602
Subscribers
No data24 hours
-57 days
-1230 days
Posts Archive
602
ምንም በሌለበት ማይነጥፍ ደስታ
ብር ያልደጋገፈው የዚህ አለም ስጦታ
ፊትን የሚያበራ ከላይ የሆነው
ዘላቂው ደስታዬ ጌታ ባንተ እኮ ነው🔥
የልቤ ደስታ ጌታ🥰
የልቤ ደስታ የሱስ
በገናዬን ልያዝ ልቀኝልህ
#ነፍሴ_ውላ_ታድራለች_በስምህ🙆 🥰🥰🥰
602
3.3.2. እግዚአብሔር ወልድ
ኢየሱስ ክርስቶስ ከዘላለም የነበረ፤ የእግዚአብሔር አብ ዘላለማዊ የባሕርይው ልጁ መሆኑን፣ ፍጹም አምላክና ፈጣሪ የሆነ፣ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ተጸንሶ ከድንግል ማርያም የተወለደ፣ ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው የሆነ፤ ኃጢአት የሌለበትና ስለ ኃጢአተኞች በመስቀል ላይ የተሰቀለ፣ የሞተ፣ የተቀበረ፤ በሦስተኛውም ቀን ከሙታን የተነሳ፣ በክብር ያረገ፣ በደሙም የኃጢአትን ሥርየት ያስገኘ፣ የዲያብሎስን ሥራ ያፈረሰና ሥልጣኑን የሻረ፣ በእግዚአብሔር አብ ቀኝ ተቀምጦ ስለ እኛ የሚማልድ ሊቀ ካህን መሆኑን፣ የቤተ ክርስቲያን ራስና መሥራች የሆነ፣በሕያዋንና በሙታን ሊፈርድ ዳግመኛ በክብር ተመልሶ የሚመጣ መሆኑን ታምናለች፡፡ (ዘፍ. 3፥15፤ ኢሳ 53፥1-12፤ ማቴ.16:18፣ ሉቃ 1:26-35
ዮሐ. 1፥1-18፣ ሐሥ. 17:31፣ ሮሜ 3:25፣ 2ቆር. 5:18፣ 21፤ኤፌ 1፥22-23፤ 2:13-16 1፥7፤ ፊል 2:6-7፣ 1៣ሞ 2:5፣3:16፣ ዕብ. 1:8፣ 2፥14-16፤ 4:15፣ 1ጴጥ.2:4 ፣ ቆላ 12:15)
602
ዋናው ነገር ስዎች ስላንተ ምን ያስባሉ ሳይሆን አንተ ስለ ራስህ ምን ተስባለህ የሚለው ነገር ነው ዋናው ፣ እችላለሁ ከልክ ትችላለህ ፣አልችልም ከልክ አትችልም ።
ማርቆስ 9 (Mark)
23፤ ኢየሱስም፡— ቢቻልህ ትላለህ፤ ለሚያምን ሁሉ ይቻላል፡ አለው።
602
ዮሐንስ 10 (John)
27፤ በጎቼ ድምፄን ይሰማሉ እኔም አውቃቸዋለሁ ይከተሉኝማል፤
28፤ እኔም የዘላለም ሕይወትን እሰጣቸዋለሁ፥ ለዘላለምም አይጠፉም፥ ከእጄም ማንም አይነጥቃቸውም።
29፤ የሰጠኝ አባቴ ከሁሉ ይበልጣል፥ ከአባቴም እጅ ሊነጥቃቸው ማንም አይችልም።
602
Repost from Yeshurun Library
👉ርዕስ፦ የሮሜ መልእክት የጥናት መምሪያ እና ማብራሪያ፣
በትምህርተ መለኮት ማስፋፊያ (ት.መ.ማ) መልክ የተዘጋጀ
✍ጸሐፊ፦ ስቲቭ ስትራውስ
🗣ትርጉም፦ ጌቱ ግዛው
✏️እርማት፦ ኃይሌ ጀናይና ግርማይ
🖨አሳታሚ፦ ኤስ. አይ. ኤም
602
በመንፈስ ቅዱስ የሆነ የእግዚአብሔር አለም አለ ።
ሮሜ 14 (Romans)
17፤ የእግዚአብሔር መንግሥት ጽድቅና ሰላም በመንፈስ ቅዱስም የሆነ ደስታ ናት እንጂ መብልና መጠጥ አይደለችምና።
602
ህይወት ማለት የእግዚአብሔር የልብን ሀሳብ መኖር ለእርሱ ፍቃድ ብቻ መኖር የልብን ሀሳብ መፈፀም ማድረግ ነው ህይወት ሙሉ የሚሆነው የእግዚአብሔር የልብን ሀሳብ በማድረግ ውስጥ ነው።
