2 699
Subscribers
+224 hours
+277 days
+5530 days
Posts Archive
ውድ ወላጆች፡-
🔹የ2019 ዓ.ም ትምህርት ለሁሉም ተማሪዎች ሰኞ፣ መስከረም 11 ቀን 2019 ዓ.ም ይጀምራል፡፡ ለጀማሪ (Pre-Kg) ክፍል ተማሪዎች የመጀመሪያው ሳምንት ግማሽ ቀን እስከ ቀኑ 6፡00 ብቻ ይሆናል፡፡
🔹ሁሉም ተማሪዎች የትምህርት ዘመኑ ከመጀመሩ በፊት የት/ቤት መታውቂያ መውሰድ ያለባቸው በመሆኑ መታወቂያ ያልወሰዳች ወላጆች ሰኞ፣ መስከረም 4 ቀን፣ 2019 ዓም ወደ ት/ቤት በመምጣት መውሰድ የምትችሉ መሆኑን ማሳወቅ እንወዳለን፡፡
🔹በተጨማሪም ክፍያ ፈጽማችሁ የተማሪ መማሪያ መጽሀፍ ያልወሰዳችሁ ወላጆችም በዚሁ ቀን (ማለትም ሰኞ፣ መስከረም 4 ቀን፣ 2019 ዓም) መጽሀፍ እንድትወስዱ እያሳወቅን በተጠቀሰው ቀን ባለመውሰዳችሁ ለሚፈጠረው የመጽሀፍ እጥረት ት/ቤቱ ሃላፊነት የማይወስድ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
🔹ደብተሮች እና መፅሃፎች በሙሉ ወደ ት/ቤት ከመላካቸው በፊት ሙሉ ስም ይፃፍባቸው፡፡ በፕላስቲክ ሽፋን ይሸፈኑ፡፡
🔹ተጨማሪ የተማሪዎች የደንብ ልብስ (ቱታ) የምትፈልጉ ወላጆች ቱታው በአቅራቢው ድርጅት ስለቀረበ
ማክስኞ ፣ መስከረም 5 ቀን ፣ 2019 ዓም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ ልጆቻችሁን በመያዝ ለክታችሁ መግዛት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
🔹የት/ቤቱን ሰርቪስ የሚጠቀሙ ተማሪዎች የትራንስፖርት ክፍያ የሚፈጸመው ቅድሚያ በመሆኑ እስከአሁን ያላስመዘገባችሁ ወላጆች ከሰኞ፣ መስከረም 4 እስክ ረብዕ፣ መስከረም 6፣ 2019 ዓም ድረስ ብቻ ክፍያ የፈጸማችሁበትን ደረሰኝ ሂሳብ ክፍል በመላክ ማወራረድ እና ማስመዝገብ ያለባችሁ በመሆኑ እናሳውቃለን፡፡ ክፍያ ፈጽሞ ያልተመዘገበ ተማሪ የትራንስፖርት አገልግሎት ማግኘት የማይችል መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
እናመሰግናለን!
የት/ቤቱ አስተዳደር።
ለትምህርት ቤታችን ማህበረሰቦች በሙሉ።
እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን!! ት/ቤታችን በ2018 ዓ.ም ላስመዘገበው ከፍተኛ ውጤት ከወረዳው ት/ጽ/ቤት ይሄንን የዕውቅና የምስክር ወረቀት ተበርክቶለታል።
ቀን፡ ነሐሴ 23 ቀን 2018 ዓ.ም
ለተከበራችሁ ወላጆች/ህጋዊ አሳዳጊዎች በሙሉ።
ጉዳዩ፡ የ2019 ዓ.ም የትምህርት ቤት ትራንስፖርት አገልግሎት ምዝገባና ክፍያን ይመለከታል።
የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ሰኞ፣ መስከረም 4 ፣ቀን 2019 ዓ.ም የሚጀምር መሆኑ ይታወቃል። የትምህርት ቤቱን የትራንስፖርት አገልግሎት አስቀድሞ በብቃት ለመደልደልና ዝግጅት ለማድረግ እንዲያመች፣ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን የምትፈልጉና እስካሁን ክፍያ ያልፈጸማችሁ ወላጆች እስከ ነሐሴ 30 ፣ ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ክፍያችሁን አጠናቃችሁ እንድታስመዘግቡ በአክብሮት እናሳውቃለን።
ክፍያውን ከፈጸማችሁ በኋላ የባንክ ደረሰኙን ወደ ትምህርት ቤቱ ፋይናንስ ቢሮ በመላክ ማወራረድ ይጠበቅብዎታል።
ማሳሰቢያ፡
👉ክፍያ የሚፈጸመው መውደድ አበራ ሳህሌ በሚል ስም
👉በንግድ ባንክየሂሳብ ቁጥር 1000481876609 ወይም
👉 በኦሮሚያ ባንክ የሂሳብ ቁጥር 1366406700001
👉የጊዜ ገደብ እስከ ነሀሴ 30፣ ቀን 2018ዓ.ም ድረስ ብቻ ሲሆን ክፍያ ያልፈጸመና ያላወራረደ ተማሪ የትራንስፖርት አገልግሎት ማግኘት የማይችል መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን።
👉 የክፍያ መጠን እና የአገልግሎት ቦታዎች፡
1. ኮዬ ወረዳ፣ መስቀለኛ እስከ ፕሮጅክት 16 (በሩብ አመት 9,500 ብር) (በወር 3,800 ብር)
2. ኮዬ አደባባይ እስከ ቂሊንጦ ኢ.ን.ባ (በሩብ አመት 8,750 ብር) (በወር 3,500 ብር)
3. ኮዬ ፕሮጀክት 17፣ በንፋስ ስልክ 18 (በሩብ አመት 10,000 ብር) (በወር 4,000 ብር)
4. ከዩኒሳ አደባባይ በአለም ባንክ እስከ ቱሉዲምቱ አደባባይ (በሩብ አመት 7,000 ብር) (በወር 2,800 ብር)
5. ስድስት ጎጆ ውስጥ እና ቱሉዲምቱ ኮንዶሚኒየም (በሩብ አመት 8,250 ብር) (በወር 3,300 ብር)
ከላቀ አክብሮት ጋር፣
የትምህርት ቤቱ ፋይናንስ ክፍል
ውድ ወላጆች/ህጋዊ አሳዳጊዎች፡ የ8ኛ ክፍል የክልላዊ (ሚኒስትሪ) ፈተና የውጤት ካርድ ትምህርት ቤታችን የደረሰ በመሆኑ፣ ወላጅ ወይም ህጋዊ አሳዳጊ ብቻ በትምህርት ቤታችን የእንግዳ መቀበያ ቢሮ በአካል በመገኘት መውሰድ የምትችሉ መሆኑን በጥብቅ እናሳውቃለን። ማሳሰቢያ፡ የውጤት ካርዱ የሚሰጠው ለወላጅ ወይም ህጋዊ አሳዳጊ ብቻ ይሆናል። ከሠላምታ ጋር! የት/ት ቤቱ አስተዳደር
ጫና እና ተነሳሽነት አንድ አይደሉም !!!
ትምህርት ቤት ሊከፈት ነው... 🔔🎒
ገና የመጀመሪያው ቀን ከመድረሱ በፊት ግን፤ ሳናስበው ለልጆቻችን ከባድ ተስፋዎችንና ጫናዎችን ማከማቸት ጀምረናል።
🗣 “ዘንድሮ ከአምናው የተሻለ ውጤት ማመጣት አለብህ።”
🗣 “አሁን እኮ ትልቅ ክፍል ደርሰሃል።”
🗣 “ከክፍልህ ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ መውጣት አለብሽ።”
🗣 “እንዳታሳፍረኝ።”
እነዚህን ነገሮች የምንናገረው መልካሙን ተመኝተንላቸው ሊሆን ይችላል። ነገር ግን ሳናውቀው፤ ልጆቻችን ትምህርት ቤት የሚሄዱት ራሳቸውን ለማስመስከር ወይም እኛን ለማስደሰት እንደሆነ እንዲሰማቸው እናደርጋቸዋለን።
ግን አይደለም ❌።
ትምህርት ቤት የሚሄዱት ለመማር ነው 📖💡!
🧠 ይረሳሉ፤ ይሳሳታሉ።
🟢 አንዳንድ ትምህርት ይቀላቸዋል፤ አንዳንዱ ደግሞ ይከብዳቸዋል።
☀️ አንድ ቀን ደስ ብሏቸው እና ኮርተው ይመጣሉ፤
🌧 ሌላ ቀን ደግሞ ተስፋ ቆርጠው እና ተናደው ይመጣሉ።
ይህ ደግሞ የእድገት እና የህይወት አካል ነው 🌱.
🔄 ስለዚህ ዘንድሮ ውይይታችንን እንቀይር!
❌ "ስንት አመጣህ/ሽ?" ብሎ ከመጠየቅ ይልቅ 👉 "ዛሬ ምን ተማርክ/ሽ?" ብለን እንጠይቅ ❓
❌ "ሊያውም በዚህ ውጤት? ለምን አንደኛ አልወጣህም?" ከማለት ይልቅ 👉 "የትኛው ትምህርት ነው የከበደህ/ሽ?" እንበላቸው ❤️።
ስህተት መስራትን እንዲፈሩ ከምናደርግ፤ ተሳስቶ መማር የተሻለ ሰው የመሆን መንገድ እንደሆነ እናስተምራቸው ።
በእርግጥ ልጆቻችን ጠንክረው መማር አለባቸው 💪📚!
በእርግጥ ሃላፊነት እንዲሰማቸው እንፈልጋለን፤ ትምህርትም ትልቅ ቦታ አለው🎯።
⚠️ ነገር ግን ጫና እና ተነሳሽነት አንድ አይደሉም!
😰 እኛን እንዳያሳፍር የሚፈራ ልጅ፤ ውጤት ብቻ ለማምጣት ይጥራል::
🤝 ድጋፋችን የማይለያቸው ልጆች ግን፤ እውቀትን እና መረዳትን ለማምጣት ይጥራሉ::
በእነዚህ ሁለቱ መካከል ደግሞ በጣም ትልቅ ልዩነት አለ ⚖️።
ስለዚህ አዎ...
🎒 ቦርሳቸውን እንግዛ፤
📓 ደብተራቸውን እንግዛ፤
👕 ዩኒፎርማቸውን እናዘጋጅ።
ነገር ግን ከሁሉም በላይ ልጁን/ልጅቷን በአእምሮ እና በስነ-ልቦና እናዘጋጃቸው 🤍።
ከእነሱ ብዙ ከመጠበቃችን በፊት፤ በቅድሚያ እራሳቸውን እንዲያምኑ እንርዳቸው ⭐️።
ምክንያቱም ዘንድሮ፤ ልጄ ባለጥሩ ውጤት ብቻ ሆኖ እንዲመጣ አልፈልግም ❌🏆።
ልጄ ወደ ቤት ሲመለስ ይህንን አምኖ እንዲመጣ ነው የምፈልገው፡
💬 "እማራለሁ፤ እታገላለሁ፤ እሳሳታለሁ፤ እንደገና እሞክራለሁ... ወላጆቼ ግን አሁንም በእኔ ይኮራሉ!" 👨👩👧👦❤️
ለልጄ የምመኘው የትምህርት ዘመን ይህንን ይመስላል 🌟።
የእናንተስ ምኞት?
ምንጭ: ሬዚንግ አደልትስ
መልዕክት ለተማሪ ወላጆች/ህጋዊ አሳዳጊዎች በሙሉ::
ውድ ወላጆች የተማሪዎች የመማሪያ መጻሕፍት የመጣ በመሆኑ ክፍያ የፈጸማችሁበትን ኦሪጅናል የባንክ ደረሰኝ በመያዝ ከማክሰኞ፣ ነሐሴ 12 ቀን፣ 2018 ዓ.ም. እስከ አርብ፣ ነሐሴ 15 ቀን ፣ 2018 ዓ.ም. ድረስ ብቻ በት/ቤቱ ቅጥር ግቢ በመገኘት መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
በተጨማሪም የተማሪዎች መታወቂያ ካርድ ተዘጋጅቶ ስላለቀ ወላጆች ወይም ህጋዊ አሳዳጊዎች ብቻ በአካል ት/ቤት በመገኘትና በመፈረም መውሰድ ትችላላችሁ።
ጥብቅ ማሳሰቢያ:-
🔹 መጽሐፍ ለመውሰድ የከፈላችሁበትን የታተመ የባንክ ደረሰኝ ይዞ መገኘት ግዴታ ነው። በስልክ ላይ የሚታይ (Soft copy) ደረሰኝ ተቀባይነት የሌለው መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
🔹 የተማሪዎች መታወቂያ የሚሰጠው ለወላጅ ወይም ለህጋዊ አሳዳጊ ብቻ ነው። መታወቂያው ቢጠፋ ወይም ቢበላሽ ምትክ ለማውጣት ተጨማሪ ክፍያ የሚጠየቅ መሆኑን እናሳስባለን።
🔹 ከተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውጪ መጻሕፍቱን ማደል ሰለማንችል፣ በተጠቀሱት ቀናት ውስጥ ብቻ መጥታችሁ እንድትወስዱ እናሳስባለን።
እናመሰግናለን!
የት/ቤቱ አስተዳደር
ውድ ወላጆች የ2019 ዓ.ም የነባር ተማሪዎች የትምህርት ምዝገባ በትላንትናው ቀን መጠናቀቁ ይታወቃል።
በመሆኑም ክፍያ ፈጽማችሁ የባንክ ደረሰኝ ለት/ቤቱ ፋይናንስ ቢሮ ያላስገባችሁ እና የምዝገባ ሂደቱን ያላጠናቀቃችሁ ወላጆች እስከ ሰኞ ፣ ሐምሌ 13 ቀን፣ 2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ የምዝገባ ሂደቱን እንድታጠናቅቁ እያሳወቅን ጊዜ ገደቡን ባለመጠበቅ ምክንያት ለሚፈጠሩ የቦታ ማጣት ችግሮች እና መጉላላት ት/ቤቱ ሃላፊነቱን የማይወስድ መሆኑን በአክብሮት ይገልፃል፡፡
እናመሰግናለን!
የት/ቤቱ አስተዳደር።
