ታሪካዊ ፎቶዎች 📷 📼
Open in Telegram
ይህ የታሪካዊ ፎቶዎች ኦፊሻል ቻናል ነው ታሪክን መዘከር ትልቅነት ነው ትውልድንም ያንፃል ‼️ Officeal channel 📡 》t.me/ @Tarikawi_potowech https://t.me/+3SO18mqWX_tiOWE0 #የጦር_ሜዳ_ውሎ https://t.me/joinchat/AAAAAFUFiN1N7T13DEKhAQ 👉 ለአስተያየትዎ @Eyoha_Bot
Show more735
Subscribers
+124 hours
-17 days
+3530 days
Posts Archive
Peace Corps volunteers Judy Hagens & Sudy Harris in
traditional Ethiopian clothing at Kombolcha in 1966 G.C
ኮምቦልቻ/ወሎ - 1958 ዓ.ም
Montclair State College:
https://msuweb.montclair.edu/~lebelp/emdeberblackandw
hite.html
@Tarikawi_fotowech
ሐረርጌ - 1940
Janice Sensenig Photograph/Tom Lehman Flickr Archive
https://www.flickr.com/photos/tlehman/5515709889/in/
album-72157625632615149/
@Tarikawi_fotowech
የሩሲያዊው አብዮተኛ፣ የሩሲያ ኮሙኒስት ፓርቲ መስራች የነበረው የቭላድሚር
ሌኒንን ሐውልት ከፈረሰ በኋላ ህፃናቶቹ ከሐውልቱ ላይ ሆነው ሲጫወቱ
ይታያሉ።
ሠኔ - 1983 ዓ.ም አዲስ አበባ
@Tarikawi_fotowech
የኢትዮጵያ ባህር ኃይል አባላት በቦስተን - 1956 ዓ.ም
2nd Picture: Captain of the H.M.S. Ethiopia hands Toni Peabody (Mrs. Endicott) a gift from Ethiopia (1964)
3rd Picture: Muriel Snowden and H.M.S. Ethiopia Captain Egil
Stokstad hold an Ethiopian flag (1964)
NORTH EASTERN UNIVERSITY LIBRARY ARCHIVES:
https://repository.library.northeastern.edu
@Tarikawi_fotowech
Today marks the 111th anniversary of the wedding of H.I.M.
Haile Selassie I and His royal consort Empress Menen. July
31,1911
@Tatrikawi_fotowech
The Commander of Ethiopian forces Col. Kebbede Gebre in South Korea in May 1951 G.C
የዝነኛው ቃኘው ሻለቃ አዛዥ ወጣቱ ኮሎኔል ከበደ ገብሬ በኮሪያ - 1943 ዓ.ም
Source Caption: Colonel Kebbede Guebre, 35, of Addis Ababa.
When the Ethiopian expeditionary force landed in South Korea, Col. Guebre said the morale of his men was very high and they were anxious "to participate in this operation as troops of amember of the United Nations" United Nations Photo Archive:
https://www.unmultimedia.org/photo/detail.jsp?id=191/
191495&key=6&query=Lt.%20General%20Kebbede%20G
uebre&lang=&sf=
@Tarikawi_fotowech
ሳር ቤት
በ1959ዓም በድርጅቱ የተፈፀሙ ዓቢይ ስራዎች ጥንታዊ የኢትዮጵያውን መኖሪያ ቤቶች ከውጭ ያለው አሰራራቸው ሳይለወጥ ውስጣቸው በዘመናዊ እቅድ ቢሰራ ለዘመኑ የሚስማማ አገልግሎት መስጠት መቻላቸውን ለማሳየትና ከዘመናዊ ቤቶች ማሰሪያ ባልበለጠ ወጪ ተሰርተው እኩል ጥቅም እንደሚሰጡ ለማሳየት በጠቅላላው $223,739.85 ወጪ ሆኖባቸው አራት ታላላቅ ቤተ ንጉሶች በዱሮው አይሮፕላን ማረፊያ አካባቢ ተሰሩ::
የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በጎ አድራጎት ድርጅት 1945-1965 ታተመ በ1965
ከ ዘሪሁን ጉልቴ የተወሰደ
@Tarikawi_fotowech
ኢሠፓ (የኢትዮጵያ ሰራተኞች ፓርቲ )
የኢትዮጵያ ሠራተኞች ፓርቲ (ኢሠፓ) በአዲስ መልክ ወደ ሀገሪቷ የፖለቲካ
መድረክ እየመጣ ነው አደራጆቹ የፓርቲውን መተዳደሪያ ደንብ እና ፕሮግራም ለሚመለከተው ክፍል አቅርበዋል።
@Tarikawi_fotowech
ትዝታ ዘሐረርጌ በአብዛኛው በግራዋና በሐረር በ1959/1960 ዓ.ም የተነሱ ፎቶግራፎች።
Rarely seen beautiful pictures you may have never seen
before Mike O'Brien/Former United States Peace Corps Volunteer:
@Tarikawi_fotowech
https://www.flickr.com/photos/8777371@N07/albums/
72157713429207297
🔝 የምኒልክ አልጋ ወራሽ ልጅ ኢያሱ ሚካዔል በብላቴን ጌታ መርስዔ ኅዘን ወልደ ቂርቆስ ዓይን፣
አቤቱ ኢያሱ በወሰን በኩል ካሉት አዳሎችና ከሱማሌዎች ጋር አስቀድመው
ወዳጅነት በመመስረት የባላባቶቹን ሴቶች ልጆች አገቡ፡፡ በ1907 ዓ.ም
የመንግሥቱን ስራ ለጠ/ሚኒስትሩ ለቢትወደድ ኃይለጊዮርጊስና
ለሚኒስትሮቻቸው ትተው ወደ አዳል ወረዱ፡፡ በጤናዬ ከተማም እስላሞችን
ለማስደሰት የሐር ግልድም አገልድመው ወደ መስጊድ ገቡ፡፡
ለአዳል ባላባቶችም ገንዘብና ሽልማት ሰጥተው ደስ አሰኟቸው፡፡ የአዳሉን ባላባት የነጋድራስ አቦከርን ልጅም ሚስት አደረጓት፡፡ አቤቶ ኢያሱ በዚሁ ጊዜ በመንዝ በኩል ሲጓዙ ባላገሩን ደስ የሚያሰኙ ስራዎችን ሰሩ፡፡ አቤቱ ኢያሱ አንድ አሽከር ብቻ በማስከተል የመንዝን ገበሬ ኑሮ ለማየት ሲሄዱ አንድ ባላገር በዶማ ሲቆፍር አገኙት፡፡
እርሳቸውም ዶማውን ተቀብለው
ትንሽ ከቆፈሩ በኋላ፣ ይኼማ ያደክማል ለምን በሬ ገዝተህ አታርስም አሉት፡፡
ባላገሩም አይ ጌታዬ በሬ የምገዛበት ከየት አግኝቼ፣ ለዚህ ለዶማዬም ጭቃ
ሹምና መልከኛ አጥር እጠር፣ ኩዳድ ቆፍር፣ አስራት አውጣ እያሉ ከአገር
ሊያባርሩኝ ነው አላቸው፡፡
እርሳቸውም ሌላ ሰው መስለው ለምን ለአቤቶ ኢያሱ አቤት አትልም ቢሉት፣ ዋ
ማን አቅርቦኝ አላቸው፡፡ እርሳቸውም መልሰው ነገ ጧት ወደ አቤቶ ኢያሱ ሰፈር
መጥተህ ብትጮህ እኔ አቀርብኃለው ብለውት ሄዱ፡፡ ያናገሩት አቤቶ ኢያሱ
እራሳቸው መሆናቸውን ያላወቀው ገበሬ በነጋታው ወደ አቤቶ ኢያሱ ሰፈር ሄዶ
አቤት አቤት እያለ ሲጮህ ከልካዮች ሲገፉት አቤቶ ኢያሱ በሩቁ ተመልክተው
ወደ ኔ አምጡት አሉ፡፡
እሱም ጭቃ ሹምና መልከኛ ያደረሱበትን በደል ልክ እንደትላንቱ ደገመላቸው፡፡ እሳቸውም 50 ብር ለበሬ መግዣ ዳርገውና የመሬቱን ግብር ወስነው ደስ አሰኝተው መለሱት፡፡ በሌላ ቀን ደግሞ እንዲሁ አንድ ፈረሰኛ ብቻ አስከትለው ሲጓዙ በመንገድ ላይ ዳቦ የምትሸጥ አንዲት ሴትን አገኟት፡፡ ከፈረሳቸው በመውረድ ዋጋውን ጠየቋት፡፡
እሷ ግን የአቤቶ ኢያሱ አሽከር ሊሆኑ ይችላሉ በማለት እንዲሁ በነጻ ብሉት
አለቻቸው፡፡ ከዳቦው ትንሽ ቀምሰው ለአጃቢቸው ካጎረሱት በኋላ ርስትና ባልስ
የለሽምን አሏት፡፡ ርስትስ አለኝ ግብሩ ግን ሊነቅለኝ ነው፣ ባሌም ብዙ ልጅ
ከወለድን በኋላ ስለሞተብኝ ቢቸግረኝ ዳቦ ሸጣለሁ አለቻቸው፡፡ እሳቸውም ሌላ
ሰው መስለው ለጌታዬ ለአቤቶ ኢያሱ እነግርልሻለሁና ነገ ወደሰፈር ነይ ብለዋት
ሄዱ፡፡ በማግስቱ ወደ ሰፈር ስትሄድ አቤቶ ኢያሱ ከሩቅ አይተው በማስጠራት ትላንት
ዳቦሽን በልቶ ዋጋ ሳይከፍል የሄደውን ሰው ከዚህ ውስጥ አሳይኝና ዋጋሽን
ላስከፍልሽ አሏት፡፡ ሴቲቱም ወደ አቤቶ ኢያሱ ዘወር ብላ አንገቷን በመድፋት
እርስዎ ንዎት አለቻቸው፡፡ እሳቸውም በመሳቅ መቶ ብርና አምሳ ዳውላ እህል
ዳረጓት፡፡ የመሬቷን ግብርም ወስነው ደስ አሰኝተው ሰደዷት፡፡
አቤቶ ኢያሱ በአንድ በኩል በሃይማኖትና በልማድ እስላሞችን እየመሰሉ
ግልድም አገልድመው መስጊድ ሲሄዱ ፎቶ ተነሱ፡፡ ይህም ለአገር አንድነት
ይጠቅማል በማለት ያደረጉት ነው ቢባልም ክርስትያኖችን የሚያስቆጣ ሆነ፡፡ አቤቶ ኢያሱ የክርስትያኑን ልማድና ሥርአት መከተላቸውም አልቀረም ነበር፡፡
አልፎ አልፎ ቤተክርስቲያን ይሳለማሉ፣ ቅዳሴም ያስቀድሳሉ፡፡
በጋብቻም ረገድ የጎጃሙን መስፍን የራስ ተ/ሃይማኖትን ልጅ ወ/ሮ ሰብለ ወንጌልን ሚስት አድርገው አንዲት ልጅ ወልደዋል፡፡ የየጁዋን ወ/ሮ ጥሩወርቅ አሊጋዝንም ሚስት አድርገዋል፣ ከተጉለቴው ደጃዝማች አንዳርጋቸው ልጅ ከወ/ሮ ትስሜም እንዲሁ ልጅ ወልደዋል፡፡ ነገር ግን ክርስቲያኑ ህዝብ ይህን ሁሉ በቂ አድርጎ ስላልተመለከተው ልጅ ኢያሱ እስላም ሆነዋል እያለ ያጉረመርም ጀመር፡፡ ይህን ለምን ያደርጋሉ ብሎ ደፍሮ የተናገረ ግን አልነበረም፡፡ ደፍሮ አለመናገሩም አንገቱን እንደሚያጣ ያውቃልና ፈርቶ ይሆናል፡፡
አቤቶ ኢያሱ መልካቸው ቀይ፣ ቁመታቸው ሎጋና ድልድል፣ አይናቸው ጉልህ፣
ጠጉራቸውም ዞማ ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜ በራሳቸው ላይ ሻሽ ያስራሉ፡፡ የጉብዝና
ወሬ ያስደስታቸዋል፡፡ መኳንንቱንም እርስ በርስ ነገር እየቀሰቀሱ ያፏክሩዋቸዋል፡፡
አንዱን ጠርተው እገሌ እኮ በሙያ እበልጥሃለሁ ብሏል እያሉ እያጋጠሟቸው
እሳቸው ዳኛ ይሆናሉ፡፡ አንድ ጊዜ በችሎት ላይ ሳሉ ደጃዝማች ቁንን በላይነህንና ፊታ/ወልደ ሚካዔል ኤዴቾን እንዲህ ሲያፏክሯቸው አይቻለሁ፡፡ ይህን
የሚያደርጉት ግን በተንኮል ከፋፍለው ለመግዛት ሳይሆን ሰዎች በግልጽ
እየተፏከሩ ሲጋጠሙ ማየት ስለሚያስደስታቸው ነው፡፡
በዳግማዊ ምኒልክ ዘመን የቤተመንግስት ገንዘብና ንብረት የመመርመር ስራ በ1905 ዓ.ም ተጀምሮ ስለነበር አቤቱ ኢያሱ ይህንኑ አስቀጠሉ፡፡ ከተመርማሪዎቹ መካከልም ትላልቅ ባለስልጣናት ይገኙበት ነበር፡፡ አቤቱ ኢያሱ ግን ሊጣሉት የፈለጉትን ሌላ ባለስልጣን ጭምር በምርመራው እያሳበቡ ማዋረድ ጀመሩ፡፡
የምኒልክን መኳንንትንም ወፍራም ናችሁ ለማለት ‘የአባቴ ሙክቶች” እያሉ
አፌዙባቸው፡፡ የመኳንንቱን ሚስቶችንም ተዳፈሩ፡፡ በአዲስ አበባ ፍልውሃ አጠገብ ባሰሩት መታጠቢያ ቤት የሚፈጽሙትን ብዙ የነውር ተግባር ሽማግሌዎች እየሰሙ ነቀፏቸው፡፡ ወጣቶቹ ግን ተባባሪያቸው ሆኑ፡፡ ማታ ማታ ሁለት እየሆኑ በየሴተኛ አዳሪዎች ቤት መዞር አበዙ፡፡አንዳንድ ጊዜም ሌሊት ከከተማ ዘበኞች ጋር ተኩስ ይጋጠሙ ነበር፡፡ በዚህ ረገድ ብዙ የሰማሁት ቢኖርም ሁሉን ለመጻፍ አልፈቅድም፡፡
አቤቶ ኢሱ ገና የ17 እና የ18 አመት አድሜ ላይ የነበሩ በመሆኑ የልጅነት ጠባይ እንዳሸነፋቸው አይጠረጠርም፡፡ የሚያሳዝነው ግን ከመጥፎ ጠባይ እንዲቆጠቡ የሚያደርግ ቁርጠኛ ወዳጅና ዘመድ ሳያገኙ መቅረታቸው ነው፡፡ አቤቶ ኢያሱ የተጠሉት በሃይማኖት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን በያንዳንዱ ሰው ላይ በግል በፈጸሙት ተግባር ጭምር ነው፡፡
የ20ኛው ክ/ዘመን መባቻ የዘመን ታሪክ ትዝታዬ ካየሁትና ከሰማሁት
(1896-1922)፣ ብላቴን ጌታ መርስዔ ኅዘን ወልደ ቂርቆስ፣ አአዩ ፕሬስ 2008
ዓ.ም፣ ገጽ 115-122
በተያያዘው ምስል የሚታዩት ልጅ ኢያሱ ሚካዔል ሲሆኑ ፎቶግራፉ የተነሳውም
በ1905/1906 ዓ.ም ነው፡፡ ፎቶግራፉ የተገኘው ፍሎረንስ ኢጣሊያ ከሚገኘው
የአሊናሪ ኦንላይን አርካይቭ ነው፡፡
Picture Credit: Alinari Archives/Florence:
http://www.alinari.it
@Tarikawi_fotowech
#1
ንግሥት ኤልዛቤት እና ጠ/ሚኒስትር ዊንስተን ቸርችልን ጨምሮ የለንደን
ነዋሪዎች ለቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ያደረጉት አቀባበል - 1946/1947 ዓ.ም
@Tarikawi_fotowech
እኛን በውጥ መስመር ከፈለጉ 👉 @Eyoha_Bot ላይ ፃፉልን
የአቡነ ጴጥሮስ አደባባይ እና የአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት - 1958 ዓ.ም
Hungarian National Archive/MTVA Photobank /Fengues
Tamas Photographs:
https://archivum.mtva.hu/photobank
@Tarikawi_fotowech
Addis Abeba Abune Petros & 'Seba Dereja' Area in '1955' G.C
Alfred Eisenstaedt photographs- Life Magazine Collection - Ethiopia Essay '55 hosted by Google
Images.google.com/hosted/life
@Tarikawi_fotowech
@Eyoha_Bot
ትግራይ/አክሱም - 1957 ዓ.ም
Images primarily taken in Axum. Specific places or descriptions
include Antiquities sign, Mai Shum, entrance gate of the house of Ras Mengesha, the churches of Abba Pantoleon & Abba Liquanos, Axumite Stonework at Abba Liquanos, Mortar with Geez inscription, thrones & throne base, Stele at the Tomb of Bazen, the Great Daron, Village scene University of York/British Institute in Eastern Africa/ Archeological Data Service/Bleaak's File:
https://archaeologydataservice.ac.uk
@tarikawi_fotowech
