ታሪካዊ ፎቶዎች 📷 📼
Open in Telegram
ይህ የታሪካዊ ፎቶዎች ኦፊሻል ቻናል ነው ታሪክን መዘከር ትልቅነት ነው ትውልድንም ያንፃል ‼️ Officeal channel 📡 》t.me/ @Tarikawi_potowech https://t.me/+3SO18mqWX_tiOWE0 #የጦር_ሜዳ_ውሎ https://t.me/joinchat/AAAAAFUFiN1N7T13DEKhAQ 👉 ለአስተያየትዎ @Eyoha_Bot
Show more735
Subscribers
+124 hours
-17 days
+3530 days
Posts Archive
☝️ የኢትዮጵያ ኢምፔሪያል አዛዥ ራድ አድሚራል እስክንድር ደስታ (የባህር ኃይል)
ከውጭ አገር መሪዎች ጋር ቀኑም 1950ዎቹ መጨረሻ ነበር
ከ 110 ዓመት በፊት ከእቴጌ ጣይቱ ብጡል የተፃፈ ደብዳቤ ፤
የተላከ ከእቴጌ ጣይቱ ብርሃነ ዘኢትዮጵያ።
ይድረስ ከማህበረ ዲር ሥልጣን ደብረገነት ኢየሩሳሌም። እንዴት ሰንብታችኋል እኔ እግዚአብሔር ይመሰገን ደህና ነኝ።
እናንተ ብትስማሙ እርስ በርሳችሁ ብትፋቀሩ አንድነታችሁን ብታጸኑ ይሻልል እንጂ ትግሬ የብቻው ነው ሸዋ የብቻው
ነው ቢገምድር ጎጃም የብቻው ነው እያላችሁ ጎሣ እየለያችሁ ብትጣሉ ምን
ትረባላችሁ።
እኛስ በእየሩሳሌም ነገር ይህንን ያህል መድከማችን ያንን ያህል ብር ባንክ አግብተን የዚያን ወለድና ለቤቱ የሚወጣውን ክራይ መስጠታችን እንዳትቸገሩ የሰው ፊት እንዳታዩ ያንን እያሰባችሁ ለኛም የጌታችንን ፆም ከፈሰሰበት ላይ ዳዊት እንድትደግሙልን እንድታዝኑልን እና እናንተም ፩ ነታችሁ
እንዲፀና ብለን ነው እንጂ ገንዘቡ ተርፎ ባገራችን በኢትዮጵያ የምንሰጠው ሰው
አጥተን አይደለም።
አሁን ስለ እግዚአብሔር ብላቹ እናንተ እርስ በራሳችሁ ተፋቀሩ ለኛም ዳዊት ድገሙልን እዘኑልኝ። ሳትቸገሩ እንዴት የድፍን አውሮፓ መሳለቂያ ትሆናላችሁ።
አሁንም ይኸው እማሆይ ወለተ ተክሌ መቃብሬ ከእዚያ ይሁን ብላ መጥታለችና አደራችሁን በምኑም በምኑም ነገር እንዳተስቀይሟት እንግዲህ ሷ እንዲህ አደረጉኝ ብላ የላከችብኝ እንደሆነ እናንተን እጥላችኋለሁ እኔንም እንዳታስቀይሙኝ። ፩፻፬ ዓመተ ምህረት አዲስ አበባ ከተማ ተፃፈ።
www.Ethiopia History Archive Website Project
@Tarikawi_fotowech
ከ 110 ዓመት በፊት ከእቴጌ ጣይቱ ብጡል የተፃፈ ደብዳቤ ፤
የተላከ ከእቴጌ ጣይቱ ብርሃነ ዘኢትዮጵያ።
ይድረስ ከማህበረ ዲር ሥልጣን ደብረገነት ኢየሩሳሌም። እንዴት ሰንብታችኋል እኔ እግዚአብሔር ይመሰገን ደህና ነኝ።
እናንተ ብትስማሙ እርስ በርሳችሁ ብትፋቀሩ አንድነታችሁን ብታጸኑ ይሻልል እንጂ ትግሬ የብቻው ነው ሸዋ የብቻው
ነው ቢገምድር ጎጃም የብቻው ነው እያላችሁ ጎሣ እየለያችሁ ብትጣሉ ምን
ትረባላችሁ።
እኛስ በእየሩሳሌም ነገር ይህንን ያህል መድከማችን ያንን ያህል ብር ባንክ አግብተን የዚያን ወለድና ለቤቱ የሚወጣውን ክራይ መስጠታችን እንዳትቸገሩ የሰው ፊት እንዳታዩ ያንን እያሰባችሁ ለኛም የጌታችንን ፆም ከፈሰሰበት ላይ ዳዊት እንድትደግሙልን እንድታዝኑልን እና እናንተም ፩ ነታችሁ
እንዲፀና ብለን ነው እንጂ ገንዘቡ ተርፎ ባገራችን በኢትዮጵያ የምንሰጠው ሰው
አጥተን አይደለም።
አሁን ስለ እግዚአብሔር ብላቹ እናንተ እርስ በራሳችሁ ተፋቀሩ ለኛም ዳዊት ድገሙልን እዘኑልኝ። ሳትቸገሩ እንዴት የድፍን አውሮፓ መሳለቂያ ትሆናላችሁ።
አሁንም ይኸው እማሆይ ወለተ ተክሌ መቃብሬ ከእዚያ ይሁን ብላ መጥታለችና አደራችሁን በምኑም በምኑም ነገር እንዳተስቀይሟት እንግዲህ ሷ እንዲህ አደረጉኝ ብላ የላከችብኝ እንደሆነ እናንተን እጥላችኋለሁ እኔንም እንዳታስቀይሙኝ። ፩፻፬ ዓመተ ምህረት አዲስ አበባ ከተማ ተፃፈ።
WWW.Ethiopia History Archive Website Project
@Tarikawi_fotowech
እዚህ በምስሉ ላይ የሚታዩትን የጦር አዛዥ ስማቸውን እና አመተ ምህረቱን ቀድሞ የመለሰ የ 100 ሞባይል ካርድ አዘጋጅተናል።
@Tarikawi_fotowech
የመጀመሪያው የድሬዳዋ ከተማ አስተዳዳሪ
ክቡር አቶ መርሻ ናሁሰናይ ከባለቤታቸው ወይዘሮ ትደንቂያለሽ መክብብ እና ከልጆቻቸው ጋር
@Tarikawi_fotowech
ነሃሴ 20 ቀን 1967 ዓ.ም
ተረኛ አልባሻቸው ስለነበርኩ ከንጉሱ ማደሪያ ለማደር ስሄድ ሻለቃ ዳንኤል አስፋው ለዛ ቀን ማደሬ እንደማያስፈልግ ነገረኝ፡፡
ወደ ንጉሱ ቀርቤ የተባለውን ስነግራቸው፣ ንጉሱ ተንበርክከው እንባቸውን እየጠረጉ፣ አይ አንቺ ኢትዮጵያ! እውነት በድለንሻል? አልደከምንልሽም? ብለው እምባቸውን
ፈነጠቁ፡፡
እኔም አማራጭ ስላልነበረኝ ጌታዬን ትቼ ወደ ቤቴ ሄድኩ፡፡ ንጉሱ ሞተው የተገኙ
እለት የመኝታ ክፍላቸው የመድሀኒት ጠረን ይሸት ነበር፡፡ በንጉሱ አንገት አካባቢ ለአንገት ማሰሪያ የሚያገለግል ፋሻ ተቀምጦ ነበር፡፡ ንጉሱ የተገደሉት ነሃሴ 20 ቀን 1967 ዓ.ም ሲሆን የተቀበሩት በማግስቱ ነሃሴ 21 ቀን 1967 ዓ.ም ነው፡፡
👉 ግድያው የተፈጸመው ከደብረብርሃን የመጣውን ልዩ ጦር በሚመራው በሻለቃ
ዳንኤል አስፋው አማካኝነት ነው፡፡ ንጉሱ ሰመመን አምጪ መድሃኒት በአፍንጫቸው እንዲያሸቱ ከተደረገ በኋላ በትራስ ታፍነው ተገድለዋል፡፡ ንጉሱን እንዲያፍን የታዘዘው ወታደር ህሊናው እምቢ ብሎት በመርበትበቱ፣ እራሱ ሻለቃ ዳንኤል አፈናውን ፈጽሞታል፡፡
ነሃሴ 21 ቀን 1967 ዓ.ም የሬሳ ሳጥንና የከፈን ጨርቅ እንዳቀርብ ታዝዤ
ሰጥቻለሁ፡፡ በ7 ሰአት ላይ በሻለቃ ዳንኤል ትእዛዝ 4 ጉርጓዶችን በ3፣ በ3 ሜትር አስቆፍሬ፣ በኮንክሪት ዘግቻለሁ፡፡ በአጭር ጌዜም በጉርጓዶቹ ላይ ቤት ተሰራ፡፡
ኢህአዲግ ሲገባ ኮሎኔል ሲለሺ መኩሪያ በሰጡት ጥቆማ፣ ከነዚሁ ጉርጓዶች
የንጉሱ አጽም ተገኝቶ ወጣ፡፡" - የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን አሟሟት
በማስመልከት ከተሰጡ ምስክርነቶች
Peter Marlow Photographs/Pitt Rivers Museum/Oxford
University/Exhibition 2010:
https://www.prm.ox.ac.uk/event/the-burial-of-emperor-haile-
selassie
Nile Perch at River Baro/Gambella in the late 1960s/early
1970s G.C
ጋምቤላ/ባሮ - 1960ዎቹ
http://www.ebay.com/itm/a-vintage-post-card-nile-
perch-baro-river-ethiopia-70s-E30-/231427627516?has
h=item35e22959fc:g:bYIAAOxykUZTfXwN
@Tarikawi_fotowech
Repost from ታሪካዊ ፎቶዎች 📷 📼
(ኢሕአፓ) የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ ቅስቀሳና ሰላማዊ ሰልፍ (በ 1968/69 ዓ.ም)
በሰልፉ ላይ የወጡት መፈክሮች:-
- ኃይሌ ፊዳ ፣ ሠናይ ልኬና ቡችሎቻቸው ይሠቀሉ
- በኤርትራ ህዝብ ላይ አንዘምትም !!
- ብሔራዊ ሀብት የአድሃሪያን ዋሻ ነው
ዶ/ር ሃይሌ ፊዳ የመኢሶን (የመላው ኢትዮጵያ ሶሻሊስት ንቅናቄ) ፓርቲ መሪ
ሲሆን ዶ/ር ሰናይ ልኬ ደግሞ የወዝሊግ ሊቀመንበር ነበር። ሁለቱም የደርግ አጋሮችና ርዕዮተ ዓለም አራማጆች የነበሩ ናቸው።
@Tarikawi_fotowech
Repost from ታሪካዊ ፎቶዎች 📷 📼
ኢሠፓ (የኢትዮጵያ ሰራተኞች ፓርቲ )
የኢትዮጵያ ሠራተኞች ፓርቲ (ኢሠፓ) በአዲስ መልክ ወደ ሀገሪቷ የፖለቲካ
መድረክ እየመጣ ነው አደራጆቹ የፓርቲውን መተዳደሪያ ደንብ እና ፕሮግራም ለሚመለከተው ክፍል አቅርበዋል።
@Tarikawi_fotowech
Repost from ታሪካዊ ፎቶዎች 📷 📼
👉 አቶ አባይ ፀሐዬ
👉 የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ (ለገሠ)
👉 አምባሳደር ብርሃነ ገብረክርስቶስ
👉 አምባሳደር ስዩም መስፍን
( ግሪክ - አቴንስ )
ሁሌም በሰው እና በመኪና የምትጨናነቀው ፒያሳ በ1950ወቹ መጀመርያ አካባቢ
ሞህሙድ ሙዚቃ ቤት ጠብቂኝ ይባል ነበር ድሮ
@Tarikawi_fotowech
ጎንደር ከ 1957 ዓ.ም እስከ 1965 ዓ.ም ድረስ
Reception of the Patriarch of Cairo Abba Shenouda/Pope
Shenouda III of Alexandria at the Holly Trinity Debre Birhan
Selassie Cathedral in Gondar; Meskel Celebration; the restored
Castle of Yohannes within the royal enclosure of the 16th century palace of Emperor Fasiledes; the Castle of Empress Mentiwab within the royal enclosure of Fasil Ghibbi; the Castle of Bakaffa; People receiving palms during a Palm Sunday Beautiful pictures you may have never seen before
United States National Museum of African Art/Smithsonian
Online Virtual Archives/Marilyn Heldman Photographs:
https://sova.si.edu/details/EEPA.2013-013#ref254
@Tarikawi_fotowech
በኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት
የአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት።
ተሽከርካሪ መኪና ለመንዳት ደንበኛ ፈተና ተደርጎ ችሎታ ከተመሰከረ በኋላ
የተሰጠ የመንጃ ፈቃድ።
(የትራንስፖርት አዋጅ ፪ኛ ዓመት ቁጥር ፯ ነጋሪት ጋዜጣ) ሶስተኛ ማዕርግ 3 የተሽከርካሪው ዓይነትና ሥራው የናፍታ ካሚዮን በ 1943 ዓ.ም
* በምስሉ ላይ የሚታየው በስተግራ በኩል የመንጃ ፍቃዱ የፊተኛው ገፅ ሲሆን በስተቀኝ በኩል የውስጠኛው ገፅ ነው።
@Tarikawi_fotowech
Repost from የጦር ሜዳ ውሎ 💪🏽
ድንቅ የጦር ሜዳ ውሎ ታሪክ
በኮ/ል ጋዲሳ ጉማ
"እኔ፥ ምትኩ ሙለታ፥ ጌታቸው ከንፈሬ እና ሚካዔል ሣህለ ማርያም
አይሮፕላኖችን እንድናመጣ ወደ ስዊድን አገር ተላክን። ስዊድን ሆቴል አድረን
ጥዋት ለቁርስ ስንነሳ ሆቴሉ በር ላይ ሰው ሞልቷል። ምንድን ነው ብለን
ስንጠይቅ እናንተን ለማየት ነው ተባልን። ጥቁር አይተው አያውቁም።"
@Yetormida_welo
