en
Feedback
Rohobot

Rohobot

Open in Telegram
602
Subscribers
No data24 hours
-57 days
-1230 days
Posts Archive
ክርስቲያን ሆናችሁ በራሳችሁ ህገ መንግስት ስርአት እና ደንብ የምትመሩ ሰዎች ..ዋ እረፉ 🙅🙅 ክርስትና በእግዚአብሔር ቃል መሰረት የምንኖረው ህይወት ብቻ ነው🙌

Repost from N/a
       #ወንጌል_የመስቀሉ_ቃል_ነው! 🤦መስቀሉ_የክርትና_ማዕከል_ነው!_መስቀሉ_የክርስትና_ትምክህት ነው!...እንጂ እፍረት አይደለም! ⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️
▪️ቃላት ምስልን ይከስታሉ። ስለዚህም አንዳንድ ቃላት ከሚከስቱት ምስል ጋር በተያያዘ ቀፋፊዎች ናቸውና ለዘብ ያሉ ሌሎች ቃላትን እየተጠቀምን እንሸፋፍናቸዋለን። ሰው ካልሰከረ፣ አእምሮውን ካልታመመና፣ ባለጌ ካልሆነ በቀር ከቀፋፊነታቸው፣ ከዘግናኝነታቸውና ከአስቀያሚነታቸው የተነሣ በይፋ የማይጠቀማቸው ቃላት ሁሌም አሉ። የምናከብራቸው ሰዎች ባሉበት የማይጠቀሱ፣ ወላጆች ከልጆቻቸው፣ ታላላቆች ከታናናሾች፣ ልጆችም ሳይቀሩ ከወላጆቻቸው የሚሰውሯቸው ቃላት በየዘመኑ ይኖራሉ። ▪️መስቀል የሚለው ቃልም የዛሬ ሁለት ሺህ ዓመት አካባቢ ከነበሩ የዚህ ዐይነት ቃላት መካከል ይገኝበታል። ከስቅለት ጋር ተያይዘው የሚመጡት ቃላት የሚከስቱት ምስል ዘግናኝ ነው። ስቅላት የሚፈጸምባቸው ወንጀለኞች ኀፍረተ ሥጋቸውን እንኳን የሚሸፍኑበት ዕራፊ አይደረግላቸውም። ነፍሳቸውም በቶሎ ስለማትወጣ ስቁላኑ ብዙ ይሠቃያሉ። ይጓጉራሉ። እያንዳንዱ የመተንፈስ ሙከራቸው በጣዕር የተሞላ ነው። አካላቸውን መቆጣጠር ስለማይችሉ በተሰቀሉበት ወደ ታች ይላቸዋል። ስለዚህም አካባቢው ይከረፋል። ዘግናኝነቱ በዚህ ብቻ አይወሰንም። በመስቀል ላይ በአይጥ፣ በጥንብ አንሣና በትል የተቦዳደሱ አስከሬኖችን ማየት በወቅቱ ብርቅ አልነበረም። ⬇️    ➡️ስለዚህ ሮማውያን የሌላ አገር ዜጎችን ካልሆነ በቀር ዜጎቻቸውን በስቅላት አይገድሉም፤ ይህ በሕግም የተወሰነ ነው። ድርጊቱን ብቻ ሳይሆን፣ ስቅለት የሚለውንም ቃል ከዜጎቻቸው ጆሮ ለማራቅ ሞክረዋል። የመስቀል ሞት የሞት ሞት መሞት ነው። መስቀል ይህንን ዘግናኝ ምስል ወደ አእምሮ ያመጣልና ቃሉ በተከበሩ ሰዎች ፊት ባይጠቀስ፣ ወላጆች በሕፃናት ፊት ባይጠቀሙት አይገርምም።     ✅ሐዋርያት ግን በየሄዱበት ስለ መስቀል ያወሩ ነበር። ጌታችን ተሰቅሎ መኖሩን በየስብታቸው ያውጁ ነበር።    ክርስትና መስቀልን ምልክቱ አድርጎ መጠቀሙ በራሱ ግራ አጋቢ ነው። እንዲህ ዐይነት ቃላት የስብከት እንቅፋቶች ናቸው። ይዘገንናሉ። ✅ለሐዋርያት ግን ወንጌል ማለት የመስቀሉ ቃል ነው፤ ስብከታቸውም የተሰቀለው ክርስቶስ ነው። የክርስትና ማዕከል መስቀል ነውና እያንዳንዳችን መስቀላችንን ተሸክመን ስቁሉን ጌታ ልንከተለው እኛንም ግብዣ ደርሶናል። ➡️የክርስትና ወንጌል ከውብ ምስል፣ ከአነቃቂ ቃላት፣ ከምቾት ዘሪ ንግግሮች ይልቅ ይህንን ቀፋፊ ምስል፣ ዘግናኝ ትዕይንት ይዞ ነው የጀመረው። ➡️እስካሁንም ድረስ የጤናማው ክርስትና ጉዞ ይኸው ነው! መስቀሉ የክርስትና ትምክህት ነው! ➡️ክርስትና በሰዎች ብልጠትና በንግግር ዘዴ ላይ ቢመሠረት ኖሮ፣ ክርስትና ልብወለድና ተረታ ተረት ቢሆን ኖሮ፣ የኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወትና ሞት ታሪካዊ እውነታ ባይሆን ኖሮ፣ የክርስትና ግብ ሰዎችን ደስ በሚያሰኙ ምርጥ ምርጥ ቃላት ማስደሰት ቢሆን ኖሮ፣ ኢየሱስን የመከተል አጀንዳ ምድራዊ ምቾትንና ብልጽግናን የማላበስ ቢሆን ኖሮ፣ ጌታን ማምለክ ቅጥ ያጣ ፈንጠዝያ ማካሄድ ቢሆን ኖሮ …ይሄ ይሆን ነበርን!!!? “ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት፣ እኔም ለዓለም የተሰቀልሁበት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር  ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ።” (ገላ. 6፥14)
⬆️ ✍በጳውሎስ ፈቃዱ ➡️በወንጌል አናፍርም‼️..በመስቀሉ ቃል አናፍርም‼️
ሮሜ 1 ¹⁶ በወንጌል አላፍርምናአስቀድሞ ለአይሁዳዊ ደግሞም ለግሪክ ሰው፥ ለሚያምኑ ሁሉ የእግዚአብሔር ኃይል ለማዳን ነውና። ⬇️ ¹⁷ ጻድቅ በእምነት ይኖራል ተብሎ እንደ ተጻፈ የእግዚአብሔር ጽድቅ ከእምነት ወደ እምነት በእርሱ ይገለጣልና።
🙌ከመስቀል-አልባ ክርስትና እግዚአብሔር ይጠብቀን!..እንደ አባቶቻችን ክርስትናችን መስቀሉን ማዕከል፣ መስቀሉን ትምክህት ያደረገ ይሁንልን!

Share it!🔥

Share it!🔥

Share it!🔥

Share it!🔥

የጠጣር ልብ አደገኛ ውጤቶች የምንኖርበት ጊዜ ልባችንን ልያጠጥር ስለሚችል ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ልባችንን በትኩረት መከታተል አለብን ፡፡ በአንድ ሌሊት አይከሰትም። አንድ ሰው ከእግዚአብሄር ጋር በንቁ ጉዞ ሊኖር ይችላል ከዚያም ቀስ በቀስ ወደ ደረቅነት ወደ ሚቀዘቅዘው ይሸጋገራል፡፡ ትክክል የሆነውን ያውቃሉ ፡፡ ግን ከእንግዲህ ግድ የላቸውም፡፡ ግዴለሽነት ልባቸውን ይገዛል። የሌላውን ችግር እንደራስ በቀላሉ ማግኘት አይቻልም። በአንድ ወቅት እምነት ጠንካራ እና ንቁ ነበር ፣ መቀዝቀዝ ፣ ጥርጣሬ እና ነቀፋ ወረረዉ፡፡ ልጅ-መሰል እምነት ይቀልጣል እናም እንቅፋትን ይታገሱታል። ጠንካራ ልብን ማዳበር የምንችልባቸው የተለያዩ መንገዶች አሉ ፣ ግን ሁለት ዋናዎች መጥቀስ ተገቢ ነው፦ 1. እዉነትን መስማት ግን ተግባራዊ አለማድረግ፡፡ ጠንካራ ልብ በቀላሉ ሊያድግ ከሚችልበት አንድ ትልቁ መንገድ ምን ማድረግ እንዳለብን ስናውቅ እርምጃ አንወስድም፡፡ የምንኖረው ከማንኛውም የበለጠ እውቀት እና ማስተዋል በሚገኝበት ትውልድ ውስጥ ነው። ሁል ጊዜ እውነትን ለመስማት እድል አለን፡፡ ችግሩ ፣ ብዙ እንሰማለን ፣ ግን በጣም ትንሽ ነገር ላይ እርምጃ እንወስዳለን፡፡ እኛ በታላላቅ አስተማሪዎች ተከብበናል፣ ግን ብዙዎች ስለእሱ ምንም አያደርጉም፣ ይህም ውሎ አድሮ ጠንካራ እና ቀዝቃዛ ወደ ሆነው እንዲያድጉ ያደርጋቸዋል፡፡ እውነት የተስማሙበት ስምምነት ላይ ብቻ ሳይሆን በተግባር እንዲሠራበት ነው፡፡ ብዙዎች የሆነ ነገር በመስማታቸው ምክንያት “እናዉቃለን” ብለው በማሰብ ተታለዋል ። ግን ያ እውነት በዕለት ተዕለት ኑሯቸው ውስጥ ንቁ እውነታ አይደለም ፡፡ እውነት በእዉነታዉ ላይ ተግባራዊ ካልተደረገ እና በውሳኔዎችዎ ውስጥ እንዲታይ እስካልተፈቀደ ድረስ እውነት ትርጉም የለውም። ሌሎች ትክክል የሆነውን ነገር በትክክል ያውቃሉ ፣ ግን እርምጃ ላለመውሰድ ይመርጣሉ። የክርስትና ሕይወት ግቡ የሰማችሁትን መውሰድ ነው ፣ ያዕቆብ 1፥22 እንደሚናገረው “ቃሉን የምታደርጉ እንጂ የምትሰሙ ብቻ አትሁኑ”፡፡ 2. የልብዎ ችግር በጊዜ መፍትሄ አለማግኘቱ፡፡ ጠንካራ ልብ የሚያዳብርበት ዋነኛው ምክንያት የተሰበሩ ልምዶች እና የተሰበሩ ጉዳዮች ሁልጊዜ የሚያስፈልገውን ፈውስ የማይቀበሉ ከሆነ ነው። አሁን ሰዎች በብዛት ከባድ እየሆኑ ነው ምክንያቱም እግዚአብሔር የሕይወታቸውን ጥልቅ ሥቃይ እንዲፈውስ ስላልፈቀዱ፡፡ ቅሬታ ለሌሎች አለማሰብን ሊያዳብሩ ከሚችሉ ዋና ነገሮች ነገሮች አንዱ ነው፡፡ ጠንካራ ልብን ካሸናፊዎቹ የሚለየው ቅሬታን እንዴት መወጣት እንዳለብን ነው ፡፡ በስህተት የተያዘ እና ጥልቅ ቅሬታ የልብ ገዳይ ሊሆን ይችላል፡፡ ጥልቅ የህመማችን ቅሬታ ለማከም ካልሞከርን ወደ ቂም መያዝ፣ መለያየት እና ወደ የከፋ መቀዝቀዝ ያመራናል፡፡ የልብ ጡንቻዎቻችን ያላቅቅብናል፡፡ ብዙዎች በሥቃይ ውስጥ እግዚአብሔርን መጋበዝ ይመርጣሉ ፡፡ ምንም እንኳን እጅግ በጣም ከባድ ቢሆንም ፣ ከዚህ በፊት የማያውቋቸውን የእግዚአብሔር ገጽታዎችን ያያሉ ፡፡ በመከራ ፣ በማጣት በብስጭት ጊዜያት ታላቅ ጥንካሬ እና ብስለት ያገኛሉ። እግዚአብሔር ጠንካራ ቦታዎችን በማለስለስ ልባችንን መፈወስ ይፈልጋል ፡፡ ይቀጥላል... ምንጭ:- www.hiyawkal.org ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

የአብርሃም ስተት እስካሁን ደርስ እየሰራ ነው!!

ቅባት

Repost from Rohobot
ወደ ራስ መመልከት (የማቴዎስ ወንጌል 7 ) ------------ 1-2፤ እንዳይፈረድባችሁ አትፍረዱ፤ በምትፈርዱበት ፍርድ ይፈረድባችኋልና፥ በምትሰፍሩበትም መስፈሪያ ይሰፈርባችኋል። 3፤ በወንድምህም ዓይን ያለውን ጉድፍ ስለምን ታያለህ፥ በዓይንህ ግን ያለውን ምሰሶ ስለ ምን አትመለከትም? 4፤ ወይም ወንድምህን፦ ከዓይንህ ጉድፍ ላውጣ ፍቀድልኝ እንዴትስ ትለዋለህ? እነሆም፥ በዓይንህ ምሰሶ አለ። 5፤ አንተ ግብዝ፥ አስቀድመህ ከዓይንህ ምሰሶውን አውጣ፥ ከዚያም በኋላ ከወንድምህ ዓይን ጉድፉን ታወጣ ዘንድ አጥርተህ ታያለህ። @robhot @robhot

🏃‍♂ብንሮጥ ነው ሚበጀው 🫵 አንተ ምታነበው አዎ አንተ አንተ ራስህ አትሮጥም እሩጥ እንጂ ወዳጄ 🦾 ወዳጄ ትግል ለውድድር እና ለጦር ሜዳ እንጂ ለዝሙት ሰፈር አይበጅም ❌ አደገኛን የሰፈር ውሻን ይሮጡታል እንጂ አይታገሉትም ❌ የኤሌትሪክ አደጋን የሸሹታል እንጂ አይዳፈሩትም ❌ ዝሙትን ወዳጄ አትታገለው እሩጠው ጀግንነት ለጦር ሜዳ ነው ሚቀጀው እንጂ አሳቻ ስፍራ እየጠበቁ ከዙሙት ጋር መታገል በአይምሬው ሰይጣን እጅ መውደቅ ነው ❌ ባይገርምህ ሸሽተህ እንጂ ገስፀህም ተዋግተህም የማታልፈው የሰይጣን ወጥመድ ዝሙት ነው ⭕️ መንፈሲዊ ሕይወትህን ከእግዚአብሔር ጋር ያለ ሕብረትህን አድርቆ መንፈሳዊ ሕይወት እንጨት እንጨት እንዲልህ ከሚያደርገው ነገር አንዱ እና ከባዱ ዝሙት ነው 👌ኦኦኦኦ እግዚአብሔር እንደ ዮሴፍ በመሮጥ ይባርከን 🤦‍♂ ለዮሴፍ ውርደት ሕልም ይዞ መተኛት እንጂ ራቆቱን መሮጥ አይደለም “ከዝሙት ሽሹ። ሰው የሚያደርገው ኃጢአት ሁሉ ከሥጋ ውጭ ነው፤ ዝሙትን የሚሠራ ግን በገዛ ሥጋው ላይ ኃጢአትን ይሠራል።” — 1ኛ ቆሮንቶስ 6፥18 t.me/GlorytoGlory1234 t.me/GlorytoGlory1234 t.me/GlorytoGlory1234   👍 Share & Join 🔥ከመንፈስ ቅዱስ ጋር መሆን ደስስስ ይላል🔥

Voice message01:04

Voice message00:44

Voice message00:22

Voice message00:22

Voice message01:10

Voice message00:57

እሄን መዝሙር የ ኢየሱስ ራሃብ ያለበት ሳዉ ብቻ ይሰማዉ 🥹🥹🥹 ናፍቀኸኛል_ኢየሱስ😭😭😭😭😭

.                    ይወደኛል   ብሩክ አበባየሁ - Live Worship     ▷ ▸ Albastros.com ◂ ◁   ▷ @yedestaye_elilta ◁              △Join Us

ወደ ሰው ቤት ደጋግመን ስንሄድ እንረክሳለን ወደ እግዚአብሔር ቤት ደጋግመን ስንሄድ እንፀድቃለን! ሰው ጋር ደጋግመን ስንደውል እንሰለቻለን እግዚአብሔር ጋ ግን ደጋግመን ስንፀልይ እንባረካለን! አያችሁ... እግዚአብሔር ይወደናል !! ምክንያቱም ልጆቹ ነንና አይሰላቸንም 🥰🥰😍