2 467
مشترکین
+324 ساعت
+147 روز
+2930 روز
آرشیو پست ها
ለ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪ ወላጆች በሙሉ።
ውድ ወላጆች በነገው እለት በቀጣይ ሳምንት ከሰኞ እስከ አርብ :- ከሰኔ 8 _ 12 ቀን፣ 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚሰጠው ከተማ አቀፍ የማጠቃለያ ፈተና በፈተና ቀናት ተፈታኞች ማወቅ ስላለባቸው የፈተና ህግ እና መሠል ነገሮች ፈተና በሚፈተኑበት ት/ቤት "ኦረንቴሽን" ስለሚሰጥ ሁሉም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች ነገ ዓርብ ፣ ሰኔ 5 ቀን፣ 2018 ዓ.ም በመደበኛው የተማሪ መግቢያ ሰዓት በት/ቤታቸው እንዲገኙ በጥብቅ ማሳሰብ እንወዳለን።
ማሳሰቢያ
👉 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ኦረንቴሽን ጠዋት ሲሆን የ8ኛ ክፍሎች ደግሞ ከሰዓት 7:00 ሰዓት ላይ የሚከናወን ይሆናል።
👉 የሁለቱም ክፍል ተማሪዎች ሙሉ ቀን በት/ቤታቸው የሚቆዪ ይሆናል።
እናመሰግናለን!
የት/ቤቱ አስተዳደር
THS Update:
Congratulations to our amazing Grade 1–3 spellers!
We successfully held our Spelling Bee Award Ceremony this morning. We are so proud of the courage, hard work, and brilliant spelling skills displayed by all our lower primary students.
Every participant is a champion! 🏆🐝
Dear parents, thank you for your support at home.
Dear Grade 6 students, please practice the questions above to help you prepare for your upcoming examinations.
ሰኞ/ሰኔ 01 ቀን/2018ዓ.ም
ውድ ወላጆች የሰኔ ወር የጥናት እና የትራንስፖርት ክፍያ የሚከፈለው ከግንቦት 25 እስከ ሰኔ 5 ቀን ፣ 2018ዓ.ም ድረስ ብቻ መሆኑን በአክብሮት እያሳወቅን ክፍያዉን ከፈጸሙ በኃላ የባንኩን ደረሰኝ ወደ ሂሳብ ክፍል በመላክ ክፍያውን እንድታወራርዱ ማሳሰብ እንወዳለን።
ማሳሰቢያ
1. የጥናት ክፍያ የሚፈጸመው
ሀ. በኦሮሚያ ባንክ አትንሳ ትምህርት እና የትምህርት ስራዎች
የሂሳብ ቁጥር 1504871000001 ወይም
ለ. በንግድ ባንክ አትንሳ ትምህርት እና የትምህርት ስራዎች
የሂሳብ ቁጥር 1000429458122
2. የትራንስፖርት ክፍያ የሚፈጸመው መውደድ አበራ ሳህሌ በሚል ስም
በኦሮሚያ ባንክ የሂሳብ ቁጥር
1366406700001 ወይም
በንግድ ባንክ
1000481876609 በሚል ብቻ መሆኑን እናሳውቃለን።
እናመሰግናለን።
የት/ቤቱ ሂሳብ ክፍል።
🌟 የ6ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች የፈተና መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም ዙሪያ ሊያውቋቸው የሚገቡ ጉዳዮች:
💥የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ እና ማጥቆር አለበት፡፡
💥 ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው አራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡
💥 ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን የአራት ማዕዘን ቅንፍ በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡
💥 በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ መልስ ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡
💥 ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
💥 መልስ በሚጠቆርበት ጊዜ እርሳሱ ከተሰጠው አራት ማዕዘን ቅንፍ መውጣት የለበትም። ከወጣም በማጥፊያ ማጥፋት ይጠበቅባችኋል።
💥 ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡
💥 በእስክሪብቶ መፃፍ አይፈቀድም። ስለዚህ እርሳስ፣ ላጲስ እና መቅረጫ አይለያችሁ!
💥 ፈተና ጨረስኩ ብሎ አላስፈላጊ የሆነ ነገር፤ ስዕል ወይም ሌላ ከጀርባም ይሁን ከፊት አይፃፍበትም።
💥 በጣም የተቀረፀ ሹል እርሳስ በምንጠቀም ወቅት ወረቀቱ እንዳይቀደድ መጠንቀቅ አለብን።
መልካም የጥናት ጊዜ!
ካነበብነው!
Grade 6 Students Model Exam Schedule:
1. Monday, June 8, 2026
Amharic and English
2. Tuesday, June 9, 2026
Math and E/Science
3. Wednesday, June 10, 2026
Moral and Afan Oromo
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
