cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

ቀሲስ ስንታየሁ የኔአባት

በዘመናዊው ቴክኖሎጂ ታግዘን ስለ ህይዎታችን የምንወያይበት፣ የምንመካከርበት እና የምንጠያይቅበት የቴሌግራም ገፅ ነው! ለማግኘት @KSintayehu ማዕከለ አራዊት ንኬልኅ አልቦ ዘይሰምዐነ እስመ አራዊት ይቤዝኁ እምኔነ መኑ ጠቢብ ወመለብው ከመ እግዚአብሔር አገው!

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
690
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
+130 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

ህዳር 25 ✝️ እንኳን ለቅዱስ መርቆሬዎስ ንግስ በአል አደረሳችኹ❤ ለክርስትና ሃይማኖት የሚከፈል ትልቁ ዋጋ ሰማዕትነት ነውና ቤተ ክርስቲያን ለምስክሮቿ ሰማዕታት ልዩ ክብር አላት። ከኮከብ ኮከብ እንዲበልጥ ሁሉ ከሰማዕታትም ቅዱስ ጊዮርጊስን እና ቅዱስ መርቆሬዎስን የመሰሉት ደግሞ ክብራቸው በእጅጉ የላቀ ነው። ቅዱስ መርቆሬዎስን ብዙ ጊዜ ሊቃውንት "ካልዕ (ሁለተኛው) ሊቀ ሰማዕታት" ሲሉ ይገልጹታል። ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ፦ በሁለተኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጨረሻ አካባቢ ከሮም ግዛቶች በአንዱ (አስሌጥ) ከአባቱና ከሚስቱ ጋር የሚኖር "አሮስ" የሚሉት ሰው ይኖር ነበር። ሚስቱ ደም ግባት የሠመረላት እርሱም ደግነት ያለው ሰው ቢሆኑም የሚያመልኩት ግን ጣዖትን ነበር። አንድ ቀን አሮስ ሚስቱን ከቤት ትቶ ለአደን ከአባቱ ጋር ወጣ። እንደ ልማዳቸው ወጥመዱን አስተካክለው ተደበቁ። የወጥመዱ ደወል ሲያቃጭል "እንስሳ ተያዘልን።" ብለው ሲሯሯጡ ዓይናቸው ያየው ነገር በድንጋጤ እንዲፈዙ አደረጋቸው። ሁለት ገጻተ ከለባት በወጥመዱ ውስጥ ተይዘው ነበር። እነዚህ ፍጡራን ሰዎች ናቸው። ግን ባልታወቀ የተፈጥሮ አጋጣሚ እንደዚህ እንደ ሆኑ ይታመናል። ግን እጅግ ግዙፍ፣ ከአንገታቸው በላይ እንደ ውሻ፣ ወገባቸው እንደ ሰው፣ ጉልበታቸው እንደ አንበሳ ሲሆን ታችኛው እግራቸው የጋለ የናስ ብረት የሚመስል ነው። እነዚህን ፍጡራን ሰማያዊ ካልሆነ ምድራዊ ፍጡር አይችላቸውም። አንበሳና ነብርን እንኳ እንደ ጨርቅ በጣጥሰው ይጥሏቸው እንደ ነበር ይነገራል። ዓይናቸው እንደ እሳት ይነድ ስለ ነበር ማንም ትክ ብሎ ሊያያቸው አይችልም። ምሥጢራቸውን ግን የሚያውቀው የፈጠራቸው አምላክ ነው። ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና አሮስና አባቱ ባዩአቸው ጊዜ ደንግጠው ወደቁ። ገጻተ ከለባቱ የብረት ወጥመዱን እንደ ክር በጣጥሰው የአሮስን አባት በቅጽበት በሉት። አሮስን ሊበሉት ሲሉ ግን ድንገት ቅዱስ መልአክ ወርዶ በእሳት ሰይፍ አጠራቸው። "ከእርሱ የሚወጣ ቅዱስ ፍሬ አለና እንዳትነኩት።" አላቸው። ወዲያውም መልአኩ ያንን ኃይለኝነታቸውን አጠፋው። በዚህ ጊዜ ሁለቱም ወደ አሮስ ሒደው ሰገዱለት። አሮስም ወደ ቤቱ ወስዶ ደበቃቸውና የሆነውን ሁሉ ለሚስቱ ነገራት። ጥቂት ቆይታም ጸንሳ ወለደች። ልጃቸውን ፒሉፓዴር (ፒሉፓተር) ሲሉ ስም አወጡለት። ትርጉሙም "መፍቀሬ አብ - የአብ ወዳጅ" ማለት ነው። ከዚያም አሮስ ሚስቱን፣ ልጁንና ሁለቱን ገጻተ ከለባት ይዞ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሒዶ ተጠመቀ። አበው ካህናት እሱን "ኖኅ"፣ ሚስቱን "ታቦት"፣ ልጁን ደግሞ "መርቆሬዎስ" ሲሉ ሰየሟቸው። መርቆሬዎስ ማለትም "ገብረ ኢየሱስ ክርስቶስ - የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ" እንደ ማለት ነው።
Hammasini ko'rsatish...
3
#የሉም_ሞተዋል የሉም ሞተዋል ሲሉን ኖረን የሉም ጠፍተዋል ሲሉን በዝተን አለን በእግዚአብሔር ሁሉን አልፈን አለን በጌታ ሁሉን አልፈን ለካ ሰው ሰለሮጠ አይቀድምም ጉልበታም ስልታገለ አይጥልም ጎልያድ ወድቋል በዳዊት ጠጠር የኛ አምላክ ስሙ ከፍ ይበል ይክበር እግዚአብሔር ስሙ ከፍ ይበል ይክበር አዝ = = = = = በሚነድ እሳት መሐል ሆነን አልሞትንም ዛሬም አለን በዝተን ያልሰማ ሁሉ ይስማ ይግረመው ያመለክነው እግዚአብሔር እንዲህ ነው(፪) አዝ = = = = = ጨክነን እኛ ሰይፉን ባንመዝ በእጃችን ጦር ጉመድን ባንይዝ ይዋጋል ዝም አይልም እግዚአብሔር ልጆቹን ፈጥሮ አይሰጥም ለፍጡር(፪) አዝ = = = = = አሕዛብ ሥጋችንን ሊያጠፉ ቢደክሙ ብዙ ዘመን ቢለፉ ካሸናፊዎች ሁሉ በልጠን አልሞትንም ዛሬም አለን በዝተን(፪)
Hammasini ko'rsatish...
አዲሳልም_የድራ_ልጅ_የሉም_ጥፍተዋል_ሲሉን_በስትን.m4a7.48 KB
👍 1👏 1
ወደ ቤተ መቅደስ ሲገቡ ስልክ ማጥፋትዎን አይርሱ ከሚል ማስታወቂያ እየቀደሱ ቲክ ቶክ ወደመግባት የተሸጋገርን ደግሞ መቼ ነው? ሰው እንዴት እንኳን እየቀደሰ ይቅርና መቅደስ ውስጥ ለምን ስልኩን ይከፍታል?
Hammasini ko'rsatish...
ንግስተ ሰማያት ንግስተ ሰማያት ወምድር ማርያም ድንግል /2/ ተፈጸመ /5/ ማኀሌተ ጽጌ /2/
Hammasini ko'rsatish...
ተፈጸመ_5_ማኅሌተ_ጽጌ_2__xAdoeHiXzJk_139.m4a9.23 KB
✏ጠሪ አክባሪ ነው ! 👉ታላቅ የመጽሐፍ ምርቃት ♣ ኅዳር ፰ ቀን ሌላ ቀጠሮ እንዳትይዙ አደራ እላለኹ! በዕለቱ፥ ስለ ጠቢበ ጠቢባን ቁም ነገርን የምትቀሥሙበት መንፈሳዊ ጉባኤ ተዘጋጅቶ ይጠብቃችኋል!! ♣ለበለጠ መረጃ፦ ኅዳር ፰ ቀን ፳፻፲፮ ዐ.ም፥ በዕለተ ቀዳሚት ሰንበት፥ ከቀኑ ፯ ሰዓት ጀምሮ በማኅበረ ቅዱሳን አዳራሽ በአካል መሳተፍ ይቻላል!! 📍ጠሪው፦ ኤፍሬም የኔሰው (የጠቢበ ጠቢባን ተርጓሚ፣ አዘጋጅ እና አሳታሚ)።
Hammasini ko'rsatish...
ምን መፍትሔ ሰጠኸውና? ያየህውን ሥራ ሁሉ እሰራለሁ የሰማኸውን ትምህርት ሁሉ እማራለሁ አትበል። ይህ የተሰወረው የቅንዓት ጠባይ ነውና። ሁሉን ልያዝ ማለትም ዝንጉ አድረጎ እንዳያስቀርህ ሁሉም ውስጥ ልኑር አትበል። --- ቆንጆዎች ቁንጅናቸው ሁሉን የሚተካ እየመሰላቸው ከዕውቀትና ከትሕትና ይርቃሉ። ሁሉንም ሰው በመልካቸው የሚማርኩት ስለሚመስላቸው ኩሩና ተንኮለኞች ይሆናሉ። አንተ ግን ቆንጆ ወዳጅን እንጂ ቆንጆ ቁመናን አትሻ፤ ቆንጆ ትዳርን እንጂ ቆንጆ ሴትን አትመኝ፤ የላይ ነገር ከንቱና ኀላፊ ነውና በሚፈርስ አካል፣ ኑሮ በሚለውጠው መልክ አትደለል። --- ቂም አፍን የሚያመር፣ ልብን የሚያነቅዝ፣ ተግባርን የሚያልፈሰፍስ ነውና ለበደለህ ሰው ቅያሜህን ግለጥለት፤ ቂመኝነት በክፉ መሸነፍ እንጂ ጀግንነት አይምሰልህ። --- ከህሊናህና ከመንፈሳዊ አማካሪህ ሳትመክር ምንም ነገር አትወስን፤ አጥርተህ ሳትሰማ ቃል አትግባ። መከራ ካልደረሰ በቀር ባል በሌለበት ቤት ውስጥ ከሚስቲቱ ጋር ብቻህን አትቀመጥ። --- የሚበልጥህ ልኩራብህ እንዳይልህ፣ ያነሰህ ልድረስብህ ብሎ እንዳያጠፋህ የሀብትህን ልክ እንዳታወራ፤ በገዛ አፍህ ባንዱ ትከብራለህ ባንዱ ትቀላለህና። --- በጣም በማክበርህ እንዳታመልከው፤ በጣም በመናቅህ እንዳታዋርደው ሠው እንዳንተ መሆኑን እወቀው። --- የእኔ መናገር ምን ይለውጣል? ብለህም ስህተትን አትለፍ፤ የእኔ አስተዋፅኦ ምን ይጠቅማል? ብለህም ስጦታህን አትጠፍ። --- መልካም ቃል ከስጦታ ይበልጣልና መልካም ቃል ተናገር፤ ማንኛውም ስጦታ ከልመና ወንበር አያስነሣም። የተስፋ ቃል ግን እንደሚያስነሣ አውቀህ ለሰዎች የተስፋ ቃል ስጣቸው። --- ትምህርት ለዕውቀት ያዘጋጃል እንጂ ዕውቀትን አይጨርስም። ዕውቀትህን የምትይዝበትን ሥነ-ሥርዓት ግን ያሳይሃል። አእምሮህን ለማረቅ ትምህርት፣ ሰውነትህን ለመግዛት ትዕግስት፣ ከማንም ጋር ለመኖር ሥነ-ሥርዓት ያስፈልግሃል። ለህሊናህ እረፍት ግን እምነት ያሻሃል። ተከታይ ለማበጀት ደግሞ ግልጽ መሆንና ታማኝነት ግድ ይልሃል። --- አንተው እውነትን ጠልተሃት ዘመኑ እውነትን ጠልቷል አትበል። ዘመን እኔና አንተ ነን፤ በራሱ ክፉና ደግ የሆነ ዘመን የለም። --- መልካም ምክር ብትሰማ ሕይወት ቀላል ይሆንልሃል። ትክክለኛም ውሳኔ ከመልካም ምክር ነውና..!! ,,,,,,,,,,,,,,,,,, (((የመጋቤ ሐዲስ እሸቱ ነው ተብሎ ፌስቡክ ላይ ሲዘዋወር የተገኘ)
Hammasini ko'rsatish...
👍 1 1
፡ "በቦታህ መምህር፤ ያለቦታህ ደግሞ ተማሪ ሁን›› ... በወጣትነት ሁሉም ነገር ትክክል ነው ከሚል መመሪያ ውጣ፤ ሁሉንም ካላየሁ አላምንም አትበል። ሰምቶ ማመን ፣ ከተጎዱት መማር አስተዋይነት መሆኑን አትርሳ። የሰማንያ ዓመት ዕውቀትን ለመገብየት ግድ ሰማንያ ዓመት መኖር የለብህም። ሰማንያ ዓመት ከኖሩት በትሕትና መጠየቅ ይገባሃል። --- ምክርን ብትሰማ በነጻ ትማራለህ። ምክርን አልሰማ ብትል ግን በዋጋ እንደምትማር እወቀው። በዋጋ መማር ግን አድካሚ ደግሞም የሚያስመርር ነው። ብልህ ከሆንህ በሰው ከደረሰው ትማራለህ፣ ሞኝ ከሆንህ ግን በራስህ ሲደርስ ትማራለህ። --- የታየህን አሳይ፣ ያልታየህን አጥራው። በደንብ ያልተረዳኸውን አታስተምረው። ያልቀመስከውን ለሰው አትጋብዝ። የሰማኸውን ሁሉ አትመን። ያየኸውን ሁሉ ስጡኝ፣ የተናገርከውን ሁሉ ፈፅሙ አትበል። የሰጠኽውን እርሳ እንጂ አታውራ። ፍፃሜውን ሳታይ ምስጋና አታብዛ። ቀኑ ሳይመሽ ቀኑ ጥሩ ነው አትበል። --- ዓይንህ የፊቱን ቢያይ ልብህ የኋላውን ያስብ። ነገ ላይ እንድትደርስ የትናንቱን አትርሳ። የምትሄድበት እናዳይጠፋህ የመጣህበትን አትዘንጋ። --- የአባቶችህን መልካም ሥራ አብነት አድርግ። ካሳለፉት ሕይወት ተማር እንጂ አወዳሽና ወቃሽ አትሁን። ሌሎች መሆን ያለባቸውን ስታውቅ አንተ መሆን ያለብህ እንዳይጠፋህ ተጠንቀቅ። ደግሞም አንተም በታሪክ ፊት መሆንህን እወቀው። --- ክፋት አይሙቅህ፣ መልካም ነገርም ብርድ ብርድ አይበልህ። ለክፋት አቅም ካለህ ለበጎ ነገርም አቅም አለህና ተግባርህ የምርጫ ውጤት ነውና አስብበት። --- ገንዘብ የሚመልሰው የገንዘብን ጥያቄ ብቻ ነውና ሁሉንም ነገር ገንዘብ ያስገኝልኛል ብለህ አታስብ። ላለው አትሩጥ፣ ምጽዋትህና ተግባርህ በአቅምህ መጠን ይሁን እንጂ ከአቅምህ አትነስ። ድሃም ሆነህ ተበድረህ ስጦታ አትስጥ። በጣም ካልቸገረህ ለቅንጦት አትበደር። ያንተን ድርሻ ከጨረስህ ያልተጨረሰ የሌሎችን ድርሻ ፈፅምላቸው። --- ለሀብታም አትሳቅ፣ የደሀ ጉልበት አይለፍብህ፣ ያለ ሰው ሰው አልሆንክምና ሰው አትጥላ፣ የወጣህበትን መሰላል አትገፍትር፣ ለመውረድም ያስፈልግሃልና፣ ያየኽውን ሴት ሁሉ የመውደድ ጠባይህ ካለቀቀህ ትዳር አትያዝ፣ ካልጋበዙህ በቀር አማካሪ አትሁን፣ ባልጠሩህ ሥፍራ አቤት አትበል፣ ካልሾሙህ መሪ አትሁን፣ ጉድለት በሌለበት ቦታ ጊዜህን አታባክን፣ የሰው ፊት ጥገኛ ሁነህ ሲስቁልህ የምትስቅ ሲቆጡህ የምታለቅስ አትሁን፣ ነገርህን በልክ፣ ቃልህን በጣዕም፣ ድምፅህን በዝግታ ፈፅመው። --- እውር እንዳይሉህ ያልታየኽን አያለሁ አትበል። ጨካኝ እንዳይሉህ ያልተሰማህን ጩኸት እሰማለሁ አትበል። ንፉግ እንዳይሉህ ያለ አቅምህ እረዳለሁ አትበል። ነገር አይገባውም እንዳይሉህ ያልገባህን እንደገባህ አድርገህ አትለፍ። አንድ በጎ ዕውቀት ሳትጨብጥ የዋልክበትን ቀን እንደ ኖርክበት አትቁጠረው፣ ስለዚህ መፅሐፍትን አንብብ፣ አዋቂዎችን ጠይቅ፣ ሁሉን ሳትንቅ ስማ። --- ሥልጣን ሲሰጥህ መሪ እንጂ አለቃ አትሁን፤ ከፊት እየቀደምህ አስከትል እንጂ ከኋላ ሆነህ አትቅደም። --- በዓላማ ኑር፤ እንቅፋቶች የሚያጸኑህ እንጂ ተግባርህን የሚያስተውህ አይሁኑ። ሕይወት ትምህርት ቤት መሆኑና ባለማወቅ ብዙ ትህምርቶች እንዳያመልጡህ ተጠንቀቅ። --- የመከራ ቀን ወዳጆችህን አትርሳ፤ የዛሬ ሰው ብቻ አትሁን፤ የትላንቱንም አስብ፤ አንገት የተፈጠረው ዞሮ ለማየት ነውና። --- ዓለም ዋዣቂ ናት። ከፍና ዝቅ ስትል አትደናገጥ፤ ፀሐይ ዝናብን ተከትላ ትፈነጥቃለች። ከመከፋትም በኋላ ትልቅ መፅናናት ይሆናል። ከሌሊት በኋላም ሌሊት አይመጣም። ከሀዘን በኋላ ደስታ ይሆናልና በርታ! --- መነቀፍን አትፍራ፤ ነቀፋህን ግን አጥራው፤ ስለ ሀሰት ሳይሆን ስለ እውነት ተገፋ፤ ሌሎችን ውደድ ፍቅር ስጦታ እንጂ ብድር አይደለምና አልወደዱኝም ብለህ በአበዳሪዎች አንቀጽ አትካሰስ፤ የገባህን አድርግ የዚህ ዓለም ሰው ሲወድህም ሲጠላህም ባለማወቅ ነው። ብዙዎች ስለወደዱህ ይወድሃል፤ ብዙዎች ስለጠሉህ ይጠላሃል። --- ሁልጊዜ የበላዮችህን አትመልከት፤ የበታቾችህንም ተመልከት። ለድምፅ አልባዎች ጩህላቸው፣ ለተጠቁት ተሟገትላቸው። እውነት እውነት በማለትህ የምታጣው ሀሰተኛ ወዳጅህን ብቻ ነው። እውነት እውነት በማለትህ የምታተርፈው ግን እውነተኛ ወዳጅን ነው። --- ደጋፊዎች ተከታዮች አይደሉም። ሰዎች ስለደገፉህም የያዝኩት እውነት ነው ብለህ መንቻካ አትሁን፤ ምናልባት ዛሬ የሚጮሁልህ ዛሬን ሊረሱብህ ሊሆን ይችላልና። ሲያለቅሱልህም ቃልህ ማርኳቸው ሳይሆን የሞተ ዘመዳቸው ትዝ ብሏቸው ሊሆን ይችላልና አለቀሱ ብለህ ንግግርህን ድንበር አታሳጣው። እውነትንም በደጋፊ ብዛት እንዳትመዝናት ተጠንቀቅ። --- ለእውነታ እንጂ ለይሉኝታ አትኑር፤ ያን ስልህ የምትኖርበት ሕዝብና ባሕል ከእውነት ጋር እስካልተጋጨ መጋፋት የለብህም። ሠዎች የሚቀበሉህ ባሕላቸውን ስታውቅና ስታከብርላቸው ነው። --- ልጅነት የለሰለሰ መሬት፣ ወጣትነት የአዝመራ ዘመን፣ ሽምግልና ደግሞ የአጨዳ ዘመን መሆኑን አስተውል። በሽምግልናህ የምታጭደው የወጣትነትህን አዝመራ ነውና ዛሬ ለምትዘራው ተጠንቀቅ። --- የሰዎችን ያለማወቅ አግዝ፤ ዕውቀትህ ባላወቁት ላይ እንድትኮራና እንድትፈርድ አያድርግህ የአዋቂ ኩሩ ቁጥሩ ካላዋቂዎች ነውና ማወቅ ባለዕዳነት እንዳይሆን አላዋቂዎችን እርዳቸው !! --- ሁሉን ወሬ ላውራ አትበል፣ የደበቁህን ምስጢር አታውጣጣ፣ የሰማኽውን ወሬና የተገለጠልህን ምስጢር ምን መፍትሔ ሰጠኸውና? ያየህውን ሥራ ሁሉ እሰራለሁ የሰማኸውን ትምህርት ሁሉ እማራለሁ አትበል። ይህ የተሰወረው የቅንዓት ጠባይ ነውና ሁሉን ልያዝ ማለትም ዝንጉ አድረጎ እንዳያስቀርህ ሁሉም ውስጥ ልኑር አትበል። --- ቆንጆዎች ቁንጅናቸው ሁሉን የሚተካ እየመሰላቸው ከዕውቀትና ከትሕትና ይርቃሉ። ሁሉንም ሰው በመልካቸው የሚማርኩት ስለሚመስላቸው ኩሩና ተንኮለኞች ይሆናሉ። አንተ ግን ቆንጆ ወዳጅን እንጂ ቆንጆ ቁመናን አትሻ፤ ቆንጆ ትዳርን እንጂ ቆንጆ ሴትን አትመኝ፤ የላይ ነገር ከንቱና ኀላፊ ነውና በሚፈርስ አካል፣ ኑሮ በሚለውጠው መልክ አትደለል። --- እወድሃለሁ ብለህ የምትናገረውን ቃል ውለታ አታድርገው፣ መውደድህን የምትናገረው እንወድሃለን እንዲሉህ አይሁን፣ ሠላም ያለው አፍቃሪ የራሱን ፍቅር ያለ ምክንያት መፈፀም የሚችል ብቻ እንደሆነ እወቅ። መወደድህን ለመስማት አትጠብቅ። --- የሰዎችን ያለማወቅ አግዝ፤ ዕውቀትህ ባላወቁት ላይ እንድትኮራና እንድትፈርድ አያድርግህ የአዋቂ ኩሩ ቁጥሩ ካላዋቂዎች ነውና ማወቅ ባለዕዳነት እንዳይሆን አላዋቂዎችን እርዳቸው። --- ዛሬ የመዝራት ዘመንህ ነገ መከርህ ነውና በእምነት እውነትን ዝራ፤ በምታውቀው ቦታ ላይ አገልጋይ በማታውቀው መልካም ተግባር ላይ ደጀን ሁን፤ በቦታህ መምህር ያለቦታህ ተማሪ ሁን፤ ክብሩ እንዳይቀንስብህ ከዕቃ ትምክህት፣ ከዕውቀት ሙግት ራቅ። --- ሁሉን ወሬ ላውራ አትበል፣ የደበቁህን ምስጢር አታውጣጣ፣ የሰማኽውን ወሬና የተገለጠልህን ምስጢር
Hammasini ko'rsatish...
1
*መቼ ነው* እውነተኛ ክርስቲያኖች የምንሆነው? *መቼ ነው* እግዚአብሔር በፈጠራቸው ነግሮች የምንማረከው? *መቼ ነው* እግዚአብሔር ለምን እንደፈጠርን የምንረዳው? *መቼ ነው* እግዚአብሔር እንደሚፈልገው መኖር የምንጀምረው? *መቼ ነው* ስለ ሀይማኖታችን በሙሉ ልብ እምንናገረው? *መቼ ነው* እማይጠቅም ንግግር ከመናገር የምንቆጠበው? *መቼ ነው* ለመልካም ስራ ምሳሌ የምንሆነው? *መቼ ነው* በስግደታችን በፆማችን የምንጠቀመው? *መቼ ነው* ጾለታችን ተሰሚነት የሚያገኝው? * *መቼ ነው* ውሎና አዳራችን በቅዱስ ቃሉ ሚሆነው? *መቼ ነው* ሙሉ በሙሉ በእግዚአብሔር ላይ የምንመካው? *መቼ ነው* ያአለምን ትልቅነት ከልባችን የምናወጣው? *መቼ ነው* ቤታችን ውስጥ ያለው የተበላሸ ሂዎት የሚስተካከለው? *መቼ ነው* ቤታችን ውስጥ መጸሐፍ ቅዱስ ውዳሴ ማሪያም የሚወራው? *መቼ ነው* ውሽት እምናቆመው? *መቼ ነው* የእግዚያአብሔርን ውሳኔ መቃውም እምናቆመው? *መቼ ነው* እኔ እኔ ማለት ትተን ውንደሜ እህቴ ማለት እምንጀምረው? *መቼ ነው* ለሰዎች ከክርስቶስ ውጪ ጌታ እንደሌለ እምንናገረው? *መቼ ነው* ጥሩና ለጋሽ መልካም ሰው የምንሆነው? *መቼ ነው። ክርስቲያንነታችንን የምናስተዋውቀው? *መቼ ነው* ለድሃ እምናዝነው?. *መቼ ነው* ትዳራችን ስላም ሚያገኝው? *መቼ ነው* የጋብቻን ጥቅም ተገንዝበት ለትዳር የምንቻኮለው? *መቼ ነው* ከሀሜት; ስውን ከመበድል; ከማስቀየምና ከማማት እምንላቀቀው? *መቼ ነው* ወላጆቻችንን እምናስደስተውና እምንታዝዝው? *መቼ ነው* ያልተጣራ ውሬ ካማውራት እምንቆጠበው? *መቼ ነው* እምንዋደደው? *መቼ ነው* እግዚአብሔር በሰጠን ነገር ደስተኞች የምንሆነው? *መቼ ነው* ስግደት ፆም ፆለት የምንላመደው? *መቼ ነው* የበድለንን ይቅር የመንለው? *መቼ ነው* ከራስ ወዳድነት እምንላቀቀው? *መቼ ነው* ከሞት ቡኃላ ላለው ሂወት ስንቅ እምናዘጋጀው? *መቼ ነው* አባቶችን እምናከብረው? *መቼ ነው* ለእውቅት ጊዜ የምንሰጠው? *መቼ ነው* ባወቅነው የምንሰራው? *መቼ ነው* የ ምንሞትበትን ቀንም ይሁን ስፍራ እንደማናውቅ ተገንዝበን በተጠንቀቅ የምንቆመው? *መቼ እረ መቼ ነው* ክርስትናን የምንኖረው? *መቼ ነው* ለእነዚህ ተግባራዊ መልስ የምንመልሰው እግዚአብሔር ይርዳን አሜን። ውስብሃት ለእግዚአብሔር ወወላዲትድንግል ወለመስቀሉ ክብር
Hammasini ko'rsatish...
አነጸና በአስተዳደሩ ደሀ ሳይበድል ፍርድ ሳያጓድል ሕዝቡን በክህነቱም ንፁህ ሆኖ እግዚአብሔርን እያገለገለ ኖረ።በስተመጨረሻም ፍጥረት ሆኖ ከመሞት ሰው ሆኖ በመቃብር ከመዋል የሚቀር አይኖርምና ንጉሣችንና አባታችን ቅዱስ ይምርሐነ ክርስቶስም የእረፍት ዘመኑ ሲደርስ እግዚአብሔር አምላክ ቃል ኪዳኑን ለዘላለም እንደሚያፀናለት ነግሮት በተባረከች በጥቅምት_19 ቀን በክብር ከመከራ ስጋ አሳረፈው። መቃብሩንም አስቀድሞ እነደነገረው በዛው በተቀደሰ ዋሻ ውስጥ አደረገለት።እናም ዛሬ ድረስ ቦታው በክብር ተጠብቆ ይኖራል።ምእመናንም ቃል ኪዳኑን በማሰብ "ማረኝ ይምርሐ" እያሉ መቃብሩን ይዞራሉ።ያንን ከሰማይ የወረደለትን መስቀልም በቤተመቅደሱ የሚያገለግሉት ካህናት አባቶች ቦታውን ለመሳለም የሚመጣውን ሕዝበ ክርስቲያን በበዓል ቀን ይባርኩበታል፡፡የቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን! አቤቱ የይምርሃነ ክርስቶስ አምላክ ሆይ! ስለወዳጅህ ስለ ቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስ ብለህ ይቅር በለኝ› እያለ ‹አባታችን ሆይ!› የሚለውን ጸሎት የሚጸልይ ዕለቱን እንደተጠመቀ አደርገዋለሁ፡፡ ነገ ማለዳ ተነሥተህ ወግረ ስሂን ወደሚባለው የዕረፍትህ ቦታ ወደሚሆነው ዋሻ ሕዝብህን አስከትለህ ሂድ፤ በዚያም ቤተ መቅደሴን ሥራ›› ብሎ ጌታችን ቃልኪዳን ከሰጠው በኋላ ሰላምታ ሰጥቶት በክብር ወደ ሰማይ ዐርገ፡፡ የቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን አሜን። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ እም እለ አብዑ ብዑላን ዘተርፈ። ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን ሰማዕታት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን ደናግል ዓዲ ወመነኮሳት ኄራን ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን እስከ አረጋዊ ልሒቅ እምንዑስ ሕፃን። ለዘጸሐፎ በክርታስ ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ ወለዘሰምዐ ቃሎ በእዝነ መንፈስ በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኲሉ እምባእስ ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ ወይፈኑ ለነ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ እምይዜ ወእስከ ለዓለም አሜን። ጌታ ሆይ ከብልጽግናቸው ብዛት የተነሳ ብዙ መባ ካገቡት ይልቅ የደሀይቱን አነስተኛ መባ እንደተቀበልህ ለሁል ጊዜ የሚያገለግሉህ አእላፍ መላእክትን እያሳሰብሁ በችግሬ ጊዜ የማቀርብልህን ምስጋና ተቀበል። እናንተም ቅዱሳን ነቢያት የወንጌል ሰባኪያን ሐዋርያት ሰማዕታትና ጻድቃን ትጉሃን መላእክት ፍጹማን ደናግል እንዲሁም ደጋጎች መነኰሳት ሆይ ልጅ አዋቂ ሳይለይ የምንሰበሰብበትን የጉባኤ ቦታ ባርኩ። ይህን መጽሐፍ ወረቀት አዘጋጅቶ ብራና ደምጦ የጻፈውንና ያጻፈውንም የተረጐመውን ቃለ ንባቡን በእርጋታ መንፈስ እና በተመስጦ ሕሊና ያዳመጠ በደለኛን ሁሉ የምታስምር የጌታ እናቱ በማርያም ጸሎት ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድነት ይማረን። አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር . ⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼ ጥቅምት 19 ቀን 2016 ዓ.ም
Hammasini ko'rsatish...
Boshqa reja tanlang

Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.