የሰለፍያ ደዕዋ በቻግኒالدعوة السلفية فى مدينة الشاغنى
ወደ ቻናሉ👇 ለመቀላቀል 👇ከፈለጉ👇 t.me/selefiyadawabechagni አስተያየታችሁን 👇ወይም 👇እርማታችሁን👇 t.me/selefiyadawabechagnibot ይፃፉልን። ይላኩልን።
Show more- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Data loading in progress...
ወደ ቻናሉ👇 ለመቀላቀል 👇ከፈለጉ👇 t.me/selefiyadawabechagni አስተያየታችሁን 👇ወይም 👇እርማታችሁን👇 t.me/selefiyadawabechagnibot ይፃፉልን። ይላኩልን።
የመደንይ ስርኣት ማለት ሰው በሰውመቱ፣ በእምነቱ፣ በአስተሳሰቡ የማይወገዝበት ሁሉን አካታች ስርኣት ነው ይላል። (ይህ ነው ትክክለኛ ትርጉሙ)
– የመደንይ ስርኣት ሸሪዓ የሚያዝበት ነው
– ኢትዮዽያ ውስጥ ኢስላማዊ ሸሪዓ አይታሰብም ማሰቡም ወንጀል ነው‼
– ኢትዮዽያ ውስጥ ኢስላማዊ ስርኣት እንዲመጣ የሚያስብ ካለ ወንጀለኛ ነው ብለን እናምናለን
– የመደንይ ስርኣት (ሰው በሰውነቱ፣ በእምነቱ፣ በአስተሳሰቡ፣ የማይወገዝበት ስርኣት) ከመጣ እምነቴን (እስልምናን) ይወክላል‼
https://t.me/bahrutekaአቡ አዩብ የሚከተለውን ሐዲስ አስተላልፏል፡- “አንድ የገጠር ሰው በሰፈር ድንገት ከረሡል ﷺ ጋር ተገናኘና የግመላቸውን ልጓም በመያዝ “የአላህ መልክተኛ ሆይ! - ሙሀመድ ሆይ!- ወደ ጀነት የሚያቀርበኝ፤ ከእሳት የሚያርቀኝን ስራ ንገሩኝ” አላቸው፤ ረሡል ﷺ መልስ ከመስጠት ተቆጠቡና ሶሃቦችን መመልከት ጀመሩ፤ ከዚያም “በእርግጥ ተገጠመ ወይም በርግጥ ተመራ” አሉ፡፡ “ምን አልክ?” በማለት ረሡል ﷺ በድጋሜ ግለሰቡን ጠየቁት፤ እርሱም በድጋሜ ነገራቸው፤ ከዚያም ነብዩ ﷺ የሚከተለውን ተናገሩ፡- “አንድንም በእርሱ ሳታጋራ አላህን ልትገዛ ነው፤ ሶላትን ደንቡን ጠብቀህ ልትስግድ፤ ዘካ ልታወጣ፤ ዝምድናን ልትቀጥል፤ ግመሏን ተዋት (ልቀቃት)፡፡” በሌላ ዘገባ “የዝምድናን ባለቤት ልትቀጥል” ነው፡፡ ሰውየው ጠይቆ ከሄደ በኋላ “ይህ ሰው ባዘዝኩት መሰረት አጥብቆ ከያዘ ጀነት ገባ” በማለት የአላህ መልክተኛ ተናገሩ፡፡
📚ቡኻሪና ሙስሊም
↪️ ዝምድና መቀጠል ውለታን በመመለስ አይደለም ዝምድና ከተቀጠለ ብቻ የሚቀጥል፤ ከቆረጡ ደግሞ የሚቆርጥ ሰው አለ፡፡ እንደዚህ አይነቱ ሰው ውለታን መላሽ እንጅ ዝምድናን ቀጣይ አይባልም፡፡
➪ እንዲህ አይነቱ ተግባር ለቅርብም ይሁን ለሩቁ ሊሆን የሚችል ነው፡፡ ውለታን መመለስ በቅርብ ዘመድ ብቻ የሚወሰን አይደለም፡፡ ትክክለኛው ዝምድናን ቀጣይ ቆረጡም ቀጠሉም ዘመዶችን ለአላህ ብሎ የሚቀጥል ነው፡፡ በዚህ ምክንያት ረሡል ﷺ የሚከተለውን ሐዲስ ተናግረዋል፡-
"ليس الواصل بالمكافئ ، ولكن الواصل الذي إذا قطعت رحمه وصلها"
📚رواه البخاري ومسلم
“ውለታ መላሽ ዝምድናን ቀጣይ አይባልም፤ ዝምድና ቀጣይ የሚባለው ዝምድናው በተቆረጠ ጊዜ የሚቀጥል ነው፡፡”
📚 (ቡኻሪ፡ 5991)
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefyዝም አንልም እኛ በህይወት እስካለን፤ ባለችው አቅማችን እንፋለማለን፤ ያበጠው ይፈንዳ ሲፈልግ ይተርተር፤ እውነት ይነገራል ቢጣፍጥም ቢመር። ያለወትን ሀሳብ 💡 ➢ @AbuImranAselefybot በሚለው ያድርሱኝ ⤵ ↪ እቀበላለሁ ↩ ⤴ ➻ በተለይ ስህተት ካዩ በፍጥነት ይጠቁሙኝ
قال الحافظ ابن حجر رحمه الله : فالسعيد من تمسك بما كان عليه السلف واجتنب ما أحدثه الخلف" 📗{فتح الباري(13\143)
#የወንድ ልጅ ሀያዕው ሴት በጎኑ ስታልፍ አይኑን ሰበር ማድርግ ነው አንቺ ሰተር ብለሽ ስትመጪ ደሞ ማየትን አይሻም ።
#ቁጥብ ሁኚ ውድ ትሆኛለሽ
ራስሽን ሰትር አድርጊ እንቁ ትሆኛለሽ ውዷዬ !
https://t.me/umusaymen👉የዚህ ቻናል አላማ በአላህ ፍቃድ ሰዎች ተውሂድ እና ሱናን እንድያውቁ ከሽርክ እና ከቢድዓ እንዲሪቁ ለማድራግ ነው ❗️❗️ በሰለፎች (በደገጎች) መንገድ !! ↪️📚የሱና ዑለማዎችና ኡስታዞች የኪታብ ቂርኣትና ሙሓደራዎች ፈታዋዎች ሌሎቹም ጠቀሚ ፅዑፎች የሚለቀቁበት ቻናል ነው 👌 👌ስህተቶች ስተገኙ አስታከክሉን በረከሏሁ ፊኩም አዳራ ግን አተሰደቡ በአደብ ። @UMU_Useymin1 እርምት መቀባያ
በአሁኑ ሰዓት አብዛኛውን ሰው busy ካደረጉት የምዕራባውያን ኮተቶች መካከል “ፕራንክ” ❮prank❯ የሚሉት ነው።
➲ Prank ማለት ራሳቸው ምዕራባውያን እንደሚከተለው ይተረጉሙታል፦
«Prank is a mischievous trick or practical joke.»
ፕራንክ ማለት የተሳሳተ ተንኮል ወይም ተግባራዊ ቀልድ ነው።
➽ ይህ የተሳሳተ ተንኮል ሰዎች ባለወቁበት መልኩ የሚያስደነግጥ ነገር ይተገበርባቸዋል። ከደነገጡ ብሎም ካለቀሱ በኋላ prank ይባላሉ። በዚህ ተግባር በርካታ አላስፈላጊ ኮተቶች አሉ።
↪️ ሙስሊሞች በዚህ ተግባር መሳተፍ የለባቸውም በፍፁም አንዳንድ ሙስሊሞች ተሳትፈውበታል። የድሮ ፍቅረኛዬ ምናምን እያሉ ወንጀላቸውን በሚዲያ የበተኑ ሙስሊም ሴቶችን አስተውያለሁ። ካፊር ሴት እያቀፈ የሚጃጃል ወንድም ተመልክቻለሁ። ሌሎችም
➪ ስለዚህ ከዚህ እና መሰል ኮተቶች መራቅ አስፈላጊ ነው። የዚህን መሰል ፈሳድ ካፊሮች ሲያመጡ መከተል እነሱን ከመወዳጀት ነው። ይህ ደግሞ አደጋ መሆኑ ግለሰፅ ነው።
«وَمَنْ يَتَوَلَّهُمْ مِنْكُمْ فَإِنَّهُ مِنْهُمْ»
[المائدة: 51]
❝ከእናንተ የተወደጃቸው ሁሉ እርሱ ከእነርሱ ነው❞
♻️ ነብዩ ﷺ ይህን አይነት መመሳሰል በግልጽ ማውገዛቸው ከማናችንም የሚሰወር አይመስለኝም።
عَنِ ابْنِ عُمَرَ قَالَ:- قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:- "مَنْ تَشَبَّهَ بِقَوْمٍ فَهُوَ مِنْهُمْ".
(صحيح أبي داود)
حسنه الألباني (3401)
ኢብኑ ዑመር ነብዩ ﷺ እንዲህ ማለታቸውን አስተላልፏል፦
“ከሆኑ ሰዎች ጋር የተመሳሰለ ከነሱው ነው”
[ሶሂህ አቡ ዳውድ]
➜ ፕራንክ የምዕራባውያን ፍብርክ መሆኑ ግልፅ ነው። በዚህ ተግባር መሰለፍ ከእነሱ መመሳሰል ነው። ሲጀመር በውስጡ ያሉ ፈሳዶች ❪ጥፋቶች❫ ፕራንክ መራቅ ካሉብን ተግባራት መሆኑን ይጠቁሙናል።
ሌላ አንድ ሀዲስ እንጨምር፦
«عَنْ أَبِي سَعِيدٍ الْخُدْرِيِّ عَنِ النَّبِيِّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ:- ((لَتَتْبَعُنَّ سَنَنَ مَنْ كَانَ قَبْلَكُمْ شِبْرًا شِبْرًا وَذِرَاعًا بِذِرَاعٍ، حَتَّى لَوْ دَخَلُوا جُحْرَ ضَبٍّ تَبِعْتُمُوهُمْ)). قُلْنَا يَا رَسُولَ اللَّهِ الْيَهُودُ وَالنَّصَارَى قَالَ:- ((فَمَنْ)).»
رواه البخار ٧٣٢٠
↪️ አብደላህ ብን ኹድሪይ እንዳስተላለፈው ነብዩ ﷺ የሚከተለውንብለዋል፦
“ከናንተ በፊት የነበሩ ሰዎችን ፈለጎች ስንዝር በስንዝር ክንድ በክንድ ትከተላላችሁ። የአርጃኖ ጉድጓድ ቢገቡ እንኳን በርግጥም ትገቡታላችሁ!” ሲሉ “አይሁድና ክርስቲያኖችን ነው (ትከተላላችሁ) የምትለን?” ብለው ቦጠይቁ “ታዲያ ማንን ነው?!”
[ቡኻሪ፡ 7320]
➲ ከዚህ ሀዲስ አንፃር የት ነን!? በፕራንክ ጉዳይ busy የሆናችሁ ሰዎች በዚህ ሀዲስ ልትገሰፁ ይገባል። እስከመቼ ይሁዳ እና ነሷራ ተከትለን እንጓዛለን!? ደግሞ ሙሉዕ የሆነ ዲን እያለን!!! እስልምና ያጓደለው ምንም የለም። እስልምና ያላስተማረው ካለና ከሰራነው በትክክል ጥመት ነው። በጥመት ተግባር መሳተፋችንንም ማወቅ አለብን። ነገሮችን ቀለል ማድረግ ትተን ከፕራንክ እና መሰል ኮተቶች መራቅ አለብን።
↪️ በነገራችን ላይ በዚህ ፕራንክ በሚሉት ኮተት ብዙ ጊዜ የሚከሰቱበት ሁለት ተግባሮች አሉ እነሱም፦
❶ኛ ሰዎችን ማሸበር ወይም ማስደንገጥ እና
❷ኛ በውሸት ቅንብር ማሳቅ ነው።
☑️ እነዚህ ሁለት ተግባራት ደግሞ በእስልምና የተከለከሉ ናቸው። ማስረጃዎችን እንመልከት፦
✅ የመጀመሪያውን በተመለከተ ሙስሊም ሌላ ሙስሊምን ማስጨነቅ ወይም ማሸበር አይፈቅድም፦
عن عبدالرحمن بن أبي ليلى قال:- قال رسول الله ﷺ "لا يحلُّ لمسلمٍ أن يروِّعَ مسلمًا"
صححه الإمام الألباني
سنن أبي داود
አብዱረህማን ኢብኑ አቢ ሌይላ እንደተዘገበው የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ አሉ፦
"አንድ ሙስሊም ሙስሊምን ማሸበር አይፈቀድለትም"
ሱነን አቢ ዳውድ
ኢማም አልባኒ ሶሂህ ብለውታል
✅✅ ሁለተኛው ደግሞ ሰዎችን ለማሳቅ በሚል ውሸት እየፈጠሩ መናገር በኢስላም አይፈቀድም። ነብዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ይላሉ፡-
وَيْلٌ لِلَّذِي يُحَدِّثُ بِالْحَدِيثِ لِيُضْحِكَ بِهِ الْقَوْمَ فَيَكْذِبُ وَيْلٌ لَهُ وَيْلٌ لَهُ»
"ሰዎችን ለማሳቅ ብሎ እየዋሸ ወሬን የሚያወራ ሰው ወዮለት! ወዮለት! ወዮለት!"
አቡነ ዳውድ፣ ነሳኢይ፣ ቲርሚዚይ
ሸይኹል አልባኒይ “ሐሰን” ብለውታል፡፡
➧ በሌላ በኩል ደግሞ የሚከተለውን ሀዲስ እናገኛለን፦
عن أبي أمامة رضي الله عنه قال:- قال رسول الله – صلى الله عليه وسلم:-
"أنا زعيم ببيت في ربض الجنة لمن ترك المراء وإن كان محقا، وببيت في وسط الجنة لمن ترك الكذب وإن كان مازحا، وببيت في أعلى الجنة لمن حسن خلقه".
سنن أبي داود
وحسنه الألباني.
♻️ አቡ ኡማማህ ረዲየሏሁ ዐንሁም እንዲህ ብለዋል፡- የአላህ መልእክተኛ - ﷺ - እንዲህ ብለዋል፡-
"እኔ እውነተኛ ቢሆን እንኳን ክርክርን ለተወ ሰው በጀነት ዙሪያ ወይም ዳርቻ ላይ ቤት እንደሚኖረው ዋስ ነኝ። ቀላጅ እንኳን ቢሆን ደግሞ ውሸትን ለተወ ሰው በጀነት መሀል ላይ ቤት እንደሚኖረው ዋስ ነኝ። ስነ ምግባሩ ላማረለት ደግሞ በጀነት የላይኛው ክፍል ውስጥ ቤት እንደሚኖረው ዋስ ነኝ።"
ሱነን አቢ ዳውድ
አል-አልባኒ ሀሰን ብለውታል።
➲ በዚህ ሀዲስ ❸ ነጥቦች ጎልተው ተጠቅሰዋል።
❶ኛ ክርክር
❷ኛ ውሸት
❸ኛ ስነ-ምግባር
✅ ውዱ ነብይ ﷺ ❝ቀላጅ እንኳን ቢሆን ደግሞ ውሸትን ለተወ ሰው በጀነት መሀል ላይ ቤት እንደሚኖረው ዋስ ነኝ።❞ በማለት በቀልዳችን መዋሸት እንደሌለብን አስረድተዋል። ስለዚህ ውድ እህት ወንድሞች በፕራንክ ቀልድ የሚደረጉ ውሸቶች ትክክል አይደሉም። እኛም ተጠንቅቀን ሌሎችንም ልናስጠነቅቅ ይገባል።
📝 አቡ ዒምራን ሙሐመድ መኮንን
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefyዝም አንልም እኛ በህይወት እስካለን፤ ባለችው አቅማችን እንፋለማለን፤ ያበጠው ይፈንዳ ሲፈልግ ይተርተር፤ እውነት ይነገራል ቢጣፍጥም ቢመር። ያለወትን ሀሳብ 💡 ➢ @AbuImranAselefybot በሚለው ያድርሱኝ ⤵ ↪ እቀበላለሁ ↩ ⤴ ➻ በተለይ ስህተት ካዩ በፍጥነት ይጠቁሙኝ