en
Feedback
Inclusive Education (Ethiopia)

Inclusive Education (Ethiopia)

Open in Telegram

This channel is created to share new ideas and developments regarding Inclusive Educatio in Ethiopia.

Show more
1 643
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-630 days
Posts Archive
+9
IERC GUIDLINE Amharic and English.pdf1.01 MB

+9
checklist_for_REB_to_access_the_functionality_level_of_IERCs.docx0.25 KB

Dear All Trainees, the documents are attached here.

የመወያያ ርዕስ፣ በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ ነው። ባለታሪኳ አንዲት ሴት አካል ጉዳተኛ እህታችን ስትሆን ያጋጠማት ጉዳይ ከቤት ክራይ ጋር ይገናኛል። ጉዳዩ እንዲህ ነው ባለታሪኳ በአንድ ጊቢ ውስጥ በክራይ ቤት የምትኖር ሲሆን አከራዮቹም ቤቱን የሰሩት ከቀበሌ በተሰጣቸው ቤት አጠገብ እንጂ የግል ጊቢያቸው ውስጥ አደለም። ይሄንን የተገነዘበችው ተከራይ በውስጥ ለውስጥ በድብቅ ወደ ቀበሌ አስተዳደሩ ትቀርብና "ቤቱ የተሰራው በቀበሌ መሬት ላይ በህገ-ወጥ መንገድ ስለሆነ ፣ እኔ ደግሞ አቅመ ደካማ አካል ጉዳተኛ እና የልጆች እናት ስለሆንኩኝ ቤቱ በቀበሌ ቤትነት ተቆጥሮ ለእኔ ይሰጠኝ" የሚል ጥያቄ ታቀርባለች። ሆኖም ግን የቀበሌ አስተዳደሩ በወቅቱ አፋጣኝ ምላሽ ስላልሰጣት ጉዳዩን እየተመላለሰች ለማስፈፀም ጥረት በምታደርግበት ወቅት ቤቱን ያከራዩት ግለሰቦች ይሰሙና ቤቱን ለቀሽ ውጪ ቢሏትም ለመውጣት ፍቃደኛ ሳትሆን ትቀራለች። በሁኔታው የተበሳጩት አከራይ የግለሰቧን የቤት ዕቃ ወደ ውጪ አውጥተው ይበትናሉ በዚህን ጊዜ ጉዳዩን ለቀበሌው አስተዳደር  አሳውቃ በተጨማሪም የአካል ጉዳተኛ ማህበራት ህብረት ሰብሳቢ ጋር ለአቤቱታ በሄደችበት እንደ አጋጣሚ ለግል ጉዳይ በዛ ሰፈር ስለነበርኩኝ ጉዳዩን ከሰማው በኃላ ወዲያውኑ የጉዳዩን ሁኔታ ለመከታተል እንድችል የግለሰቧን ስምና ስልክ ተቀብዬ ሄጃለሁ። በመቀጠልም ግለሰቧ አባል ወደ ሆነችበት የሴት አካል ጉዳተኛ ማህበር ጊዚያዊ ተወካይ  ጋር በመደወል ጉዳዩን እንድትከታተል አሳውቄ እገኛለሁ። አሁን ላይ ከእርሷ በደረሰኝ መረጃ መሰረት የቀበሌ አስተዳደሩ ቤቱን ለአከራዩት ግለሰቦች ተከራይዋ ቤት ፈልጋ እስክትወጣ ድረስ ለአምስት በቀን እንዲታገሱ ከማሳሰብ የዘለለ መፍትሔ ሊሰጡ አልቻሉም። የመወያያ ጥያቄዎች 👇 1👉 ለመሆኑ አንድ ግለሰብ በህጉ መሰረት ከሆነ ከቀበሌ በክራይ የተቀበለው ቤት ላይ ሌላ ቤት በግሉ ቀጥሎ መገንባት እና አከራይቶ መጠቀም ይችላልን? 2👉ከላይ ለተነሳው ጥያቄ መልሶ "አይችልም" ከሆነ .... ቤቱን ለተከራየችው አካል ጉዳተኛ ግለሰብ አሳልፎ ሊሰጥ የሚችልበት የህግ አግባብ ካለ ብትጠቁሙን መልካም ነው። 3👉 በህጉ መሰረት ተከራይ ቤት ለቆ እንዲወጣ አከራይ ለተከራይ ሊሰጠው የሚገባው ቀነ ገደብ 5 ቀን ብቻ ነው ብላቹ ታስባላቹ? ካልሆነ የቀበሌ አስተዳደሩን ውሳኔ እንዴት ገመገማቹት? በዚህ አጋጣሚ ግለሰቧን በሙያቹ ማገዝ የምትፈልጉ ሰዎች አድራሻዋን በውስጥ መስመር ማግኘት ትችላላችሁ። አመሰግናለሁ! ተሻለ መዝገቡ

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በትምህርት ዘርፉ አካታችነት ዙሪያ ከኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌዴሬሽንና የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ጋር ተወያዩ …………………………..//…………
+1
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በትምህርት ዘርፉ አካታችነት ዙሪያ ከኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌዴሬሽንና የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ጋር ተወያዩ …………………………..//……………………… መስከረም 26/2016ዓ/ም (የትምህርት ሚኒስቴር) የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌዴሬሽንና የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን አመራሮች ከትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ጋር ተወያይተዋል። የሀገሪቱ የትምህርት ስርዓት አካል ጉዳተኞችን ተደራሽ እና አካታች ከማድረግ አንፃር ያለበትን ችግር ተወካዮቹ ለፕሮፌሰር ብርሃኑ አብራርተዋል ። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋም በትምህርት ፖሊሲው አካል ጉዳተኞችን በሚመለከት የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ ትኩረት እንደተደረገ ገልጸዋል። ይሁን እንጂ በመርህ ደረጃ የትምህርት ስርዓቱን አካታች ለማድረግ ስምምነትና ፍላጎት ቢኖርም በትግበራ ወቅት እንደ ሃገር ያለውን የመንግስት የአቅም ውስንነት ከግንዛቤ በማስገባት አቅም በፈቀደ መጠን ደረጃ በደረጃ የሚተገበር መሆኑን አስረድተዋል።

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE ሚኒስትሩን ያስደናገጣቸው ቁጥር ? ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፦ " ከዚህ ፈተና አንድ #ሊያስደነግጠን የሚገባ ነገር ከተፈተኑት ጠቅላላ ተማሪዎች ውስጥ 50 ከመቶ የሚሆኑት እና ከዛ በላይ 26 ከመቶ
#MoE ሚኒስትሩን ያስደናገጣቸው ቁጥር ? ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፦ " ከዚህ ፈተና አንድ #ሊያስደነግጠን የሚገባ ነገር ከተፈተኑት ጠቅላላ ተማሪዎች ውስጥ 50 ከመቶ የሚሆኑት እና ከዛ በላይ 26 ከመቶ ነው ያገኙት። ከ845 ሺህ ፤ 422,500 ሺህ ተማሪ ከ26 በታች ነው ያገኘው። እንደው ዝም ብሎ አንድ ተማሪ ፈተናውን በግምት ቢሞላ እንኳን ሊያገኘው የሚችለው ውጤት ነው። ለዚህ ነው ከታች ጀምሮ በደንብ አጥርተን መስራት አለብን የምንለው። " ስለ 2015 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ቁጥሮች ምን ይላሉ ? - በ2015 የተፈተኑ ተማሪዎች ብዛት 845,099 ፤ 50 በመቶና በላይ ያመጡ 27,267 ተማሪዎች (3.2%) ብቻ ናቸው። ከነዚህ ውስጥ ፦ • ከተፈጥሮ ሳይንስ ያለፉ 19,017 ተማሪዎች • ከማህበራዊ ሳይንስ ያለፉ 8,250 ተማሪዎች - በማታ የተፈተኑ 16,541 ያለፉ 12 ተማሪዎች ብቻ - በግል የተፈተኑ 169,502 ያለፉ 498 ተማሪዎች ብቻ - በመደበኛ የተፈተኑ 659,056 ያለፉ 26,757 ተማሪዎች ብቻ - የ12ኛ ክፍል ፈተና ካስፈተኑ 3,106 ት/ቤቶች፤ 1,328 ትምህርት ቤቶች #አንድም_ተማሪ ማሳለፍ አልቻሉም / ምንም ተማሪ አላሳለፉም። - በሀገሪቱ ካሉትና የ12ኛ ክፍል ፈተና ካስፈተኑት ትምህርት ቤቶች 42.8 በመቶ የሚሆኑት አንድም እንኳን ተማሪ ማሳለፍ አልቻሉም። - 27 ሺህ 267 ተማሪዎች በቀጥታ ፍሬሽ ማን ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲገቡ 160 ሺህ ገደማ ተማሪ በሬሜዲያል ይገባሉ። #TikvahEthiopia @tikvahethiopia

የአጠቃላይ ትምህርት የ2016 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሂደቱ የሚመራበት ሀገር አቀፍ የትምህርት ካላንደር ማሳሰቢያ :- ክልሎች በብሔራዊ ፈተናና በተለያዩ ክልላዊ ነባራዊ ሁኔታዎች መነሻ የ
የአጠቃላይ ትምህርት የ2016 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሂደቱ የሚመራበት ሀገር አቀፍ የትምህርት ካላንደር ማሳሰቢያ :- ክልሎች በብሔራዊ ፈተናና በተለያዩ ክልላዊ ነባራዊ ሁኔታዎች መነሻ የተወሰኑ የቀናት ለውጦች ሊያደርጉ እንደሚችሉ ታሳቢ ይደረግ

ጥሩነዉ ግንመሬት ይወርድ ይሆን ?

" የኢንተርኔት አገልግሎት ባለባቸው አካባቢዎች ፈተናው በኦንላይን ይሰጣል (ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ) " - የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ትምህርት ሚኒስቴር በሚቀጥለው የትምህርት ዘመን #በዩኒቨርሲቲዎች የሚሰጠው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የኢንተርኔት አገልግሎት ባለባቸው አካባቢዎች በ #ኦንላይን እንደሚሰጥ አሳውቋል። ይህን ያሳወቁት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ናቸው። ሚኒስትሩ ፤ በ2016 የትምህርት ዘመን አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት በሁሉም የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተግባራዊ እንደሚሆን አሳውቀዋል። ለዚህም ተግባራዊነት ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን ጠቁመዋል። ፕ/ር ብርሃኑ ፤ በሚቀጥለው የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንደሚሰጥ ጠቁመው የኢንተርኔት አገልግሎት ባለባቸው አካባቢዎች ፈተናው በኦንላይን እንደሚሰጥም ገልጸዋል። በሌላ በኩል ፤ ከአዲሱ የትምህርት ስርዓት ጋር በተያያዘ በመጽሐፍት ሕትመትና ስርጭት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተሰራ ነው በዋል። በመጀመሪያና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ የመጽሐፍት እጥረት ማጋጠሙን የጠቆሙት ሚኒስትሩ ፤ ችግሩ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ እንዳያጋጥም ቀደም ብሎ ጨረታ በማውጣት መጽሐፍትን በወቅቱ ለማድረስ እየተሠራ ነው ብለዋል። መጽሐፍት እስከ መስከረም ወር መጨረሻ ድረስ እንደሚቀርቡ የትምህርት ሚኒስትሩ ጠቁመዋል፡፡ @tikvahethiopia

መልካም ተግባር ነዉ። በርቱ

ትመህርት ሚኒሰቴር ከላይት ፎር ዘ ወርልድ ጋር በመተባባር የልዩ ፍላጎት/አካቶ ትምህርት ስትራቴጂን ለሁለተኛ ጊዜ መከለሱ ይታወሳል፡፡ በተጨማሪም ስትራቴውን ወደ መሬት ለማውረድ የሚያስችል የአፈጻጸም
+1
ትመህርት ሚኒሰቴር ከላይት ፎር ዘ ወርልድ ጋር በመተባባር የልዩ ፍላጎት/አካቶ ትምህርት ስትራቴጂን ለሁለተኛ ጊዜ መከለሱ ይታወሳል፡፡ በተጨማሪም ስትራቴውን ወደ መሬት ለማውረድ የሚያስችል የአፈጻጸም መመሪየ ያዘገጀ ሲሆን ከነሀሴ 24-25 /2015 ዓ.ም በደብረዘይት ከተማ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በረቂቅ መመሪያው ላይ ምክክር ተደርጓል፡፡ ከመድረኩም መመሪያውን ሊያጠናክሩ የሚየስችሉ በርካታ ምክረ ሀሳቦች የተገኘ ሲሆን፣ መመሪያው አልቆና በሚመለከተው አካል ጸድቆ ስራ ላይ ሲውል አካቶ ትምህርትን በመተግበር ሂደት ያጋጠሙና የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በዘላቂነት ይፈታል ተብሎ ይታመናል፡፡

ትመህርት ሚኒሰቴር ከላይት ፎር ዘ ወርልድ ጋር በመተባባር የለዩ ፍላጎት/አካቶ ትምህርት ስትራቴጂን ለሁለተኛ ጊዜ መከለሱ ይታወሳል፡፡ በተጨማሪም ስትራቴውን ወደመሬት ለማውረድ የሚያስችል የአፈጻጸም
ትመህርት ሚኒሰቴር ከላይት ፎር ዘ ወርልድ ጋር በመተባባር የለዩ ፍላጎት/አካቶ ትምህርት ስትራቴጂን ለሁለተኛ ጊዜ መከለሱ ይታወሳል፡፡ በተጨማሪም ስትራቴውን ወደመሬት ለማውረድ የሚያስችል የአፈጻጸም መመሪየ ያዘገጀ ሲሆን ከነሀሴ 24-25 /2015 ዓ.ም በደብረዘይት ከተማ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በረቂቅ መመሪያው ላይ ምክክር ተደርጓል፡፡ ከመድረኩም መመሪያውን ሊያጠናክሩ የሚየስችሉ በርካታ ምክረ ሀሳቦች የተሰበሰቡ ሲሆን፣ መመሪያው አልቆና በሚመለከተው አካል ጸድቆ ስራ ላይ ሲውል አካቶ ትምህርትን በመተግበር ረገድ የሚታዩ ተግዳሮቶችን በዘላቂነት ይፈታል ተብሎ ይታመናል፡፡

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር የአለም መምህራን ቀንን ምክንያት በማድረግ ከ October 10-11/2023 G.C በጅጅጋ ዩኒቨርስቲ ላዘጋጀው የጥናትና ምርምር ኮንፈረንስ ተወዳድራችሁ ስራችሁን ማቅረብ
የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር የአለም መምህራን ቀንን ምክንያት በማድረግ ከ October 10-11/2023 G.C በጅጅጋ ዩኒቨርስቲ ላዘጋጀው የጥናትና ምርምር ኮንፈረንስ ተወዳድራችሁ ስራችሁን ማቅረብ የምትፈልጉ ሁሉ በተመረጡት የመነሻ ሀሳቦች ዙሪያ ተቀራራቢ የሆነና የተጠናቀቀ የምርምር ስራ ይህን call for papers በማየት በተጠቀሰዉ ቀንና አድራሻ አስፈላጊውን ሰነድ እንድታስገቡ እንጠይቃለን ። የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር

photo content
+1

ቤተልሄም ሽትዬ በጣም የሚገርም ልዩ ተሰጥኦ ያላት መስማት የተሳናት ድንቅ ተመራቂ ናት። እስከዛሬዋ ቀን በአአዩ በልዩ ፍላጎትና አካቶ ትምህርት ክፍል በቅድመ ምረቃ ፕሮግራም ያልተመዘገበ ከ3.90 በ
ቤተልሄም ሽትዬ በጣም የሚገርም ልዩ ተሰጥኦ ያላት መስማት የተሳናት ድንቅ ተመራቂ ናት። እስከዛሬዋ ቀን በአአዩ በልዩ ፍላጎትና አካቶ ትምህርት ክፍል በቅድመ ምረቃ ፕሮግራም ያልተመዘገበ ከ3.90 በላይ ነጥብ በማምጣት በእጅግ ከፍተኛ ማዕረግ ከመመረቅዋም በላይ 3 ልዩ ሽልማቶችን (ሜዳሊያ) ጠራርጋ ወስዳለች። በመውጫ ፈተናም 93/100 በማምጣት አሰደማሚነትዋን አሳይታለች። ያገኘቻቸው ሜዳልያዎች፦የኮሌጅ ሜዳሊያ፣ የሴት ምሩቃን ሜዳሊያና የአካል ጉዳተኞች ሜዳልያ ናቸው። መስማት አለመቻል የማይታይ የአካል ጉዳት ስለሆነ የሚዲያ ትኩረት አላገኘችም። አካል ጉዳተኞች እንደሚችሉ ለማሕበረሰቡ ጥሩ ማሳያ (አስተማሪ) ይሆን ነበር። ዶር አለማየሁ ተክለማሪያም

ተመልከቱ ፅናት 🙏 ልጇን ለ4 አመት በዊልቸር እያመላለሰች አብራ ክፍል ውስጥ ቁጭ ብላ ፅፋ ያስተማረችው እናት ልጇን በማዕረግ አስመርቃለች። "አራት ዓመት ልጄን በዊልቸር እያመላለስኩ አስተምሬ በማ
+1
ተመልከቱ ፅናት 🙏 ልጇን ለ4 አመት በዊልቸር እያመላለሰች አብራ ክፍል ውስጥ ቁጭ ብላ ፅፋ ያስተማረችው እናት ልጇን በማዕረግ አስመርቃለች። "አራት ዓመት ልጄን በዊልቸር እያመላለስኩ አስተምሬ በማዕረግ አስመርቄያለሁ" ወይዘሮ እህተ በቀለ ወይዘሮ እህተ በቀለ ይባላሉ። ልጃቸው ዮርዳኖስ ወሮታው አካሏን በራሷ ማንቀሳቀስ የማያስችል ጉዳት አለባት። ይህ ግን ለዮርዳኖስም ለእናቷም የዛሬ ስኬት እንቅፋት አልሆነባቸውም። ዮርዳኖስ በእናቷ ድጋፍ ዛሬ ትምህርቷን አጠናቃ ከአዲስ አበባ ዮኒቨርሲቲ ከሳይኮሎጂ ትምህርት ክፍል በማዕረግ ተመርቃለች፡፡ "አራት ዓመት ሙሉ ልጄን በዊልቸር እያመላለስኩ አስተምሬ አጠናቅቄያለሁ። አራት ዓመት ለእኔ እንደ አራት ቀን ነው:: ምንም አልተሰማኝም ደስ ብሎኝ አልፏል" ብለዋል፤ እናት፡፡ በአራት ዓመት የትምህርት ቆይታዋ የሚሰጣትን ትምህርት ክፍል ውስጥ አብረዋት ቁጭ ብለው እየጻፉላት እንዳስተማሯት እናት ለኢፕድ ተናግረዋል። "ዮርዳኖስ የማንበብ ችሎታዋን እወድላታለሁ። ያነበበችውን አለመርሳቷንና አስተዋይነቷን እወድላታለሁ፤ ልጄ ትጉህ ናት" ብለዋል፡፡ ዮርዳኖስ እስከ 12ኛ ክፍል በሞግዚት ድጋፍ የተማረች መሆኑን ጠቅሰው እንደምትችል መታየት አለበት ብዬ አራት ዓመት በዩኒቨርሲቲ አብሬያት ዘልቀናል ብለዋል፡፡ አትችልም የተባለች ልጅ ለዚህ በመብቃቷ ትልቅ ደስታ እንደተሰማቸው ጠቅሰው፤ የእርስዋ ብርታት እንደ ልጃቸው ቤት ለተዘጋባቸው ልጆች አርአያ የሚሆን መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ መኖሪያ ቤታቸው ከዮኒቨርሲቲው ራቅ ያለ በመሆኑ ጠዋት 12 ሰዓት ተነስተው ለአራት ዓመታት ልጃቸውን ወደ ትምህር ገበታዋ በዊልቸር በማመላለስ ለምረቃ ያበቁት እናት ዛሬ ደስታቸው እጥፍ ድርብ ሆኖ ተመልክተናል። ዘገባው የፕሬስ ድርጅት ነው!!

ጠቃሚ መረጃ የአጥንት መሳሳት (Osteoporosis) ምንድን ነው? -Osteoporosis የምንለው የሰውነታችን የአጥንት መሳሳት ችግር ሲሆን የአጥንት የሚነራል ክምችት (Bone mineral density) በእጅጉ እንዲቀንስ የሚያደርግ ችግር ነው። በአለም ላይ በየአመቱ በሚሊዮን የሚቆጠር ህዝብ በዚህ ችግር ተጠቂ ነው። -አጥንቶቻችን ያለማቋረጥ ሊሰባበሩ የሚችሉ ከዛም በምትካ አካል ነው። ነገር ግን አዲስ አጥንት መተካት ሳይችል ሲቀር የአጥንት መሳሳት ሊያመጣ ይችላል። ማንን ያጠቃል? -የአጥንት መሳሳት ሴቶችም ወንዶችም ላይ ሊከሰት የሚችል በተለይም እድሜያቸው ገፋ ያሉ ሴቶች ላይ እና ከማረጥ በዃላ (post menopause) ፣ እድሜ እየገፋ ሲሄድ የEstrogen hormone እየቀነሰ ስለሚሄድ ፣ ወንዶች ላይ ደግሞ የtestesretone hormone ማነስ መንስኤ ሊሆኑ ይችላሉ ምክንያቱ ደግሞ እነዚህ hormones ለአጥንት መጠንከር አስፈላጊ ስለሆኑ ነው። ለአጥንት መሳሳት የሚያጋልጡን ተጨማሪ ነገሮችስ? -የተመጣጠነ ምግብ እጥረት (Malnutrition) -መድሀኒቶች ለምሳሌ Corticosteroid የምንላቸው ለቀላሉም ለከባዱም ህመም በተደጋጋሚ የምንወስዳቸው ማስታገሻዎች ፣ ለአስም የሚወሰዱ, በተጨማሪ Anticonvulsant የምንላቸው የሚጥል በሽታ መድሀኒቶች -ሲጋራ ማጨስ ፣ አልኮል መጠጥ -የኩላሊት ፣ የጉበት ችግር ፣ የአንጀት መቆጣት ችግር ምልክቶቹስ? -በአብዛኛው ጊዜ የአጥንት መሳሳት ስበራት እስኪኖር ድረስ ምልክት ላያሳይ ይችላል። -ምልክት የሚያሳይ ከሆነ አጥንት አካባቢ የህም ስሜት ፣ የቁመት መቀነስ(height loss) የሚያመጣውስ ችግር? - በመውደቅ ወይም በግጭት አንዳንዴ ጎንበስ ስንል እንኳን የአጥንት መሰበር በተለይም የጀርባ አከርካሪት እና የዳሌ አጥንት ስብራት በቀላሉ መሰበር (Hip fracture) እሰከ የእለት ከእለት አንቅስቃሴ ማገድ ድረስ፣ሊያደርስ ይችላል። ይህ ሲሆን ደግሞ የሰውነት ክብደት መጨመር ከዛም ከውፍረት መጨመር ጋር ተያይዞ ለስኳር ፣ ለልብ በሽታ ተጋላጭነት ይጨምራል። -የአከርካሪ እና የዳሌ አጥንት ስብራት እሰከ ሞትም ሊያደርስ ይችላል። እንዴት መከላከል እንችላለን? -በቂ የሆነ የፀሀይ ብርሀን ማግኘት Vitamin D የምናገኝበት ስለሆነ እና Vitamin D ደግሞ ለአጥንት ጥንካሬ በጣም ወሳኝ እና ዋነኛው ነገር ነው -የተመጣጠነ በካልሽየም የበለፀጉ ምግቦችን መመገብ ለምሳሌ ወተት እና የወተት ተዋፅኦ ፣ የአሳ ምርቶች እንዲሁም በzinc ፣ magnesium ፣ የበለፀጉ ምግቦች ፣ የብርቱካን ጭማቂ -በቂ የአካል በቃት እንቅስቃሴ ማድረግ -ተመጣጣኝ የሰውነት ክብደት እንዲኖረን ማድረግ -ቡና እና ጨው አለማብዛት ምክንያቱም ካልሽየም በብዛት በሽንት እንዲወጣ ስለሚያደርጉ የአጥንት መሳሳት እንዴት ማረጋጋጥ እንችላለን? -የአጥንት ሚንራል ክምችት በcentral dual-energy x-ray absorbitometry (DXA) ታይቶ መረጋገጥ ይችላል። ህክምናውስ? -አጥንት እንዲደራጅ እና የስብራት ተጋላጭነት አንዲቀንስ የሚያደርጉ መድሀኒቶች መስጠት የአጥንትን የሚነራል ክምችት ሙሉ በሙሉ መመለስ ባይቻልም በተወሰነ መለኩ መመለስ ይችላል። -ያረጡ ሴቶች ላይ Estrogen የመተካት ህክምና። (ጋንዲ መታሰቢያ ሆ/ል)