ጃዚኤል (ማኅሌት)Speech & Language therapy🗣👂🗣
Open in Telegram
ጀዚኤል( ማህሌት) ስፒች ቴራፒ የተከፈተው ስለዚህ ህክምና እና በዚህ ህክምና ስለሚሰጡት እክሎች ግንዛቤ ለመፍጠር፣ ህክምና፣ማማከርና ስልጠና ለመስጠት ነው።በዚህ ህክምና የሚሰጡት -ለንግግር እክሎች፣ ለቋንቋ እክሎች፣ ለመዋጥ እክሎች፣ ለድምጽ እክሎች፣ ለመስማት እክሎችና ናቸው።ከእነዚህም ውስጥ ኦቲዝም፣ ስትሮክ፣ መንተባተብ፣ የቋንቋ መዘግየት፣ሲንድሮምስ... @Jazielspeechtherapyclinic1
Show more1 661
Subscribers
No data24 hours
-67 days
-630 days
Posts Archive
ስፒች ቴራፒ ለምትፈልጉ
☎️0954999933
0940103047
📍መገናኛ ሲቲ ሞል 3ኛ ፎቅ
#ስፒች_ቴራፒ_በኢትዮዽያ #ጃዚኤል_ስፒች_ቴራፒ #speechtherapyinethiopia #speechtherapyinaddisababa #ማሕሌትስፒችቴራፒ @ማኅሌት Speech Therapist
ኮክሌር ኢምፕላንት
ኮክሌር ኢምፕላንት ከተደረገ በኋላ የንግግር ቴራፒስቶች የሚያከናውኗቸው 5 ዋና ዋና ተግባራት፡
1 ድምፅን ማስተዋወቅ: አካባቢያዊ ድምፆችን እንዲሰሙና እንዲለዩ ማሰልጠን።
2 ድምጾችን ማወዳደር: የቃላትን፣ የድምፅ ከፍታ እና ቃና ልዩነቶችን ማጥናት።
3 ቋንቋ ማዳበር: የቃላት ዝርዝርን ማስፋፋት እና አረፍተ ነገር መገንባት።
4 በመስማት ብቻ መነጋገር (AVT): በመስማት ችሎታ ላይ ብቻ ተመስርቶ ንግግርን ማዳበር።
5 የቤተሰብ ስልጠና: ወላጆች በቤት ውስጥ ሊያደርጉዋቸው የሚገቡ የልምምድ እቅዶችን ማዘጋጀት።
ስፒች ቴራፒ ለምትፈልጉ
☎️0954999933
0940103047
📍መገናኛ ሲቲ ሞል 3ኛ ፎቅ
#ስፒች_ቴራፒ_በኢትዮዽያ #ጃዚኤል_ስፒች_ቴራፒ #speechtherapyinethiopia #speechtherapyinaddisababa #ማሕሌትስፒችቴራፒ @ማኅሌት Speech Therapist
ዳውን ሲንድረም ኖሮባት የመጀመሪያዋ ሕግ ባለሙያ (ጠበቃ) በመሆን የዓለም ታሪክ የሰራችው የ25 አመቷ አና ቪክቶሪያ
አና ቪክቶሪያ የተባለችው የ25 ዓመቷ የዛካቴካስ ሜክሲኮ ተወላጅ ዳውን ሲንድረም (Down syndrome) ኖሮባት የመጀመሪያዋ ሕግ ባለሙያ (ጠበቃ) በመሆን በዓለም ታሪክ ሰርታለች።
ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት አና ቪክቶሪያ ኤስፒኖ ደ ሳንቲያጎ በዛካቴካስ፣ ሜክሲኮ የሕግ ዲግሪዋን በማጠናቀቅና ተቋማዊ መድልዎዎችን በማለፍ አዲስ የዓለም ታሪክ አስመዝግባለች።
በአፈጣጠር የጤና እክሏ ምክንያት ከአንድ ዩኒቨርሲቲ ውድቅ ከተደረገች በኋላ፣ በሌላ ተቋም ለአምስት ዓመታት ትምህርቷን ተከታትላ አጠናቅቃለች። አሁን ደግሞ የልዩ ፍላጎት (የአካል ጉዳተኞች) መብቶችን ለመሞገት በስቴቷ ፓርላማ የወንበር እጩ ሆና ለመወዳደር አቅዳለች።
ዳውን ሲንድረም ያለበት ልጅ ቋሚ የህክምና ክትትልና ድጋፍ ከተደረገለት ያሰበውን ማንኛውንም ነገር ማሳካት እንደሚችል ማሳያ መሆኗም ተነግሯል።
DireTube
ስፒች ቴራፒ ለምትፈልጉ
☎️0954999933
0940103047
📍መገናኛ ሲቲ ሞል 3ኛ ፎቅ
#ስፒች_ቴራፒ_በኢትዮዽያ #ጃዚኤል_ስፒች_ቴራፒ #speechtherapyinethiopia #speechtherapyinaddisababa #ማሕሌትስፒችቴራፒ @ማኅሌት Speech Therapist
የመዋጥ_እክል #swallowingdisorders
ስፒች ቴራፒ ለምትፈልጉ
☎️0954999933
0940103047
📍መገናኛ ሲቲ ሞል 3ኛ ፎቅ
ሀይፐርሌክሲያ (Hyperlexia)
ሀይፐርሌክሲያ ምንድነ ነው?
ሀይፐርሌክሲያ በህጻንነት ዕድሜ ላይ የማንበብ ችሎታ እና ፊደላት እና ቁጥሮች የመለየት የላቀ ችሎታ ነው።
ሀይፐርሌክሲያ ያለው ልጅ የማንበብ ችሎታው ከሌሎች ትናንሽ ልጆች አቅም በላይ ነው፡፡
ሃይፐርሌክሲያ ከኦቲዝም እና ሌሎች የእድገት ችግሮች ጋር አብሮ ሊከሰት ይችላል።
ሀይፐርሌክሲያ ሶስት አካላት አሉት
- በጊዜ የንባብ ችሎታ - አንዳንድ ጊዜ ተወዳጅ ንባብ ተብሎ ይጠራል።
- የቃል ቋንቋ መዘግየት
-የማህበራዊ ግንኙነት እክል።
የሀይፐር አሌክሲያ ምልክቶች
-ከእኩዮች ጋር ሲወዳደር በጣም ጥሩ የንባብ ችሎታ (ብዙውን ጊዜ ዕድሜያቸው ከ 5 ዓመት በፊት)
-በቁጥሮች እና ፊደሎች ላይ መመሰጥ
- የመረዳት እና የቃል ቋንቋን የመጠቀም ችሎታ እክል
-ጥያቄዎችን የመመለስ እክል - ማን ፣ ምን ፣ የት ፣ መቼ ፣ ለምን?
- የእይታ ተማሪዎች
- ከማህበራዊ መስተጋብር ጋር መታገል (ውይይት መጀመር ፣ ውይይቶችን ማቆየት ፣ ተራዎችን መውሰድ ፣ ወዘተ)
- በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴዎች ላይ ሽግግሮች ወይም ለውጦች ጋር በተያያዘ የሚፈትኑ ሁኔታዎች ፡፡
-የማስታወስ ችሎታ
- ከዕድሜ ደረጃቸው በላይ ቃላትን ማንበብ ፣ ራስ ወዳድነት (ከ 5 ዓመት በፊት ይታያል)
- የቃል ቋንቋን የመረዳት እክል
- በሚያስደንቅ ሁኔታ ፊደሎችን ፣ ቁጥሮችን ፣ ካርታዎችን ወይም የእይታ መልኮችን መጠቀም
- ድግግሞሽ( echolalia )
-መደበኛ እድገቱ ከ 18 እስከ 24 ወራት ድረስ ይጠናቀቃል ከዚያም እንደገና ወደ ኋላ መመለስ
-ረቂቅ ፅንሰ-ሀሳቦችን የ ፣ ተጨባጭ በሆነ መልኩ ፣ ቃል በቃል ያስባል
- ልዩ ወይም ያልተለመዱ ፍርሃቶች
- የስሜት ህዋሳት
- ጠንካራ የመስማት እና የእይታ ማህደር(ትውስታ)
ጃዚኤል or ማኅሌት Speech and Language Therapy clinic
አድራሻ :- መገናኛ -ሲቲሞል 3ኛ ፎቅ ስለሺ ስህን ህንፃ አጠገብ
☎️ 0940103047
0954999933
የህንጻ ተቋራጩ አላሳክምም ሲል"ልጄን ለማዳን ቤቴን ሸጫለሁ"😭💔
ታዳጊ አቤል መለሰ (ቤቢ) በፒያሳ ሀገር ፍቅር ቲያትር አካባቢ በእግረኛ መንገድ ላይ በመጓዝ ላይ እያለ፣ በመገንባት ላይ ከነበረ ህንፃ ላይ ከ37 ኪሎ በላይ ክብደት ያለው ከባድ ቁስ አካል በላዩ ላይ በመውደቁ አሰቃቂ አደጋ ደርሶበታል። ይህ ክፉ አደጋ ከደረሰበት ቅጽበት ጀምሮ፣ ቤተሰቦቹ የልጃቸውን ህይወት ለማትረፍ እጅግ ከባድ የሆኑ የህይወት ፈተናዎችን እና ውጣ ውረዶችን በማሳለፍ ላይ ይገኛሉ።
ጎበዙ ተማሪ አቤል ላለፉት ስድስት ወራት በከፍተኛ የህክምና ክትትል ውስጥ ይገኛል። ሆኖም በአደጋው ቀጥተኛ ተጠያቂ የሆነው የህንፃው ተቋራጭ በድንገት የህክምና ወጪውን በማቋረጡ፣ ቤተሰቡ ወደባሰ ጭንቀት ገብቷል። የአቤል አባት አቶ መለሰ፣ ልጃቸውን ለማዳን እያደረጉት ስላለው ልብ የሚነካ ትግል፣ ስላጋጠማቸው አስከፊ ፈተና፣ እንዲሁም ስለ ህክምናውና የህግ ሂደቱ ወቅታዊ ሁኔታ አጣዳፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
አቶ መለሰ እንደሚያስረዱት፣ የልጃቸውን ህይወት ለማዳን እጅግ ፈታኝ መንገዶችን አልፈዋል ።አቤል ሦስት ጊዜ ከባድና ቀላል የጭንቅላት ቀዶ ህክምና (ሰርጀሪ) ተደርጎለታል። የመጀመሪው አደጋው በተከስት እለት 4 ሰዕት የፈጀ ሰርጀሪ ፣ ሁለተኛው 04/05/2018 ሰባት ሰዓታትን የፈጀ ሰርጀሪ ተደርጎለታል።
ጭንቅላቱ ላይ ፈሳሽ በመሙላቱ በቲዩብ እንዲወጣ ተደርጓል። በኋላም ለሶስተኛ ጊዜ መጋቢት 6/2018 አነስተኛ የጭንቅላት ቀዶ ህክምና (Mini-surgery) ተካሂዶለታል።ከሚኒ ሰርጀሪው በኋላ ለ አንድ ወር TPN በትልቁ የደም ስር በቀን 15 ሺህ ብር እየተከፈለ ህይወቱን ማቆየት መቻሉን አስረድተዋል።
እስካሁን ለህክምና፣ ለመድኃኒት እና ለሌሎች ህክምናዎች ወጪ የሸፈኑ ቢሆንም፣ ከሁለት ወር ከ15 ቀን በኋላ ግን "በቃ አንከፍልም" በማለት ወጪውን ሙሉ በሙሉ አቋርጠዋል። አደጋው በደረሰበት ቅጽበት የኤፍ.ኢ ኮንስትራክሽን የፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ በአጋጣሚ በቦታው ስለነበር፣ በራሱ መኪና አቤልን እና አብሮት የነበረውን ጓደኛውን ወደ አቤት ሆስፒታል ወስዷቸዋል። ከአቤት ሆስፒታል የሲቲ ስካን እና የራጅ ምርመራዎች በኋላ፣ ታዳጊው ወዲያውኑ ወደ ላንሴት ሆስፒታል እንዲዛወር ተደርጓል።
በወቅቱ የተቋራጩ ተወካዮች ለመጀመሪያ ማስያዣ 350 ሺህ ብር በመክፈል ህክምናው እንዲጀመር አድርገዋል ። በዚህም ተቋራጩ የሁለቱን ቀዶ ጥገናዎች ወጪን ጨምሮ ፣ ለህክምና አጠቃልይ 5 ሚሊየን 666 ሺህ 960 ብር አውጥቷል። ሆኖም ግን ያልተገባ ምክንያት በመፍጠር የህክምና ወጪውን አልሸፍንም በማለት አቁሟል ብለዋል ።
እንደ አቶ መለሰ ገለጻ ፤ ታዳጊ አቤል በጽኑ ህክምና ክፍል (ICU) ውስጥ በሰው ሰራሽ የመተንፈሻ ማሽን (Ventilator) እየተረዳ ባለበት ወቅት ፤ የሳንባ ምች (Necrotizing Pneumonia) የተከሰተበት ሲሆን፣ የመተንፈስ አቅሙም ከማሽን ጋር ሆኖ 60% ብቻ ሆኗል ።
በተጨማሪም ህይወትን ሊያሳጣ የሚችል አደገኛ የሆነ የሳምባ ኢንፌክሽን በመከሰቱ፣ አይሲዩ (ICU) ውስጥ ሆኖ ጥብቅ ክትትል ሊደረግለት እንደሚገባ ተነግሯቸዋል።የህክምና ባለሙያዎች አቤል በዚህ አደገኛ የኢንፌክሽን ስጋት ውስጥ ሆኖ፣ እንዲሁም ከጽኑ ህክምና ክፍል (ICU) ሳይወጣ ወደ ሌላ ሆስፒታል መዛወር እንደሌለበት በተደጋጋሚ አስረድተዋል።
ሆኖም ግን፣ የህንፃው አስተዳደር እና ተቋራጩ የህክምና ወጪው እየጨመረ መምጣቱን ተከትሎ፣ "ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል እንውሰደው፣ ካልሆነ ግን ከዚህ በኋላ ያለውን ወጪ አንሸፍንም፤ ኃላፊነቱንም አንወስድም" የሚል ማስፈራሪያና ማደናገሪያ ደብዳቤ ጽፈዋል።
የሆስፒታሉ የህክምና ወጪ 2 ሚሊየን የሚጠጋ ገንዘብ ልናወጣ እና ቀሪ እዳ አለባችሁ ሲባሉ ፣ የተቋራጩ ዋና ስራ አስኪያጁ "በምክንያታዊ ምክንያት የሚል ድፍን ያለ መልስ የተሰጠንና በውቅቱ በቀን ሁለት ጊዜ ጭምር ብንመላለስም በአካል በፍጹም ሊያገኙን ፍቃደኛ ሳይሆኑ መቅረታቸውን አቶ መለሰ አብራርተዋል።
"የህክምና ክፍያው እንዳይቋረጥና ልጃችን ከጽኑ ህክምና ክፍል እስኪወጣ ድረስ እንዲታገሱን ተማፅነን ነበር... ነገር ግን ተቋራጩ ለሰው ህይወት ሳይሆን ለወጪያቸው (Cost) ቅድሚያ በመስጠት የልጃችንን ህይወት አደጋ ላይ በሚጥል ሁኔታ ክፍያውን አቆመ።" ይላሉ አባቱ በሀዘን።
በዚህም የተነሳ፣ ወላጅ አባት ከሆስፒታሉ የተጠየቁትን ወደ ሁለት ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ወጪ ለመክፈል የመኖሪያ ቤታቸውን ለመሸጥ ተገደዋል። በሙያቸው የሂሳብ ሰራተኛ (Accountant) የሆኑት አቶ መለሰ፣ ባላቸው የገቢ አቅም ይህንን ግዙፍ ወጪ መሸፈን እንደማይችሉ ይገልጻሉ።
"ልጄን ለማሳከም ላለፉት አምስት ወራት ከስራ ገበታዬ ርቄያለሁ። አሁን ላይ ሌሎች ልጆችም ያሉኝ ሲሆን፣ ምንም አይነት ገቢ የለኝም" በማለት ያጋጠማቸውን መሪር ፈተና አጋርተዋል።
ብዙ ሰዎች "ተቋራጩን ህግ ያስገድደዋል" የሚል ሀሳብ ያነሳሉ። በህግ ደረጃ አቤል እስኪድን ድረስ ሙሉ የህክምና ወጪውን የመሸፈን ግዴታ እንዳለባቸው እሙን ነው። ነገር ግን የሀገራችን የህግ ሂደት እጅግ ረጅም እና አድካሚ ነው።
አቶ መለሰ ሁኔታውን ሲያስረዱ፦ "አሁን ገና በሞግዚትነት ጉዳይ ላይ ነን (አደጋው ሲደርስ ገና 18 ዓመት ስላልሞላው እንዲሁም አሁን ላይ ሞልቶትም ባለመንቃቱ ምክንያት ስለ መብቶቹ መጠየቅ፣ማስረዳትና ስለ ራሱ መወሰን ስልማይችል ሞግዚትነትን በማስወስን ሂደት ላይ ነን)።ከዛ በኋላ የችሎት/የዳኝነት ክፍያ፣ ማስረጃ ማጣራት፣ የቀጠሮ ረጅም ሂደት የሚፈጥሩት መዘግየት አለ።
በወራት ምናልባትም ከዚያም በላይ በህግ ውሳኔ አግኝተን ለቤቢ ህክምና የሚሆን ገንዘብ ማግኘት አንችልም።" ብለዋል። ህጉ በራሱ መንገድ እየሄደ ቢሆንም፣ የልጃቸው ህይወት ግን የሰከንድ እና የደቂቃ ጉዳይ በመሆኑ፣ የአቶ መለሰ ዋነኛ ትኩረት የህግ ውሳኔን መጠበቅ ሳይሆን የልጃቸውን ህይወት ማትረፍ ነው።
ታዳጊ አቤል (ቤቢ) በጽኑ ህክምና ክፍል ህይወቱ እና ሞቱ አፋፍ ላይ ባለችበት በዚህ ወሳኝ ሰዓት፣ ረጅሙን የህግ ሂደት መጠበቅ ህይወቱን ከፍተኛ አደጋ ላይ ይጥለዋል።
ስለዚህ ሁላችንም በምንችለው አቅም ሁሉ ከዚህ አሳዛኝ ቤተሰብ ጎን በመቆም የታዳጊውን ህይወት እንታደግ። ድጋፍ ለማድረግ የባንክ አካውንት (ወላጅ እናት) እታለማሁ አሰፋ ወ/መድህን
CBE:- 1000348860538
ስልክ ፦ 0911398024
0931534451
*ማስታወሻ :- መረጃውን ለሌሎች በማጋራት ለታዳጊ አቤል ድጋፍ እንዲደረግለትና ፣ህክምናውን በአግባብቡ መከታተል እንዲችል የበኩላችንን እናድርግ ፤እናግዝ!❤️🙏
+2
አባትነት ፀዴ ነገር ነው። ትልቅ ሃላፊነት ነው። መስዋዕትነት ይጠይቃል። እራስን አሳልፎ መስጠት ይፈልጋል።
በሃብት'ና በዝና ብቻ የማይሟሉ የልጆች ፍላጎቶች አሉ። በተለይ የዕድገት ውስንነት ፣ እገዛ የሚያስፈልጋቸው ልጆች ሲሆኑ እንደ ወላጅ የምናደርጋቸው ጥቃቅን ነገሮች ሳይቀሩ እነሱ ላይ በጥሩም ሆነ በመጥፎ የሚያሳድሩት ተፅኖዎች ቀላል አይደሉም። ይሄን የሚረዱ ወላጆች ጥቂቶች ናቸው !
የዓለም ዋንጫን ያነሳው የስፔኑ ተጫዋች ኩኩሬያ ለዚህ ትልቅ ምሳሌ መሆን የሚችል አባት ነው። ኩኩሬያ ከምንም በላይ ከኦቲዝም ጋር ለሚኖረው ለ 4 ዓመት ልጁ ቅድሚያ ይሰጣል። ምንም ነገር ሲወስን ከእሱ ጋር በተያያዘ እንደሆነ ይገልፃል። ከልጁ ምቾት ውጪ ቅድሚያ የሚሰጠው ነገር የለውም !
ኩኩሬላ ሌላው ቀርቶ ብዙዎች 'አረ ተቆረጠው...' የሚሉትን ፀጉሩን እንኳን ያሳደገው ፣ ልጁ እሱ የሚጫወትባቸውን ግጥሚያዎች በቴሌቭዥን ሲያይ በቀላሉ እንዲለየው አስቦ እንደሆነ ይናገራል። አንዳንድ ነገሮች ከምክንያታቸው በኋላ በተለየ እንድታያቸው ያስገድዱሃል። የኩኩሬያ ረዥም ፀጉር እንዲሁ ፀጉር ብቻ አይደለም። ለኦቲዝም ልጁ አባቱን የሚለይበት ምልክቱ'ና የደስታ ምንጩ ነው።
አይፀዳም ወይ ?
ስፒች ቴራፒ ለምትፈልጉ
☎️0954999933
0940103047
📍መገናኛ ሲቲ ሞል 3ኛ ፎቅ
#ስፒች_ቴራፒ_በኢትዮዽያ #ጃዚኤል_ስፒች_ቴራፒ #speechtherapyinethiopia #speechtherapyinaddisababa #ማሕሌትስፒችቴራፒ @ማኅሌት Speech Therapist
ስፒች ቴራፒ ለምትፈልጉ
☎️0954999933
0940103047
📍መገናኛ ሲቲ ሞል 3ኛ ፎቅ
#ስፒች_ቴራፒ_በኢትዮዽያ #ጃዚኤል_ስፒች_ቴራፒ #speechtherapyinethiopia #speechtherapyinaddisababa #ማሕሌትስፒችቴራፒ @ማኅሌት Speech Therapist
ስፒች ቴራፒ ለምትፈልጉ
☎️0954999933
0940103047
📍መገናኛ ሲቲ ሞል 3ኛ ፎቅ
#ስፒች_ቴራፒ_በኢትዮዽያ #ጃዚኤል_ስፒች_ቴራፒ #speechtherapyinethiopia #speechtherapyinaddisababa #ማሕሌትስፒችቴራፒ @ማኅሌት Speech Therapist
ስፒች ቴራፒ ለምትፈልጉ
☎️0954999933
0940103047
📍መገናኛ ሲቲ ሞል 3ኛ ፎቅ
#ስፒች_ቴራፒ_በኢትዮዽያ #ጃዚኤል_ስፒች_ቴራፒ #speechtherapyinethiopia #speechtherapyinaddisababa #ማሕሌትስፒችቴራፒ @ማኅሌት Speech Therapist
10 ወላጆች ሊያውቋቸው የሚገቡ ስለ ስፒችና ላንጉጅ ቴራፒ በኦቲዝም ጥላ ስር ለሚገኙ ልጆች
1. ስፒች ቴራፒ የንግግር ህክምና ማለት መናገር ብቻ አይደለም ማለትም ልጅዎት መናገር ብቻ አይማርም፤ መግባባት፣ እጅ ምልክት (gesture)፣የዓይን መገናኘትና ሌሎችን መረዳት ይማራል።
2. ስፒች ቴራፒ ቀደም ብሎ ከትንሽ ዕድሜ ጀምሮ መጀመር በጣም አስፈላጊ ነው።
3. እያንዳንዱ ልጅ ልዩ ነው
አንዳንድ ልጆች ሊናገሩ ይችላሉ፣ አንዳንዶች ልጆች ቶሎ አይናገሩም። ቴራፒው ሁሉም ለልጆችዎት ተመጣጣኝ ይሆናል።
4. ጨዋታ ዋና መማሪያ መንገድ ነው
ልጆች በመጫወት ይማራሉ፤ ስለዚህ ቴራፒው እንደ ጨዋታ ይመስላል።
5. ወላጆች የቴራፒው ዋና አካል ናቸው።
ወላጆች በቤት ውስጥ እንዴት ልጃቸውን እንደሚረዱ ይማራሉ። ይህ የልጆችን ለውጥና እድገትን ያፋጥናል።
6. መግባባት ከመናገር ብቻ አይመጣም።
ልጅዎት የምልክት ቋንቋ (sign language)፣ ስዕሎች (PECS) እና መሣሪያዎች (AAC) ሊጠቀም ይችላል።
ይህ ንግግርን አያቋርጥም፤ ይበልጥ ይረዳል።
7. ማህበራዊ ተግባቦት በጣም አስፈላጊ ነው።
ልጅዎት ተራ መጠበቅ፣ የዓይን ግንኙነትነኣ ውይይት መጀመር ይማራል።
8.ለውጥ ትንሽ ቢሆንም በጣም ወሳኝና አስፈላጊ ነው።
ለምሳሌ:- የእጅ ምልክት መጠቀም ወይም አንድ ቃል መናገር ትልቅ እርምጃ ነው።
9. ቀጣይነትያለው ቴራፒ አስፈላጊ ነው።
በየቀኑ በቤት ውስጥ መልሶ መስራት እና መደበኛ ቴራፒ በጣም ይረዳል።
10. የቴራፒ ዓላማ እንደየ ልጆቹ ባህርይ፣ ተግባቦት፣ ማህበራዊ ግንኙነት ይለዋዋጣል።
ስፒች ቴራፒ ለምትፈልጉ
☎️0954999933
0940103047
📍መገናኛ ሲቲ ሞል 3ኛ ፎቅ
#ስፒች_ቴራፒ_በኢትዮዽያ #ጃዚኤል_ስፒች_ቴራፒ #speechtherapyinethiopia #speechtherapyinaddisababa #ማሕሌትስፒችቴራፒ @ማኅሌት Speech Therapist
