cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

የሰለፍያ ደዕዋ በቻግኒالدعوة السلفية فى مدينة الشاغنى

ወደ ቻናሉ👇 ለመቀላቀል 👇ከፈለጉ👇 t.me/selefiyadawabechagni አስተያየታችሁን 👇ወይም 👇እርማታችሁን👇 t.me/selefiyadawabechagnibot ይፃፉልን። ይላኩልን።

Show more
The country is not specifiedAmharic7 424Religion & Spirituality66 639
Advertising posts
549
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-2730 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

«ﺍﻟﺪﻳﻦ ﺍﻟﻨﺼﻴﺤﺔ»_ «ዲን ምክክር ነው»_በአቡ ጁበይር .m4a
Show all...
# السلام عليكم ورحمة الله وبركاته. * እኔ የሚገርመኝ fb ላይ ያለው ሁሉ በእውቀት ደረጃ ተመሳሳይ የሚመስለው ሰው ነው ። ስለ አህለል ቢድአ የሆነ አካል በመረጃ ሲናገር /ሲፖስት/ " የእኔ እና አንተ ቤጤ/አምሳያ/አርፈን ብንቀመጥ ይሻላል ይልህል።" እኔ ማንኝ ? አንተ ማነህ ? ራስህን ስለ ዲንህ ባለህ የእውቀት ደረጃ ፈትሽ። እፈትሻለሁ። * ትኩረታችን ከጉዳዮ ነው ሀቅ ከገጠመ ትቀበላለህ ካልገጠመ ጣለው። * ይህን ለመመዘን ግን በመጠኑም ቢሆን ስለ ዲንህ ማወቅ ይጠበቅብሀል። * ከዚያ ውጭ ግን ሀቅ ሲነገር እኔና አንተ እያሉ ማዘናጋት የሀቅ ሰዎችን ወደ ሗላ እንደማይላቸው እወቅ። እንዲያውም ያጠነክራቸዋል። * ስለዚህ fb ላይ በዲናቸው ከእኛ የታሻሉ ሰዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ መገንዘብም አስፈላጊ ነው። * የበዲን ላይ ያለ እወቅት ከመናገር አሏህ ይጠብቀን። * ምክንያቱም ከተላላቅ ወንጀሎች የሚመደብና ከሺርክ ጋር ተቆራኝቶ የተገለፀ ገባድ ወንጀል ነው። قال سبحانه وتعالى:– [قُلْ إِنَّمَا حَرَّمَ رَبِّيَ الْفَوَاحِشَ مَا ظَهَرَ مِنْهَا وَمَا بَطَنَ وَالْإِثْمَ وَالْبَغْيَ بِغَيْرِ الْحَقِّ وَأَن تُشْرِكُوا بِاللَّهِ مَا لَمْ يُنَزِّلْ بِهِ سُلْطَانًا وَأَن تَقُولُوا عَلَى اللَّهِ مَا لَا تَعْلَمُونَ] {«ጌታዬ እርም ያደረገው መጥፎ ሥራዎችን፣ ከርሷ የተገለጸውንና የተደበቀውን ኃጢኣትንም፣ ያላግባብ መበደልንም፣ በርሱም ማስረጃ ያላወረደበትን (ጣዖት) በአላህ ማጋራታችሁን፣ በአላህም ላይ የማታውቁትን መናገራችሁን ብቻ ነው» በላቸው፡፡} * ያለ እውቀት መናገር ከሸይጧን የሚመጣ ትዛዝ ነው። قال سبحانه وتعالى:– [إِنَّمَا يَأْمُرُكُم بِالسُّوءِ وَالْفَحْشَاءِ وَأَن تَقُولُوا عَلَى اللَّهِ مَا لَا تَعْلَمُونَ] {(እርሱ) የሚያዛችሁ በኃጢኣትና በጸያፍ ነገር በአላህም ላይ የማታውቁትን እንድትናገሩ ብቻ ነው፡፡} * ስለዚህ ሸይጧንን በየትኛውም ጉዳይ ልንታዘዘው እንደማይችል ለሁሉም ሙስሊም ግልፅ ነው። ሆኖም ግን አብዛኛው ሰው በተለይ በዚህ ጉዳይ (በዲን ላይ ያለ እውቀት በመናገር) አብዛኛው ሰው በተግባር ሲታዘዘው ይታያል። * ይህ ደግሞ አደጋው በእኛ ብቻ የማይገደብና ወደ ሌሎች የሚሸጋገር መሆኑ ይበልጥ የከፋ ያደርገዋል። اللهم ارزقنا علما نافعا وعملا صالحا خالصا لوجهك الكريم. ونعوذ بك من علم لاينفع ومن قلب لاتخشع. 📝 አቡ ጃቢር ሙሐመድ ወደ ቻናሉ👇 ለመቀላቀል 👇ከፈለጉ👇 t.me/selefiyadawabechagni አስተያየታችሁን 👇ወይም 👇እርማታችሁን👇 t.me/selefiyadawabechagnibot ይፃፉልን። ይላኩልን
Show all...
የሰለፍያ ደዕዋ በቻግኒالدعوة السلفية فى مدينة الشاغنى

ወደ ቻናሉ👇 ለመቀላቀል 👇ከፈለጉ👇 t.me/selefiyadawabechagni አስተያየታችሁን 👇ወይም 👇እርማታችሁን👇 t.me/selefiyadawabechagnibot ይፃፉልን። ይላኩልን።

የአቡ በከር አሕመድ ጅህልና በአቡ በከር አሕመድ ላይ ረድ ክፍል ሁለት ➶➶➶➶ ክፍል አንድን ለማግኘት ⬇️ https://t.me/bahruteka/3734አቡ በከር አሕመድ ከሚቀጥፋቸው ቅጥፈቶች ውስጥ – የሳውዲ ስርኣት የመደንይ ስርኣት ነውመደንይ የሚለውን በንጉሳዊ አገዛዝ መተርጎሙ ቀጥሎየመደንይ ስርኣት ማለት ሰው በሰውመቱ፣ በእምነቱ፣ በአስተሳሰቡ የማይወገዝበት ሁሉን አካታች ስርኣት ነው ይላል። (ይህ ነው ትክክለኛ ትርጉሙ) – የመደንይ ስርኣት ሸሪዓ የሚያዝበት ነው ኢትዮዽያ ውስጥ ኢስላማዊ ሸሪዓ አይታሰብም ማሰቡም ወንጀል ነው‼ – ኢትዮዽያ ውስጥ ኢስላማዊ ስርኣት እንዲመጣ የሚያስብ ካለ ወንጀለኛ ነው ብለን እናምናለን – የመደንይ ስርኣት (ሰው በሰውነቱ፣ በእምነቱ፣ በአስተሳሰቡ፣ የማይወገዝበት ስርኣት) ከመጣ እምነቴን (እስልምናን) ይወክላልhttps://t.me/bahruteka
Show all...
قال العلامة الفوزان: (فهذا الإمام - أحمد - يجب أن نعرف موقفه من أجل أن نقتدي به، وأن نعرف- أيضا- موقفنا من الفرق الضالة والفرق المخالفة لأهل السنة والجماعة حتى لا نتساهل معها، ونعمل عملية تجميع، ونقول: نحن نجمع ولا نفرق كما تقوله بعض الجماعات!. بل يجب أن نفرق بين أهل الحق وأهل الباطل، نحن مع أهل الحق وإن قلوا، ولسنا مع أهل الباطل وإن كثروا، هذا هو الموقف الصحيح. فالإمام أحمد وحده وقف في وجه أمة، ونصره الله عليهم، ولا بد أن الإنسان يناله أذى في مقابل موقفه وصبره وثباته، لكن ما دام على الحق لا يهمه ذلك، وهذا في موازينه وفي حسناته عند الله) إعانة المستفيد
Show all...
قال يحيى بن يحيى شيخ البخاري ومسلم رحمه الله : الذب عن السنة أفضل من الجهاد . 📚 نقض المنطق : (12)
Show all...
«ﺍﻟﺪﻳﻦ ﺍﻟﻨﺼﻴﺤﺔ»_ «ዲን ምክክር ነው»_ክፍል አንድ_—①_ በአቡ ጁበይር..m4a
Show all...
ዝምድና የመቀጠል ጥቅሞች! =======> ❶ኛ ዝምድናን መቀጠል ወንጀል ለማስማር ምክንያት ይሆናል፡፡ 🍥 عن ابن عمر رضي الله عنه قال:أتى النبي صلى الله عليه وسلم رجل فقال : إني أذنبت ذنبا عظيما ، فهل لي من توبة ؟ فقال : النبي صلى الله عليه وسلم " : هل لك من أم؟"قال:لا . قال " فهل لك من خالة ؟ " قال : نعم . قال " : فبرها" 🍥 ኢብን ዑመር የሚከተለውን ሐዲስ አስተላልፈዋል፡- አንድ ሰው ወደ ነብዩ ﷺ በመምጣት “ታላቅ ወንጀል ፈጽሜያለሁ ፤ ጸጸት (ተውበት) ይኖረኝ ይሆን? አላቸው፡፡ “እናት አለችህ?” አሉት፡፡ “የለኝም” አለ፤ “አክስት አለችህ?” አሉት፤ “አዎ” አለ፡፡ “ለእርሷ በጎ ስራ” አሉት፡፡ 📚ቲርሚዚይ ❷ኛ ዝምድና መቀጠል ሲሳይ ለመስፋት፤ እድሜ ለመርዘም ምክንያት ይሆናል፡፡ 👈 عن علي بن أبي طالب رضي الله عنه ، عن النبي صلى الله عليه وسلم قال" :من سره أن يمد له في عمره ، ويوسع له في رزقه ، ويدفع عنه ميتة السوء ، فليتق الله ، وليصل رحمه " 📚 رواه الحاكم والبزار بسند جيد. 👉 ዓልይ ብን አቢ ጧሊብ 4 የሚከተለውን ሐዲስ አስተላልፈዋል፡- “የእድሜው መጨመር፤ የሲሳዩ መስፋት፤ ከእርሱ ላይ መጥፎ ፍጻሜ መወገዱ የሚያስደስተው ሰው አላህን ይፍራ፤ ዝምድናን ይቀጥል፡፡”وعن أنس رضي الله عنه أن رسول الله صلى الله عليه وسلم قال" :من أحب أن يبسط له في رزقه ، وينسأ له في أثره ، فليصل رحمه" 📚 رواه البخاري ومسلم.አነስ የሚከተለውን ሐዲስ አስተላልፈዋል፡- “ሲሳዩ እንዲሰፋለት፤ እድሜው እንዲረዝምለት የሚፈልግ ሰው ዝምድናን ይቀጥል፡፡” 📚ቡኻሪና ሙስሊም ዝምድናን መቀጠል ከአላህ ዘንድ ተወዳጅ ከሆኑ ተግባራት አንዱ ነው፡፡ ረሡል ﷺ ከሶሃቦች ጋር እያሉ ከኸይሰም ጎሳዎች አንድ ሰው መጣ፡፡ “ረሡል ነኝ የምትለው አንተ ነህ እንዴ?” አልኳቸው ይላል፡፡ እርሳቸውም “አዎ” አሉ፡፡ “የአላህ መልክተኛ ሆይ! ወደአላህ ተወዳጅ የሆነው ስራ የቱ ነው?” አልኳቸው፡፡ “በአላህ ማመን” አሉኝ ፡፡ “የአላህ መልክተኛ ሆይ! ከዚያስ” አልኳቸው፤ “ዝምድናን መቀጠል ነው” አሉኝ፡፡ “የአላህ መልክተኛ ሆይ!ከአላህ ዘንድ የሚያስቆጣ ተግባር ምንድን ነው?” አልኳቸው ፤ “በአላህ ማጋራት” አሉኝ፡፡ ከዚየም “የአላህ መልክተኛ ሆይ! ከዚያስ?” አልኳቸው፡፡ “ዝምድናን መቁረጥ ነው” አሉኝ፡፡ አቡ የዕላ ፊሙስነዲሂ፡ ጀይድ ጥሩ በሆነ ሰነድ አውርቶታል፡፡ዝምድናን መቀጠል ጀነት ለመግባት ከእሳት ለመዳን ምክንያት ይሆናል፡፡ ☑️ አቡ አዩብ የሚከተለውን ሐዲስ አስተላልፏል፡- “አንድ የገጠር ሰው በሰፈር ድንገት ከረሡል ﷺ ጋር ተገናኘና የግመላቸውን ልጓም በመያዝ “የአላህ መልክተኛ ሆይ! - ሙሀመድ ሆይ!- ወደ ጀነት የሚያቀርበኝ፤ ከእሳት የሚያርቀኝን ስራ ንገሩኝ” አላቸው፤ ረሡል ﷺ መልስ ከመስጠት ተቆጠቡና ሶሃቦችን መመልከት ጀመሩ፤ ከዚያም “በእርግጥ ተገጠመ ወይም በርግጥ ተመራ” አሉ፡፡ “ምን አልክ?” በማለት ረሡል ﷺ በድጋሜ ግለሰቡን ጠየቁት፤ እርሱም በድጋሜ ነገራቸው፤ ከዚያም ነብዩ ﷺ የሚከተለውን ተናገሩ፡- “አንድንም በእርሱ ሳታጋራ አላህን ልትገዛ ነው፤ ሶላትን ደንቡን ጠብቀህ ልትስግድ፤ ዘካ ልታወጣ፤ ዝምድናን ልትቀጥል፤ ግመሏን ተዋት (ልቀቃት)፡፡” በሌላ ዘገባ “የዝምድናን ባለቤት ልትቀጥል” ነው፡፡ ሰውየው ጠይቆ ከሄደ በኋላ “ይህ ሰው ባዘዝኩት መሰረት አጥብቆ ከያዘ ጀነት ገባ” በማለት የአላህ መልክተኛ ተናገሩ፡፡ 📚ቡኻሪና ሙስሊም ↪️ ዝምድና መቀጠል ውለታን በመመለስ አይደለም ዝምድና ከተቀጠለ ብቻ የሚቀጥል፤ ከቆረጡ ደግሞ የሚቆርጥ ሰው አለ፡፡ እንደዚህ አይነቱ ሰው ውለታን መላሽ እንጅ ዝምድናን ቀጣይ አይባልም፡፡እንዲህ አይነቱ ተግባር ለቅርብም ይሁን ለሩቁ ሊሆን የሚችል ነው፡፡ ውለታን መመለስ በቅርብ ዘመድ ብቻ የሚወሰን አይደለም፡፡ ትክክለኛው ዝምድናን ቀጣይ ቆረጡም ቀጠሉም ዘመዶችን ለአላህ ብሎ የሚቀጥል ነው፡፡ በዚህ ምክንያት ረሡል ﷺ የሚከተለውን ሐዲስ ተናግረዋል፡- "ليس الواصل بالمكافئ ، ولكن الواصل الذي إذا قطعت رحمه وصلها" 📚رواه البخاري ومسلم “ውለታ መላሽ ዝምድናን ቀጣይ አይባልም፤ ዝምድና ቀጣይ የሚባለው ዝምድናው በተቆረጠ ጊዜ የሚቀጥል ነው፡፡” 📚 (ቡኻሪ፡ 5991) https://t.me/AbuImranAselefy https://t.me/AbuImranAselefy https://t.me/AbuImranAselefy
Show all...
Abu Imran Muhammed Mekonn

ዝም አንልም እኛ በህይወት እስካለን፤ ባለችው አቅማችን እንፋለማለን፤ ያበጠው ይፈንዳ ሲፈልግ ይተርተር፤ እውነት ይነገራል ቢጣፍጥም ቢመር። ያለወትን ሀሳብ 💡 ➢ @AbuImranAselefybot በሚለው ያድርሱኝ ⤵ ↪ እቀበላለሁ ↩ ⤴ ➻ በተለይ ስህተት ካዩ በፍጥነት ይጠቁሙኝ

ወንድም እህቶቼ 🔶መስጅድ ስንገባ ጫማችንን በፔስታል ይዘን እንገባለን ወይም የሚጠብቅ ካለ እንሰጣለን፣......... ይሄ ሁሉ ጥንቃቄ ጫማችን በሌባ እንዳይሰረቅ ነው!!! ጡሩ። አቂዳችንና መንሃጃችንስ እንዳይሰረቅ ምን እያደረግን ነው❓ እኔ ከታዘብኩት ላካፍላችሁ፦ ⛔️ምኑንም የማያውቁትን ሰው ፣ በሚድያ ብቻ ድምፁን ሰምተው ወደውት አቂዳና መንሃጃቸውን አሳልፈው የሰጡ ብዙ ሰወች አሉ‼️ በቃ ዓሊም ይሁን መሃይም ይሁን ምኑንም ሳያውቁ ሚድያ ላይ የዘለለንና የጮኸን እንደጅራት የሚከተሉ በጣም ብዙ ናቸው‼️ በተለይ በተለይ ውጭ ሃገሩ ያሉ እህቶቻችን (ሁሉም)አይደሉም ግን አብዛኞቹን በሚባል ደረጃ ምንም አያውቁም 👉 ኪታብ አይደለም ቁርአን ያልጀመሩ ግን በአፈቅቤ ወንዶች ተሸውደው የሱን ጀልባ ተሳፍረው እየነጎዱ ነው። ዓላመቱ ሷሊህ አል'ፈውዛን አላህ ይጠብቃቸውና እንድህ ይላሉ፦ #አንተ አንተ ሸቀጣሸቀጥ ለመግዛት ስትፈልግ ፤ መኪና ለመግዛት ስትፈልግ ወይም ሌላ ትንሽ ነገር ለመግዛት ፈልገህ ሰለዛ እቃ ምንም እውቀት ከሌለህ #ተሳስተህ_የማይሆን ነገር እንዳትገዛ #ፈርተህ ስለዛ እቃ #ወደሚያወቅ_ሰው_ሄደህ_ትጠይቃለህ!!!👈ይሄ በዱኒያዊ ጉዳይ ነው። 👉 #በድንህ_ጉዳይ #ለምንድነው❓ አዋቂወችን፣ አላህን የሚፈሩትን ፣የእውቀት ባለቤቶችን #የማትጠይቀው❓ #ለዱኒያህ_እየመረመርክ_ለድንህ_ለምድነው_የማትመረምረው»❓ ምንጭ፦ሚን አዳቢ አል'ሙፍቲ ወአል'ሙስተፍቲ ⛔️ በቃ የወደዱትን ሰው ሌላ ሰው በመረጃ ጥፋቱን ቢናገርም በቃ ተናጋሪው ማንም ይሁን‼️ ለምን ዓሊም፣ ሸይኽ አይሆንም አውርደው ከመፈጥፈጥ ወደሗላ አይሉም‼️ ምን ያክል ተዓሱብ እንዳሰከራቸው በግልጽ እያየነው ያለ ጉዳይ ነው። ደግሞ ወደሰለፊያ (የውሸት)መጠጋታቸው ነገሩን ይበልጥ አስጠሊታ ያደርገዋል። ለምን ካላችሁ ሙሪድነት ሰለፊያ ላይ ፈፅሞ ተቀባይነት የሌለው ጉዳይ ስለሆነ ነው። ⛔️ ከወንዶች ደግሞ እዚህ ሚድያ ላይ የታዘብኩት👉 ፉላን የነቃ ነው ፣ እሱ ትንሽ እውቀት አለው ፣ አስተዋይና በሳል ነው፣........ ብለን የምናስባቸው የተመዩዕ ፊትና ስትመጣ ብጥስጥሳቸው ወጥቶ ፣ ሹቡሃ ጠራርጎ ወሰዳቸው። በዚህም አልበቃቸውም ሰለፊያን ከጠላቶቿ ጎን ቆመው መዋጋት ጀመሩ‼️ ለካ ተሳስተን ነበር ብለናል። وَتَحْسَبُهُمْ أَيْقَاظًا وَهُمْ رُقُودٌ ۚ እነሱም የተኙ ሆነው ሳሉ (ዓይኖቻቸው በመከፈታቸው) ንቁዎች ናቸው ብለህ ታስባቸዋለህ፡፡ ሱራ አል'ካህፍ:18 ↪️ ይሄን ያክል ርቀት የተጓዛችሁለት ሰው የሰለፊያን የማይቀማ ሰርቲፊኬት ማነው የሰጠው❓ አወ በፊት ሰለፊይ ሊሆን ይችላል!!! ታድያስ❓ በህይወት ያለ ሰውኮ ፊትና አይታመንለትም!!! ሊጠም ይችላል በል እንዳውም ከሃድም ሊሆን ይችላል‼️ ታድያስ❓ ማነው ግለሰብ ላይ ተጣበቁ ያላችሁ❓ 🔰ዓበደላህ ኢብኑ መስዑድ ረድየላሁ ዓንሁ እንድህ ብለዋል፦ «ሰዎችን መከተል የፈለገ የሞቱትን ይከተል፡፡ በህይወት ያለው ፈተና ላይ ላለመውደቁ ዋስትና የለም፡፡ እነዚያ የሙሐመድ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ሰሐቦች ከዚህ ኡማ በላጭ ህዝብ ነበሩ፡፡ ቅን ልቦና ያላቸው፣ እውቀታቸው የጠለቀ፣ መፈላፈል የማያበዙ ነበሩ፡፡ አላህ የሱን ነብይ እንዲጎዳኙ፣ ዲኑን እንዲያቃኑ የመረጣቸው ሰዎች ናቸው፡፡ ደረጃቸውን እወቁላቸው፡፡ ትውፊቶቻቸውን ተከተሉ፡፡ በተቻላችሁ ስነ-ምግባራቸውንና ዲናቸውን አጥብቃችሁ ያዙ፡፡ ምክኒያቱም እነሱ ቀጥ ያለው ጎዳና ላይ ነበሩና፡፡» 📚 [(ጃሚዑል በያን፡ 2/97) ሊ ኢብኒ ዐብዱልበር] ✅ሸይኸል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያ ረሂመሁላህ እንድህ ብለዋል፦ « ሸይኽን ወይም ዓሊምን እሱ የሚለውንና የሚሰራውን በሙሉ በመከተል የያዘ ሁሉ⏩ ከረሡል ዓለይሂ ሶላት ወሰላም ውጭ ከእሱ(ከሸይኹ ወይም ዓሊሙ) #ጋር_የተስማማን_የሚወዳጅ_ከሆነ‼️‼️‼️⏩#ከሱ_ጋር_የማይስማማን_ጠላት_የሚያደር_ከሆነ‼️‼️‼️⏩#እሱ_ሙብተድዕ_ጠማማ_ነው👉ከኪታብና(ከቁርአን) ከሱና ያፈነገጠ ነው» 📚ጃሚዑ አልመሳኢል:7/464 #በህይወት_ያለ_ሰው_ፈተና_አይታመንለትም ኢብኑ ዑሰይሚን ረሂመሁላህ እንድህ ብለዋል፦ ↪️ « #በፊት_በትክክለኛው_አቂዳ ቀጥ ብለው #በሗላ_ግን_የሚፈተን ስንትና ስንት ሰው አለ? #ይሄን ጊዜ #ቀጥ_ብሎ_በነበረበት ሁኔታ #ተከትለኸው ፣ እሱ በሄደበት ሄደህ፣ #መሪ_አድርገህ_ይዘኸው!!! #አንተ_በእሱ ላይ #እምነት_አሳድረህ #አንተ_ሳታውቅ_ሊያፈነግጥ_ይችላል‼️ይሄን ጊዜ #አብረኸው_ትከስራለህ‼️በህይወት ያለ ሰው ፊትና አይታመንለትም» 📖ሸርሁ አል'ዓቂደቱ አል'ተድሙሪያ:20 https://t.me/nu_selefochin_enketel
Show all...
«ኑ ሰለፎችን እንከተል» channel

قال الحافظ ابن حجر رحمه الله :  فالسعيد من تمسك بما كان عليه السلف واجتنب ما أحدثه الخلف" 📗{فتح الباري(13\143) 

#የወንድ ሀያዕ! ~  ~      #ወንድ ልጅ  በተፈጥሮው ሀያዕ ያላትን ሴት ይፈራል! ያፍራልም! ሰተር ያልሽና ቁጥብ ከሆንሽ ሊላከፍሽ ይቅርና ቀና ብሎ አንቺን ለማየት አይደፍርም ።     #ራስሽን ካከበርሽ ወንድ ልጅ ያከብርሻል ለራስሽ ክብር ከሌለሽ ደግሞ ወንድ ልጅ ሊያከብርሽ አይችልም ።       #ክብርሽን ስትጠብቂ ከነ_ክብረሽ ሊወስድሽ ወላጆችሽን ይማፀናል!       #ራስሽን ስታረክሺ ግን ጊዜ ለማሳለፊያ እንጂ ለቁም ነገር አይፈልግሽም ።     #ሴት ልጅ ራሷን ሰብሰብ አድርጋ ስትኖር ወንድ ሊያት ያፍራል በጎኑ እንኳን ብታልፍ ቀና ብሎ አያይም ።     #የወንድ ልጅ ሀያዕው ሴት በጎኑ ስታልፍ አይኑን ሰበር ማድርግ ነው አንቺ ሰተር ብለሽ ስትመጪ ደሞ ማየትን አይሻም ።      #ቁጥብ ሁኚ ውድ ትሆኛለሽ ራስሽን ሰትር አድርጊ እንቁ ትሆኛለሽ ውዷዬ ! https://t.me/umusaymen
Show all...
የተፈጠርንለት ዋና ዓላማ አላህን በብቸኝነት መገዛት ነው እዚህች ምድር ለይ ላጭር ጊዜ ቆይተን ከዛም እንሞታለን 🖼

👉የዚህ ቻናል  አላማ በአላህ ፍቃድ ሰዎች ተውሂድ እና ሱናን እንድያውቁ ከሽርክ እና ከቢድዓ እንዲሪቁ ለማድራግ ነው ❗️❗️ በሰለፎች (በደገጎች) መንገድ !! ↪️📚የሱና ዑለማዎችና ኡስታዞች የኪታብ ቂርኣትና ሙሓደራዎች ፈታዋዎች ሌሎቹም ጠቀሚ ፅዑፎች የሚለቀቁበት ቻናል ነው 👌 👌ስህተቶች ስተገኙ አስታከክሉን በረከሏሁ ፊኩም አዳራ ግን አተሰደቡ  በአደብ ። @UMU_Useymin1 እርምት መቀባያ

የምን ፕራንክ ነው!? እንዴ!!!መሰልጠን እና መሰይጠን ለዩ        ❪„„„„„„„„„„„„„„„„„❫ ✅ ባለንበት የተደበላለቀ ዘመን የጠራ እውቀት ላይ ሆኖ ዲኑን እና ክብሩን የጠበቀ ታድሏል። ♻️ በአሁኑ ሰዓት አብዛኛውን ሰው busy ካደረጉት የምዕራባውያን ኮተቶች መካከል “ፕራንክ” ❮prank❯ የሚሉት ነው። ➲ Prank ማለት ራሳቸው ምዕራባውያን እንደሚከተለው ይተረጉሙታል፦ «Prank is a mischievous trick or practical joke.» ፕራንክ ማለት የተሳሳተ ተንኮል ወይም ተግባራዊ ቀልድ ነው።ይህ የተሳሳተ ተንኮል ሰዎች ባለወቁበት መልኩ የሚያስደነግጥ ነገር ይተገበርባቸዋል። ከደነገጡ ብሎም ካለቀሱ በኋላ prank ይባላሉ። በዚህ ተግባር በርካታ አላስፈላጊ ኮተቶች አሉ። ↪️ ሙስሊሞች በዚህ ተግባር መሳተፍ የለባቸውም በፍፁም አንዳንድ ሙስሊሞች ተሳትፈውበታል። የድሮ ፍቅረኛዬ ምናምን እያሉ ወንጀላቸውን በሚዲያ የበተኑ ሙስሊም ሴቶችን  አስተውያለሁ። ካፊር ሴት እያቀፈ የሚጃጃል ወንድም ተመልክቻለሁ። ሌሎችም ➪ ስለዚህ ከዚህ እና መሰል ኮተቶች መራቅ አስፈላጊ ነው። የዚህን መሰል ፈሳድ ካፊሮች ሲያመጡ መከተል እነሱን ከመወዳጀት  ነው። ይህ ደግሞ አደጋ መሆኑ ግለሰፅ ነው። «وَمَنْ يَتَوَلَّهُمْ مِنْكُمْ فَإِنَّهُ مِنْهُمْ» [المائدة: 51] ❝ከእናንተ የተወደጃቸው ሁሉ እርሱ ከእነርሱ ነው❞ ♻️ ነብዩ ﷺ ይህን አይነት መመሳሰል በግልጽ ማውገዛቸው ከማናችንም የሚሰወር አይመስለኝም። عَنِ ابْنِ عُمَرَ قَالَ:- قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:- "مَنْ تَشَبَّهَ بِقَوْمٍ فَهُوَ مِنْهُمْ". (صحيح أبي داود) حسنه الألباني (3401) ኢብኑ ዑመር  ነብዩ ﷺ እንዲህ ማለታቸውን አስተላልፏል፦ “ከሆኑ ሰዎች ጋር የተመሳሰለ ከነሱው ነው” [ሶሂህ አቡ ዳውድ]ፕራንክ የምዕራባውያን ፍብርክ መሆኑ ግልፅ ነው። በዚህ ተግባር መሰለፍ ከእነሱ መመሳሰል ነው። ሲጀመር በውስጡ ያሉ ፈሳዶች ❪ጥፋቶች❫ ፕራንክ መራቅ ካሉብን ተግባራት መሆኑን ይጠቁሙናል። ሌላ አንድ ሀዲስ እንጨምር፦ «عَنْ أَبِي سَعِيدٍ الْخُدْرِيِّ عَنِ النَّبِيِّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ:- ((لَتَتْبَعُنَّ سَنَنَ مَنْ كَانَ قَبْلَكُمْ شِبْرًا شِبْرًا وَذِرَاعًا بِذِرَاعٍ، حَتَّى لَوْ دَخَلُوا جُحْرَ ضَبٍّ تَبِعْتُمُوهُمْ)). قُلْنَا يَا رَسُولَ اللَّهِ الْيَهُودُ وَالنَّصَارَى قَالَ:- ((فَمَنْ)).» رواه البخار ٧٣٢٠ ↪️ አብደላህ ብን ኹድሪይ እንዳስተላለፈው ነብዩ ﷺ የሚከተለውንብለዋል፦ “ከናንተ በፊት የነበሩ ሰዎችን ፈለጎች ስንዝር በስንዝር ክንድ በክንድ ትከተላላችሁ። የአርጃኖ ጉድጓድ ቢገቡ እንኳን በርግጥም ትገቡታላችሁ!” ሲሉ “አይሁድና ክርስቲያኖችን ነው (ትከተላላችሁ) የምትለን?” ብለው ቦጠይቁ “ታዲያ ማንን ነው?!”   [ቡኻሪ፡ 7320]ከዚህ ሀዲስ አንፃር የት ነን!? በፕራንክ ጉዳይ busy የሆናችሁ ሰዎች በዚህ ሀዲስ ልትገሰፁ ይገባል። እስከመቼ ይሁዳ እና ነሷራ ተከትለን እንጓዛለን!? ደግሞ ሙሉዕ የሆነ ዲን እያለን!!! እስልምና ያጓደለው ምንም የለም።  እስልምና ያላስተማረው ካለና ከሰራነው በትክክል ጥመት ነው። በጥመት ተግባር መሳተፋችንንም ማወቅ አለብን። ነገሮችን ቀለል ማድረግ ትተን ከፕራንክ እና መሰል ኮተቶች መራቅ አለብን። ↪️ በነገራችን ላይ በዚህ ፕራንክ በሚሉት ኮተት ብዙ ጊዜ የሚከሰቱበት ሁለት ተግባሮች አሉ እነሱም፦ ❶ኛ ሰዎችን ማሸበር ወይም ማስደንገጥ እና ❷ኛ በውሸት ቅንብር ማሳቅ ነው። ☑️ እነዚህ ሁለት ተግባራት ደግሞ በእስልምና የተከለከሉ ናቸው። ማስረጃዎችን እንመልከት፦የመጀመሪያውን በተመለከተ ሙስሊም ሌላ ሙስሊምን ማስጨነቅ ወይም ማሸበር አይፈቅድም፦ عن عبدالرحمن بن أبي ليلى قال:-  قال رسول الله ﷺ "لا يحلُّ لمسلمٍ أن يروِّعَ مسلمًا"        صححه الإمام  الألباني           سنن أبي داود አብዱረህማን ኢብኑ አቢ ሌይላ እንደተዘገበው የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ አሉ፦ "አንድ ሙስሊም ሙስሊምን ማሸበር አይፈቀድለትም" ሱነን አቢ ዳውድ ኢማም አልባኒ ሶሂህ ብለውታል ✅✅ ሁለተኛው ደግሞ ሰዎችን ለማሳቅ በሚል ውሸት እየፈጠሩ መናገር በኢስላም አይፈቀድም። ነብዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ይላሉ፡- وَيْلٌ لِلَّذِي يُحَدِّثُ بِالْحَدِيثِ لِيُضْحِكَ بِهِ الْقَوْمَ فَيَكْذِبُ وَيْلٌ لَهُ وَيْلٌ لَهُ» "ሰዎችን ለማሳቅ ብሎ እየዋሸ ወሬን የሚያወራ ሰው ወዮለት! ወዮለት! ወዮለት!" አቡነ ዳውድ፣ ነሳኢይ፣ ቲርሚዚይ ሸይኹል አልባኒይ “ሐሰን” ብለውታል፡፡በሌላ በኩል ደግሞ የሚከተለውን ሀዲስ እናገኛለን፦ عن أبي أمامة رضي الله عنه قال:- قال رسول الله – صلى الله عليه وسلم:- "أنا زعيم ببيت في ربض الجنة لمن ترك المراء وإن كان محقا، وببيت في وسط الجنة لمن ترك الكذب وإن كان مازحا، وببيت في أعلى الجنة لمن حسن خلقه".  سنن أبي داود وحسنه الألباني. ♻️ አቡ ኡማማህ ረዲየሏሁ ዐንሁም እንዲህ ብለዋል፡- የአላህ መልእክተኛ - ﷺ - እንዲህ ብለዋል፡- "እኔ እውነተኛ ቢሆን እንኳን ክርክርን ለተወ ሰው በጀነት ዙሪያ ወይም ዳርቻ ላይ ቤት እንደሚኖረው ዋስ ነኝ። ቀላጅ እንኳን ቢሆን ደግሞ ውሸትን ለተወ ሰው በጀነት መሀል ላይ ቤት እንደሚኖረው ዋስ ነኝ። ስነ ምግባሩ ላማረለት ደግሞ በጀነት የላይኛው ክፍል ውስጥ ቤት እንደሚኖረው ዋስ ነኝ።" ሱነን አቢ ዳውድ አል-አልባኒ ሀሰን ብለውታል። ➲ በዚህ ሀዲስ ❸ ነጥቦች ጎልተው ተጠቅሰዋል። ❶ኛ ክርክር ❷ኛ ውሸት ❸ኛ ስነ-ምግባር ውዱ ነብይ ﷺቀላጅ እንኳን ቢሆን ደግሞ ውሸትን ለተወ ሰው በጀነት መሀል ላይ ቤት እንደሚኖረው ዋስ ነኝ።❞ በማለት በቀልዳችን መዋሸት እንደሌለብን አስረድተዋል። ስለዚህ ውድ እህት ወንድሞች በፕራንክ ቀልድ የሚደረጉ ውሸቶች ትክክል አይደሉም። እኛም ተጠንቅቀን ሌሎችንም ልናስጠነቅቅ ይገባል። 📝 አቡ ዒምራን ሙሐመድ መኮንን https://t.me/AbuImranAselefy https://t.me/AbuImranAselefy https://t.me/AbuImranAselefy
Show all...
Abu Imran Muhammed Mekonn

ዝም አንልም እኛ በህይወት እስካለን፤ ባለችው አቅማችን እንፋለማለን፤ ያበጠው ይፈንዳ ሲፈልግ ይተርተር፤ እውነት ይነገራል ቢጣፍጥም ቢመር። ያለወትን ሀሳብ 💡 ➢ @AbuImranAselefybot በሚለው ያድርሱኝ ⤵ ↪ እቀበላለሁ ↩ ⤴ ➻ በተለይ ስህተት ካዩ በፍጥነት ይጠቁሙኝ