድርግ" እርሷም ቃሉን ተቀብላ ከእርሱ ጋር ተስማማች። ❤ ከዚህም በኋላ ትቷት ወደ አስቄጥስ ገዳም ሒዶ በአባ መቃርስ ገዳም ውስጥ መነኰሰ ብዙ ዘመናትም በገድል ተጠምዶ ኖረ። ከእርሱ በፊት የነበረ ሊቀ ጳጳሳትም በዐረፈ ጊዜ ይህን ቅዱስ አባት ሚናስን ያለውዴታው ወስደው ሊቀ ጵጵስና ሾሙት በወንጌላዊ ቅዱስ ማርቆስም ወንበር ላይ መንጋዎቹን በቅን ፍርድ እየጠበቃቸው እያስተማራቸው ዐሥራ ስምንተሰ ዓመት ኑሮ ኅዳር 15 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን የአባ ሚናስ በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የኅዳር15 ስንክሳር።                                                      ✝ ✝ ✝ ❤ #ሕፃኑ_ቅዱስ_ቂርቆስ፦ በዚያንም ወራት የክብር ባለቤት የሆነ ክርስቶስን በሚያምኑ የክርስቲያን ወገኖች ላይ ታላቅ መከራና ስደት ሆነ። ስሟ ኢየሉጣ የሚባል አንዲት ሴት ነበረች እርሷም ከታናሽነቷ ጀምራ ደግ ናት ስደትም እንደሆነ በሰማች ጊዜ መኰንኑን ከመፍራት የተነሣ ሕፃኗን ይዛ ከሮሜ ከተማ ተሰዳ የኪልቅያ አውራጃ ከሆነ ከጠርሴስ ደርሳ ከዚያም በአገሮች ውስጥ እየተዘዋወረች ተቀመጠች። ወደዚያች አገርም ያ ከእርሱ የሸሸችው መኰንን እለእስክድሮስ መጣ ጭፍሮቹም ክርስቲያኖችን ፈለጓቸው። ይቺንም ቅድስት ኢየሉጣን አግኝተው ያዝዋትና ወደ መኰንኑ አደረሷት የክርስቲያን ወገንም እንደሆነች ነገሩት። ❤ መኰንኑም "ሴትዮ ተናገሪ ከወዴት ሕዝብ ወገን ነሽ ነገድሽ ምንድን ነው አገርሽስ ወዴት ነው" አላት። የከበረች ኢየሉጣም እንዲህ ብላ መለሰችለት "የአንጌቤን ሰው ለሆንኩ ለእኔ ወገኖቼ ኤሳውሮሳውያን ናቸው እኔም በአንተ ምክንያት ሸሽቼ ነበር እነሆ ዛሬ ግን በእጅህ ውስጥ ነኝ" አለችው። መኰንኑም "በእጄ ውስጥ እንደተገኘሽ ታውቂያለሽን" አላት "አሁንም የሚሻልሽን ምረጪ ስምሽንም ተናገሪ እኔንም እሺ በይኝና ለአማልክት ሠዊ" የከበረች ኢየሉጣም አለችው "ለረከሱ አማልክት እኔ አልሠዋም"

 🕊  ጾመ ነቢያት   🕊     🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟 የጾመ ነብያት ምስጢር ምንድነው ? ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨      ጾመ ነቢያት [ የገና ጾም ] ከልደት አስቀድሞ የሚጾም ጾም ነው፡፡ ከህዳር ፲፭ [ 15 ] ጀምሮ ለ ፵፫ [43] ቀናት የሚጾም ሲሆን ፋሲካው [ ፍቺው ] በልደት በዓል ነው፡፡ ይህም ጾም በዘመነ ብሉይና በዘመነ ሐዲስ ቅዱሳንና ምዕመናን ጾመውታል፡፡ ጾመ ነብያት ስያሜውን ያገኘው ነቢያት የተናገሩት ትንቢት ስለተፈጸመበት ነው፡፡ በየዘመናቱ የተነሡ ነቢያት እግዚአብሔር ወደፊት ሊያደርግ ያሰበውን በእምነት ዓይን እያዩ ምስጢር ተገልጦላቸው የራቀው ቀርቦ ፣ የረቀቀው ገዝፎ ጎልቶ እየተመለከቱ ትንቢት ተናገሩ ፤ ያዩትም መልካም ነገር እንዲደርስላቸው ጾሙ ጸለዩ፡፡ ነቢያት ከእመቤታችን ስለ መወለዱ ፥ ወደ ግብፅ ስለ መሰደዱ ፥ በባሕረ ዮርዳኖስ ስለ መጠመቁ ፥ ብርሃን በሆነው ትምህርተ ወንጌል ጨለማውን ዓለም ስለ ማብራቱ ፥ ለሰው ልጆች ድኅነት ጸዋትወ መከራ ስለመቀበሉና ስለ መሰቀሉ ፥ ስለ ትንሣኤው ፥ ስለ ዕርገቱና ስለ ዳግም ምጽአቱ ትንቢት ተናግረው አላቆሙም፡፡ ለአዳም የተሠጠው ተስፋ ተገልጦላቸው ለተናገሩት ትንቢት ፍፃሜ እንዲያደርሳቸው ፈጣሪያቸውን ተማፀኑትም እንጂ፡፡ በየዘመናቸው ፦ "አንሥእ ኃይልከ ፣ ፈኑ እዴከ" እያሉ ጮኹ፡፡ በጾምና በጸሎት ተወስነውም እግዚአብሔር ሰው የሚሆንበትን ጊዜ በቀናት ፣ በሳምንታት ፣ በወራትና በዓመታት ቆጠሩ፡፡ ለምሳሌ ነቢዩ ኤርምያስ ስለ ሥጋዌው ትንቢት በተናገረ በ፬፵፮ ዓመት ጌታችን ከእመቤታችን ከሥጋዋ ሥጋን ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ሰው ሆኗል፡፡ ነቢያት ተስፋው በዘመናቸው ተፈጽሞ በዓይነ ሥጋ ለማየት ባይችሉም እግዚአብሔር ፦ "አያደርገውን አይናገር የተናገረውን አያስቀር" ብለው አምነው ከወዲሁ ተደሰቱ፡፡ ለዘመነ ሥጋዌ ቅርብ የነበሩ እነ ነቢዩ ኢሳይያስ ጾሙ እንዴት መፈጸም እንዳለበት ተናግረዋልም፡፡ [ኢሳ.፶፰፥፩]፡፡ በመሆኑም በጌታ ልደት ትንቢተ ነቢያት ስለተፈጸመበት ይህ ጾም "የነቢያት ጾም" ይባላል፡፡ የወልደ እግዚአብሔርን ሰው መሆን ያስተማሩበት ስለሆነም "ጾመ ስብከት" ይባላል፡፡ ይህንን ጾም በዘመነ ብሉይና በዘመነ ሐዲስ ብዙ ቅዱሳን ጾመውታል፤ በዚህም ምክንያት የሚከተሉት ስያሜዎች አሉት፡፡ እነርሱም፦ † ፩. [    ጾመ አዳም   ] ፦ አዳም ዕፀ በለስን በልቶ ከገነት ከተባረረ በኋላ በፈጸመው በደል አዝኖ ፥ ተክዞ ፤ አለቀሰ [እንባ ቢያልቅበት እዥ እስከሚያፈስ ፤ እዥ ቢያልቅበት ደም በዓይኑ እስከሚፈስና ዓይኑ ይቡስ ወይም ደረቅ እስከሚሆን ድረስ አለቀሰ] ፥ ጾመ፣ ጸለየ፡፡ ከልብ የሆነ ጸጸቱን፣ ዕንባውን፣ በራሱ መፍረዱንም እግዚአብሔር አይቶ ተስፋ ድኅነት ሰጠው፡፡ "ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ ፣ በደጅህ ድኼ ፣ በዕፀ መስቀል ተሰቅዬ፣ ሞቼ አድንሃለሁ፡፡" የሚል ነው፡፡ [ገላ. ፬፥፬፣ መጽ.ቀሌምንጦስ] ስለዚህ ጾሙ የተሰጠው ተስፋ ፥ የተቆጠረው ሱባኤ ስለተፈጸመበት "ጾመ አዳም" ይባላል፡፡ † ፪. [   ጾመ ነቢያት   ] ፦ ነቢያትም የምሥጢረ ሥጋዌ ነገር ተገለጦ ስለታያቸው ፣ ክርስቶስ ለሰው ልጅ የሚከፍለውን የፍቅር ዋጋ በትንቢት ተመልክተው ጾመውታልና ጾመ ነቢያት ይባላል፡፡ ይህ ጾም ከአባታችን አዳም እስከ መጥምቁ ዮሐንስ ድረስ የተነሱ አበውና እናቶች : ድኅነትንና ረድኤትን ሲሹ የጾሙት ጾም ነው:: በተለይ አባታችን አዳም : ቅዱስ ሙሴ : ቅዱስ ኤልያስ ፣ ቅዱስ ዳንኤልና ቅዱስ ዳዊት በጾማቸው የተመሰከረላቸው ቅዱሳን ናቸው:: [ዘዳ.፱፥፲፱ ፣ ነገ.፲፱፥፰ ፣ ዳን.፱፥፫ መዝ.፷፰፥፲ ፻፰፥፳፬] ቅዱሳን ነቢያት በጭንቅ በመከራ ሆነው የጾሙት ጾም ወደ መንበረ ጸባኦት ደርሶ: ወልድን ከዙፋኑ ስቦታል:: ለሞትም አብቅቶታል:: † ፫.  [   ጾመ ሐዋርያት  ] ፦ ሐዋርያት "ትንሣኤን ዐቢይ ጾምን ጾመን እናከብራለን ፣ ልደትን ምን ሥራ ሠርተን እናከብረዋለን?" ብለው ከልደተ ክርስቶስ በፊት ያሉትን ፵፫ ዕለታት ጾመዋልና፡፡ † ፬.  [   ጾመ ማርያም   ] ፦ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እግዚአብሔር አምላክ ቅድስናዋን አይቶ በቅዱስ ገብርኤል ብሥራት ወልደ አምላክን ያለ ሰስሎተ ድንግልና በግብረ መንፈስ ቅዱስ ጸንሳ እንደምትወልደው ቢነግራትም የትሕትና እናት ናትና "ምን ሠርቼ የሰማይና ምድርን ፈጣሪ እችለዋለሁ?" ብላ ጌታን ከመውለዷ አስቀድማ ጾማለችና "ጾመ ማርያም" ይባላል፡፡ † ፭.  [   ጾመ ፊልጶስ   ] ፦ ሐዋርያው ቅዱስ ፊልጶስ በአረማውያን ዘንድ ገብቶ እያስተማረ ሳለ በሰማዕትነት ሲሞት ፤ አስክሬኑ ከደቀመዛሙርቱ ስለተሰወረ ፤ እግዚአብሔር የተሰወረውን የመምህራቸውን አስክሬን እንዲገለጽላቸው ከኅዳር ፲፮ ጀምረው ጾመው በሦስተኛው ቀን የመምህራቸው አስክሬን ተመልሶላቸዋል፤ ነገር ግን አስከሬኑ ቢመለስላቸውም ጾሙን ግን እስከ ልደት ቀጥለዋል፡፡ † ፮.  [   ጾመ ስብከት  ] ፦ የወልደ እግዚአብሔርን ሰው መሆን ያስተማሩበት ፥ የሰው ልጆች ተስፋ የተመሰከረበት ፥ የምስራች የተነገረበት ስለሆነ ጾመ ስብከትም ይባላል፡፡ † ፯.  [   ጾመ ልደት   ] ፦ የጾሙ መጨረሻ [ መፍቻ ] በዓለ ልደት ስለሆነ "ጾመ ልደት" ይባላል፡፡ በጾማችን በጸሎታችን - ስለ ቤተክርስቲያን ፥ ስለ ሀገር እና ስለ ሕዝብ በማሰብ በእንባ እራሳችንን ዝቅ በማድረግ እንጾም ዘንድ ይገባል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡ ወለወላዲቱ ድንግል ፡ ወለመስቀሉ ክቡር፡፡

የወይራ ሠፈር ኆኅተ ገነት ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ቀጠሎ ወደመ። ኢኦተቤ-አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ኅዳር ፲፬/፳፻፲፰ ዓ/ም በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በኮሎፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ሥር የወይራ ሠፈር ገነተ ሰማይ ቅድስት አርሴማና መንበረ ብርሃን እጨጌ አቡነ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን የሚገኝ ሲሆን ዛሬ ሌሊት በእሳት አደጋ ምክንያት የቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን  ሙሉ በሙሉ ወድሟል። የቃጠሎው መነሻ የኤሌክትሪክ መስመር ችግር እንደሆነም የተገለጸ ሲሆን ከታቦቱ በስተቀር ሌሎች ንዋየተ ቅድሳት ሙሉ በሙሉ በአደጋው ምክንያት መውደማቸው ነው የተገለጸው። ሊያገለግሉበት ሲሄዱ ቦታውን ያጡት ሊስቀድሱበት የገሰገሱበት ቤተ ክርስቲያን በእሳት እንዳልሆነ ሆኖ ሲያዩት ልባቸው የከዳቸው  ካህናትና ምእመናን በከፍተኛ ኀዘን ላይ እንደሚገኙም የደረሰን መረጃ ያለመክታል። አቤቱ ማረን ይቅር በለን! © የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ስለ አንዲት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን

✨✨✨ህዳር ሚካኤል ✨✨✨
+8
✨✨✨ህዳር ሚካኤል ✨✨✨