en
Feedback
የጦር ሜዳ ውሎ 💪🏽

የጦር ሜዳ ውሎ 💪🏽

Open in Telegram

👉 የቻናሉ መከፈት ዋና አላማው ታሪክ የሚያጠፋውን ትውልድ በመቃወም ታሪክ የሚሰራ ትውልድ መገንባት ነው!! 🗣 Official Channel 👇🏽 📡 https://t.me/joinchat/AAAAAFUFiN1N7T13DEKhAQ Group Chanel 👥 @yetormida_welo 》》t.me/ @Tarikawi_fotowech 👉 ለአስተያየዎ @Eyoha_Bot ላይ ይፃፉልን

Show more
461
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
February '23
February '23
+4
in 0 channels
January '23
+8
in 0 channels
Get PRO
December '22
+15
in 0 channels
Get PRO
November '22
+9
in 0 channels
Get PRO
October '22
+12
in 0 channels
Get PRO
September '22
+33
in 0 channels
Get PRO
August '22
+10
in 0 channels
Get PRO
July '22
+2
in 0 channels
Get PRO
June '22
+8
in 0 channels
Get PRO
May '22
+11
in 0 channels
Get PRO
April '22
+14
in 0 channels
Get PRO
March '22
+8
in 0 channels
Get PRO
February '22
+8
in 0 channels
Get PRO
January '22
+28
in 0 channels
Get PRO
December '21
+36
in 0 channels
Get PRO
November '21
+14
in 0 channels
Get PRO
October '21
+30
in 0 channels
Get PRO
September '21
+56
in 0 channels
Get PRO
August '21
+91
in 0 channels
Get PRO
July '21
+24
in 0 channels
Get PRO
June '21
+15
in 0 channels
Get PRO
May '21
+39
in 0 channels
Get PRO
April '21
+38
in 0 channels
Get PRO
March '21
+31
in 0 channels
Get PRO
February '21
+27
in 0 channels
Get PRO
January '21
+366
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
24 February0
23 February+1
22 February0
21 February0
20 February0
19 February0
18 February0
17 February0
16 February0
15 February0
14 February0
13 February0
12 February0
11 February0
10 February0
09 February0
08 February0
07 February+1
06 February+1
05 February0
04 February0
03 February0
02 February+1
01 February0
Channel Posts
በህዳር 14 ቀን የተረሸኑት ባለስልጣናት የተለያየ የክስ ቻርጅ የቀረበባቸው ነበር በዚህም መሰረት ሀ. ‹‹ኃይላቸውን ከህግ አግባብ ውጭ ተጠቅመዋል›› በሚል ውንጀላ የተገደሉ ባለስልጣኖች ባለስልጣኖች (‹‹Gross Abuse of Power››) 1. ፀሃፌትዕዛዝ ጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተወልድ 2. ልዑል አስራተ ካሳ 3. እንዳልካቸው መኮንን 4. ራስ መስፍን ስለሺ 5. አቶ አበበ ረታ 6. ሌተናል ኮሎኔል ታምራት ይገዙ 7. አቶ አካለወርቅ ሀብተወልድ 8. ዶ/ር ተስፋዬ ገብረእግዚዕ 9. አቶ ሙላቱ ደበበ 10. ደጃዝማች ሰለሞን አብርሃ 11. ደጃዝማች ለገሰ በዙ 12. ደጃዝማች ሳህሉ ድፋዬ 13. ደጃዝማች ወርቅነህ ወልደአማኑኤል 14. ደጃዝማች ክፍሌ እርገቱ 15. ደጃዝማች ወርቁ እንቁሥላሴ 16. ደጃዝማች አዕምሮሥላሴ አበበ 17. ደጃዝማች ከበደ ዓሊ ወሌ ለ. ‹‹ስልጣናቸውን ከህግ አግባብ ውጭ ተጠቅመዋል›› በሚል ውንጀላ የተገደሉ ባለስልጣኖች (‹‹Gross Abuse of Authority››) 1) አቶ ነብየልዑል ክፍሌ 2) ኮሎኔል ሰለሞን ከድር 3) አፈንጉስ አበጀ ደባልቅ 4) አቶ ይልማ አቦዬ 5) አቶ ተገኝ የተሻወርቅ 6) አቶ ሰለሞን ገብረማርያም 7) አቶ ኃይሉ ተክሉ ብላታ አድማሱ ረታ 9) ልጅ ኃይሉ ደስታ 10) ፊታውራሪ አመዴ አበራ 11) ፊታውራሪ ደምስ አላምረው 12) ፊታውራሪ ታደሰ እንቁሥላሴ 13) ሌተናል ጄኔራል አብይ አበበ 14) ሌተናል ጄኔራል ከበደ ገብሬ 15) ሌተናል ጄኔራል ድረሴ ዱባለ 16) ሌተናል ጄኔራል አበበ ገመዳ 17) ሌተናል ጄኔራል ይልማ ሽበሽ 18) ሌተናል ጄኔራል ኃይሌ ባይከዳኝ 19) ሌተናል ጄኔራል አሰፋ አየን 20) ሌተናል ጄኔራል በለጠ አበበ 21) ሌተናል ጄኔራል ኢሳያስ ገብረሥላሴ 22) ሌተናል ጄኔራል አሰፋ ደምሴ 23) ሌተናል ጄኔራል አበበ ኃይለማርያም 24) ሜጀር ጄኔራል ስዩም ገድለጊዮርጊስ 25) ሜጀር ጄኔራል ጋሻው ከበደ 26ኛ) ሜጀር ጄኔራል ታፈሰ ለማ 27) ሪር አድሚራል እስክንድር ደስታ 28) ብርጋዴር ጄኔራል ሙሉጌታ ወልደዮሐንስ 29) ብርጋዴር ጄኔራል ግርማ ዮሐንስ 30) ኮሎኔል ያለምዘውድ ተሰማ 31) ኮሎኔል ጣሰው ሞጆ 32) ኮሎኔል ይገዙ ይመኔ 33) ሻለቃ ብርሃኑ ሜጫ 34) ካፒቴን ሞላ ዋቅኬኔ ሐ. ‹‹የእርስ በእርስ ጦርነት ለመቀስቀስ በተሸረበ ደባ እና ታላቁን የለውጥ እንቅስቃሴ ለመግታት በተደረገ አሻጥር›› በሚል ክስ ተወንጅው የተገደሉ 1. ካፒቴን ደምሴ ሽፈራው 2. ካፒቴን በላይ ጸጋዬ 3. ካፒቴን ወልደዮሐንስ ዘርጋው 4. ላንስ ኮርፖራልተክሉ ኃይሉ 5. ወታደር በቀለ ወልደጊዮርጊስ መ). ‹‹ለመስሪያ ቤት የተገባን ቃል ኪዳን ባለመጠበቅ እና በጦር ኃይሉ ውስጥ ክፍፍል ለመፍጠር ሙከራ ማድረግ›› በሚል ክስ ተወንጅለው የተገደሉ 1). ሌተናል ጄኔራል አማን ሚካኤል አንዶም 2). ሌቴናል ጄኔራል ተስፋዬ ተክሌ 3). ጁኒየር ኤርክራፍትማን ዮሐንስ ፍትዊ ✍ ገዳዮቹ... በየትኛውም ስርአት ወታደር የበላይ አለቃውን ትዕዛዝ የመቀበል ሙያዊ ግዴታ እንዳለበት የታወቀ ቢሆንም አንዳንድ ግዜ ደግሞ ከሙያዊ ግዴታ ይበልጥ የህሊና ጥያቄን ማዳመጥ ተገቢ ሳይሆን አይቀርም። ሊገድል የመጣን መግደል አንድ ነገር ሆኖ እራሱን ለመከላከል እድሜ ጤናና ሁኔታው ያልፈቀደለትን ፡ የፊጥኝ በካቴና ታስሮ ለነብሱ የሚማጸንን ሰው በመግደል ውስጥ ግን ያለውን የህሊና እረፍት ማጣት እራሳቸው ገዳዮቹ እድሜ ሰጥቷቸው የመሰከሩትን የህሊና ስብራት በብዛት አድምጠናል። በዛች ቅዳሜ ምሽት የመንግስቱ ኃይለማርያም የግድያ አስፈጻሚ በሆነው በኮሎኔል ዳንኤል አስፋው ትእዛዝ ተቀባይነትና በሻለቃ ጌታቸው ሺበሺ የቡድን መሪነት ሀምሳ ዘጠኙ ሰዎች የመትረየስ ጥይት ተርከፍክፎባቸው ቅሪተ አካላቸው እንዳይገኝ በመቃብራቸው ላይ ኖራ ተነስንሶበታል። የግድያውን ሁኔታ ያጠናው ልዩ አቃቤ ህግ እንደመሰከረው ከሆነ በእለቱ በጠቅላላው 393 ጥይቶች መተኮሳቸው ተረጋግጧል። (በአማካይ ለአንድ ሟች 7 ጥይት እንደማለት ነው) ይህ ቁጥር በደርግ አባላቱ ብቻ የተተኮሰውን የሚያካትት እንጂ በሌሎች ወታደሮች የተተኮሰውን አይጨምርም። ለደርጉ ሃላፊዎች አዲስ አበባ ወህኒ ቤት ግቢ (በተለምዶአዊ አጠራሩ ከርቸሌ በሚባለውና በአሁን ግዜ የአፍሪካ ህብረት ዋና ጽህፈት ቤት በተገነባበት ግቢ) ውስጥ በአካል ተገኝተው የአፄ ኃይለስላሴን ጄኔራሎችና ሚኒስትሮች ተኩሰው የገደሉ የደርግ አባላት ስም ዝርዝርና የተኮሱት ጥይት መጠን በሻለቃ ጌታቸው ሺበሺ ሪፖርት በተደረገው መሠረት፣ - ሻለቃ ጌታቸው ሺበሺ - 43 ጥይት - ሻምበል ተፈራ - 32 ጥይት - ሻምበል ኃይሌ መለስ - 25 ጥይት - ባሻ ተፈራ ጅፋር - 60 ጥይት - 50 አለቃ በቀለ ደጉ - 32 ጥይት - ፒቲ ኦፊሰር ሚካኤል - 25 ጥይት - 50 አለቃ ዳምጤ - 16 ጥይት - ወታደር ደጀኔ አ/አገኘሁ - 40 ጥይት - ወታደር ገብረ ጊዮርጊስ ብርሃኑ - 50 ጥይት - ሻለቃ ባሻ ለማ ኩምሳ - 7 ጥይት - ምክትል አስር አለቃ ግርማ አየለ-3 ጥይት ተኩሰው ርሸናውን በትዕዛዙ መሰረት መፈጸማቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ✍ ለግድያው የተሰጠው ደረሰኝ። የግድያውን አፈጻጸም አስገራሚ ከሚያደርጉ ነገሮች አንዱ ለግድያው የተሰጠው ደረሰኝ ነው። በዛች እለት በትዕዛዙ መሰረት ሰዎቹ ተገደሉ። የወህኒ ቤቱ አባል ሻምበል ነጋሽ ማሞ የ60 ሰዎችን አስክሬን ተረክቦ ደረሰኝ ሰጠ። 60ኛው በዛው ዕለት ከደርጉ ጋር ተዋግተው እራሳቸውን የገደሉት የጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግ የመጀመሪያው ሊቀመንበር የነበሩት የሌ/ጄኔራል አማን አምዴ ሚካኤል አንዶም አስክሬን ነበር። ይህ ከሆነ እነሆ ዛሬ 48 ዓመት አስቆጥሯል !!! ህዳር 14 ቀን 1967 ዓ.ም 👉 ጀኔራሎቹ @Tarikawi_fotowech @yetormida_welo

2
ህዳር 14 ቀን 1967 ዓ.ም..... ጸለምት ቅዳሜ !!! ለኢትዮጵያ ፖለቲካዊ አለመግባባቶች መግደል መፍትሄ እንደሆነ ሰይጣናዊ ምክር የተቀበልንበት ለሀገር ለወገን ያገለገልከው ግልጋሎት በግልብ ፖለቲከኞች ዘንድ ሚዛን እንደማይደፋ የተረጋገጠበት በጥቂቶች እጅ በትረ ስልጣን ከወደቀ ሀገርን ሊያጠፉ እምደሚችሉ ያሳዩበት ስልሳ ሰዎችን በአንድ ሰው ፊርማ መግደል እንደሚቻል ያየንበት በአንዳንድ ጸሀፍት ዘነድ “ ጸለምት ቀዳሚት” #ጨለማዋ_ቅዳሜ ተብላ የምትጠራዋ ህዳር 14 1967 በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ጥቁር ነጥብ አኑራ እንርሳሽ ቢሏት የማትረሳ የጥፋቶች ሁላ መነሻ ሆና ተመዝግባለች። ህዳር 14 ቀን 1967 ዓ.ም ምሽት ላይ ከሰአታት በፊት በመኖሪያ ቤታቸው በተኩስ ልውውጥ የተገደሉትን ሌፍተናንት ጀነራል አማን አምዶምን ጨምሮ ስልሳ የቀድሞው መንግስት ሹማምንት ተጨፈጨፉ፡፡ የብዙ ሺህ አመታት ዘውዳዊ መንግስትም ተገርስሶ በወታደራዊ ጁንታ ተተካ፡፡ ከዚያም ወዲያማ ህዳር 14 ያስጀመረች የክፋት ቡራኬ ለአስራ ሰባት ተጋግሞና ግድያን የፖለቲካ ልዩነት ማሸነፊያ አድርጎ ከረመ፡፡ ሃገራችንን ለብዙ የፖለቲካና የማህበራዊ ምስቅልቅል የዳረገች ይህች ክፉ ቀን ቀደም ብላ ታስባ የታሰበባትና የተጠናች ውሳኔ ነች? ወይስ በሂደት በደርጉ አባላትና እና መሪዎቹ በስሜታዊነት ድንገት የተፈጸመች? እርግጥ ይህ ጉዳይ ዛሬም ቢሆን አወዛጋቢነቱ ያበቃለት አጀንዳ አልሆነም። በህይወት የተረፉም ይሁኑ አንዳንድ የታሪክ ምሁራን በአንድ አይነት ሀሳብ ለመስማማት አልተቻላቸውም። አንዳንዶች በተለይ የወቅቱ ምክትል ሊቀመንበር ሻለቃ መንግስቱ ኃይለማርያምን ለግድያው ዋና ተጠያቂ በማድረግ “ከመነሻው ጀምሮ ሲያውጠነጥኑት የነበረ ሴራ ውጤት ነው” ሲሉ ሌሎች ደግሞ “እጅ በማውጣት የግድያውን ውሳኔ ሲያጸድቁ የነበሩ የደርጉ አባላት ስሜታዊ ውሳኔ ነው” ይላሉ። ሌተና ኮሎኔል ፍስሀ ደስታ "እኛና አብዮቱ"በተሰኘው መጽሀፋቸው እንደመሰከሩት ከሆነ ግን የደርጉ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር ሻለቃ መንግስቱ በጻፉት የትእዛዝ ደብዳቤ የስልሳዎቹ ግድያ መፈጸሙን ይመሰክራሉ። እንደ ኮሎኔል ፍስሀ ደስታ አባባል ግድያው ህዳር 14 ሊፈጸምና ህዳር 14 ደርጉ ተሰብስቦ ሊወስን አንድ ቀን ቀደም ብሎ ህዳር 13 ቀን እጃቸውን የሰጡ የቀድሞ መንግስት ሹማምንት ላይ እርምጃ ይወሰድባቸው የሚል የምክትል ሊቀመንበሩ የሻለቃ መንግስቱ ኃይለማርያም ፊርማ ያረፈበት የትእዛዝ ደብዳቤ በአንድ አጋጣሚ እጃቸው ገብቶ መመልከታቸውን መስክረዋል፡፡ ከጥቂት ግዜ በኋላም ታደሰ ቴሌ ሳልቫኖ በመጽሃፋቸው የደብዳቤውን ኮፒ ይፋ አድርገዋል። ሻለቃ (የኋላው ፕሬዚደንት) መንግስቱ ኃይለማርያም በፊርማቸው አስደግፈው ለደርግ ጥበቃና ዘመቻ መምሪያ መኮንን( ለያኔው ዋና የግድያ አስፈጻሚያቸው) ለኮሎኔል ዳንኤል አስፋው የይረሸኑ ደብዳቤ ቀደም ብለው ልከውለታል፡፡ (ግድያው ህዳር 14 ቀን ሊፈጸም ህዳር 13 ቀን መላካቸው ለይሙት በቃ የሚሰበሰቡት የደርግ አባላት ውሳኔውን ከማስተላለፋቸው በፊት መሆኑን ልብ ይሏል)፡፡ ግደል የተባለውን ያለማመንታት በመፈጸም የሚታወቀው ኮሎኔል ዳንኤልም በምላሹ የደብዳቤው ግርጌ ላይ "በትዕዛዙ መሰረት እንተገብራለን" በማለት የአለቃውን ትእዛዝ ለመፈጸም እንደማያወላዳ አረጋግጧል። ✍ ቀዳሚው ሰለባ ኮዳ ትራሱ.... ደርጎች በህዝቡም በሰራዊቱም ዘንድ እውቅና እንደሌላቸው በሚገባ ስለተረዱ ነበር በቀዳማዊ ኃይለስላሴ መንግስት ውስጥ ጉልህ ጀብድ በመፈጸም የሚታወቁትንና "ኮዳ ትራሱ"በሚል። ተቀጽላ የሚታወቁትን ሌፍተናንት ጀነራል አማን አምዶምን ሊቀመንበር እንዲሆኗቸው የጠየቋቸው።ከፖለቲከኛነትና ከዲፕሎማትነት ይልቅ የቆፍጣና ወታደርነት ባህሪያቸው እንደሚያዘነብልባቸው አብረዋቸው የሰሩ ሰዎች የሚመሰክሩላቸው ጀነራል አማን: ከደርጎች ጋር ተስማምተውና ተግባብተው የሊቀመንበርነታቸውን ወንበር ከሁለት ወር በላይ ሊቆዩበትት አልተቻላቸውም ነበር። ከሻለቆቹና ከሻምበሎቹ ጋር መግባባት የተሳናቸው ሌፍተናንት ጀነራል አማን አምዶም ነገር አለሙን ትተው ጦር ሀይሎች አካባቢ ይገኝ ከነበረው መኖሪያቸው ውስጥ መቀመጥን መረጡ። በጦሩ ዘንድ ያላቸውን ተወዳጅነት ተጠቅመው መልሰው ሊያጠቁን ይችላሉ ብለው የሰጉት ደርጎችም ገዳይ ቡድን ቤታቸው ድረስ ልከውባቸውና ለረዥም ሰአት ከጀነራሉ ጋር ተታኩሰው ገደሏቸው። የአማን አምዶም ግድያም ለቀሩት ሀምሳ ዘጠኝ ሰዎች ግድያ ማስጀመሪያ ፊሽካ ሆነች። እጃቸውን በሰላም ነበር የሰጡትእድሜ አግኝተው ታሪክን ለመመስከር የበቁ የደርግ ባለስልጣናት ስለ ሌሎች የቀይ ሽብር ሰማዕታት ጉዳይ እምብዛም ጸጸት ሲሰማቸው ባይታይም( ኮሎኔል መንግስቱ ሀይለማርያምን ጨምሮ) በስልሳዎቹ ላይ የተደረገው ግድያ ግን ፍጹም ስህተት እንደነበር ይመሰክራሉ። ለነገሩ ጸጸታቸው የፈሰሰ ውሀ የማያሳፍስ: የጠፋውን ጥፋት የማይመልስ ነበር፡፡ በጥይት ተደብድበው የተገደሉት ሰዎች ሀገርና ወገንን ያገለገሉና ብዙ ሊያገለግሉ የሚችሉ ምናልባትም መጠነኛ ጥፋታቸው ተቆጥሮ መጠነኛ ቅጣት ብቻ የሚገባቸው ሰዎች ነበሩ። (በስልጣን ዘመናቸው ያጠፉትን ጥፋት ለማጣራት የተቋቋመው የመርማሪ ኮሚሽን ሪፖርት የሚያረጋግጠውም ይሄንኑ ነው፡፡) የመጋቢት 1966 ህዝባዊ አመጽን ተከትሎና ከሚያዝያ አጋማሽ ወር ጀምሮ በርካታ የቀዳማዊ ኃይለስላሴ ሹማምንት ከያሉበት እየተያዙ እስር ቤት እየታጎሩ ነበር፡፡ አመጹ እየተፋፋመ ሄዶ በመጨረሻም ደርግ መስከረም 2 ቀን 1967 በትረ ስልጣኗን ሲይዝ እጁ ላይ የወደቁትን (ንጉሰ ነገስት ቀዳማዊ ኃይለላሴን እና አክሊሉ ሃብተወልድን ጨምሮ) በርካታ ሹማምንት ተገቢዉን ፍርድ እሰጣቸዋለሁ በማለት ለህዝብ ቃል ገባ፡፡ ለዚህም መርማሪ ኮሚሽን በአዋጅ ተቋቁሞ ስራዉን መስራትም ጀምሮ ነበር፡፡ ሆኖም ግን የመርማሪ ኮሚሽኑ አዝማሚያ የፈለገውን አይነት ቅጣት ማድረግ እንደማያስችለው ያወቀው የደርጉ መንግስት ፍርድን እራሱ ሊሰጥ ወሰነ፡፡ በመጀመሪያ “እርምጃ እንዲወሰድባቸው” ስማቸው የቀረበው 250 ሰዎች የነበሩ ሲሆን በመጨረሻ ቁጥራቸው ወደ 141 ዝቅ ብሎ፣ ከመካከላቸው ለግድያ የተመረጡት ባለሥልጣናት ስም ተራ በተራ እየተነበበ ድምጽ እንዲሰጥባቸው ተደረገ፡፡ በዚህም መሰረት 59 ሰዎች በጥይት ተደብድበው እንዲገደሉ በአብላጫ ድምጽ ተወሰነ። በዚያች ክፉ ቀን ብቻ... 👉 ሁለቱ ጠቅላይ ሚኒስትሮች 👉 አንዱ ልዑል 👉 አንዱ ሪር አድሚራል 👉 አስራ ሰባቱ ሚኒስትሮች 👉 አስራ አንዱ የጠቅላይ ግዛት እንደራሴዎችና የአውራጃ ገዥዎች 👉 አንዱ ገበሬ 👉 ዘጠኙ ሌፍተናንት ጀነራሎች 👉 ሶስቱ ሜጀር ጀነራሎች 👉 ሶስቱ ብርጋዴር ጀነራሎች 👉 ሶስቱ ኮሎኔሎች 👉 ሰባቱ መስመራዊ መኮንኖችና 👉 ሁለት የበታች ሹማምንት የመትረየስ ጥይት ዘንቦባቸው ተረሽነዋል። ከተረሸኑት ስልሳ ባለስልጣናት መካከል ሀምሳዎቹ ከኢጣልያ ወረራ ጀምሮ ሀገራቸውን በተለያየ መልኩ ሀገራቸውን ያገለገሉ እስከ 45 አመት የሚደርስ የአገልግሎት ዘመናቸው የሚቆጠር፣ ከእነዚህም ውስጥ 17 አርበኞች ይገኙበታል። የእድሜያቸው ነገር ሲነሳ ደግሞ በ 19 አመት የአፍላነት እድሜው ከተረሸነው አንስቶ እስከ 75 አመት የሚደርሱ አዛውንቶች የጥይት እራት ሆነዋል። 3 ወንድማማቾችና ሎሎች 2 ወንድማማቾች የወንድማቸውን ሞት እያዩ እንዲገደሉ ተደርገዋል። የሚያሰቃያቸውን ደዌ እያስታመሙ ካሉበት ሆስፒታል አልጋ ሁለት በሽተኞች ግሉኮሳቸው ተነቅሎ ተወስደው ተገድለዋል። ✍ ስልሳዎቹ...
212
3
ህዳር 14 ቀን 1967 ዓ.ም..... ጸለምት ቅዳሜ !!! 👇👇 @Tarikawi_fotowech @yetormida_welo+3
ህዳር 14 ቀን 1967 ዓ.ም..... ጸለምት ቅዳሜ !!! 👇👇 @Tarikawi_fotowech @yetormida_welo
156
4
በህዳር 14 ቀን የተረሸኑት ባለስልጣናት የተለያየ የክስ ቻርጅ የቀረበባቸው ነበር በዚህም መሰረት ሀ. ‹‹ኃይላቸውን ከህግ አግባብ ውጭ ተጠቅመዋል›› በሚል ውንጀላ የተገደሉ ባለስልጣኖች ባለስልጣኖች (‹‹Gross Abuse of Power››) 1. ፀሃፌትዕዛዝ ጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተወልድ 2. ልዑል አስራተ ካሳ 3. እንዳልካቸው መኮንን 4. ራስ መስፍን ስለሺ 5. አቶ አበበ ረታ 6. ሌተናል ኮሎኔል ታምራት ይገዙ 7. አቶ አካለወርቅ ሀብተወልድ 8. ዶ/ር ተስፋዬ ገብረእግዚዕ 9. አቶ ሙላቱ ደበበ 10. ደጃዝማች ሰለሞን አብርሃ 11. ደጃዝማች ለገሰ በዙ 12. ደጃዝማች ሳህሉ ድፋዬ 13. ደጃዝማች ወርቅነህ ወልደአማኑኤል 14. ደጃዝማች ክፍሌ እርገቱ 15. ደጃዝማች ወርቁ እንቁሥላሴ 16. ደጃዝማች አዕምሮሥላሴ አበበ 17. ደጃዝማች ከበደ ዓሊ ወሌ ለ. ‹‹ስልጣናቸውን ከህግ አግባብ ውጭ ተጠቅመዋል›› በሚል ውንጀላ የተገደሉ ባለስልጣኖች (‹‹Gross Abuse of Authority››) 1) አቶ ነብየልዑል ክፍሌ 2) ኮሎኔል ሰለሞን ከድር 3) አፈንጉስ አበጀ ደባልቅ 4) አቶ ይልማ አቦዬ 5) አቶ ተገኝ የተሻወርቅ 6) አቶ ሰለሞን ገብረማርያም 7) አቶ ኃይሉ ተክሉ ብላታ አድማሱ ረታ 9) ልጅ ኃይሉ ደስታ 10) ፊታውራሪ አመዴ አበራ 11) ፊታውራሪ ደምስ አላምረው 12) ፊታውራሪ ታደሰ እንቁሥላሴ 13) ሌተናል ጄኔራል አብይ አበበ 14) ሌተናል ጄኔራል ከበደ ገብሬ 15) ሌተናል ጄኔራል ድረሴ ዱባለ 16) ሌተናል ጄኔራል አበበ ገመዳ 17) ሌተናል ጄኔራል ይልማ ሽበሽ 18) ሌተናል ጄኔራል ኃይሌ ባይከዳኝ 19) ሌተናል ጄኔራል አሰፋ አየን 20) ሌተናል ጄኔራል በለጠ አበበ 21) ሌተናል ጄኔራል ኢሳያስ ገብረሥላሴ 22) ሌተናል ጄኔራል አሰፋ ደምሴ 23) ሌተናል ጄኔራል አበበ ኃይለማርያም 24) ሜጀር ጄኔራል ስዩም ገድለጊዮርጊስ 25) ሜጀር ጄኔራል ጋሻው ከበደ 26ኛ) ሜጀር ጄኔራል ታፈሰ ለማ 27) ሪር አድሚራል እስክንድር ደስታ 28) ብርጋዴር ጄኔራል ሙሉጌታ ወልደዮሐንስ 29) ብርጋዴር ጄኔራል ግርማ ዮሐንስ 30) ኮሎኔል ያለምዘውድ ተሰማ 31) ኮሎኔል ጣሰው ሞጆ 32) ኮሎኔል ይገዙ ይመኔ 33) ሻለቃ ብርሃኑ ሜጫ 34) ካፒቴን ሞላ ዋቅኬኔ ሐ. ‹‹የእርስ በእርስ ጦርነት ለመቀስቀስ በተሸረበ ደባ እና ታላቁን የለውጥ እንቅስቃሴ ለመግታት በተደረገ አሻጥር›› በሚል ክስ ተወንጅው የተገደሉ 1. ካፒቴን ደምሴ ሽፈራው 2. ካፒቴን በላይ ጸጋዬ 3. ካፒቴን ወልደዮሐንስ ዘርጋው 4. ላንስ ኮርፖራልተክሉ ኃይሉ 5. ወታደር በቀለ ወልደጊዮርጊስ መ). ‹‹ለመስሪያ ቤት የተገባን ቃል ኪዳን ባለመጠበቅ እና በጦር ኃይሉ ውስጥ ክፍፍል ለመፍጠር ሙከራ ማድረግ›› በሚል ክስ ተወንጅለው የተገደሉ 1). ሌተናል ጄኔራል አማን ሚካኤል አንዶም 2). ሌቴናል ጄኔራል ተስፋዬ ተክሌ 3). ጁኒየር ኤርክራፍትማን ዮሐንስ ፍትዊ ✍ ገዳዮቹ... በየትኛውም ስርአት ወታደር የበላይ አለቃውን ትዕዛዝ የመቀበል ሙያዊ ግዴታ እንዳለበት የታወቀ ቢሆንም አንዳንድ ግዜ ደግሞ ከሙያዊ ግዴታ ይበልጥ የህሊና ጥያቄን ማዳመጥ ተገቢ ሳይሆን አይቀርም። ሊገድል የመጣን መግደል አንድ ነገር ሆኖ እራሱን ለመከላከል እድሜ ጤናና ሁኔታው ያልፈቀደለትን ፡ የፊጥኝ በካቴና ታስሮ ለነብሱ የሚማጸንን ሰው በመግደል ውስጥ ግን ያለውን የህሊና እረፍት ማጣት እራሳቸው ገዳዮቹ እድሜ ሰጥቷቸው የመሰከሩትን የህሊና ስብራት በብዛት አድምጠናል። በዛች ቅዳሜ ምሽት የመንግስቱ ኃይለማርያም የግድያ አስፈጻሚ በሆነው በኮሎኔል ዳንኤል አስፋው ትእዛዝ ተቀባይነትና በሻለቃ ጌታቸው ሺበሺ የቡድን መሪነት ሀምሳ ዘጠኙ ሰዎች የመትረየስ ጥይት ተርከፍክፎባቸው ቅሪተ አካላቸው እንዳይገኝ በመቃብራቸው ላይ ኖራ ተነስንሶበታል። የግድያውን ሁኔታ ያጠናው ልዩ አቃቤ ህግ እንደመሰከረው ከሆነ በእለቱ በጠቅላላው 393 ጥይቶች መተኮሳቸው ተረጋግጧል። (በአማካይ ለአንድ ሟች 7 ጥይት እንደማለት ነው) ይህ ቁጥር በደርግ አባላቱ ብቻ የተተኮሰውን የሚያካትት እንጂ በሌሎች ወታደሮች የተተኮሰውን አይጨምርም። ለደርጉ ሃላፊዎች አዲስ አበባ ወህኒ ቤት ግቢ (በተለምዶአዊ አጠራሩ ከርቸሌ በሚባለውና በአሁን ግዜ የአፍሪካ ህብረት ዋና ጽህፈት ቤት በተገነባበት ግቢ) ውስጥ በአካል ተገኝተው የአፄ ኃይለስላሴን ጄኔራሎችና ሚኒስትሮች ተኩሰው የገደሉ የደርግ አባላት ስም ዝርዝርና የተኮሱት ጥይት መጠን በሻለቃ ጌታቸው ሺበሺ ሪፖርት በተደረገው መሠረት፣ - ሻለቃ ጌታቸው ሺበሺ - 43 ጥይት - ሻምበል ተፈራ - 32 ጥይት - ሻምበል ኃይሌ መለስ - 25 ጥይት - ባሻ ተፈራ ጅፋር - 60 ጥይት - 50 አለቃ በቀለ ደጉ - 32 ጥይት - ፒቲ ኦፊሰር ሚካኤል - 25 ጥይት - 50 አለቃ ዳምጤ - 16 ጥይት - ወታደር ደጀኔ አ/አገኘሁ - 40 ጥይት - ወታደር ገብረ ጊዮርጊስ ብርሃኑ - 50 ጥይት - ሻለቃ ባሻ ለማ ኩምሳ - 7 ጥይት - ምክትል አስር አለቃ ግርማ አየለ-3 ጥይት ተኩሰው ርሸናውን በትዕዛዙ መሰረት መፈጸማቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ✍ ለግድያው የተሰጠው ደረሰኝ። የግድያውን አፈጻጸም አስገራሚ ከሚያደርጉ ነገሮች አንዱ ለግድያው የተሰጠው ደረሰኝ ነው። በዛች እለት በትዕዛዙ መሰረት ሰዎቹ ተገደሉ። የወህኒ ቤቱ አባል ሻምበል ነጋሽ ማሞ የ60 ሰዎችን አስክሬን ተረክቦ ደረሰኝ ሰጠ። 60ኛው በዛው ዕለት ከደርጉ ጋር ተዋግተው እራሳቸውን የገደሉት የጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግ የመጀመሪያው ሊቀመንበር የነበሩት የሌ/ጄኔራል አማን አምዴ ሚካኤል አንዶም አስክሬን ነበር። ይህ ከሆነ እነሆ ዛሬ 48 ዓመት አስቆጥሯል !!! ህዳር 14 ቀን 1967 ዓ.ም 👉 ጀኔራሎቹ @Tarikawi_fotowech
1
5
ህዳር 14 ቀን 1967 ዓ.ም..... ጸለምት ቅዳሜ !!! ለኢትዮጵያ ፖለቲካዊ አለመግባባቶች መግደል መፍትሄ እንደሆነ ሰይጣናዊ ምክር የተቀበልንበት ለሀገር ለወገን ያገለገልከው ግልጋሎት በግልብ ፖለቲከኞች ዘንድ ሚዛን እንደማይደፋ የተረጋገጠበት በጥቂቶች እጅ በትረ ስልጣን ከወደቀ ሀገርን ሊያጠፉ እምደሚችሉ ያሳዩበት ስልሳ ሰዎችን በአንድ ሰው ፊርማ መግደል እንደሚቻል ያየንበት በአንዳንድ ጸሀፍት ዘነድ “ ጸለምት ቀዳሚት” #ጨለማዋ_ቅዳሜ ተብላ የምትጠራዋ ህዳር 14 1967 በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ጥቁር ነጥብ አኑራ እንርሳሽ ቢሏት የማትረሳ የጥፋቶች ሁላ መነሻ ሆና ተመዝግባለች። ህዳር 14 ቀን 1967 ዓ.ም ምሽት ላይ ከሰአታት በፊት በመኖሪያ ቤታቸው በተኩስ ልውውጥ የተገደሉትን ሌፍተናንት ጀነራል አማን አምዶምን ጨምሮ ስልሳ የቀድሞው መንግስት ሹማምንት ተጨፈጨፉ፡፡ የብዙ ሺህ አመታት ዘውዳዊ መንግስትም ተገርስሶ በወታደራዊ ጁንታ ተተካ፡፡ ከዚያም ወዲያማ ህዳር 14 ያስጀመረች የክፋት ቡራኬ ለአስራ ሰባት ተጋግሞና ግድያን የፖለቲካ ልዩነት ማሸነፊያ አድርጎ ከረመ፡፡ ሃገራችንን ለብዙ የፖለቲካና የማህበራዊ ምስቅልቅል የዳረገች ይህች ክፉ ቀን ቀደም ብላ ታስባ የታሰበባትና የተጠናች ውሳኔ ነች? ወይስ በሂደት በደርጉ አባላትና እና መሪዎቹ በስሜታዊነት ድንገት የተፈጸመች? እርግጥ ይህ ጉዳይ ዛሬም ቢሆን አወዛጋቢነቱ ያበቃለት አጀንዳ አልሆነም። በህይወት የተረፉም ይሁኑ አንዳንድ የታሪክ ምሁራን በአንድ አይነት ሀሳብ ለመስማማት አልተቻላቸውም። አንዳንዶች በተለይ የወቅቱ ምክትል ሊቀመንበር ሻለቃ መንግስቱ ኃይለማርያምን ለግድያው ዋና ተጠያቂ በማድረግ “ከመነሻው ጀምሮ ሲያውጠነጥኑት የነበረ ሴራ ውጤት ነው” ሲሉ ሌሎች ደግሞ “እጅ በማውጣት የግድያውን ውሳኔ ሲያጸድቁ የነበሩ የደርጉ አባላት ስሜታዊ ውሳኔ ነው” ይላሉ። ሌተና ኮሎኔል ፍስሀ ደስታ "እኛና አብዮቱ"በተሰኘው መጽሀፋቸው እንደመሰከሩት ከሆነ ግን የደርጉ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር ሻለቃ መንግስቱ በጻፉት የትእዛዝ ደብዳቤ የስልሳዎቹ ግድያ መፈጸሙን ይመሰክራሉ። እንደ ኮሎኔል ፍስሀ ደስታ አባባል ግድያው ህዳር 14 ሊፈጸምና ህዳር 14 ደርጉ ተሰብስቦ ሊወስን አንድ ቀን ቀደም ብሎ ህዳር 13 ቀን እጃቸውን የሰጡ የቀድሞ መንግስት ሹማምንት ላይ እርምጃ ይወሰድባቸው የሚል የምክትል ሊቀመንበሩ የሻለቃ መንግስቱ ኃይለማርያም ፊርማ ያረፈበት የትእዛዝ ደብዳቤ በአንድ አጋጣሚ እጃቸው ገብቶ መመልከታቸውን መስክረዋል፡፡ ከጥቂት ግዜ በኋላም ታደሰ ቴሌ ሳልቫኖ በመጽሃፋቸው የደብዳቤውን ኮፒ ይፋ አድርገዋል። ሻለቃ (የኋላው ፕሬዚደንት) መንግስቱ ኃይለማርያም በፊርማቸው አስደግፈው ለደርግ ጥበቃና ዘመቻ መምሪያ መኮንን( ለያኔው ዋና የግድያ አስፈጻሚያቸው) ለኮሎኔል ዳንኤል አስፋው የይረሸኑ ደብዳቤ ቀደም ብለው ልከውለታል፡፡ (ግድያው ህዳር 14 ቀን ሊፈጸም ህዳር 13 ቀን መላካቸው ለይሙት በቃ የሚሰበሰቡት የደርግ አባላት ውሳኔውን ከማስተላለፋቸው በፊት መሆኑን ልብ ይሏል)፡፡ ግደል የተባለውን ያለማመንታት በመፈጸም የሚታወቀው ኮሎኔል ዳንኤልም በምላሹ የደብዳቤው ግርጌ ላይ "በትዕዛዙ መሰረት እንተገብራለን" በማለት የአለቃውን ትእዛዝ ለመፈጸም እንደማያወላዳ አረጋግጧል። ✍ ቀዳሚው ሰለባ ኮዳ ትራሱ.... ደርጎች በህዝቡም በሰራዊቱም ዘንድ እውቅና እንደሌላቸው በሚገባ ስለተረዱ ነበር በቀዳማዊ ኃይለስላሴ መንግስት ውስጥ ጉልህ ጀብድ በመፈጸም የሚታወቁትንና "ኮዳ ትራሱ"በሚል። ተቀጽላ የሚታወቁትን ሌፍተናንት ጀነራል አማን አምዶምን ሊቀመንበር እንዲሆኗቸው የጠየቋቸው።ከፖለቲከኛነትና ከዲፕሎማትነት ይልቅ የቆፍጣና ወታደርነት ባህሪያቸው እንደሚያዘነብልባቸው አብረዋቸው የሰሩ ሰዎች የሚመሰክሩላቸው ጀነራል አማን: ከደርጎች ጋር ተስማምተውና ተግባብተው የሊቀመንበርነታቸውን ወንበር ከሁለት ወር በላይ ሊቆዩበትት አልተቻላቸውም ነበር። ከሻለቆቹና ከሻምበሎቹ ጋር መግባባት የተሳናቸው ሌፍተናንት ጀነራል አማን አምዶም ነገር አለሙን ትተው ጦር ሀይሎች አካባቢ ይገኝ ከነበረው መኖሪያቸው ውስጥ መቀመጥን መረጡ። በጦሩ ዘንድ ያላቸውን ተወዳጅነት ተጠቅመው መልሰው ሊያጠቁን ይችላሉ ብለው የሰጉት ደርጎችም ገዳይ ቡድን ቤታቸው ድረስ ልከውባቸውና ለረዥም ሰአት ከጀነራሉ ጋር ተታኩሰው ገደሏቸው። የአማን አምዶም ግድያም ለቀሩት ሀምሳ ዘጠኝ ሰዎች ግድያ ማስጀመሪያ ፊሽካ ሆነች። እጃቸውን በሰላም ነበር የሰጡትእድሜ አግኝተው ታሪክን ለመመስከር የበቁ የደርግ ባለስልጣናት ስለ ሌሎች የቀይ ሽብር ሰማዕታት ጉዳይ እምብዛም ጸጸት ሲሰማቸው ባይታይም( ኮሎኔል መንግስቱ ሀይለማርያምን ጨምሮ) በስልሳዎቹ ላይ የተደረገው ግድያ ግን ፍጹም ስህተት እንደነበር ይመሰክራሉ። ለነገሩ ጸጸታቸው የፈሰሰ ውሀ የማያሳፍስ: የጠፋውን ጥፋት የማይመልስ ነበር፡፡ በጥይት ተደብድበው የተገደሉት ሰዎች ሀገርና ወገንን ያገለገሉና ብዙ ሊያገለግሉ የሚችሉ ምናልባትም መጠነኛ ጥፋታቸው ተቆጥሮ መጠነኛ ቅጣት ብቻ የሚገባቸው ሰዎች ነበሩ። (በስልጣን ዘመናቸው ያጠፉትን ጥፋት ለማጣራት የተቋቋመው የመርማሪ ኮሚሽን ሪፖርት የሚያረጋግጠውም ይሄንኑ ነው፡፡) የመጋቢት 1966 ህዝባዊ አመጽን ተከትሎና ከሚያዝያ አጋማሽ ወር ጀምሮ በርካታ የቀዳማዊ ኃይለስላሴ ሹማምንት ከያሉበት እየተያዙ እስር ቤት እየታጎሩ ነበር፡፡ አመጹ እየተፋፋመ ሄዶ በመጨረሻም ደርግ መስከረም 2 ቀን 1967 በትረ ስልጣኗን ሲይዝ እጁ ላይ የወደቁትን (ንጉሰ ነገስት ቀዳማዊ ኃይለላሴን እና አክሊሉ ሃብተወልድን ጨምሮ) በርካታ ሹማምንት ተገቢዉን ፍርድ እሰጣቸዋለሁ በማለት ለህዝብ ቃል ገባ፡፡ ለዚህም መርማሪ ኮሚሽን በአዋጅ ተቋቁሞ ስራዉን መስራትም ጀምሮ ነበር፡፡ ሆኖም ግን የመርማሪ ኮሚሽኑ አዝማሚያ የፈለገውን አይነት ቅጣት ማድረግ እንደማያስችለው ያወቀው የደርጉ መንግስት ፍርድን እራሱ ሊሰጥ ወሰነ፡፡ በመጀመሪያ “እርምጃ እንዲወሰድባቸው” ስማቸው የቀረበው 250 ሰዎች የነበሩ ሲሆን በመጨረሻ ቁጥራቸው ወደ 141 ዝቅ ብሎ፣ ከመካከላቸው ለግድያ የተመረጡት ባለሥልጣናት ስም ተራ በተራ እየተነበበ ድምጽ እንዲሰጥባቸው ተደረገ፡፡ በዚህም መሰረት 59 ሰዎች በጥይት ተደብድበው እንዲገደሉ በአብላጫ ድምጽ ተወሰነ። በዚያች ክፉ ቀን ብቻ... 👉 ሁለቱ ጠቅላይ ሚኒስትሮች 👉 አንዱ ልዑል 👉 አንዱ ሪር አድሚራል 👉 አስራ ሰባቱ ሚኒስትሮች 👉 አስራ አንዱ የጠቅላይ ግዛት እንደራሴዎችና የአውራጃ ገዥዎች 👉 አንዱ ገበሬ 👉 ዘጠኙ ሌፍተናንት ጀነራሎች 👉 ሶስቱ ሜጀር ጀነራሎች 👉 ሶስቱ ብርጋዴር ጀነራሎች 👉 ሶስቱ ኮሎኔሎች 👉 ሰባቱ መስመራዊ መኮንኖችና 👉 ሁለት የበታች ሹማምንት የመትረየስ ጥይት ዘንቦባቸው ተረሽነዋል። ከተረሸኑት ስልሳ ባለስልጣናት መካከል ሀምሳዎቹ ከኢጣልያ ወረራ ጀምሮ ሀገራቸውን በተለያየ መልኩ ሀገራቸውን ያገለገሉ እስከ 45 አመት የሚደርስ የአገልግሎት ዘመናቸው የሚቆጠር፣ ከእነዚህም ውስጥ 17 አርበኞች ይገኙበታል። የእድሜያቸው ነገር ሲነሳ ደግሞ በ 19 አመት የአፍላነት እድሜው ከተረሸነው አንስቶ እስከ 75 አመት የሚደርሱ አዛውንቶች የጥይት እራት ሆነዋል። 3 ወንድማማቾችና ሎሎች 2 ወንድማማቾች የወንድማቸውን ሞት እያዩ እንዲገደሉ ተደርገዋል። የሚያሰቃያቸውን ደዌ እያስታመሙ ካሉበት ሆስፒታል አልጋ ሁለት በሽተኞች ግሉኮሳቸው ተነቅሎ ተወስደው ተገድለዋል። ✍ ስልሳዎቹ...
1
6
No text...
1
7
☝️☝️ ይህ የሆነው መስከረም 13/1969 ዓም ከዛሬ 46 ዓመት በፊት በዛሬዋ ዕለት ነው። ለ17 ዓመት ኢትዮጵያን የመሩት ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማሪያም ከዘጠኝ ጊዜ በላይ ስለተደረጉባቸዉ የግድያ ሙከራዎች ሲናገሩ "እኔ በትርፍ ህይወት ነው የኖርኩት" ይላሉ ከነዚህ 9ኝ የመግደል ሙከራዎች ስለ አንዱ ምክትላቸው የነበሩት ኮሎኔል ፍስሀ ደስታ" አብዮቱ እና ትዝታዬ" በተሰኘው መጽሀፋቸው የሚከተለውን አስፍረዋል ኮሎኔል መንግሰቱ ሃይለማርያምን ለመግደል ከተካሄዱ ዘጠኝ ሙከራዎች ውሰጥ አራቱ ከመስከረም 8-12 ባሉ ቀናቶች ነው ከሁሉም የበለጠው ግን መሰከረም 13 1969 የተደረገው ሙከራ ነው መሰከረም 13 ከምሸቱ ሁለት ሰአት ተኩል ገደማ ኮሎኔል መንግሰቱ ከታላቁ ቤተመንግሥት ወጥተው ወደ ቤታቸው ማምራት እንደጀመሩ ቢጫ ቶዮታ መኪና ከአጃቢዎቻቸው ኃላ ሆና ተከትላቸው በፖሊሰ ጋራዥ ፣በአምባሳደር ቲያትር፣በጋንዲ ሆስፒታል በኩል አድርገው ወደ አራተኛ ክፍለ ጦር በሚጓዙበት ወቅት ልክ አዲሰ አበባ ስታዲየም እንደደረሱ ቢጫ ቶዮታዋ መኪና አጃቢዎቻቸው ላይ የተኩስ ናዳ አወረደችባቸው በዚህ ጊዜ ጓድ መንግስቱን ለመግደል ትእዛዝ የተሰጣት ነጭ ናድሰን መኪና ኮሎኔል መንግሰቱ ላይ የተኩሰ እሩምታ አወረዱባቸው የኮሎኔል መንግሰቱ ሹፌር ለረጅም ጊዜ በኦጋዴን የውጊያ ቀጠና ያገለገለ ሰለነበር ተኩሱ የደፈጣ መሆኑን በመገንዘብ ሳይደናገጥ ይዞት ከነበረው ከቀኝ መንገድ ማከፋፈያውን በመጣስ ወደ ግራ ወደ ቀኝ እየነዳ ለገዳዮቹ ኢላማ ችግር ፈጠረ ዮሴፍ ት/ቤትን አልፎ ወደ አራተኛ ክፍለ ጦር መግቢያ ሲጠማዘዝ አካባቢውን ያናወጠ ከፍተኛ ፈንጂ ፈነዳ ሾፌሩ ግን እንደምንም አራተኛ ክፍለ ጦር ቢደርሰም ለወትሮ ኮሎኔል መንግሰቱና ኮሎኔል አጥናፉ ሳይገቡ ተዘግቶ የማያውቀው በር በዚያ ሰአት ተከርችሞ ነበር የመኪና ድምጽ ቢያሰማም የሚከፍትለት በማጣቱ በሩን ገንጥሎ ገባ በነጋታው ኮሎኔል መንግሰቱ የደርግ ዋና ሊቀመንበር ብርጋዴር ጀነራል ተፈሪ በንቲና ኮሎኔል አጥናፉ በተገኙበት እግራቸውን እጥፍ ዘርጋ እያደረጉ አንዲት የቀዘቀዘች ጥይት በቀላል ቀዶ ጥገና እንደወጣላቸውና አሁን በመልካም ጤንነት ላይ መሆናቸው በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን በቀጥታ ሰርጭት ለህዝብ ተናገሩ ኮሎኔሉ ይጓዙባት የነበረች ላንድሮቨር መኪናም የደረሰባት ጉዳት አብሮ እንዲታይ በመደረጉ ከዚህ መትረፋቸው ለማመን የሚያቅት ትልቅ ተአምር ነበር አብዮቱና ትዝታዬ ሌተናል ኮሎኔል ፍሰሐ ደሰታ(ነፍስ ይማር) ©Teboren Beyene
453
8
ከዘጠኝ የመግደል ሙከራ ያመለጡት መሪ 👇👇 @Yetormida_welo+1
ከዘጠኝ የመግደል ሙከራ ያመለጡት መሪ 👇👇 @Yetormida_welo
345
9
መልካም ልደት የጀግናው 18ኛ ተራራ ክፍለጦር መሪና የላቀ የጦር ሜዳ ጀብዱ ተሸላሚ ሜጀር ጄነራል መርዳሳ ሌሊሳ 81ኛ ዓመት ሆናቸው፣ የቀድሞው የኢትዮጵያ ሰራዊት @Tarikawi_fotowech
መልካም ልደት የጀግናው 18ኛ ተራራ ክፍለጦር መሪና የላቀ የጦር ሜዳ ጀብዱ ተሸላሚ ሜጀር ጄነራል መርዳሳ ሌሊሳ 81ኛ ዓመት ሆናቸው፣ የቀድሞው የኢትዮጵያ ሰራዊት @Tarikawi_fotowech
537
10
@Yetormida_welo
@Yetormida_welo
0
11
የኢትዮጵያ ሠራተኞች ፓርቲ (ኢሠፓ)ን ወደ ፓለቲካ መድረኩ ከ 31 አመታት በሗላ መምጣት አስመልክቶ በድጋሚ የተለጠፈ ከተወልደ በየነ (ተቦርነ) ክምችት ትዝታ የኢሠፓ የፓርቲ ምሥረታ ኢሠፓአኮ 1972 ዓ_ም ተቋቋመ። አደራጅ ኮሚሽን ሆኖ ለ5 ዓመታት እንደፓርቲ አመራር ሰጥቷል። በ1975 ዓ_ም 2ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ለ5ቀናት አካሄደ። ጉባኤው ስለሀገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታ ፡ስለጦርነቱ ፣ ስለ ኢኮኖሚዉ እና ኢሠፓአኮ ስላደረገው አስተዋፅኦ ተወያየ። ፕሬዝደንት መንግሥቱ ኃይለማሪያም ከዚህ በላይ ፓርቲያችንን ለመመስረት መቆየት የለብንም የሚል ሀሳብ ሰነዘሩ። ተሰብሳቢው በሀሳቡ መስማማቱን በጭብጨባ አፀደቀ። ከዛም ለ11 ወራት ቅድመ ዝግጅት ተደረገ። ከጳጉሜ 1_5 1976 ዓ_ም በተደረገ ጠቅላላ ጉባኤ መስከረም 1 1977 ዓ_ም ኢሠፓ ተመሠረተ። በመስራች ጉባኤው ላይ ከ2000 በላይ የኢሠፓአኮ አባላት እና 350 ታዛቢዎች ተሳትፈዋል። የጉባኤው ተሳታፊዎች የማህበራዊ ስብጥር በመቶኛ ሲሰላ ~ሠራተኛው 19•26 ~ገበሬዎች 11•81 ~ወታደሮች እና ልዩልዩ የመንግሥት ሠራተኞች 68•93 በመቶ ያህል ነበሩ። 136 የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት 64ተለዋጭ አባላት 11 የፖሊት ቢሮ አባላት 6 ተለዋጭ የፖሊት ቢሮ አባላት አካቶ ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማሪያምን ሊቀመንበር አድርጎ መረጠ። በጉባኤው ላይ ከተገኙ የውጭ እንግዶች ~የምሥራቅ ጀርመኑ ኤሪክ ሆኒከር ~የጅቡቲው ሀሰን ጉሌት ኦፕቲዶን ~የዛንቢያው ኬኔት ካውንዳ ጥቂቶቹ ነበሩ። የኢህድሪ መንግሥት ጉባኤውን ያደረገው ለኢሠፓ ምሥረታ አሰርቶ ባስመረቀው እና ስያሜውን ከጉባኤው በወሰደው አዳራሽ ነው። የምሥረታውን አጭር ድባብ ከቪዲዮው ተጋበዙ 👇👇 @Yetormida_welo
0
12
ድንቅ የጦር ሜዳ ውሎ ታሪክ በኮ/ል ጋዲሳ ጉማ "እኔ፥ ምትኩ ሙለታ፥ ጌታቸው ከንፈሬ እና ሚካዔል ሣህለ ማርያም አይሮፕላኖችን እንድናመጣ ወደ ስዊድን አገር ተላክን። ስዊድን ሆቴል አድረን ጥዋት ለቁ
ድንቅ የጦር ሜዳ ውሎ ታሪክ በኮ/ል ጋዲሳ ጉማ "እኔ፥ ምትኩ ሙለታ፥ ጌታቸው ከንፈሬ እና ሚካዔል ሣህለ ማርያም አይሮፕላኖችን እንድናመጣ ወደ ስዊድን አገር ተላክን። ስዊድን ሆቴል አድረን ጥዋት ለቁርስ ስንነሳ ሆቴሉ በር ላይ ሰው ሞልቷል። ምንድን ነው ብለን ስንጠይቅ እናንተን ለማየት ነው ተባልን። ጥቁር አይተው አያውቁም።" @Yetormida_welo
0
13
ጀግናው ደጃዝማች መሸሻ የራስ ካሳ ጦር የጠላትን የተንቤን የብረት አጥር ሰብሮ እንዲወጣ ሽፋን በመስጠት የራስ ካሳ ጦር ከጠላት ከበባ ሰብሮ እንዲወጣ አድርጓል፡፡ ይሁን እንጂ ከዚህ በኋላ እያፈገፈገ ሲዋጋ በአንድ የእጅ ቦንብና በ3 የመትረየስ ጥይቶች ሆዱን ተመቶ ወደቀ፡፡ በወደቀበት ቦታ የሞተ ሰው መስሎ ከዋለ በኋላ ሲጨልም እንደ እባብ እየተሳበ ወደ ጫካ በመግባቱ የትግል ጓዶቹ አንስተው ወደ ጦር ሰፈር ወሰዱት፡፡ ይህ የከምባታ ጀግና 3 የመትረየስ ጥይቶችን በሆዱ ይዞና ሰውነቱ በቦምብ ተበሳስቶ 3 ቀንና ሌሊት በፈረስ ተጉዞ ዛሬ ከዋናው የጦር ሰፈራችን ደርሶ ራስ ካሳ ካዘጋጁለት ቦታ እንዲያርፍ ተደረገ፡፡ ነገር ግን ይህ የጀግኖች ጀግና ሁለት ሰአት ያህል አርፎ ጓዶቹንና አለቆቹን ከተሰናበተ በኋላ ከስቃዩ ተገላገለ፡፡ በጀግኖቹና በደፋሮቹ የከምባታ ልጆች መሪ ሞት ሁላችንም አዘንን፡፡ ... Amharic Story Credit: የሃበሻ ጀብዱ፣ አዶልፍ ፓርለስካ እንደጻፉት፣ ተጫነ ጆብሬ እንደተረጎሙት፣ አአዩ ፕሬስ እንዳተመው፣ ገጽ 285-297፣ 272-282 Images primarily taken in Addis Ababa & the Ogaden front by Daily Mirror photographer George Greenwell in 1935 G.C You can read the source captions by clicking each picture https://www.gettyimages.com/photos/ethiopia-1935
328
14
☝️☝️የሰላሌው አብቹና የከምባታው ደጃዝማች መሸሻ ገድል በማይጨው ጦር ግንባር፣ ጨለማን ተገን በማድረግ ብቻ ከሰቆጣ ተነስተን 5 ቀን ያህል ከተጓዝን በኋላ ኮረም ደረስን፡፡ በምስራቅ ከአዘቦዎችና ከራያዎች ጋር ከሚያዋስኑት ተራራዎች ላይ ስንደርስ የንጉሡ መለዮ ለባሽ መደበኛ ወታደሮች ከታች ሲርመሰመሱ ይታያሉ፡፡ እንዲህ አይነት ወታደራዊ ልብስ የለበሱ ወታደሮችን ያየሁት አዲስ አበባ ብቻ ነው፣ እዚህ ያለው ወታደር አብዛኛው ሸማ ለባሽ የገበሬ ወታደር ነው፡፡ ብዙም ሳንቆይ በንጉሡ ዋሻ ውስጥ እራሳችንን አገኘን፣ ንጉሡ ያለምንም ፕሮቶኮል ተቀበሉን፡፡ በዚህ ዋሻ ውስጥ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት እንደሚገኙ የሚጠቁም ምንም ነገር የለም፡፡ በዚህች ዋሻ ውስጥ ከአንድ መናኛ ወታደራዊ ጠረጴዛ፣ 4 ታጣፊ የሸራ ወንበሮችና በዋሻው የቀኝ ክንፍ ላይ በተራ ብርድልብስ ከተሸፈነ አንድ ተራ የወታደር አልጋ ውጭ ሌላ ነገር የለም፡፡ ጃንሆይ የአውሮጳውያን ሻጥር ከገባቸው በኋላ እንደ ቀደምት የኢትዮጵያ ነገሥታት ሁሉ መትረየሳቸውን ጠምደው፣ ሽጉጣቸውን ታጥቀው፣ ጠመንጃቸውን አንግተው ከጠላት ጋር በጦርነት ገጥመው ለመሞት ተሰልፈዋል፡፡ እናት አገር ወይም ሞት! ጃንሆይ ድንገት የንግግራቸውን አቅጣጫ በመለወጥ ልጁን አይታችሁት ታውቃላቸው ሲሉ ጠየቁን፡፡ ሩሲያዊው አማካሪያቸው ኮሎኔል ኮኖቫሎቭ ይቅርታ ጃንሆይ ከኔ ይልቅ አዶልፍ ፓርለስካ የአቢቹ የቅርብ ወዳጅ ስለሆነ እሱ ሊያብራራልዎት ይችላል በማለት መለሰላቸው፡፡ ከየት ጀምሬ እንደማስረዳቸው ሳሰላስል ጃንሆይ ጣልቃ ገብተው ግዴለም እንደናንተም ባይሆን ይቺ አንድ ፍሬ ደጃዝማች ከኛም በላይ ትልቅ ጀብዱ እየሰራች እንደሆነ እንሰማለን በማለት አቋረጡኝ፡፡ … ዛሬ አዝማሪው ሳይቀር ስለራሶች ጀግንነትና ስለ ንጉሠ ነገሥቱ ታላቅነት ማንጎራጎሩን ርግፍ አድርጎ ትቶታል፡፡ በኮረም የጦር ሰፈር መሸትሸት ሲል በተንቤን ጦርነት ጓዶቹን እንኳን ለመቅበር እድል ያላገኘው የከፋው ወታደር እሳቱን አንድዶ ሽንብራውን እየቆረጠመ በማሲንቆ የተደገፈች የአንድ የሰላሌ ልጅ ሙዙቃን ማዳመጡን ተያይዞታል፡፡ አንጀት የምትበላዋ የማሲንቆ እንጉርጉሮ ስለ ጀግናው ስለ አቢቹ ነበረች፣ አቢቹ ደራ ደራ አቢቹ ደራ ደራ አቢቹ በዚህ ጦርነት የወደቁት 2 ወንድሞቹ ብቸኛ ወራሽና በማዕረግም ፊታውራሪ ቢሆንም ህጋዊ የማዕረግ ስሙን ተጠቅሞ አያውቅም፡፡ አቢቹ በደጃዝማች አበራ የሚመራው የሰላሌው ጦር አባልና ለመሪው ደጃዝማች አበራ ታማኝ ነው፡፡ ነገር ግን የራሱን ጦር እየመራ ከደጃዝማች አበራ ጦር እየራቀ ከጠላት ጦር በሚዘርፈው ሀብት ጦሩን የሚያስተዳድርና በሁለቱ ራሶች ሳይቀር እንደሽፍታ የሚቆጠር ነው፡፡ የአብቹ ጦር በሀብቶም የሚመሩ የኤርትራ ልጆች የተቀላቀሉበት እንዲሁም የትግራይና የዳሞት ልጆችን ያቀፈ ቢሆንም አብዛኞቹ የሰላሌ ልጆች ናቸው፡፡ የአብቹ ጦር ለከሃዲውና ለባንዳው የደጃዝማች ኃይለ ሥላሴ ጉግሳ ጦር የእግር እሳት ሆኗል፡፡ የአቢቹ ጦር የከምባታ ልጆችን ጋይላ ላይ ከጠላት መንጋጋ ፈልቅቆ አውጥቷቸዋል፡፡ የራስ ካሳን ጦር ከጠላት የብረት አጥር ለማስመለጥ የተሰለፈው የከንባታ ልጆች ጦር የብረት አጥሩን ከሰበረ በኋላ እራሱ በጠላት ጦር መውጫ አጥቶ ተከበበ፡፡ የከንባታ ልጆች መውጫ አጥተው በነበረበት ሰአት የአቢቹ ደቦል አንበሶች ከየት መጡ ሳይባል ከጣልያን ጦር ብብት ውስጥ በመግባት እየኮረኮሩ ጠላትን እየደመሰሱ እንዲያፈገፍግ በማድረግ ካለቀለት ውጊያ ውስጥ የወገናቸውን የከምባታውን ጦር መንጥቀው አወጡት፡፡ ... እ.ኤ.አ መጋቢት 31 ቀን 1935 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሰራዊት እየተኮሰ፣ እየፎከረና እየሸለለ በሺዎች ረድፍ ተሰልፎ ማይጨው በመሸገው የጠላት ጦር ላይ ዘመተ፡፡ የጠላት ጦር ግን አስቀድሞ ከከሃዲዎች ባገኘው መረጃ በምሽጉ ሆኖ ኢትዮጵያውያንን በመትረየስ ያረግፋቸው ጀመር፡፡ የኢትዮጵያ ሰራዊት ግን የሚወድቁ ወገኖቹን እሬሳ እየተራመደ በ3 ራሶች መሪነት በ3 ረድፍ ተሰልፎ ህይወቱን ለእናት አገሩ ሊሰዋ እየፎከረ ወደፊት መገስገሱን ቀጠለ፡፡ የኢትዮጵያ ጦር የጠላትን አንገት በጎራዴው እየቀላ፣ በጦሩ ደረት እየበሳና በጥይቱ ግንባር እየበረቀሰ የመጀመሪያውን ጠንካራ የኢጣሊያ ምሽግ ሰብሮ ገባ፡፡ በዛሬው ጦርነት እግዚአብሔር ጀግንነትን ለኢትዮጵያውያን መርቆ የሰጣቸው ተፈጥሮ መሆኑን በድጋሚ አረጋገጥኩ፡፡ ድል በኢትዮጵያውያን እጅ የገባች መሰለች፡፡ በዚች ቅጽበትም የአድዋ ድል ሊደገም ጥቂት ሰአታት ብቻ ቀረው፡፡ ይሁን እንጂ ለሰላሳ ሽልንግና ለጣሊያን መሳሪያ እራሳቸውን የሸጡ ከሃዲ ባንዳዎች የገዛ ወንድማቸውን ከጀርባ ገብተው ጨፈጨፉት፡፡ ድል ለመጨበጥ የደረሰውን የእናታቸውን ልጅ ድል ነሱት፡፡ ብዙ ቂም የተያዘበት የአብቹ ጦርም ትልቅ ጉዳት ደረሰበት፡፡ ሁለት ምርጥ አዋጊና ተዋጊ ጄኔራሎቹን አጣ፣ እጅግ በርካታ የሰላሌው የአብቹ ጦር አባላት በማይጨው ግንባር ለእናት አገራቸው በክብር ወደቁ፡፡ ጃንሆዬም በወርቅ የተንቆጠቆጠው ወታደራዊ ልብሳቸው በደም ፍንጣቂና በጭቃ ተለውሶ ተመለሱ፡፡ ቀኛዝማች ሼህ ሁሴን አባ ወርቁም በልጃቸው ላይ የተተኮሰውን ጥይት በደረታቸው በመቀበል ልጃቸውን በማዳን እሳቸው በክብር ወደቁ፡፡ …. ጀንበር እንደጠለቀች ብዙም ውሃ ከሌላት የተንቤን መጨረሻ የአበርገሌ አዋሳኝ ከሆነችው ትንሽ ወንዝ በመድረስ ተሻግረን የአበርገሌ ጫካ ውስጥ ገባን፡፡ አንበሳው ፈረሴ ንጋት ላይ ከፈረሰኛው ጦራችን ጋር ቀላቀለኝ፡፡ ጦራችንን እንዳገኘሁ በጣም ተደስቼ መጀመሪያ ያገኘሁትን ወታደር አለቃችሁ ማነው ስለው ደጃዝማች ጨቡዴ! በማለት በታላቅ ኩራት መለሰልኝ፡፡ ወዲያው ከሩቅ ደጃዝማች ጨቡዴ ሊቀበለኝ መጣ፡፡ ከተያየን ሰንብቶ ስለነበር ረጅሙን የኢትዮጵያ ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ ደጃዝማች ‘ወዳጄ እዚህ አደጋ የበዛበት ቦታ ስለሆነ አሁኑኑ ወደ ዋናው ጦር ሰፈር መመለስ አለብህ’ አለኝ፡፡ እውነትም ከርቀት ስፍር ቁጥር የሌላቸው የጣሊያን ወታደሮችን ድንኳን አየሁ፡፡ በድንኳኖቻቸው ዙሪያ እሳት አቀጣጥለው የደራ ጨዋታ ይዘዋል፡፡ የጣሊያን ጄኔራሎች በአንድ ሌሊት አስቸጋሪውን ተራራ አልፈን ከሰፈሩበት መድረሳችንን ፈጽሞ አልተገነዘቡም፡፡ ደጃዝማች ጨቡዴ ቢለምነኝም ለመመለስ ፈቃደኛ ባለመሆን ወደ ቀጣዩ የኮረም ግንባር ጦራችንን እየመራን ለመሄድ በፈረሶቻችን ላይ ተቀመጥን፡፡ ይሁን እንጂ አስቸጋሪውን ተራራማና ገደላማ መንገድ እየተጓዝን በመጨለሙ እስኪነጋ እረፍት እንድናደርግ ተወሰነ፡፡ ነግቶ ብዙ ከተጓዝን በኋላ አሁንም መሸና በጋይላ ወንዝ ዳርቻ እረፍት አደረግን፡፡ ብዙም ሳይቆይ ተነሳ ተራመድ የሚለው የኢትዮጵያ ወታደሮች ጡሩንባ አነቃኝ፡፡ የጋይላ ወንዝ በሆዷ ቋጥራ ከያዘችው ውሃ እንድንጠጣ መፍቀድ ባቻ ሳይሆን ከጠላት የሞት አሞራዎች/አይሮፕላኖች አይንም ደብቃናለችና ጋይላ ምስጋና ይገባታል፡፡ አሁን በጋይላ ወንዝ ጉያ ሆነን ወደኋላ የቀሩ የትግል ጓዶቻችንን በተለይም ክፉኛ የቆሰለውን የከንባታ ልጆች ጦር መሪ ደጃዝማች መሸሻን እየጠበቅን ነው፡፡
256
15
የሰላሌው አብቹና የከምባታው ደጃዝማች መሸሻ ገድል በማይጨው ጦር ግንባር 👇👇👇+2
የሰላሌው አብቹና የከምባታው ደጃዝማች መሸሻ ገድል በማይጨው ጦር ግንባር 👇👇👇
220
16
መጋቢት 21 ቀን 1953 ዓ.ም ከ 61 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን የታኅሣሥ ግርግር በመባል በታሪክ መዝገብ የሚታወቀውን የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ በግንባር ቀደምነት ያካሄዱት የነበሩት የክብር ዘ+2
መጋቢት 21 ቀን 1953 ዓ.ም ከ 61 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን የታኅሣሥ ግርግር በመባል በታሪክ መዝገብ የሚታወቀውን የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ በግንባር ቀደምነት ያካሄዱት የነበሩት የክብር ዘበኛ አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል መንግሥቱ ንዋይ በተቀበሉት ፍርድ መሠረት በስቅላት የተቆጡበት ዕለት ነበር። @tarikawi_fotowech
285
17
የኢትዮጵያ ቃኘው ሻለቃ ወደ ኮሪያ ከመጓዙ በፊት በአዲስ አበባ ተመርቆ እየተሸኘ ነው - 1943 ዓ.ም በሽኝቱ ላይ የተገኘኙት የሐይማኖት አባት ወታደሮቻችን የአሜሬካኖችን ምግብ በኮርያ እንዲበሉ ልዩ
የኢትዮጵያ ቃኘው ሻለቃ ወደ ኮሪያ ከመጓዙ በፊት በአዲስ አበባ ተመርቆ እየተሸኘ ነው - 1943 ዓ.ም በሽኝቱ ላይ የተገኘኙት የሐይማኖት አባት ወታደሮቻችን የአሜሬካኖችን ምግብ በኮርያ እንዲበሉ ልዩ ፍቃድ እየሰጡ ነው። @tarikawi_fotowech
538
18
☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️ የኢትዮጵያ ቃኘው ሻለቃ በኮሪያ ካንግንዩ/Kangnyu ጦር ግንባር ከ 70 አመት በፊት - 1943/1944 ዓ.ም Heroes from afar: A rare footage of
☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️ የኢትዮጵያ ቃኘው ሻለቃ በኮሪያ ካንግንዩ/Kangnyu ጦር ግንባር ከ 70 አመት በፊት - 1943/1944 ዓ.ም Heroes from afar: A rare footage of the hailed Ethiopian soldiers of the Korean war captured about 70 years back in 1951/1952 “At the conclusion of the war, the Ethiopians were the only contingent that had no prisoners to collect since no Kagnew soldier ever surrendered. Another distinction was that they never left their dead behind ......” Korean JoongAng Daily Korean OldTube: @yetormida_welo @yetormida_welo
328
19
ሜጀር ጀነራል ፋንታ በላይ (በራሪው የሰማዩ ንስር) በደርግ ዘመነ መንግስት የአየር ሃይል ዋና አዛዥ ቀጥሎ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የነበሩ ፤ በግንቦት 8 1981 ዓ.ም በተደረገው የመፈንቅለ መንግስት
ሜጀር ጀነራል ፋንታ በላይ (በራሪው የሰማዩ ንስር) በደርግ ዘመነ መንግስት የአየር ሃይል ዋና አዛዥ ቀጥሎ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የነበሩ ፤ በግንቦት 8 1981 ዓ.ም በተደረገው የመፈንቅለ መንግስት በመምራት ከተሳተፉት ከፍተኛ መኮንኖች መካከል አንዱ ሲሆኑ ከላይ የሚታየው ቪዲዮ ሜ/ጀነራል ፋንታ በላይ በወቅቱ የመንግስት ግልበጣው ከከሸፈ በኋላ እንዲሁም ከመገደላቸው በፊት ያደረጉት ቃለ- መጠይቅ ፤ @tarikawi_fotowech
277
20
በሕይወት ዘመኔ ከፈፀምኩት ወይም ካየሁት መካከል የሚያስደስቱኝና የሚያስደንቁኝ:- 1. ምንም ዓይነት ትምህርት ከሌላቸው የገጠር ነዋሪዎች ተወልጄ በመሀል ቢሆን የመማር ዕድል ዓይኔን መክፈቴ ያስደስተ
በሕይወት ዘመኔ ከፈፀምኩት ወይም ካየሁት መካከል የሚያስደስቱኝና የሚያስደንቁኝ:- 1. ምንም ዓይነት ትምህርት ከሌላቸው የገጠር ነዋሪዎች ተወልጄ በመሀል ቢሆን የመማር ዕድል ዓይኔን መክፈቴ ያስደስተኛል ፤ 2. እኔ በማውቀው መጠን ከሰው ጋር ያለኝ ግንኙነት ጤናማ በመሆኑ ደስ ይለኛል ፤ 3. ከአብራኬ የተፈጠሩ ልጆቼ ሁሉ ጤናማ መሆናቸው ያስደስተኛል፤ 4. ሰውን ለማጥፋት በተለየ ጥረት ያደረግኩበት ጊዜ መኖሩን ስለማላስታውስ ደስ ይለኛል ፤ 5. ይብዛም ይነስም ኃላፊነት ተሰጥቶኝ መወጣት ያቃተኝ ቀን ባለመኖሩ ደስ ይለኛል በተለይም:- (ሀ) የምፅዋ ሁኔታ እጅግ አሳሳቢ ሆኗልና የአስመራውን ሥራ ለኮሎኔል ከፈለኝ ሰጥተህ ወደ ስፍራው በመነቃነቅ ይህን ታሪካዊ ቦታ አድን ተብሎ ሕዳር 9 ቀን 1970 ዓ.ም የተሰጠኝ ግዳጅ በመወጣት ማዳኔ ፤ (ለ) የምፅዋ ሁኔታ ላላ ሲል የአስመራ ሁኔታ አሳሳቢ በመሆኑ የምፅዋት ጥበቃ ለኮሎኔል እስጢፋኖስ ገብረመስቀል አስረክበህ አስመራን ለማዳን ወደዚያ ተነቃነቅ በማለት ጥር 18 ቀን 1970 ዓ.ም ባስተላለፉልኝ ቴሌግራም መሠረት ተነቃንቄ የአስመራን ከተማ ለማዳን መቻሌ በአጠቃላይም በኤርትራ ክፍለሀገር ጥበቃ መላላት የኢትዮጵያ ካርታ ያለመለወጡ የተለየ ደስታና ክብር እንዲሰማኝ ያደርጉኛል። የኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም መርዕድ ንጉሤ (ሜጀር ጀነራል) ጥር/1973 ዓ.ም
305