en
Feedback
🔥𝑺𝒆𝒏𝒋𝒐 𝑫𝒂𝒊𝒍𝒚 𝑵𝒆𝒘𝒔 𝑶𝒇𝒇𝒊𝒄𝒊𝒂𝒍 💯

🔥𝑺𝒆𝒏𝒋𝒐 𝑫𝒂𝒊𝒍𝒚 𝑵𝒆𝒘𝒔 𝑶𝒇𝒇𝒊𝒄𝒊𝒂𝒍 💯

Open in Telegram

👉የቀኑ አዳዲስ ቀናዊ ውሎዎች ዜናዎች እንደደረሱ እናቀርብሎታለን 👉የደረሱንን ዜናዎች አጠናክረን እናቀርባለን 👉ስለ ሴንጆ ፕሪምየር ሊግ ውጤቶች እናወራለን 👉ትኩስ ዜና ካሎት ለቦቱ ይላኩ ቢቻል ከፎቶ እና ከነ ሙሉ መረጃው ብትልኩልን ምርጥዬ ነው ብቻ እርሶ ቻናላችንን ሼር ያርጉ ሀሳብ አስተያየቶን @senjonewsgp ያድርሱን @senjonewssbot

Show more
2 381
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
የcallids batch መፅሄት ብልሽት የ2015E.C የCallidus batch መፅሄት ከወራት ጥበቃ እና እንግልት በኋላ በየካቲት ወር መጨረሻ ላይ ተጠናቆ መምጣቱን ገልፀን ነበር እናም አልቆ የመጣው መፅሄት እንደተመለከትነው እጅግ በጣም አሳፋሪ ሆኖ አጊኝተነዋል። ጉድለቶቹ እና ጥፋቶቹ ከመፅሄቱ መጀመርያ አንስቶ እስከ መጨረሻ ድረስ በጉልህ ሰፍሮ የሚታይ ሲሆን ጥፋቶቹ ተቆጥረው የማያልቁ እጅግ አሳፋሪ ስራ ነው። ከጥፋቶቹ ውስጥ ጥቂቶቹን ለመግለፅ ያክል ብራቸውን ከፍለው መፅሄት እንዲታተምላቸዉ ያዘዙ ተማሪዎች ከነአካቴዉ በመፅሄቱ ላይ ያለመካተታቸዉ፣የመፅሄት ፅሁፍ አስገብተው በመፅሄቱ ላይ ያልተፃፈላቸው እንዲሁም የተሳሳቱ መግባት የሌለባቸው ፎቶዎች እንዲሁም የተበላሹ ምስል አገባቦች ከታዩ ጥፋቶች በጥቂቱ ሲሆኑ የተቀሩትን ጥፋቶች እዛዉ መፅሄቱ ላይ በግላጭ መመልከት የምትችሉት ሀቅ ነው። የምረቃ ኮሚቴው እነዚህን ጥፋት እና ጉድለቶች ለማስቀረት እናም በጥሩ ህትመት ቤቶች ስራውን ለማከናወን የሞከረ እና የጣረ ቢሆንም ከላይ በነበሩት አካላት (በምረቃ ኮሚቴው መሪ በነበረው አካል )እንቢተኝነት ለግል ጥቅም በተደረገ ሴራ ምክንያት የምረቃ ኮሚቴው ጥረት ሳይሳካ አሁን ለደረሰው ጥፋት መንስኤ ሆኗል። መፅሄቱን ለመቀበል የሄዱ ተማሪች የደረሰውን ጥፋት ለመጠየቅ ጉዳዩ ይመለከታቸዋል ወደተባሉት አካላት ቅሬታው ለማቅረብ ቢሄዱም በ"ምን አገባኝ" ምላሽ ከቢሮ የተሰናበቱበት ሁኔታም ነበር። ከላይ ለተጠቀሱት ሁሉ ጥፋቶች እና ጉድለቶች የምረቃ ኮሚቴ "መሪ" የነበረው አካል ሙሉ ሀላፊነቱን የሚወስድ ይሆናል። ለደረሱት ጉድለቶች እና ጥፋቶች በተማሪዎች ተወክለው የነበሩ የምረቃ ኮሚቴ አባላቶች ስም ታላቅ ይቅርታ ለወከሉን ተማሪዎች እንጠይቃለን። ከላይ የተዘረዘሩት ጉዳዮች ቀጣይ ለሚመጡ ተመራቂ ተማሪዎች የማንቂያ ደውል ሆኖ ሊጠቀስ ይገባል። Big love & Big respect All of Callidus batch students❤️‍🩹 [የምረቃ ኮሚቴው] @senjonews @senjonewsgp

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
የፌስቡክ አገልግሎት ተመለሰ። ለሰዓታት ተቋረጠው ከነበሩት በሜታ ስር ከሚገኙት አገልግሎቶች አንዱ ፌስቡክ ዳግም መስራት ጀምሯል። እዚህ ኢትዮጵያ ኢንስታግራም እና ትሬድ አሁንም እየሰሩ እንዳልሆነ ለ
+1
የፌስቡክ አገልግሎት ተመለሰ። ለሰዓታት ተቋረጠው ከነበሩት በሜታ ስር ከሚገኙት አገልግሎቶች አንዱ ፌስቡክ ዳግም መስራት ጀምሯል። እዚህ ኢትዮጵያ ኢንስታግራም እና ትሬድ አሁንም እየሰሩ እንዳልሆነ ለመረዳት ተችሏል። የሜታ አገልግሎቶች በምን ምክንያት እንደተቋረጡ እስካሁን በኩባንያው በኩል በይፋ የተባለ ነገር የለም። @tikvahethiopua

🚨 ከስፖርት ውጭ | ፌስቡክ፣ ኢንንስታግራም እና ሜሴንጀር በመላው ዓለም ተቋረጡ በሜታ ኩባንያ ስር የሚንቀሳቀሱት ፌስቡክ፣ ኢንስታግራም እና ሜሴንጀር በመላው ዓለም በድንገት መቋረጣቸውን የሚያመለክ
🚨 ከስፖርት ውጭ | ፌስቡክ፣ ኢንንስታግራም እና ሜሴንጀር በመላው ዓለም ተቋረጡ በሜታ ኩባንያ ስር የሚንቀሳቀሱት ፌስቡክ፣ ኢንስታግራም እና ሜሴንጀር በመላው ዓለም በድንገት መቋረጣቸውን የሚያመለክቱ መረጃዎች እየወጡ ነው። እነዚህ የማህበራዊ ትስስር አይነቶች መቋረጣቸው በተለያዩ መገናኛ ብዙሀን ሰበር ዜና ሆኖ እየወጣ ይገኛል።[EBC] @Bisrat_Sport_433et @Bisrat_Sport_433et

🚨ለ2015 የቅዱስ ዮሴፍ አዳማ Callidus batch ለነበራቹ በሙሉ🚨 ከወራት በፊት ትዕዛዝ ላይ የነበረው መፅሄት በመጠናቁ ከነገ 27/2016 ጀምሮ ትምህርት ቤት በመሄድ ከስቶር የትናየት ጋር በመሄድ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን ልናሳውቅ እንወዳለን። ራቅ ያለ ዩንቨርስቲ የምትገኙ ወላጆቻቹ እንዲቀበሉላቹ ማድረግ የምትችሉ መሆኑን አያይዘን እንገልፃለን። @senjonews @senjonewsgp

🚨ሰኞ እለት ወደ መደበኛው የትምህርት ጊዜ የምትመለሱ ይሆናል።

🚨Breaking🚨 ለቅዱስ ዮሴፍ አዳማ ተማሪዎች በሙሉ አሁን በደረሰን መረጃ መሰረት ነገ የካቲት 22/2016 ዓ.ም እንደ ኦሮሚያ ክልል በወጣ ትእዛዝ ከነገ ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ
🚨Breaking🚨 ለቅዱስ ዮሴፍ አዳማ ተማሪዎች በሙሉ አሁን በደረሰን መረጃ መሰረት ነገ የካቲት 22/2016 ዓ.ም እንደ ኦሮሚያ ክልል በወጣ ትእዛዝ ከነገ ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የመምህራን ስልጠና በመኖሩ ነገ የመደበኛ ትምህርት እንደማይኖር ልናሳውቅ እንወዳለን። እንዲሁም በዕለተ እሁድ ሊከናወን ታቅዶ የነበረው የወላጆች ቀን በአልም በዚሁ ምክንያት ለሌላ ቀን መዘዋወሩንም ለመግለፅ እንወዳለን። [ወ/ም አማኑኤል ሰይፉ] #Share_Share📱📲 @senjonews @senionewsgp

Repost from Tikvah-University
በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች ምዝገባ እየተካሔደ ነው። ተፈታኝ ተማሪዎችን የመመዝገብ ሥራ ከየካቲት 3/2016 ዓ.ም ጀምሮ እስከ የካቲት 30/2016 ዓ.ም እንደሚ
+1
በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች ምዝገባ እየተካሔደ ነው።
ተፈታኝ ተማሪዎችን የመመዝገብ ሥራ ከየካቲት 3/2016 ዓ.ም ጀምሮ እስከ የካቲት 30/2016 ዓ.ም እንደሚከናወን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገልጿል። ምዝገባ የጀመሩ አካባቢዎች መኖራቸውን የጠቆሙት ኃላፊው፤ ምዝገባ ያልተጀመረባቸው አካባቢዎች በቀጣይ ምዝገባውን እንደሚያካሒዱ የአገልግሎቱ ም/ዋ/ዳይሬክተር ተፈራ ፈይሳ ገልጸዋል። በመደበኛ እና በማታ መርሐግብር የመልቀቂያ ፈተናውን የሚወስዱ ተማሪዎች ምዝገባ በትምህርት ቤቶች ይከናወናል የተባለ ሲሆን በግል፣ በርቀት እና በበይነ መረብ ተምረው የሚፈተኑ ተማሪዎች ምዝገባ በክ/ከተማ፣ በልዩ ወረዳ እና በወረዳ የትምህርት ጽ/ቤቶች እንደሚካሔድ ም/ዋ/ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። በ2016 ዓ.ም የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ከ870 ሺህ በላይ ተማሪዎች እንደሚፈተኑ ይጠበቃል። @tikvahuniversity

Repost from Tikvah-University
#MoE ትምህርት ሚኒስቴር በ2016 ዓ.ም በሚሰጡ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የትምህርት አይነቶች ላይ ውሳኔ አሳልፏል። በዚህም በሁለቱም የትምህርት መስኮች እያንዳንዳቸው በስድስት የትምህርት አይ
+1
#MoE ትምህርት ሚኒስቴር በ2016 ዓ.ም በሚሰጡ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የትምህርት አይነቶች ላይ ውሳኔ አሳልፏል። በዚህም በሁለቱም የትምህርት መስኮች እያንዳንዳቸው በስድስት የትምህርት አይነቶች ፈተናው እንዲሰጥ ተወስኗል፡፡ የተፈጥሮ ሣይንስ፦ እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ ፊዚክስ፣ ኬሚስትሪ፣ ባዮሎጂ እና ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ቴስት የማኅበራዊ ሣይንስ፦ እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ ታሪክ፣ ጂኦግራፊ፣ ኢኮኖሚክስ እና ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ቴስት ለሁሉም ክልሎች እና ለሁለቱ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች የተፃፈው ሰርኩላር፤ የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዝግጅትንም ያብራራል። በዚህም የኢኮኖሚክስ ፈተና ለ2016 ዓ.ም ከ12ኛ ክፍል ብቻ ፈተናው የሚዘጋጅ ሲሆን ሌሎች የትምህርት አይነቶች ከ9-11ኛ ክፍሎች በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት እንዲሁም የ12ኛ ክፍል በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት እንደሚሆን ያትታል። ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ቴስት ወደፊት ጥናት ተጠንቶ እስከሚለይ ድረስ በነበረው አሠራር መሠረት ውጤት ተደምሮ የሚገለጽ መሆኑንም ገልጿል። የፈተና አሰጣጡን በተመለከተ ለተማሪዎች፣ ለወላጆች፣ ለመምህራን እና ለትምህርት ማህበረሰቡ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ ከወዲሁ እንዲያውቁት እንዲደረግ ሚኒስቴሩ አሳስቧል። @tikvahuniversity

Repost from Tikvah-University
#ArbaminchUniversity አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም ለሪሚዲያል ፕሮግራም የተመደቡ ተማሪዎች መግቢያ እሁድ ጥር 5/2016 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል። አቀባበል ሰኞ ጥር 6፣ ምዝገባ
#ArbaminchUniversity አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም ለሪሚዲያል ፕሮግራም የተመደቡ ተማሪዎች መግቢያ እሁድ ጥር 5/2016 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል። አቀባበል ሰኞ ጥር 6፣ ምዝገባ ማክሰኞ ጥር 7 የሚደረግ ሲሆን ትምህርት ረቡዕ ጥር 8/2016 ዓ.ም ይጀምራል ተብሏል። የምዝገባ ቦታ፦ ➧ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በዓባያ ካምፓስ (አርባ ምንጭ ከተማ) ➧ የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች - ስማቸው ከ A-S የሚጀምር በጫሞ ካምፓስ (አርባ ምንጭ ከተማ) - ስማቸው ከ T-Z የሚጀምር በሳውላ ካምፓስ (ሳውላ ከተማ) ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦ ➭ የ8ኛ ክፍል ሰርተፍኬት ዋናውና ሁለት ኮፒ፣ ➭ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ሁለት ኮፒ፣ ➭ የ12ኛ ክፍል ውጤት ዋናውና ሁለት ኮፒ፣ ➭ የፓስፖርት መጠን ሁለት ጉርድ ፎቶግራፍ፣ ➭ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ የትራስ ጨርቅ፣ የስፖርት ትጥቅ፡፡ @tikvahuniversity

Repost from Tikvah-University
#DireDawaUniversity ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም አዲስ የተመደቡ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ከጥር 15 እስከ 17/2016 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል። ወደ ዩኒቨርሲቲው
+1
#DireDawaUniversity ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም አዲስ የተመደቡ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ከጥር 15 እስከ 17/2016 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል። ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦ ➭ የ8ኛ ክፍል ስርተፍኬት ዋናውና ኮፒው፣ ➭ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣ ➭ የ12ኛ ክፍል ፈተና ሰርተፍኬት ዋናውና ኮፒው፣ ➭ ስምንት 3×4 ፎቶግራፍ፣ ➭ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ ትራስ ጨርቅ፡፡ @tikvahuniversity

እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳቹ!!! ……………✝️✝️✝️…………… ✝️🙏✝️   መልካም በዓል   ✝️🙏✝️ @senjonews

2023 moments class of 2023 callidus batch❤️‍🔥🔥🫶🤌🏾 @senjonews

Repost from Tikvah-University
#DillaUniversity ዲላ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ትምህርት ዘመን አዲስ ገቢ ተማሪዎችን በመቀበል ላይ ይገኛል። ዩኒቨርሲቲው በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው የዩኒቨርሲቲ መግቢ
#DillaUniversity ዲላ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ትምህርት ዘመን አዲስ ገቢ ተማሪዎችን በመቀበል ላይ ይገኛል። ዩኒቨርሲቲው በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ በማምጣት ዲላ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ 222 ተማሪዎች እንዲሁም በሪሚዲያል ፕሮግራም በዲላ ዩኒቨርሲቲ ሲማሩ የነበሩና ማለፍያ ነጥብ ያስመዘገቡ 1,936 ተማሪዎች በድምሩ 2,158 አዲስ ገቢ ተማሪዎችን እየተቀበለ ይገኛል። @tikvahuniversity

Repost from Tikvah-University
#MoE የሪሚዲያል ፕሮግራም ምደባ መመልከቻ፦ በድረ-ገፅ፦ https://result.ethernet.edu.et በቴሌግራም ቦት፦ https://t.me/moestudentbot የተቋም ይቀየርልኝ ጥያቄ #የማ
#MoE የሪሚዲያል ፕሮግራም ምደባ መመልከቻ፦ በድረ-ገፅ፦ https://result.ethernet.edu.et በቴሌግራም ቦት፦ https://t.me/moestudentbot የተቋም ይቀየርልኝ ጥያቄ #የማያስተናግድ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል። @tikvahuniversity

Repost from Tikvah-University
#ArbaMinchUniversity በ2016 የትምህርት ዘመን አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ መደበኛ ተማሪዎች እና በ2015 ዓ.ም አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የአቅም ማሻሻያ (Remedial)
#ArbaMinchUniversity በ2016 የትምህርት ዘመን አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ መደበኛ ተማሪዎች እና በ2015 ዓ.ም አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች መግቢያ እሁድ ኅዳር 30/2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲው አሳውቋል፡፡ አቀባበል ሰኞ ታኅሣሥ 01/2016 ዓ.ም፣ ምዝገባ ማክሰኞ ታኅሣሥ 02/2016 ዓ.ም እንዲሁም ትምህርት የሚጀመረው ረቡዕ ታኅሣሥ 03/2016 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል፡፡ የምዝገባ ቦታ፦ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች፦ አርባ ምንጭ ከተማ በሚገኘው ዓባያ ካምፓስ የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች፦ የስም ዝርዝራችሁ ከ“A” እስከ “S” የሚጀምር በጫሞ ካምፓስ፣ አርባ ምንጭ ከተማ የስም ዝርዝራችሁ ከ“T” እስከ “Z” የሚጀምር በሳውላ ካምፓስ፣ ሳውላ ከተማ ወደ ተቋሙ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፡- ➢ የ8ኛ ክፍል ሰርተፍኬት ዋናውና ሁለት ኮፒ፣ ➢ ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ሁለት ኮፒ፣ ➢ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ዋናውና ሁለት ኮፒ፣ ➢ ሁለት ፓስፖርት መጠን ጉርድ ፎቶግራፍ፣ ➢ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ እና ትራስ ልብስ፣ ➢ የስፖርት ትጥቅ፡፡ @tikvahuniversity

Repost from Tikvah-University
#HawassaUniversity ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም በመደበኛ የዲግሪ ፕሮግራም አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች እንዲሁም በ2015 ዓ.ም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ት
#HawassaUniversity ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም በመደበኛ የዲግሪ ፕሮግራም አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች እንዲሁም በ2015 ዓ.ም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ትምህርት ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ነባር የሪሚዲያል ተማሪዎች የምዝገባ  ጊዜ ታህሳስ 08 እና 09/2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡ የምዝገባ ቦታ፦ • የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በዋናው ግቢ • የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ወደ ተቋሙ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፡- ➢ የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ዋናውና ኮፒው፣ ➢ ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣ ➢ አራት ጉርድ ፎቶግራፍ፣ ➢ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ እና ትራስ ጨርቅ፣ ➢ የስፖርት ትጥቅ፡፡ @tikvahuniversity

Repost from Tikvah-University
#AAU በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ2016 የትምህርት ዘመን በመደበኛ የዲግሪ ፕሮግራም አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች ሪፖርት ማድረጊያ ጊዜ ታህሳስ 05 እና 06/2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳ
#AAU በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ2016 የትምህርት ዘመን በመደበኛ የዲግሪ ፕሮግራም አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች ሪፖርት ማድረጊያ ጊዜ ታህሳስ 05 እና 06/2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡ የምዝገባ ቦታ፦ በየተመደባችሁበት የዩኒቨርሲቲው ካምፓሶች ወደ ዩኒቨርሲቲዉ ከመምጣታችሁ በፊት https://portal.aau.edu.et ላይ በመግባት Freshman የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም የግል መረጃቻችሁን እንድታሟሉ ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል፡፡ አዲስ ገቢ ተማሪዎች ወደ ተቋሙ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፡- ➢ የ12ኛ ክፍል ፈተና ማጠቃለያ ፈተና ውጤት ዋናውና ኮፒው፣ ➢ አራት ጉርድ ፎቶግራፍ፣ ➢ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ እና ትራስ ጨርቅ፣ ➢ የስፖርት ትጥቅ፡፡ Note: በተጠቀሱት ቀናት ከአዲስ አበባ ውጪ ለምትመጡ ተማሪዎች በመርካቶ አውቶብስ ተራ፣ በላም በረት፣ በአቃቂ እና በአስኮ የመኪና መናኸሪያዎች በመገኘት ዩኒቨርሲቲው የትራንስፖርት አገልግሎት ያቀርባል፡፡ ነዋሪነታችሁ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሆኖ ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች ሪፖርት የምታደርጉት ታህሳስ 08/2016 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል፡፡ የ2016 ዓ.ም የመጀመሪያ ሴሚስተር መልሶ ቅበላ ከታህሳስ 08 እስከ 12/2016 መሆኑ ተመላክቷል፡፡ ለተጨማሪ መረጃ፦ https://portal.aau.edu.et/ ወይም http://aau.edu.et @tikvahuniversity

📚 የ AASTU 2016 FRESH STUDENTS ዶርም ድልድል በዚህ ሊንክ ገብታችሁ ማዬት ትችላላችሁ👇 http://www.aastu.edu.et/freshmaninfo/ ትምህርት ሚኒስቴር ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️ https://t.me/Tmhrt_Minister https://t.me/Tmhrt_Minister