ቀሲስ ስንታየሁ የኔአባት
Open in Telegram
በዘመናዊው ቴክኖሎጂ ታግዘን ስለ ህይዎታችን የምንወያይበት፣ የምንመካከርበት እና የምንጠያይቅበት የቴሌግራም ገፅ ነው! ለማግኘት @KSintayehu ማዕከለ አራዊት ንኬልኅ አልቦ ዘይሰምዐነ እስመ አራዊት ይቤዝኁ እምኔነ መኑ ጠቢብ ወመለብው ከመ እግዚአብሔር አገው!
Show more690
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Data loading in progress...
Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
February '24
February '240
in 0 channels
January '24
+4
in 0 channels
Get PRO
December '23
+17
in 0 channels
Get PRO
November '23
+15
in 0 channels
Get PRO
October '23
+15
in 0 channels
Get PRO
September '23
+11
in 0 channels
Get PRO
August '23
+14
in 0 channels
Get PRO
July '23
+15
in 0 channels
Get PRO
June '23
+19
in 0 channels
Get PRO
May '23
+17
in 0 channels
Get PRO
April '23
+37
in 0 channels
Get PRO
March '23
+21
in 0 channels
Get PRO
February '23
+49
in 0 channels
Get PRO
January '23
+43
in 0 channels
Get PRO
December '22
+36
in 0 channels
Get PRO
November '22
+19
in 0 channels
Get PRO
October '22
+5
in 0 channels
Get PRO
September '22
+7
in 0 channels
Get PRO
August '22
+97
in 0 channels
Get PRO
July '22
+37
in 0 channels
Get PRO
June '22
+10
in 0 channels
Get PRO
May '22
+9
in 0 channels
Get PRO
April '22
+29
in 0 channels
Get PRO
March '22
+6
in 0 channels
Get PRO
February '22
+3
in 0 channels
Get PRO
January '22
+7
in 0 channels
Get PRO
December '21
+3
in 0 channels
Get PRO
November '21
+3
in 0 channels
Get PRO
October '21
+10
in 0 channels
Get PRO
September '21
+12
in 0 channels
Get PRO
August '21
+96
in 0 channels
Get PRO
July '21
+94
in 0 channels
Get PRO
June '21
+23
in 0 channels
Get PRO
May '21
+25
in 0 channels
Get PRO
April '21
+16
in 0 channels
Get PRO
March '21
+526
in 0 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 15 February | 0 | |||
| 14 February | 0 | |||
| 13 February | 0 | |||
| 12 February | 0 | |||
| 11 February | 0 | |||
| 10 February | 0 | |||
| 09 February | 0 | |||
| 08 February | 0 | |||
| 07 February | 0 | |||
| 06 February | 0 | |||
| 05 February | 0 | |||
| 04 February | 0 | |||
| 03 February | 0 | |||
| 02 February | 0 | |||
| 01 February | 0 |
Channel Posts
ህዳር 25
✝️ እንኳን ለቅዱስ መርቆሬዎስ ንግስ በአል አደረሳችኹ❤
ለክርስትና ሃይማኖት የሚከፈል ትልቁ ዋጋ ሰማዕትነት ነውና ቤተ ክርስቲያን ለምስክሮቿ ሰማዕታት ልዩ ክብር አላት። ከኮከብ ኮከብ እንዲበልጥ ሁሉ ከሰማዕታትም ቅዱስ ጊዮርጊስን እና ቅዱስ መርቆሬዎስን የመሰሉት ደግሞ ክብራቸው በእጅጉ የላቀ ነው።
ቅዱስ መርቆሬዎስን ብዙ ጊዜ ሊቃውንት "ካልዕ (ሁለተኛው) ሊቀ ሰማዕታት" ሲሉ ይገልጹታል።
ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ፦
በሁለተኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጨረሻ አካባቢ ከሮም ግዛቶች በአንዱ (አስሌጥ) ከአባቱና ከሚስቱ ጋር የሚኖር "አሮስ" የሚሉት ሰው ይኖር ነበር። ሚስቱ ደም ግባት የሠመረላት እርሱም ደግነት ያለው ሰው ቢሆኑም የሚያመልኩት ግን ጣዖትን ነበር።
አንድ ቀን አሮስ ሚስቱን ከቤት ትቶ ለአደን ከአባቱ ጋር ወጣ። እንደ ልማዳቸው ወጥመዱን አስተካክለው ተደበቁ። የወጥመዱ ደወል ሲያቃጭል "እንስሳ ተያዘልን።" ብለው ሲሯሯጡ ዓይናቸው ያየው ነገር በድንጋጤ እንዲፈዙ አደረጋቸው። ሁለት ገጻተ ከለባት በወጥመዱ ውስጥ ተይዘው ነበር።
እነዚህ ፍጡራን ሰዎች ናቸው። ግን ባልታወቀ የተፈጥሮ አጋጣሚ እንደዚህ እንደ ሆኑ ይታመናል። ግን እጅግ ግዙፍ፣ ከአንገታቸው በላይ እንደ ውሻ፣ ወገባቸው እንደ ሰው፣ ጉልበታቸው እንደ አንበሳ ሲሆን ታችኛው እግራቸው የጋለ የናስ ብረት የሚመስል ነው።
እነዚህን ፍጡራን ሰማያዊ ካልሆነ ምድራዊ ፍጡር አይችላቸውም። አንበሳና ነብርን እንኳ እንደ ጨርቅ በጣጥሰው ይጥሏቸው እንደ ነበር ይነገራል። ዓይናቸው እንደ እሳት ይነድ ስለ ነበር ማንም ትክ ብሎ ሊያያቸው አይችልም።
ምሥጢራቸውን ግን የሚያውቀው የፈጠራቸው አምላክ ነው።
ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና አሮስና አባቱ ባዩአቸው ጊዜ ደንግጠው ወደቁ። ገጻተ ከለባቱ የብረት ወጥመዱን እንደ ክር በጣጥሰው የአሮስን አባት በቅጽበት በሉት። አሮስን ሊበሉት ሲሉ ግን ድንገት ቅዱስ መልአክ ወርዶ በእሳት ሰይፍ አጠራቸው።
"ከእርሱ የሚወጣ ቅዱስ ፍሬ አለና እንዳትነኩት።" አላቸው። ወዲያውም መልአኩ ያንን ኃይለኝነታቸውን አጠፋው። በዚህ ጊዜ ሁለቱም ወደ አሮስ ሒደው ሰገዱለት። አሮስም ወደ ቤቱ ወስዶ ደበቃቸውና የሆነውን ሁሉ ለሚስቱ ነገራት።
ጥቂት ቆይታም ጸንሳ ወለደች። ልጃቸውን ፒሉፓዴር (ፒሉፓተር) ሲሉ ስም አወጡለት። ትርጉሙም "መፍቀሬ አብ - የአብ ወዳጅ" ማለት ነው። ከዚያም አሮስ ሚስቱን፣ ልጁንና ሁለቱን ገጻተ ከለባት ይዞ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሒዶ ተጠመቀ።
አበው ካህናት እሱን "ኖኅ"፣ ሚስቱን "ታቦት"፣ ልጁን ደግሞ "መርቆሬዎስ" ሲሉ ሰየሟቸው። መርቆሬዎስ ማለትም "ገብረ ኢየሱስ ክርስቶስ - የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ" እንደ ማለት ነው።
| 2 | #የሉም_ሞተዋል
የሉም ሞተዋል ሲሉን ኖረን
የሉም ጠፍተዋል ሲሉን በዝተን
አለን በእግዚአብሔር ሁሉን አልፈን
አለን በጌታ ሁሉን አልፈን
ለካ ሰው ሰለሮጠ አይቀድምም
ጉልበታም ስልታገለ አይጥልም
ጎልያድ ወድቋል በዳዊት ጠጠር
የኛ አምላክ ስሙ ከፍ ይበል ይክበር
እግዚአብሔር ስሙ ከፍ ይበል ይክበር
አዝ = = = = =
በሚነድ እሳት መሐል ሆነን
አልሞትንም ዛሬም አለን በዝተን
ያልሰማ ሁሉ ይስማ ይግረመው
ያመለክነው እግዚአብሔር እንዲህ ነው(፪)
አዝ = = = = =
ጨክነን እኛ ሰይፉን ባንመዝ
በእጃችን ጦር ጉመድን ባንይዝ
ይዋጋል ዝም አይልም እግዚአብሔር
ልጆቹን ፈጥሮ አይሰጥም ለፍጡር(፪)
አዝ = = = = =
አሕዛብ ሥጋችንን ሊያጠፉ
ቢደክሙ ብዙ ዘመን ቢለፉ
ካሸናፊዎች ሁሉ በልጠን
አልሞትንም ዛሬም አለን በዝተን(፪) | 326 |
| 3 | ወደ ቤተ መቅደስ ሲገቡ ስልክ ማጥፋትዎን አይርሱ ከሚል ማስታወቂያ እየቀደሱ ቲክ ቶክ ወደመግባት የተሸጋገርን ደግሞ መቼ ነው?
ሰው እንዴት እንኳን እየቀደሰ ይቅርና መቅደስ ውስጥ ለምን ስልኩን ይከፍታል? | 258 |
| 4 | ንግስተ ሰማያት
ንግስተ ሰማያት ወምድር ማርያም ድንግል /2/
ተፈጸመ /5/ ማኀሌተ ጽጌ /2/ | 233 |
| 5 | No text... | 247 |
| 6 | ✏ጠሪ አክባሪ ነው !
👉ታላቅ የመጽሐፍ ምርቃት
♣ ኅዳር ፰ ቀን ሌላ ቀጠሮ እንዳትይዙ አደራ እላለኹ! በዕለቱ፥ ስለ ጠቢበ ጠቢባን ቁም ነገርን የምትቀሥሙበት መንፈሳዊ ጉባኤ ተዘጋጅቶ ይጠብቃችኋል!!
♣ለበለጠ መረጃ፦ ኅዳር ፰ ቀን ፳፻፲፮ ዐ.ም፥ በዕለተ ቀዳሚት ሰንበት፥ ከቀኑ ፯ ሰዓት ጀምሮ በማኅበረ ቅዱሳን አዳራሽ በአካል መሳተፍ ይቻላል!!
📍ጠሪው፦ ኤፍሬም የኔሰው (የጠቢበ ጠቢባን ተርጓሚ፣ አዘጋጅ እና አሳታሚ)። | 205 |
| 7 | ምን መፍትሔ ሰጠኸውና? ያየህውን ሥራ ሁሉ እሰራለሁ
የሰማኸውን ትምህርት ሁሉ እማራለሁ አትበል። ይህ
የተሰወረው የቅንዓት ጠባይ ነውና። ሁሉን ልያዝ ማለትም
ዝንጉ አድረጎ እንዳያስቀርህ ሁሉም ውስጥ ልኑር አትበል።
---
ቆንጆዎች ቁንጅናቸው ሁሉን የሚተካ እየመሰላቸው
ከዕውቀትና ከትሕትና ይርቃሉ። ሁሉንም ሰው በመልካቸው
የሚማርኩት ስለሚመስላቸው ኩሩና ተንኮለኞች ይሆናሉ።
አንተ ግን ቆንጆ ወዳጅን እንጂ ቆንጆ ቁመናን አትሻ፤ ቆንጆ
ትዳርን እንጂ ቆንጆ ሴትን አትመኝ፤ የላይ ነገር ከንቱና ኀላፊ
ነውና በሚፈርስ አካል፣ ኑሮ በሚለውጠው መልክ አትደለል።
---
ቂም አፍን የሚያመር፣ ልብን የሚያነቅዝ፣ ተግባርን
የሚያልፈሰፍስ ነውና ለበደለህ ሰው ቅያሜህን ግለጥለት፤
ቂመኝነት በክፉ መሸነፍ እንጂ ጀግንነት አይምሰልህ።
---
ከህሊናህና ከመንፈሳዊ አማካሪህ ሳትመክር ምንም ነገር
አትወስን፤ አጥርተህ ሳትሰማ ቃል አትግባ። መከራ ካልደረሰ
በቀር ባል በሌለበት ቤት ውስጥ ከሚስቲቱ ጋር ብቻህን
አትቀመጥ።
---
የሚበልጥህ ልኩራብህ እንዳይልህ፣ ያነሰህ ልድረስብህ
ብሎ እንዳያጠፋህ የሀብትህን ልክ እንዳታወራ፤ በገዛ አፍህ
ባንዱ ትከብራለህ ባንዱ ትቀላለህና።
---
በጣም በማክበርህ እንዳታመልከው፤ በጣም በመናቅህ
እንዳታዋርደው ሠው እንዳንተ መሆኑን እወቀው።
---
የእኔ መናገር ምን ይለውጣል? ብለህም ስህተትን አትለፍ፤
የእኔ አስተዋፅኦ ምን ይጠቅማል? ብለህም ስጦታህን
አትጠፍ።
---
መልካም ቃል ከስጦታ ይበልጣልና መልካም ቃል ተናገር፤
ማንኛውም ስጦታ ከልመና ወንበር አያስነሣም። የተስፋ ቃል
ግን እንደሚያስነሣ አውቀህ ለሰዎች የተስፋ ቃል ስጣቸው።
---
ትምህርት ለዕውቀት ያዘጋጃል እንጂ ዕውቀትን
አይጨርስም። ዕውቀትህን የምትይዝበትን ሥነ-ሥርዓት ግን
ያሳይሃል። አእምሮህን ለማረቅ ትምህርት፣ ሰውነትህን
ለመግዛት ትዕግስት፣ ከማንም ጋር ለመኖር ሥነ-ሥርዓት
ያስፈልግሃል። ለህሊናህ እረፍት ግን እምነት ያሻሃል።
ተከታይ ለማበጀት ደግሞ ግልጽ መሆንና ታማኝነት ግድ
ይልሃል።
---
አንተው እውነትን ጠልተሃት ዘመኑ እውነትን ጠልቷል
አትበል። ዘመን እኔና አንተ ነን፤ በራሱ ክፉና ደግ የሆነ
ዘመን የለም።
---
መልካም ምክር ብትሰማ ሕይወት ቀላል ይሆንልሃል።
ትክክለኛም ውሳኔ ከመልካም ምክር ነውና..!!
,,,,,,,,,,,,,,,,,,
(((የመጋቤ ሐዲስ እሸቱ ነው ተብሎ ፌስቡክ ላይ
ሲዘዋወር የተገኘ) | 149 |
| 8 | ፡
"በቦታህ መምህር፤ ያለቦታህ ደግሞ ተማሪ ሁን››
...
በወጣትነት ሁሉም ነገር ትክክል ነው ከሚል መመሪያ
ውጣ፤ ሁሉንም ካላየሁ አላምንም አትበል። ሰምቶ ማመን
፣ ከተጎዱት መማር አስተዋይነት መሆኑን አትርሳ። የሰማንያ
ዓመት ዕውቀትን ለመገብየት ግድ ሰማንያ ዓመት መኖር
የለብህም። ሰማንያ ዓመት ከኖሩት በትሕትና መጠየቅ
ይገባሃል።
---
ምክርን ብትሰማ በነጻ ትማራለህ። ምክርን አልሰማ ብትል
ግን በዋጋ እንደምትማር እወቀው። በዋጋ መማር ግን
አድካሚ ደግሞም የሚያስመርር ነው። ብልህ ከሆንህ
በሰው ከደረሰው ትማራለህ፣ ሞኝ ከሆንህ ግን በራስህ
ሲደርስ ትማራለህ።
---
የታየህን አሳይ፣ ያልታየህን አጥራው። በደንብ
ያልተረዳኸውን አታስተምረው። ያልቀመስከውን ለሰው
አትጋብዝ። የሰማኸውን ሁሉ አትመን። ያየኸውን ሁሉ
ስጡኝ፣ የተናገርከውን ሁሉ ፈፅሙ አትበል። የሰጠኽውን
እርሳ እንጂ አታውራ። ፍፃሜውን ሳታይ ምስጋና አታብዛ።
ቀኑ ሳይመሽ ቀኑ ጥሩ ነው አትበል።
---
ዓይንህ የፊቱን ቢያይ ልብህ የኋላውን ያስብ። ነገ ላይ
እንድትደርስ የትናንቱን አትርሳ። የምትሄድበት እናዳይጠፋህ
የመጣህበትን አትዘንጋ።
---
የአባቶችህን መልካም ሥራ አብነት አድርግ። ካሳለፉት
ሕይወት ተማር እንጂ አወዳሽና ወቃሽ አትሁን። ሌሎች
መሆን ያለባቸውን ስታውቅ አንተ መሆን ያለብህ
እንዳይጠፋህ ተጠንቀቅ። ደግሞም አንተም በታሪክ ፊት
መሆንህን እወቀው።
---
ክፋት አይሙቅህ፣ መልካም ነገርም ብርድ ብርድ
አይበልህ። ለክፋት አቅም ካለህ ለበጎ ነገርም አቅም
አለህና ተግባርህ የምርጫ ውጤት ነውና አስብበት።
---
ገንዘብ የሚመልሰው የገንዘብን ጥያቄ ብቻ ነውና ሁሉንም
ነገር ገንዘብ ያስገኝልኛል ብለህ አታስብ። ላለው አትሩጥ፣
ምጽዋትህና ተግባርህ በአቅምህ መጠን ይሁን እንጂ
ከአቅምህ አትነስ። ድሃም ሆነህ ተበድረህ ስጦታ አትስጥ።
በጣም ካልቸገረህ ለቅንጦት አትበደር። ያንተን ድርሻ
ከጨረስህ ያልተጨረሰ የሌሎችን ድርሻ ፈፅምላቸው።
---
ለሀብታም አትሳቅ፣ የደሀ ጉልበት አይለፍብህ፣ ያለ ሰው
ሰው አልሆንክምና ሰው አትጥላ፣ የወጣህበትን መሰላል
አትገፍትር፣ ለመውረድም ያስፈልግሃልና፣ ያየኽውን ሴት
ሁሉ የመውደድ ጠባይህ ካለቀቀህ ትዳር አትያዝ፣
ካልጋበዙህ በቀር አማካሪ አትሁን፣ ባልጠሩህ ሥፍራ አቤት
አትበል፣ ካልሾሙህ መሪ አትሁን፣ ጉድለት በሌለበት ቦታ
ጊዜህን አታባክን፣ የሰው ፊት ጥገኛ ሁነህ ሲስቁልህ
የምትስቅ ሲቆጡህ የምታለቅስ አትሁን፣ ነገርህን በልክ፣
ቃልህን በጣዕም፣ ድምፅህን በዝግታ ፈፅመው።
---
እውር እንዳይሉህ ያልታየኽን አያለሁ አትበል። ጨካኝ
እንዳይሉህ ያልተሰማህን ጩኸት እሰማለሁ አትበል። ንፉግ
እንዳይሉህ ያለ አቅምህ እረዳለሁ አትበል። ነገር
አይገባውም እንዳይሉህ ያልገባህን እንደገባህ አድርገህ
አትለፍ። አንድ በጎ ዕውቀት ሳትጨብጥ የዋልክበትን ቀን
እንደ ኖርክበት አትቁጠረው፣ ስለዚህ መፅሐፍትን አንብብ፣
አዋቂዎችን ጠይቅ፣ ሁሉን ሳትንቅ ስማ።
---
ሥልጣን ሲሰጥህ መሪ እንጂ አለቃ አትሁን፤ ከፊት
እየቀደምህ አስከትል እንጂ ከኋላ ሆነህ አትቅደም።
---
በዓላማ ኑር፤ እንቅፋቶች የሚያጸኑህ እንጂ ተግባርህን
የሚያስተውህ አይሁኑ። ሕይወት ትምህርት ቤት መሆኑና
ባለማወቅ ብዙ ትህምርቶች እንዳያመልጡህ ተጠንቀቅ።
---
የመከራ ቀን ወዳጆችህን አትርሳ፤ የዛሬ ሰው ብቻ አትሁን፤
የትላንቱንም አስብ፤ አንገት የተፈጠረው ዞሮ ለማየት ነውና።
---
ዓለም ዋዣቂ ናት። ከፍና ዝቅ ስትል አትደናገጥ፤ ፀሐይ
ዝናብን ተከትላ ትፈነጥቃለች። ከመከፋትም በኋላ ትልቅ
መፅናናት ይሆናል። ከሌሊት በኋላም ሌሊት አይመጣም።
ከሀዘን በኋላ ደስታ ይሆናልና በርታ!
---
መነቀፍን አትፍራ፤ ነቀፋህን ግን አጥራው፤ ስለ ሀሰት
ሳይሆን ስለ እውነት ተገፋ፤ ሌሎችን ውደድ ፍቅር ስጦታ
እንጂ ብድር አይደለምና አልወደዱኝም ብለህ በአበዳሪዎች
አንቀጽ አትካሰስ፤ የገባህን አድርግ የዚህ ዓለም ሰው
ሲወድህም ሲጠላህም ባለማወቅ ነው። ብዙዎች
ስለወደዱህ ይወድሃል፤ ብዙዎች ስለጠሉህ ይጠላሃል።
---
ሁልጊዜ የበላዮችህን አትመልከት፤ የበታቾችህንም
ተመልከት። ለድምፅ አልባዎች ጩህላቸው፣ ለተጠቁት
ተሟገትላቸው። እውነት እውነት በማለትህ የምታጣው
ሀሰተኛ ወዳጅህን ብቻ ነው። እውነት እውነት በማለትህ
የምታተርፈው ግን እውነተኛ ወዳጅን ነው።
---
ደጋፊዎች ተከታዮች አይደሉም። ሰዎች ስለደገፉህም
የያዝኩት እውነት ነው ብለህ መንቻካ አትሁን፤ ምናልባት
ዛሬ የሚጮሁልህ ዛሬን ሊረሱብህ ሊሆን ይችላልና።
ሲያለቅሱልህም ቃልህ ማርኳቸው ሳይሆን የሞተ
ዘመዳቸው ትዝ ብሏቸው ሊሆን ይችላልና አለቀሱ ብለህ
ንግግርህን ድንበር አታሳጣው። እውነትንም በደጋፊ ብዛት
እንዳትመዝናት ተጠንቀቅ።
---
ለእውነታ እንጂ ለይሉኝታ አትኑር፤ ያን ስልህ የምትኖርበት
ሕዝብና ባሕል ከእውነት ጋር እስካልተጋጨ መጋፋት
የለብህም። ሠዎች የሚቀበሉህ ባሕላቸውን ስታውቅና
ስታከብርላቸው ነው።
---
ልጅነት የለሰለሰ መሬት፣ ወጣትነት የአዝመራ ዘመን፣
ሽምግልና ደግሞ የአጨዳ ዘመን መሆኑን አስተውል።
በሽምግልናህ የምታጭደው የወጣትነትህን አዝመራ ነውና
ዛሬ ለምትዘራው ተጠንቀቅ።
---
የሰዎችን ያለማወቅ አግዝ፤ ዕውቀትህ ባላወቁት ላይ
እንድትኮራና እንድትፈርድ አያድርግህ የአዋቂ ኩሩ ቁጥሩ
ካላዋቂዎች ነውና ማወቅ ባለዕዳነት እንዳይሆን
አላዋቂዎችን እርዳቸው !!
---
ሁሉን ወሬ ላውራ አትበል፣ የደበቁህን ምስጢር
አታውጣጣ፣ የሰማኽውን ወሬና የተገለጠልህን ምስጢር
ምን መፍትሔ ሰጠኸውና? ያየህውን ሥራ ሁሉ እሰራለሁ
የሰማኸውን ትምህርት ሁሉ እማራለሁ አትበል። ይህ
የተሰወረው የቅንዓት ጠባይ ነውና ሁሉን ልያዝ ማለትም
ዝንጉ አድረጎ እንዳያስቀርህ ሁሉም ውስጥ ልኑር አትበል።
---
ቆንጆዎች ቁንጅናቸው ሁሉን የሚተካ እየመሰላቸው
ከዕውቀትና ከትሕትና ይርቃሉ። ሁሉንም ሰው በመልካቸው
የሚማርኩት ስለሚመስላቸው ኩሩና ተንኮለኞች ይሆናሉ።
አንተ ግን ቆንጆ ወዳጅን እንጂ ቆንጆ ቁመናን አትሻ፤ ቆንጆ
ትዳርን እንጂ ቆንጆ ሴትን አትመኝ፤ የላይ ነገር ከንቱና ኀላፊ
ነውና በሚፈርስ አካል፣ ኑሮ በሚለውጠው መልክ አትደለል።
---
እወድሃለሁ ብለህ የምትናገረውን ቃል ውለታ አታድርገው፣
መውደድህን የምትናገረው እንወድሃለን እንዲሉህ አይሁን፣
ሠላም ያለው አፍቃሪ የራሱን ፍቅር ያለ ምክንያት መፈፀም
የሚችል ብቻ እንደሆነ እወቅ። መወደድህን ለመስማት
አትጠብቅ።
---
የሰዎችን ያለማወቅ አግዝ፤ ዕውቀትህ ባላወቁት ላይ
እንድትኮራና እንድትፈርድ አያድርግህ የአዋቂ ኩሩ ቁጥሩ
ካላዋቂዎች ነውና ማወቅ ባለዕዳነት እንዳይሆን
አላዋቂዎችን እርዳቸው።
---
ዛሬ የመዝራት ዘመንህ ነገ መከርህ ነውና በእምነት
እውነትን ዝራ፤ በምታውቀው ቦታ ላይ አገልጋይ
በማታውቀው መልካም ተግባር ላይ ደጀን ሁን፤ በቦታህ
መምህር ያለቦታህ ተማሪ ሁን፤ ክብሩ እንዳይቀንስብህ
ከዕቃ ትምክህት፣ ከዕውቀት ሙግት ራቅ።
---
ሁሉን ወሬ ላውራ አትበል፣ የደበቁህን ምስጢር
አታውጣጣ፣ የሰማኽውን ወሬና የተገለጠልህን ምስጢር | 111 |
| 9 | *መቼ ነው* እውነተኛ ክርስቲያኖች የምንሆነው?
*መቼ ነው* እግዚአብሔር በፈጠራቸው ነግሮች የምንማረከው?
*መቼ ነው* እግዚአብሔር ለምን እንደፈጠርን የምንረዳው?
*መቼ ነው* እግዚአብሔር እንደሚፈልገው መኖር የምንጀምረው?
*መቼ ነው* ስለ ሀይማኖታችን በሙሉ ልብ እምንናገረው?
*መቼ ነው* እማይጠቅም ንግግር ከመናገር የምንቆጠበው?
*መቼ ነው* ለመልካም ስራ ምሳሌ የምንሆነው?
*መቼ ነው* በስግደታችን በፆማችን የምንጠቀመው?
*መቼ ነው* ጾለታችን ተሰሚነት የሚያገኝው?
*
*መቼ ነው* ውሎና አዳራችን በቅዱስ ቃሉ ሚሆነው?
*መቼ ነው* ሙሉ በሙሉ በእግዚአብሔር ላይ የምንመካው?
*መቼ ነው* ያአለምን ትልቅነት ከልባችን የምናወጣው?
*መቼ ነው* ቤታችን ውስጥ ያለው የተበላሸ ሂዎት የሚስተካከለው?
*መቼ ነው* ቤታችን ውስጥ መጸሐፍ ቅዱስ ውዳሴ ማሪያም የሚወራው?
*መቼ ነው* ውሽት እምናቆመው?
*መቼ ነው* የእግዚያአብሔርን ውሳኔ መቃውም እምናቆመው?
*መቼ ነው* እኔ እኔ ማለት ትተን ውንደሜ እህቴ ማለት እምንጀምረው?
*መቼ ነው* ለሰዎች ከክርስቶስ ውጪ ጌታ እንደሌለ እምንናገረው?
*መቼ ነው* ጥሩና ለጋሽ መልካም ሰው የምንሆነው?
*መቼ ነው። ክርስቲያንነታችንን የምናስተዋውቀው?
*መቼ ነው* ለድሃ እምናዝነው?.
*መቼ ነው* ትዳራችን ስላም ሚያገኝው?
*መቼ ነው* የጋብቻን ጥቅም ተገንዝበት ለትዳር የምንቻኮለው?
*መቼ ነው* ከሀሜት; ስውን ከመበድል; ከማስቀየምና ከማማት እምንላቀቀው?
*መቼ ነው* ወላጆቻችንን እምናስደስተውና እምንታዝዝው?
*መቼ ነው* ያልተጣራ ውሬ ካማውራት እምንቆጠበው?
*መቼ ነው* እምንዋደደው?
*መቼ ነው* እግዚአብሔር በሰጠን ነገር ደስተኞች የምንሆነው?
*መቼ ነው* ስግደት ፆም ፆለት የምንላመደው?
*መቼ ነው* የበድለንን ይቅር የመንለው?
*መቼ ነው* ከራስ ወዳድነት እምንላቀቀው?
*መቼ ነው* ከሞት ቡኃላ ላለው ሂወት ስንቅ እምናዘጋጀው?
*መቼ ነው* አባቶችን እምናከብረው?
*መቼ ነው* ለእውቅት ጊዜ የምንሰጠው?
*መቼ ነው* ባወቅነው የምንሰራው?
*መቼ ነው* የ ምንሞትበትን ቀንም ይሁን ስፍራ እንደማናውቅ ተገንዝበን በተጠንቀቅ የምንቆመው?
*መቼ እረ መቼ ነው* ክርስትናን የምንኖረው?
*መቼ ነው* ለእነዚህ ተግባራዊ መልስ የምንመልሰው
እግዚአብሔር ይርዳን
አሜን።
ውስብሃት ለእግዚአብሔር
ወወላዲትድንግል
ወለመስቀሉ ክብር | 136 |
| 10 | አነጸና በአስተዳደሩ ደሀ ሳይበድል ፍርድ ሳያጓድል ሕዝቡን በክህነቱም ንፁህ ሆኖ እግዚአብሔርን እያገለገለ ኖረ።በስተመጨረሻም ፍጥረት ሆኖ ከመሞት ሰው ሆኖ በመቃብር ከመዋል የሚቀር አይኖርምና ንጉሣችንና አባታችን ቅዱስ ይምርሐነ ክርስቶስም የእረፍት ዘመኑ ሲደርስ እግዚአብሔር አምላክ ቃል ኪዳኑን ለዘላለም እንደሚያፀናለት ነግሮት በተባረከች በጥቅምት_19 ቀን በክብር ከመከራ ስጋ አሳረፈው። መቃብሩንም አስቀድሞ እነደነገረው በዛው በተቀደሰ ዋሻ ውስጥ አደረገለት።እናም ዛሬ ድረስ ቦታው በክብር ተጠብቆ ይኖራል።ምእመናንም ቃል ኪዳኑን በማሰብ "ማረኝ ይምርሐ" እያሉ መቃብሩን ይዞራሉ።ያንን ከሰማይ የወረደለትን መስቀልም በቤተመቅደሱ የሚያገለግሉት ካህናት አባቶች ቦታውን ለመሳለም የሚመጣውን ሕዝበ ክርስቲያን በበዓል ቀን ይባርኩበታል፡፡የቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!
አቤቱ የይምርሃነ ክርስቶስ አምላክ ሆይ! ስለወዳጅህ ስለ ቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስ ብለህ ይቅር በለኝ› እያለ ‹አባታችን ሆይ!› የሚለውን ጸሎት የሚጸልይ ዕለቱን እንደተጠመቀ አደርገዋለሁ፡፡ ነገ ማለዳ ተነሥተህ ወግረ ስሂን ወደሚባለው የዕረፍትህ ቦታ ወደሚሆነው ዋሻ ሕዝብህን አስከትለህ ሂድ፤ በዚያም ቤተ መቅደሴን ሥራ›› ብሎ ጌታችን ቃልኪዳን ከሰጠው በኋላ ሰላምታ ሰጥቶት በክብር ወደ ሰማይ ዐርገ፡፡
የቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን አሜን።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ
እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ
ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ
እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ
እም እለ አብዑ ብዑላን ዘተርፈ።
ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን
ሰማዕታት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን
ደናግል ዓዲ ወመነኮሳት ኄራን
ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን
እስከ አረጋዊ ልሒቅ እምንዑስ ሕፃን።
ለዘጸሐፎ በክርታስ
ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ
ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ
ወለዘሰምዐ ቃሎ በእዝነ መንፈስ
በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኲሉ እምባእስ
ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ
ወይፈኑ ለነ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ
እምይዜ ወእስከ ለዓለም አሜን።
ጌታ ሆይ ከብልጽግናቸው ብዛት የተነሳ ብዙ መባ ካገቡት ይልቅ የደሀይቱን አነስተኛ መባ እንደተቀበልህ ለሁል ጊዜ የሚያገለግሉህ አእላፍ መላእክትን እያሳሰብሁ በችግሬ ጊዜ የማቀርብልህን ምስጋና ተቀበል።
እናንተም ቅዱሳን ነቢያት የወንጌል ሰባኪያን ሐዋርያት ሰማዕታትና ጻድቃን ትጉሃን መላእክት ፍጹማን ደናግል እንዲሁም ደጋጎች መነኰሳት ሆይ ልጅ አዋቂ ሳይለይ የምንሰበሰብበትን የጉባኤ ቦታ ባርኩ።
ይህን መጽሐፍ ወረቀት አዘጋጅቶ ብራና ደምጦ የጻፈውንና ያጻፈውንም የተረጐመውን ቃለ ንባቡን በእርጋታ መንፈስ እና በተመስጦ ሕሊና ያዳመጠ በደለኛን ሁሉ የምታስምር የጌታ እናቱ በማርያም ጸሎት ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድነት ይማረን። አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
. ⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼
ጥቅምት 19 ቀን 2016 ዓ.ም | 182 |
| 11 | ዛሬ ይምርሃነ ክርስቶስ መታሰቢያ ቀን ነው
።።።።።።።።።።።።
ጻድቁ ንጉሥ ቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስ
ከላስታ (ከዛጉዌ) ነገሥታት መካከል ቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስ፣ ቅዱስ ገብረ ማርያም፣ ቅዱስ ላሊበላና ቅዱስ ነአኵቶለአብ እነዚህ አራቱ ነገሥታት እንደ መልከጼዴቅ (ዘፍ 14፡18) ክህነትን ከንግሥና፣ ቅድስናን ከንጽሕና ጋር አንድ አድርገው በመያዝ እግዚአብሔርንም ሰውንም በቅድስና አገልግለው አልፈዋል፡፡ በንግሥናቸው ሀገርን በመልካም ሥራና በቅድስና ከማስተዳደራቸው በተጨማሪ ቅዱሳን ጻድቃን ሆነው እግዚአብሔርን በብዙ ድካም በመልካም ተጋድሎአቸው ያገለገሉና አገልግሎታቸውም ሆነ ቅድስናቸው በእግዚአብሔር ዘንድ የተመሰከረላቸው ቅዱሳን ናቸው፡፡ ከእነርሱም ውስጥ ሞትን ሳያይ እንደነ ሄኖክና ኤልያስ የተሰወረ አለ፤ ከእነርሱም ውስጥ በባሕር ላይ ቤተ መቅደሱን ያነጸ አለ፤ ከእነርሱም ውስጥ የታዘዘ መልአክ መጥቶ ወደ ሰማይ ነጥቆ ወስዶት የቤተ መቅደሶቹን አሠራር ራሱ ጌታችን በቃሉ ያስረዳው አለ፡፡ ከእነርሱም ውስጥ በክህነቱ ሲቀድስ 40 ዓመት ሙሉ ቅዱስ ቁርባኑን መላእክት ከሰማይ እያመጡለት የነበረ አለ፡፡ እነዚህ ቅዱሳን ነገሥታት ገድላቸውና ትሩፋታቸው፣ ምግባር ሃይማኖታቸው እጅግ ድንቅ ነው፡፡
ከ10ኛው እስከ 13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን (920-1253 ዓ.ም ገደማ) በላስታ ቡግና ምድር የነገሡ የላስታ ቡግና ተወላጅ የሆኑ የኢትዮጵያ ቅዱሳን ነገሥታት የንግሥናቸው መጠሪያ ‹‹የዛጉዌ ሥርወ መንግሥት›› ወይም ‹‹የላስታ መንግሥት›› በመባል ይታወቃል፡፡ ከዛጉዌ ነገሥታት ውስጥ የመጀመሪያው ንጉሥ መራ ተክለሃይማኖት የዐፄ ድልነአድን ልጅ መሶበወርቅን አግብቶ አራት ልጆችን ወልዷል፡፡ ሦስቱ ወንዶች ጠንጠውድም፣ ግርማ ስዩምና ዣን ስዩም ይባላሉ፡፡ ጠንጠውድም ገብረ መስቀልን ወለደ፣ ግርማ ስዩም ቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስ ወለደ፣ ዣን ስዩም ደግሞ ቅዱስ ገብረማርያምንና ቅዱስ ላሊበላን ወለደ፡፡ ገብረ መስቀልም ጣራው ክፍት ሆኖ ዝናብ የማያስገባውን ገዳም የመሠረቱትን የመቄቱን ታላቁን አባት አቡነ አሮንን ወለደ፡፡ ቅዱስ ገብረማርያም ደግሞ ቅዱስ ነዓኵለአብን ወለደ፡፡
ቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስ በቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ሳለ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ‹‹ከጠንጠውድም በኋላ የምትነግሠው አንተ ነህ›› በማለት ከነገረው በኋላ በመንገዱ ሁሉ እየተራዳው ወደ ኢትዮጵያ ይዞት መጥቷል፡፡ በቤተ መቅደስ ገብቶ ሲቀድስ መላእክት ሰማያዊ ኅብስትንና ጽዋን አምጥተው እየሰጡት እርሱም ለሕዝቡ ሁሉ ያቆርባቸው ነበር፡፡ ሕዝቡን የሚባርክበትም መስቀል ከሰማይ ነው የወረደለት፡፡ ዛሬም ድረስ አለ፣ በዓል ሲሆን ካህናት አባቶች እያወጡ ሕዝበ ክርስቲያኑን ይባርኩበታል፡፡ ጌታችን ለይምርሃነ ክርስቶስ በአካል ተገልጦለት እስከ ዕለተ ምፅዓት ድረስ እንደማይፈርስ ቃልኪዳን የሰጠውንና አሁን በላስታ ላሊበላ ያለውን ቤተመቅደሱን በባሕር ላይ እንዲሠራ ነግሮት በኋላም በቦታው ላይ እጅግ አስደናቂ ቃልኪዳን ሰጥቶታል ደግ ንጉሥ፤ፃድቅ ካህን፤ቤተ መቅደሱን በባህር ላይ ያነፀ መሀንዲስ ከ፲፩የዛጉዌ ነገስታት አንዱ ንጉስም ቅዱስም የነበረው ይህ ቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስ ልደቱ ግንቦት 19 ቀን ነው። በላስታ ወረዳ ሳይ (ዛሬ ሸጐላ ማርያም) ከምትባል ቦታ ላይ ወንጌልን እያስተማረ፣ ድውያንን እየፈወሰ ተቀምጦ ፡፡ ትምህርቱንና ተአምራቱን ያዩት የአካባቢው ሰዎችም ‹‹ነፃነትና ፍቅር የሚገኝብህ የእግዚአብሔር ሰው ሆይ! እኛ ሰላማዊ ብርሃናዊ ብለን ስም አወጣንልህ፣ ያንተ ግን ስምህ ማን ይባላል ንገረን›› አሉት፡፡ እርሱም ‹‹ስሜ ይምርሃነ ክርስቶስ ነው›› አላቸው ይህኔ ሕዝቡ ሁሉ በሹክሹክታ ‹‹ይምርሃነ ክርስቶስ የሚባል ሲነግሥ ሃይማኖት ይቀናል፣ ፍርድ ይስተካከላል›› እያሉ አባቶቻችን ሲናገሩ ሰምተናል አሉ፡፡ ከጠንጠውድምም ሞት በኋላ ማንም እንዳልነገሠ ሲያረጋግጡ የማን ልጅ እንደሆነ እንዲነግራቸው በእግዚአብሔር ስም ለመኑትና የጠንጠውድም ታናሽና የዣን ስዩም ታላቅ ወንድም የሆነው የግርማ ስዩም ልጅ እንደሆነ ነገራቸው፡፡ እነርሱም ‹‹የተነገረው ትንቢት ደርሷልና ሳንዘገይ እናንግሠው›› ብለው ሥርዓተ መንግሥቱን ፈጽመው በዙፋን ላይ አስቀመጡት፡፡
ቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስ በትረ መንግሥቱን ከያዘ በኋላ ሁሉም ሰው በተለያዩ እንቅስቃሴዎቹ ውስጥ እንደ ወንጌሉ ቃል እንዲኖር በግዛቱ ሁሉ አወጀ፡፡ እግዚአብሔርም የሚመሰገንበትን ቤት መሥራት አሰበና የተፈቀደለትን ቦታ እንኪያገኝ ድረስ ዛዚያ በምትባል ልዩ በሆነች ስፍራ ድንኳን ተክሎ እንደ ሙሴ አምላኩን ማገልገል ጀመረ፡፡ በዚህም ቦታ ሕዝቡን ከሰማይ በወረደለት መስቀል እየባረከና እርሱ ለቅዳሴ በሚገባበት ጊዜ ከአምላኩ የሚሰጠውን ሰማያዊ ኅብስትና ጽዋ እያቆረበ ለ22 ዓመት በድንኳኗ ውስጥ ኖረ፡፡ ከነዚህ ሁሉ ዓመታት በኋላም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በክብር ተገለጠለትና እንዲህ አለው፡- ‹‹ወዳጄ ይምርሃነ ክርስቶስ ይህን ሥፍራ (ዛዚያን) ልቀቅ፣ ከእንግዲህ ወዲህ በዚህ ቦታ ሰማያዊ ኅብስትና ሰማያዊ ጽዋ አይወርድልህም፡፡ ወደማሳይህ ቦታ ተነሥተህ ሂድ፣ በዚያም እስከ ዕረፍትህ ቀን ድረስ ሰማያዊ ኅብስትና ሰማያዊ ጽዋ ይወርድልሀል፡፡ ይህን ዓለም ለማሳለፍ እስከምመጣበት እስከ ዕለተ ምፅዓት ድረስ የእኔ ጌትነት የአንተም የቅድስና ሕይወት የሚነገርበት፣ የሥጋህ የዕረፍት ቦታ የሚሆንበት፣ ለምትሠራው መቅደስ ክዳን የሚሆን ሣር የማትፈልግበት ሰፊ ዋሻ እሰጥሀለው ፣ በዚያ ቤተ መቅደሴን ሥራ፣ እኔ በምትሠራው ቤተ መቅደስ ከአንተ ጋር ለዘለዓለም ቃልኪዳኔን አቆማለሁ፡፡ በምታንጸው ቤተ መቅደስ ውስጥ ‹አቤቱ የይምርሃነ ክርስቶስ አምላክ ሆይ! ስለወዳጅህ ስለ ቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስ ብለህ ይቅር በለኝ› እያለ ‹አባታችን ሆይ!› የሚለውን ጸሎት የሚጸልይ ዕለቱን እንደተጠመቀ አደርገዋለሁ፡፡ ነገ ማለዳ ተነሥተህ ወግረ ስሂን ወደ ሚባለው የዕረፍትህ ቦታ ወደሚሆነው ዋሻ ሕዝብህን አስከትለህ ሂድ፤ በዚያም ቤተ መቅደሴን አንጽ›› ብሎ ቃልኪዳን ሰጠው።
ይምርሐነ ክርሰቶስም ሕዝቡን ይዞ ተነሳና አሁን ከቅዱስ ላሊበላ ቤተ መቅደሶች 42 ኪ,ሜ ርቀት ላይ ወደሚገኘውና ጥቁር አለታማ ተራራ ሥር ወዳለው የውግረ ስሂን ዋሻ አመራ። ሲደርስም ቦታው የሰዎች ይዞታ ሆኖ ስላገኘው እኔ ንጉሥ ነኝ ብሎ እነርሱን በግፍ ሳያስለቅቅ ካሳ ከፍሎ ስፍራውን ተረከባቸው። ውስጡ ግን ውሀ የቆመበት ባህርና ርኩሳት መናፍስት የሞሉት ስለነበር መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል መናፍስቱን አባሮ በባሕሩ ላይ ቤተ መቅደሱን እንዴት እንደሚያንጽ ገለጠለት።
እርሱም በተነገረው መሠረት ለግንባታው የሚያስፈልጉ እቃዎችን ከኢየሩሳሌም አስመጥቶ ማነጽ ጀመረ።የውሀውን ክፍል እንጨት ረብርቦ አፈር እየበተነ ደለደለው።
ሰዎች በባህር ላይ መሠራቱን እንዳይጠራጠሩም አነስተኞ መስኮትነገር አበጀለት። (በዚህችም አሁን ድረስ በክንድ ርቀት ያህል ከሥር ያለው ውሀ ይነካል።)ከበላዩም ስስ ሆነው የተፈለጡ ድንጋዮችን በኖራ እያቦካ በማያያዝ በእኩል መጠን እየገነባ በመሀከላቸው እንደ መቀነት የተጠረቡ እንጨቶችን በማስገባት አሳምሮ አነፀው። ውስጡንም በሦስት ቤተ መቅደሶች ከፈለው በየመስኮትና በየበሮቹም ላይ እንደ ዐይነ እርግብ ሆነው የተፈለፈሉ ሐረጎችን አደረገበት ጣሪያውንም በሰባቱ ሰማያት ምሳሌ ምስጢር ባላቸው የተለያዩ ቅርፆች አስዋበው።ይህን አድርጎ ሥራውን ከጨረሰ በኋላም የቅዱስ ገብርኤልን የእመቤታችንንና የቅዱስ ቂርቆስን ታቦታት አስገባበት።በድጋሚም ቤተ መንግሥቱን በዛው ዋሻ ውስጥ | 123 |
| 12 | No text... | 102 |
| 13 | «ሄሮድስ» በሚለው ስም የተጠሩ ነገሥታት
★ ★ ★
''ሄሮድስ'' የሚለው ስም ከኤዶም ዘር የተገኙ ቤተሰቦች ስም ነው። እነዚኽ ቤተሰቦች የአይሁድን ሃይማኖት ተቀብለው ቅድመ ልደተ ክርስቶስ ከ፵፯ ዓ.ዓ አስከ ፸፱ ዓ.ም የኖሩ የአይሁድ አገር ነገሥታትና ገዥዎች ሲሆኑ ከፍተኛ የማስተዳደር ችሎታ ነበራቸው። ነገር ግን ከሌላ ዘር በመሆናቸው (የሚመኩ ስለሆኑ)፣ ብዙ ብልግናም በመሥራታቸው፣ ሥልጣናቸውንም ከሮም መንግሥት ስለተቀበሉ፣ በአይሁድ መካከል የሚገኝ «የሄሮድስ ወገን» የሚባል ክፍለ ግዛት ነበራቸው። ቅዱስ ማርቆስ እንደጻፈልን። ክርስቶስ በምኵራብ እጁ የሰለለችበትን ሰው ሲያድን አይተው። «____እንዴት እንዲያጠፉት ከሄሮድስ ወገን ጋር መከሩበት።» [ማር ፫:፮] ነው የሚለው። በተጨማሪም በማር ፲፪:፲፫ ተመሣሣይ ነገር እናገኛለን። የሄሮድስ ወገን የሚላቸው በሄሮድስ ስም የተጠሩና የሄሮድስ ዘመዶች ናቸው። እነዚኽ የሄሮድስ ወገን ተብለው የተጠሩ በተለይም «ሄሮድስ» ተብለው የተጠሩ ነገሥታት ከክፋታቸው ብዛት አንጻር ጌታችንን «ከፈሪሳውያንና ከሄሮድስ እርሾ ተጠበቁ» ሲል አስገንዝቧል።
+ መጽሐፍ ቅዱስ ከዚኽ ቤተሰብእ መካከል የሚከተሉትን ሰዎች ስም ይጠቅሳል። ትቂቶችን ለመመልከት:-
➊. ታላቁ ሄሮድስ
- የአይሁድ ንጉሥ ሆኖ በ፴፯ ዓ.ዓ ነገሠ።
- በእስራኤል ሀገር ያለውን የቂሣርያ ከተማ ቆረቆረ።
- ቤተ መቅደሱን ማሳደስና ማስጌጥ ጀመረ።
- ጌታችንን ኢየሱስን አሳደደ።
- የቤተልሔም ሕፃናትንም አስገደለ። (ማቴ ፪:፩-፲፰)
- አሥር ሚስቶችን አገባ።
- ከቤተሰቡና ከውጭ ብዙ ሰዎችን ፈጀ።
- ከሞተ በኋላ መንግሥቱ ለሦስት ተከፈለ።
- ታላቁ ሄሮድስ የሞተበትን ጊዜ በትክክል ማወቅ ባይቻልም ሕፃኑ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በስደት በግብጽ ባለበት ጊዜ ስለሆነና ይኽ ንጉሥ በሞት እንደተለዬ ቅዱሱ መልአክ ገልጦላቸዋልና ከግብጽ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል። (ማቴ ፪:፳፩)
➋. ሄሮድስ አርኬላኦስ
- የታላቁ ሄሮድስ ልጅ ነው።
- በአባቱ በታላቁ ሄሮድስ ፋንታ በይሁዳ ነግሧል። (ማቴ ፪:፳፪)
- እስከ ፮ ዓ.ም ድረስ ይሁዳን ገዝቷል።
➌. ሄሮድስ ፊልጶስ
- የታላቁ ሄሮድስ ልጅ ነው። (ማቴ ፲፬:፫)
➍. ሄሮድስ አንቲጳስ
- የታላቁ ሄሮድስ ልጅ ሲሆን እስከ ፴፱ ዓ.ም ድረስ ገሊላን ገዝቷል።
- የወንድሙን የሄሮድስ ፊልጶስን ሚስት ሲያገባ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ስለዚህ ቢገሥጸው አሰረው። በሰይፍም አስቆረጠው። (ማቴ ፲፬:፩-፲፪)
- ይኽ ንጉሥ ኢየሱስ ክርስቶስ ቀበሮ ብሎ በመጥራት ጠባዩን ገለጠበት። (ሉቃስ ፲፫:፴፪)
- በጌታችን ሕማም ጊዜ ንጉሡ ጲላጦስ ኢየሱስን ሲልክለት ሄሮድስ በመናቅ ዘበተበት። ከሠራዊቱ ጋር አቃለለው። አፌዘበት። (ሉቃስ ፳፫:፮-፲፪)
➎. ሄሮድያዳ ብእሲተ ፊልጶስ
- የፊልጶስ ሚስት የነበረች ስትሆን ንጉሥ አግብታ ንግሥትነት መባል ስለፈለገች ፊልጶስን ትታ ወንድሙን ሄሮድስ አንቲጳስን ያገባች ናት።
- ከክፋት እንድትመለስ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ቢገሥጻት ንጉሡን አግባብታ ቅዱስ ዮሐንስን በሰይፍ አስቆረጠች። (ማቴ ፲፬:፩-፲፪)
- በኀጢአቱ ብዛት መሬት አፏን ከፍታ የዋጠቻት አረመኔ ሴት ናት።
እነዚኽን ጨምሮ በርካታ አላውያን ንግሥናቸውን፣ ሥልጣናቸውንና ታዋቂነታቸውን ተጠቅመው በርካታ የክፋት ሥራ ሠርተው አልፈዋል። የተመኩበት ሥልጣን አያስቀራቸውምና በክፉ አሟሟት ተወስደዋል። ከንግሥና ወርደው አፈር ትቢያ ሆነዋል። የሁላችንም መምህር የሆነው ቅዱሱ ንጉሥ ልበ አምላክ ነቢዩ ዳዊት እንዲህ አለ:-
«ኢይድኅን ንጉሥ በብዝኀ ሠራዊቱ። ወያርብሕኒ ኢድኅነ በብዝኀ ኀይሉ። ወፈረስኒ ሐሰተ ኢያድኅን። ~ ንጉሥ በሠራዊቱ ብዛት አይድንም። ኃያልም በኃይሉ ብዛት አያመልጥም። ፈረስም ከንቱ ነው፥ አያድንም።» (መዝ ፴፪:፲፮)
በኃላፊ ጠፊ ሟችና በስባሽ (በጉልበቱ በስክጣኑ ነገር ጭምር) የሚመካ ሰው ከንቱ ሰው ነው። መመካት የሚችል ግን በእግዚአብሔር አምኖ በእርሱ ይመካል እንጂ ራሱን እግዚአብሔርን ታግሎ መጣል አይቻልም። ይኽ መገዳደራቸው ነገሥታቱን ክብር እንዲያጡ አድርጓቸዋል። «ከእግዚአብሔር ጋር የሚጣሉ ይደቅቃሉ።» እንዲል (፩ኛ ሳሙ ፪:፲)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ይቆዬን !!! | 133 |
| 14 | በስመአም ወወልድ ውመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን
,በመስቀል መባረክ
ስልጣን ክህነት ያላቸዉ ካህናት በቅዱስ መስቀል እንዲባረኩና ምእመናንንም እንዲባረኩ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ታዛለች ።
[ በቅዱስ መስቀል የመባረክ እና የመባረክ ምሲጥር ]
1, በጌታችን ቅዱስ መስቀል አማካኝነት ስርአትን ኃጢያትን ለመቀበል
2, በጌታችን ቅዱስ መስቀል አማካኝነት ቡራኬን ማለት መንፈሳዊ ክብርንና ጸጋን ለመቀበል ነዉ።
==>> በመስቀል ምሳሊ በረከትንና ምርቃትን መስጠት በዘመነ ኦሪትም የተለመደነዉ ።በእርግጥ በኦሪት ዘመን መስቀል አልነበረም ። ስለዚህም አበዉ በመስቀል ምሳሊ እጃቸዉን እየዘረጉ ልጆቻቸዉን ይባርኩ እንደነበር መጽሓፍ ቅዱስ ይነግረናል። ለምሳሊ በዚሁ ቀጥሎ ያለዉን እንመልከት። ያቆብ በሸመገለ ጊዜ የልጅ ልጆቹን ኤፍሬምን ና ምናሴን ሊባርካቸዉ ፈለገ ፡ አባታቸዉ ዮሴፍም ሁለቱን ልጆቹን በያቆብ ቀኝእና ግራ አቆማቸዉ ፡እጆቹን አመሳቅሎ ባረካቸዉ ዘፍጥ. ( 48፡13)
==>>በዚሁ ዓይነት ካህናተ ኦሪት እጆቻቸዉን በማሳትና በማመሳቀል ህዝቡን ይባርኩ ነበር ። የቡራኬም ሥርአት ከእግዛአብሔር የተነገረ ነዉ ። እግዛአብሔር ለሙሴ እንዲህ ብሎ ነግሮት ነበር ፡ ""እግዛአብሔርም ሙሴን እንዲህ ብሎ ተናገረዉ ።ለእሮንና ለልጆቹ ንገራቸዉ። የእስራኤልን ልጆች ስትባርኩአቸዉ. እንዲህ በሉአቸዉ እግዛአብሔር ይባርክህ ፣ ይጠብቅህ፣ እግዛአብሔርም ፊቱን ያብራልህ ፣ይራራልህም እግዛአብሔር ፊቱን ወደአንታ ያንሣ ፣ሰላምንም ይስጥህ እንዲሁ ስሜን በስራኤል ልጆችላይ ያደርጋሉ እኔም እባርካችሆለሁ (ዘኁ 6፡22)
==>>የበረከት ባለቤት ና የበረከት መገኛ የሆነዉ ጌታችን እየሱስ ክርስቶስም ወንጌል በሚያስተምርበት ጌዜ የተቀደሱ እጆቹን እያነሳ (እያመሳቀለ )ምእመናን ይባርክ ነበር ። ለምሳሌ በሰንከተ ወንጌል. ጊዜ ለመባረክ ወደ እሱ የመጡትን ህፃናት ተቀብሎ እንዳቀፋቸዉና ቅዱስ ወንጌል ይመሰክራል (ማር 10፡10) ። ከሞት ተለይቶም ከተነሳም በሆላ ወደ ሰማያት ከማረጉ በፊት ደቀ መዛምርቱን ሰብስቦ. እጆቹን አንስቶ (አመሳቅሎ)ባረካቸዉ ፡እንደባረካቸውም ወደ ሰማያት ማረጉን ልቃስ መስክሮል (ሉቃ 24፡50)
==>ስለዚህ ጊታችን በሠራዉ ሥርዓት መሰረት የጌታችን ተከታይ ዋች የሆኑት ሊቃን ጳጳሳት ኢጲስ ቆጶሳትን ካህናት (ቀሳዉስት)በቅዱስ መስቀሉና እጆቻቸዉን በማመሳቀል ምእመናን ና ምእመናትን እንዲባርኩ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቴያን ታስተምራለች
ካህናት አባቶችንም እግዛአብሔር ለሙሴ ና ለአሮን የእስራኤል ልጆች ስትባርኩ እንዲህ በሉአቸዉ. በተባሉበት የቡራኬ ቃል መሰረት ይባርኩናል ። (ዘፍ 6፡22)
በረከታቸዉ ይደርብን አሜን
ወስብሃት ለእግዛብሔር
ወላወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክብር ይቆየን ~አሜን | 146 |
| 15 | “ባትመለሱ እግዚአብሔር ሰይፉን ይስላል” (መዝ.7፡12)፡፡
እግዚአብሔር እንደዚህ ዓይነት አነጋገርን የሚናገረው ለምን ይኾን? ሰማዕያኑ ከቁሳዊነት ጋር ካላቸው ቁርኝት የተነሣና በእነዚህ ጥንቱንም በሚያውቋቸው መንገዶች ሊያስፈራቸው ሊያስደነግጣቸው ብሎ ነው፡፡ ልብ በሉ! ወታደሮች የጦር ዕቃ መሣሪያን የሚታጠቁት ጠላታቸውን ለመቅጣት ነው፡፡ እግዚአብሔር የጦር ዕቃ መሣሪያ እንደ ያዘ ኾኖ መታየቱ ግን ሰዎችን ለመቅጣት ሳይኾን ፈርተን ወደ ቀልባችን እንድንመለስና ከመከራ [ሥጋ ከመከራ ነፍስ] እንድንድን ብሎ ነው፡፡ ስለዚህ “ሰይፍ” ብሎ መናገሩ የጥልቅ ፍቅሩ ምልክት ነውና የምንደነግጥ አንኹን፡፡
ቃላቱ ለመስማት እንኳን ጭንቅ የኾኑት ከፍጹም ቸርነቱ የተነሣ ነው፡፡ እንደምታውቁት፥ አባቶች ልጆቻቸውን እንዳይቀጧቸው ሲፈልጉ አምርረው ይቈጧቸዋል፡፡ እግዚአብሔርም እንደዚሁ በኃይላተ ቃላቱ ፍርሐታችንን ከፍ የሚያደርገው እንዳይቀጣን ስለሚፈልግ ነው፡፡ እሳተ ገሃነም እንዳዘጋጀ የሚነግረን በእሳተ ገሃነም እንዳይቀጣን ብሎ ነው፡፡ ስለ መንግሥተ ሰማያት ከተነገረው በላይ በወንጌላት ውስጥ ስለ ምረረ ገሃነም ተጽፎ የምናገኝበት ዋናው ምክንያትም ይህ ነው፡፡ ልል ዘሊላን የኾኑ ሰዎች ዘንድ የምረረ ገሃነም ፍርሐት ያህል ወደ ምግባር ስለማይመራቸውና ከክፋት እንዲርቁ ስለማያደርጋቸው፥ ስለዚሁ ምክንያት እግዚአብሔርም ከጣዕመ መንግሥተ ሰማያት ይልቅ አብዝቶ ስለ ምረረ ገሃነም ይናገራል፡፡ ስለዚህ የሚያስፈሩ የሚያስነግጡ ቃላትን ባደመጥን ጊዜ የሚሰጡን በቁዔት ብዙ የብዙ ብዙ ነውና የምንታወክ አንኹን፡፡
ይልቅ የእግዚአብሔር በአንድ መልኩ ታጋሽ፥ በሌላ መልኩ ደግሞ ፈታሒ በጽድቅ ኰናኒ በርትዕ መኾኑን እናስብ፡፡ አስታውሱ! እግዚአብሔር ታጋሽ ነው፡፡ ስለዚህም ተስፋ ድኅነት የለንም አንበል፡፡ ግን ደግሞ እግዚአብሔር እውነተኛ ፈራጅም ነው፡፡ ስለዚህም ልል ዘሊላን አንኹን፡፡ በዚህ ዓለም ብዙ የብዙ ብዙ ይታገሣል፤ በወዲያኛው ዓለም ግን እዚህ ካሳያቸው ትዕግሥቱ ረብ ጥቅም ያላገኙት ሰዎች ለምረረ ገሃነም አሳልፎ ይሰጣቸዋል፡፡ እንግዲያውስ ዕጣ ፈንታችን ፅዋ ተርታችን ይህ እንዳይኾን በዚህ ዓለም ሳለን ከትዕግሥቱ የምንጠቀም እንኹን ብዬ እነግራችኋለሁ፡፡
(#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ በ ገብረ እግዚአብሔር ኪደ) | 216 |
| 16 | ክርስቲያንን እወቅ!
==========
ክርስቲያን የተነሣ ቀን ከተማን ምድረበዳ የሚያደርግ እሳት መኾኑን ላልተገነዘብክ ወዮልህ!
ክርስቲያን የኢያሪኮን ግንብ የሚያፈርስ መኾኑን ሳታውቅ በተከበብክበት አጥር ለተመካህ ወዮልህ!
ክርስቲያን በጠጠር ብረት ለበሱን የገነደሰ መኾኑን ያላወቅከው ጎልያድ ኾይ ወዮልህ!
ክርስቲያን በእጅ በተያዘች በትር ባህርን ከፍሎ ንጒሥን ከነሠራዊቱ ያሰጠመ መኾኑን የዘነጋህ ፈርኦን ኾይ ወዮልህ!
ክርስቲያን ሲሞን መሠርይን በነፋስ አውታር አንሳፎ መልሶ ወደምድር የፈጠፈጠው መኾኑን ያላወቅህ ወዮልህ!
ክርስቲያን ጠላቶቹን አፈር ከድሜ እስኪያበላ ድረስ ፀሐይን እንኳን የገዘተ መኾኑን ያልተገነዘብክ ወዮልህ!
ክርስቲያን መስቀለ ክርስቶስን በዓለም ላይ ኃያል ከሚባል ንጉሥ እጅ በጥቂት ቀናት ውስጥ ያስለቀቀ መኾኑን ያልሰማህ ወዮልህ!
ክርስቲያን ጣልያንን እንደክክ የከካ፣ እንደሊጥ ያቦካ መኾኑን የረሳህ ወዮልህ!
ክርስቲያን ምድርን ጭምር በመገዘት ጠላትን ምድሪቱ እንትፍ ብላ እንድትተፋው ማድረጉን የረሳህ ወዮልህ!
ዐርበኛውን ብጹዕ ወቅዱስ ቅዱስ ጴጥሮስን የረሳህ ተላላኪ ኾይ ወዮልህ ወዮታ አለብህ!
የምኒልክን ደቋሽ ክንድ የረሳህ ወዮልህ!
የአሉላ አባነጋን ጥበብ ዘንግተህ ሰላይ ባልካቸው ሰላላ አሽከሮችህ የተማመንክ ኾይ ወዮልህ!
አውሎ ነፋሱ ዳርሳሞ ኬሮን የረሳኸው ኾይ ወዮልህ ወዮታ አለብህ!
ናቡከደነጾርና በተዳፈረ ጊዜ ለሰባት ዓመታት ጥፍርና ጅራት አስበቅሎ ሣር ያስጋጠውን የረሳህ ትምክህተኛ ወዮልህ!
የሐማን ጉድ ያልሰማህ ባንዳ ኾይ ወዮልህ!
ቅዱስ ገብርኤል ሲቈጣ መጋረጃውን ከኹለት እንደሰነጠቀው፣ ሰይፉ እስከ ኅልቀተ ዓለም እንደሚሰጥምም ያልሰማህ ኾይ ወዮልህ!
እነዚያ ቤተመቅደሱን የተዳፈሩትን መሬት ተከፍታ እንደዋጠቻቸው ያልሰማኸው ተረኛ ዳታን ኾይ፣ ተረኛ አቤሮን ኾይ ወዮልህ!
ለዕለት ዕንጀራ ስትል ብኵርናህን የሸጥከው ኤሳው ኾይ ወዮልህ!
አውሮጳ ሞኝ አይደለም ጅል ነው። ቀድሞ እራሱ መጥቶ አፈር ተድሜ መብላቱን እያወቀ አንተን ተላላኪውን አሰልጥኖ መላኩ ጅል ያሰኘዋል።
በሮማው ፖፕ መድፍ አስባርኮ ኢትዮጵያን ካቶሊክ አደርጋለሁ ብሎ የደከመው እንዳልተሳካለት እያወቀ አንተን አሰልጥኖ ኢትዮጵያን ፕሮቴስታንት አደርጋለሁ ማለቱ ጅል ያሰኘዋል።
ዐረቡ ጅል ነው!
ከጣልያን ውርደት ያልተማረው ዐረቡ ጅል ነው። በሥጋ ዘመድ የሚኾነው ገበዝ ጊዮርጊስ በኢትዮጵያ ጉዳይ ለማንም እንደማይራራ የረሳው ዐረቡ ጅል ነው።
ላንተ ግን ወዮልህ!
እነዚህን ኹሉ ጌቶችህ አድርገህ ቤተክርስቲያንን ከፍ ዝቅ አድርገህ ላየሃት ወዮልህ!
እንደይሁዳ በአንደበትህ እየሸነገልክ ፓትርያርክ አበውን ዕቅፍ አድርገህ የሳምክ፣ በልቦናህ ግን አሳልፈህ ለመስጠት ያሴርክ ላንተ ወዮልህ!
ክርስቲያኖች አፈርና ውሃ ብቻ ሳይኾኑ ነፋስና እሳትም እንደኾኑ ዘንግተኻልና ወዮልህ!
የቅዱስ ጴጥሮስ ልጆች ዝም ቢሉ አጠገብህ የሌሉ መስሎሃልና ወዮልህ!
የምኒልክን ልጆች ረስተሃልና ወዮልህ!
የሀብተጊዮርጊስን ልጆች ዘንግተሃልና ወዮልህ!
የጣይቱን ልጆች ዘንግተሃልና ወዮልህ!
የቴድሮስን ልጆች ረስተሃልና ወዮልህ!
የበላይ ዘለቀን ልጆች ረስተሃልና ወዮልህ!
የቃቄ ወርድወትን ልጆች ረስተሃልና ወዮልህ!
የብጹዕ አባ ሚካኤልን ልጆች ረስተሃቸዋልና ወዮልህ!
የቀዳማዊ ኃይለሥላሴን ልጆች ረስተሃቸዋልና ወዮልህ!
ብዙ ሠራዊት አለኝ አልክ!
ክርስቲያን በአህያ መንጋጋ እልፎችን ያረገፈ መኾኑን ዘንግተሃልና ወዮልህ!
ጌድዮን በጥቂት ሠራዊት የሰራውን ተአምር ዘንግተሃልና ወዮልህ!
አንተ ዘንድ ካሉ ሥጋ ለበሶች ይልቅ እኛ ዘንድ ያሉት እጅግ እንደሚበዙ ኤልሣዕ የነገረህን መስማት አልፈለግክምና ወዮልህ!
በእግዚአብሔርና በማደሪያው ላይ አፍህን ከፍተሃልና ወዮልህ!
አሕዛብን በብረት በትር የሚገዛቸውን ንጉሥ የወለደችውን ሴት ትዋጋ ዘንድ በባሕር አሸዋ ላይ ቆመሃልና ወዮልህ!
ሙሴን ያስተማረችው ኢትዮጵያን ትገዳደራት ዘንድ ተልእኮህን ለመፈጸም ሽተኻልና ወዮልህ!
በምድራውያን ሠራዊት ከመከበብህ የተነሣ እግዚአብሔር ተዋጊ መኾኑን ረስተሃልና ወዮልህ!
በዲ.ን ዶክተርኢያሱ አንጋኒ | 219 |
| 17 | Kitaabotni maxxansi isaanii dhumee RAAJII MAARIYAAMII FI SINKISAARAA ture Suuqii Waldaa Duuka Bu'ootaa Finfinneetti ni argamu
0931656264 bilbiluun bakka jirtanii ajajachuu dandeessu | 300 |
| 18 | *+* ድርሳንና የገድል ልዩነት ምንድን ነው? *+* ፨ ¶¶¶
<><><><><> * ተ * <><><><><>
“በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ብዙ ጊዜ ድርሳንና ገድል ሲባል እንሰማለን፡፡
የድርሳንና የገድል ልዩነት ምንድነው ?
የድርሳንና የገድልን አንድነትና ልዩነትን እንመልከት!
+* ድርሳንና ገድል በቤተ ክርስቲያን የማይነሡበት ጊዜ የለም፡፡
+* "የኑሮአቸውን ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነት ምሰሏቸው” ዕብ.(13፥7 )
እንደተባለው በሃይማኖትና በምግባር ለመጠንከር ገድለ ቅዱሳንን የያዙ
መጻሕፍትን እናነባለን፤ እንጸልይባቸዋለን፡፡ የቅዱሳን መላእክትንም ጠባቂነት፣
የሊቃውንትን ተግሣጽ ትርጓሜና ምክር የዕለተ ሰንበትን ክብር እና የኢየሱስ
ክርስቶስን የቤዛነት ሥራ የሚናገሩ ድርሳናትን ሁል ጊዜ እናነባለን እናደርሳለን፡፡
*አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መጽሐፈ ሰዋሰው ወግሥ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ
በተባለው መጽሐፋቸው “ድርሳን” የሚለውን ቃል እንዲህ ብለው ይፈቱታል
“ድርሳን በቁሙ “የተደረሰ፣ የተጣፈ፣ ቃለ ነገር፣ ሰፊ ንባብ፣ ረዥም ስብከት፣
ትርጓሜ፣ አፈታት፣ ጉሥዐተ ልብ፣ መዝሙር፣ ምሥጢሩ የሚያጠግብ፣ ቃሉ
የተሳካ፣ ጣዕመ ቃሉና ኃይለ ቃሉ ደስ የሚያሰኝ ልብ የሚነካ” ማለት ነው፡፡
*+ ድርሳን ስለ ቅዱሳን መላእክት፣ ተራዳኢነት ስለ እመቤታችን ቅድስት
ድንግል ማርያም አማላጅነት ክብርና ጸጋ፣ ስለ ዕለተ ሰንበት ክብርና ስለ ኢየሱስ
ክርስቶስ የማዳን ሥራ የሚናገሩ /የሚያትቱ/ መጻሕፍት ማለታችን ነው፡፡
*እስከ 2000 ዓ.ም በተደረገው ጥናት ወደ 138 የሚሆኑ በድርሳን ስያሜ
የሚጠሩ መጻሕፍት እንዳሉ ታውቋል፡፡ ከእነዚህም ውስጥ 11ዱ የመላእክት
ድርሳናት ሲሆኑ የ11ዱ መላእክት ስምም ቅዱስ ሚካኤል፣ ቅዱስ ገብርኤል፣
ቅዱስ ሩፋኤል፣ ቅዱስ ራጉኤል፣ ቅዱስ ዑራኤል፣ ቅዱስ አፍኒን፣ ቅዱስ ፋኑኤል፣
ቅዱስ ሳቁኤል፣ ቅዱስ ሱርያል፣ ቅዱስ ሱራፌልና ቅዱስ ኪሩቤል ናቸው፡፡
+* የመላእክት ድርሳናት በአብዛኛው ተመሳሳይነት ባሕርይ አላቸው፡፡
የውስጥ ይዞታቸውም በ5 ይከፈላል፡፡ እነሱም፦
+* መቅድም፣
+* ድርሳን፣
+* ተአምራት፣
+* አርኬና ,
+* መልክእ ናቸው፡፡
* ከእነዚህ ክፍሎች ውስጥ ድርሳን የምንለው የባለ ድርሳኑን መልአክ ግብር
በፈጣሪው ዘንድ ያለውን ሞገስ የሠራቸውን ተአምራት ከመጽሐፍ ቅዱስና
ከሌሎች ቅዱሳት መጻሕፍት ጋር እያጣቀሰ የሚያብራራ ክፍል ነው፡፡
<><>< * በአጠቃላይ ድርሳንን በ4 መክፈል ይቻላል፡፡
+* ድርሳነ መላእክት የሚባለው ድርሳነ ሚካኤል ድርሳነ ገብርኤልን
የመሳሰሉትን
. ነው፡፡
+* ድርሳነ ሰንበት ስለ ዕለተ ሰንበት ክብር የሚያብራራ መጽሐፍ ነው።
+* ድርሳነ መስቀል ደግሞ የመስቀሉን ታሪክና አመጣጥ ይተርካል፡፡
+* ድርሳነ ሊቃውንት ደግሞ የእነ ቅዱስ አትናቴዎስ የእነ ቅዱስ ኤፍሬም ድርሳን
. የሚባለው ነው፡፡ ድርሳን ዘቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ድርሳን
ዘቅዱስቄርሎስንም
. ያጠቃልላል፡፡
+* ድርሳነ ማኅየዊና ድርሳነ መድኀኔ ዓለም የመሳሰሉት ድርሳናት የኢየሱስ
. ክርስቶስን ጸዋትወ መከራ የሚያዘክሩ ድርሳናት ናቸው፡፡
+* ገድል፡-
+* “በቁሙ ትግል ፈተና ውጊያ ሰልፍ ድልና አክሊል እስኪገኝ ድረስ የሚደክሙት
ድካም የሚሠሩት ሥራ የሚቀበሉት መከራ ማለት ነው” ሲሉ ደስታ ተክለ ወልድ
በመዝገበ ቃላት ፍቺያቸው አስቀምጠውታል፡፡
+* አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌም ገድል ማለት ጻድቃንና ሰማዕታት በሕይወት
ዘመናቸው እያሉ የሠሩትን ሥራ የሚናገር መጽሐፍ እንደሆነ አብራርተዋል።
* ደስታ ተክለ ወልድ 2036፣ *አለቃ ኪዳለ ወልድ ክፍሌ 301/ የገድል
መጻሕፍት ጻድቃን፣ ሰማዕታት ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ትእዛዘ እግዚአብሔር
እንዲከበር ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን እንዲጠበቅ ከአላውያን ነገሥታት፣ ከቢጽ
ሐሳውያን፣ ከጠላት ዲያብሎስና ከፈቃደ ሥጋ ጋር ያደረጉትን ተጋድሎ የሚያወሱ
መጻሕፍት ናቸው፡፡
ሃይማኖታቸው በኑሮአቸው እንዴት እንደተገለጠ የሚያሳዩን የሕይወታቸው
መስተዋቶች ናቸው፡፡
* ስለዚህ ገድል ስንል የቅዱሳን ታሪክ፣ ተአምራት፣ ቃል ኪዳንና መልእክት የያዘ
መጽሐፍ ነው፡፡ይህ እንዲህ ይሆናል ይቻላል ተብሎ የተነገረው ቃል በእውነት
የሚኖር በቃልና በሥራም የሚገለጥ እንደሆነ የምናየው በቅዱሳን ገድል ነው፡፡
/ማቴ.10፥37፣ ሉቃ.14፥27፣ 1ቆሮ.11፥26-28/
ገድል መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት አለው። /2ቆሮ.11፥23-22
ዕብ.11፥32-40/ ራሱ የሐዋርያት ሥራ የምንለው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል
የሐዋርያትን ግብር /ሥራ/ ገድልና ዜና የሚያስረዳ መጽሐፍ ነው፡፡
*ከብሉይ ኪዳንም መጽሐፈ ጦቢት መጽሐፈ አስቴር፣ መጽሐፈ ሶስና፣
የመሳሰሉት በሰዎቹ ኑሮ የተገለጠውን የእምነታቸውን ፍሬ የሚያሳዩ የገድል
መጻሕፍት ናቸው፡፡
*+* ገድላት በ3 ይከፍላሉ እነሱም፡-
ገድለ ሰማዕታት፡- ለምሳሌ ገድለ ጊዮርጊስ፣ ገድለ ፋሲለደስ፣ ገድለ
ኢየሉጣ
ገድለ ሐዋርያት፡- በአንድነት የተሰበሰቡ የሐዋርያት አገልግሎት ተአምራት
መከራ የያዙ መጽሐፍት።
ገድለ ጻድቃን፡- ገድለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት፣ ገድለ ገብረ መንፈስ ቅዱስና
የመሳሰሉትን ነው፡፡
ምላሹን ለማጠቃለል ድርሳን ሲባል የመላእክትን ግብር በፈጣሪያቸው ዘንድ
ያላቸውን ሞገስና የሠሯቸውን ገቢረ ተአምራት እየዘረዘሩ የሚናገሩ፣ ስለ ዕለተ
ሰንበትና ቅዱስ መስቀል ክብር የሚያስረዱ ድርሳነ ሰንበትንና የድርሳነ መስቀል፣
የመጻሕፍት ትርጓሜ ምክርና ተግሣጽ እንዲሁም ርትዕት የሆነችውን ሃይማኖት
የመሰከሩበት የሊቃውንት መጻሕፍት፣ በመጨረሻም የኢየሱስ ክርስቶስን
ጸዋትወ መከራ የሚያስታውሱ እንደእነ ድርሳነ ማኅየዊ ያሉት መጻሕፍት በድርሳን
ሥር ይጠቃለላሉ፡፡
ገድል ደግሞ ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ጥበብ
የቅዱሳንን መከራ ተጋድሎ፣ ተአምራትና ቃል ኪዳን የያዙ የቤተ ክርስቲያን
ሕያውነት የሚገለጥባቸው መጻሕፍትናቸው፡፡
ድርሳናትም ሆኑ ገድላት ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር የማይጋጩ መጽሐፍ ቅዱስን
የሚያብራሩ የሚተረጉሙና የሚተነትኑ መጻሕፍት ናቸው፡፡
ሰፋ ያለ ግንዛቤ እንዲያገኙ ሐመረ ተዋሕዶ 1999፥61፣ ሐመር ጥር/
የካቲት 2000፥27 አዋልድ መጻሕፍት ማኅበረ ቅዱሳን፣ ሜጋ ማተሚያ ቤት
1995፣ የኢዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትናንት ዛሬና ነገ፣ ብራና
ማተሚያ ቤት፣ ማኅበረ ቅዱሳን፣ 1995፥16 የሚሉ መጻሕፍትና መጽሔቶችን
ቢያነቧቸው መልካም ነው፡፡ .ይቆየን
+* እግዚአብሔር አምላክ በመላእክት ተራዳኢነት በቅዱሳን ጸሎት ሁላችንንም
. ይጠብቀን፡፡ አሜን።
<> ዲ/ ን ኅሩይ ባየ.
<> ጥር 30 /2004 ዓ.ም | 194 |
| 19 | በህይወት እስካለህ ልትሳሳት ፣ ልትወድቅ ትቸላለህ ፣ ሰዎች ላይቀበሉህ ይችላሉ ፣ ወይም ሀሳብህን ላይረዱህ ፣ ቦታ ላይሰጡህ ይችላሉ ፣ በእጅህ ላይ ያለው ሙሉ በሙሉ አመድ ሆኖ ልታገኘው ትችላለህ ፣ ሰዎች ሊጠሉህ ፣ ሊያሙህ ፣ ወይ ስም ሊያወጡልህ ፣ አሊያም ሊስቁብህ ፣ ይችላሉ።
:
" በህይወት ውስጥ ትልቁ ስህተት ለሁሉም ሰው ትክክለኛ ሆኖ ለመታየት መሞከር ነው። መልካም ብትሆን ክፉዎች ይጠሉሀል። አዋቂ ብትሆን አላዋቂዎች ባዶነታቸውን ስለምትገልጥባቸው አብዝተው ይፀየፉሀል። ብርሃናዊ ራዕይ ቢኖርህ የጨለምተኞችን ጨለማ ስለምታሳይ መኖርህ ያንገበግባቸዋል። ነፃ አውጭ ብትሆን ጨቋኞች ያሳድዱሀል።
:
ምናለፋህ በአለም ስትኖር በሙሉ ድምፅ ልትወደድም፣ ልትጠላም አትችልም። ስለዚህ በደረስክበት ሁሉ ልክ እንደ ውሃ ቅርፅህን አትቀያይር! ከምንም በላይ በፈጣሪህ ፊት ትክክል ሁን!"
አንድ ነገር ልንገራችሁ!
:
በህይወታችሁ ማንንም አትውቀሱ
ጥሩ ሰዎች ደስታን ይሰጡዃችሀል
መጥፎ ሰዎች ልምድ ይሆኑዃችሀል
ክፉ ሰዎች ማስጠንቀቂያ ይሆኑዃችሀል
ምርጥ ሰዎች ትዝታ ይሆኑዃችሀል
በፍቅር ዋሉ♥
ዛጉዌያዊ እይታዎች ! | 157 |
| 20 | ሁለት ምክር
1 አገው ምድር ተወልደህ አገው ሁነህ እውነት ፍልሚያው ስርዓቱ ጋር ነው ብለህ ሳታውቅ የገባህ ፋኖ የተባለው ቡድን ጋር ተሰልፈህ ወገንህን አብረህ የምትወጋ ካለህ ራስህን ለይ !
ፍልሚያው እና ትግሉ መስመር ሌላ ነው ።
2 አገው ምድር ተወልደህ ውጊያውን ከስርአቱ ጋር እና ከገዢ መደቡ ጋር ነው ብለህ በገንዘብ በቁሳቁስ የምትረዳ ተቆጠብ እየገደሉ ያሉት ምስኪን የአገው ምድር አርሶ አደሮችን ነው።
=> እየተደረገ ያለው በክልል3 ያሉ ሌላ ቋንቋ ተናጋሪዎችን ማጥፋት ዘመቻ ነው እንጂ ስርዓቱጋ እየተዋጉ እንዳልሆነ እወቁ🙏
ምክሬ ለሚሰሙ ሲሆን በቡና አተላ የተገዙትን እና የሻዕቢያን ፍርፋሪውችን አይመለከትም! | 231 |
