en
Feedback
Rohobot

Rohobot

Open in Telegram
602
Subscribers
No data24 hours
-57 days
-1230 days
Posts Archive
Hafuuraa qulqulluu by milkii christian media.pdf4.19 KB

ለማርያም፣ ለሚካኤል እንድሁም ለተለየዩ ምስሎች መስገድ አይፈቀድም!! ለምስሎች መስገድ ጣኦትን ማምለክ ነው። አንድ አማኝ በክርስቶስ ያለውን እምነቱን ከጀመረበት ቀን አንሥቶ ራሱን ከጣዖታትና ከጣዖት አምልኮ ጋር ከሚዛመድ ነገር ሁሉ መለየት አለበት:: ከዚያ በኋላ የጣዖታትን ስም መጥ ራት፥ የፊት ገጽና መጽሐፍ ገላጭ ጠንቋዮችንም ማማከር የለበትም፡፡ በተጨማሪ ራስን ከአሕዛብ ቤተ ጣዖታት ማራቅና የተቀረፁ ምስሎች የማምለክ ሐሳብን ከማስተናገድም መቆጠብ አለበት፡፡ ይህ በጣም ሊተኮርበት የሚገባ ጉዳይ ነው:: አማኞች ዛሬ ከጣዖታት ሙሉ በሙሉ ካልተለዩ ወደፊት ከሚመጣው ከትልቁ ጣዖት ማለትም:- ከክርስቶስ ተቃዋሚ ምስል እንዴት ሊያመልጡ ይችላሉ? መመለክ የሌለባቸው የተቀረጹ ወይም የተገነቡ ነገሮች ብቻ ሳይሆኑ፣ ሕያው የሆነ ወይም ሕይወት ያለው ሁሉ እንደዚሁ መመለክ የለበትም:: "የክርስቶስ" ወይም "የማርያም ነው" የሚባለው ምሥል እንኳ ሊመለክ አይችልም። ማንኛውንም ምስል ያለማምለክ ልማድ በሰው ውስጥ ሊሠርጽ (ሊያድግ) ይገባል፡፡ እግዚአብሔር ምስልን በመቅረጽና ሥዕሎችን በመሳል ሳይሆን በመንፈስና በእውነት የሚያመልኩትን ይፈልጋል:: ስለዚህ እግዚአብሔር በመንፈስና በእውነት እንጂ ምስሎችን (ሥዕሎችን) ማምለክ የለብንም። እግዚአብሔር መንፈስ ነው፤ የተቀረፀ ምስል አይደለም፡፡ ይህን ማወቅ ብዙ አማኞችን በክርስቶስ ተቃዋሚ መምጣት አስተዋጽኦ ከምታደርገው የሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ላይ ከመውደቅ ያድናቸዋል፡፡ ከጣዖታት የእግዚአብሔርን ልጅ ዳግም ምጽአት ወደመጠበቅ መዞር አለበን። ምንም ዐይነት የጌታ ኢየሱስ ምስል ማስቀመጥ የለብንምየትኛውም እውነተኛ አምሳያው ስላልሆነ፣ ዋጋ የለውም:: በቫቲካን ሙዚየም ውስጥ የጌታ ኢየሱስ ናቸው የተባሉ ከሁለት ሺህ በላይ የተለያዩ ምስሎች ይገኛሉ:: እነዚህ ሁሉ የሰዓሊያን የምናብ ውጤቶች እንጂ የትኞቹም የጌታ ኢየሱስ ትክክለኛ ምስል አይደሉም። ብዙ ሰዓሊያን ጌታ ኢየሱስን እንዲሁ ነው ብለው ይስላሉ፣ ይሄ የእግዚአብሔርን ክብር መንካት ነው:: እርሱ ቀናተኛ አምላክ በመሆኑ፣ እንዲህ ያለውን ነገር አይታገሠውም:: ምስሎች የባዕድ አምልኮ ምንጭ ስለሆኑ መወገድ አለባቸው:: ይህም ብቻ አይደለም፤ የጣዖት አምልኮ ንክኪም ቢሆን መጠረግ አለበት፡፡ 🙏የጌታ ፀጋና ሠላም ይብዛላችሁ!🙏       ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ ነው።         🤝ይቀላቀሉ🤝 @TheMinistryOfDoingGodsWill       🤝ይቀላቀሉ🤝

+7
1_ረቡኒ_Rebuni_አስተምረኝ_EP_ቢኒያም_ደሳለኝ_Biniyam_Desalegn.m4a3.44 MB

ሕዝቅኤል 43 (Ezekiel) 1፤ ወደ ምሥራቅም ወደሚመለከተው በር አመጣኝ፡— 2፤ እነሆም፥ የእስራኤል አምላክ ክብር ከምሥራቅ መንገድ መጣ፤ ድምፁም እንደ ብዙ ውኆች ይተምም ነበር፥ ከክብሩም የተነሣ ምድር ታበራ ነበር። 3፤ ያየሁትም ራእይ ከተማይቱን ለማጥፋት በመጣሁ ጊዜ እንዳየሁት ራእይ ነበረ፤ ራእዩም በኮበር ወንዝ እንዳየሁት ራእይ ነበረ፤ እኔም በግምባሬ ተደፋሁ። 4፤ የእግዚአብሔርም ክብር ወደ ምሥራቅ በሚመለከት በር ወደ መቅደሱ ገባ። 5፤ መንፈሱም አነሣኝ ወደ ውስጠኛውም አደባባይ አገባኝ፤ እነሆም፥ የእግዚአብሔር ክብር መቅደሱን ሞልቶት ነበር።

✍️ በጸጋ ላይ አትዋሹ!! ** ✍ ጸድቃችኋልና እንደፈለጋችሁ በኃጢአት ተጨመላለቁ የሚል የጸጋ ወንጌል አስተማሪ ጆሮዬ ሰምቶ አያውቅም ካለም ደግሞ ፈጽሞ የክርስቶስን ሥራ የሚያንቋሽሽ ከአባት ሳይሆን ከአጋንንት የሆነ ትምህርት ነው!! 📌 ከኃጢአት ለመሸሽ ወደ ጸጋ ይሮጣል እንጂ ጸጋ ተይዞ ወደ ኃጢአት አይሮጥም!! ✍️ ብዙ የተማረ ብዙ ይወዳል እንጂ ብዙ ኃጢአት አይሰራም!! ✍ ኃጢአትን በጸጋ ከካዱ በሗላ ጸጋ ለኃጢአት ፈቃድ ይሰጣል ማለት ጸጋ ላይ መዋሸት ነው!! 📌 ስለምን ጸጋ ላይ ዋሸህ? ✍ መንፈስ ቅዱስ 👉 አንዴ ድኛለሁና እንደፈለግኩ የኃጢአት ጭቃ አቦካለሁ እንዳትል የሚረዳህ የጸጋው መንፈስ ነው!! 📌 ጸጋ ለኃጢአት ፈቃድ ያሳጣል!! ✍️ ባልሽ በጣም ስለሚያፈቅርሽ ምንም ብታደርጊ አይተውሽም ማለት ባልሽ ላይ እንደፈለግሽ ማመንዘር ትችያለሽ የሚል አቻ ፍች የለውም!!  👉 አላዋቂ መተርጉማን ካልተረጎሙልሽ በቀር!! ✍️ በአብ ፊት ክርስቶስ ድፍረት የሆነለት ሰው የድፍረት ኃጢአት አይገዛውም!! 📌 ጸጋው የሰጠን በአብ ፊት የመቅረብ ድፍረት እንጂ ኃጢአት የመሥራት ድፍረት አይደለም!! ✍️ እውነተኛ አማኝ እግዚአብሔር ኃጢአትን እንደሚጠላ እርሱም ኃጢአትን ይጠላል!! 📌 ኃጢአት አንተን በመግደል አፍቃሪህን መስቀል ላይ ያንጠለጠለ ጠላትህ ነው!! ✍️ እንዲሁ በጸጋ እያላችሁ በኃጢአት ጭቃ የምትጨማለቁም ካላችሁ ከእንግዲህ አትጨማለቁ.....ይልቁን በጸጋው አርነት ውጡ!! #ፀጋ_ተወርቶ_ኃጢአት #ሕግ_ተወርቶ_ጽድቅ_የለም!! #ሕግ_ተወርቶ_ኃጢአት #ፀጋ_ተወርቶ_ጽድቅ_ግን_አይቀሬ_ነው!! 📌 #መስቀል_ላይ_የዋለው_ፍቅር ከኃጢአት ያልመለሰው ሰው #ሲና_ላይ_የተገለጠው_ድንጋይ አያቆመውም!! 📌 ድንጋይ ከያዙ አገልጋዮች ተጠበቁ!! ✍️ በጸጋ ላይ አትዋሹ!! #ሄኖክ_አሸብር

#ስለ እምነት ማወቅ ያለብን እውነታዎች #እምነት ህግ ነው ። እምነት የእግዚአብሔር መንግሥት የሚሰራበት ህግ ነው ለሁሉ የሚሰራ ደግሞም ሁልጊዜ የሚሰራ ነው ። ህግ ሁሉንም በእኩል የሚያስተናግድ ለማ
#ስለ እምነት ማወቅ ያለብን እውነታዎች #እምነት ህግ ነው ። እምነት የእግዚአብሔር መንግሥት የሚሰራበት ህግ ነው ለሁሉ የሚሰራ ደግሞም ሁልጊዜ የሚሰራ ነው ። ህግ ሁሉንም በእኩል የሚያስተናግድ ለማንም የተለየ የአሰራር መንገድ የሌለው ነገር ነው ። #እምነት ምኞት አይደለም ባባዶ ነገር ላይ ያለ ፉከራ አይደለም ። ታዲያ ምንድነው ? እምነት የእግዚአብሔር ቋንቋ ነው ። የመንፈሳዊ አለም መገበያያ የእግዚአብሔር ህግ ነው ። #ሌላው ስለእምነት መወቅ ያለብን ኢየሱስ በምድር በነበረው ቆይታ የኖረው በእምነት ነው ሐዋሪያት አባቶቻችን የኖሩት በእምነት ነው ። #“ጻድቅ ግን በእምነት ይኖራል ወደ ኋላም ቢያፈገፍግ፥ ነፍሴ በእርሱ ደስ አይላትም።”   — ዕብራውያን 10፥38 እምነት የፅድቅ ፍሬ ነው ። እምነት በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን የሚገኝ የፅድቅ ፍሬ ነው ። እምነት በፆም ፀሎት ወይም በብዙ ጥረት የሚመጣ አይደለም ። ሰው በክርስቶስ ሲያምን የእግዚአብሔር ባህሪ ማንነት ተካፋይ ይሆናል ። #እምነት ምርጫ ነው ። በማንም ሰው ላይ የሚሆነው ግለሰቡ ያመነው ነገር ነው ። እግዚአብሔር ህይወትን አለመጥፋትን ፋቅዶ ሰው ግን ሰው ግን ከእግዚአብሔር አሳብ ይልቅ ሞትንና ጥፋትን ቢያምን የሚሆንበት የእግዚአብሔር አሳብ ሳይሆን ግለሰቡ በልቡ ያመነው ነገር ነው ። ስለዚህ ፃድቅ ሲመላለስ እምነት ያስፈልገዋል ያለ እምነት ፃድቅ አይኖርም ። #ከመለኮታዊ እምነት መፅሐፍ የተወሰደ ይህን መፅሐፍ የምትፈልጉ በውስጥ አናግሩን ፃፉልን #መልእህክቱን ሼር በማድረግ ለሌሎች አካፍሉ https://t.me/focusinternationalministry

በእውነተኛው ወንጌል መዳን በእውነተኛው ወንጌል መኖር እውነተኛውን ወንጌል መስበክ!!

ክርስትና ቢሉ-ማዕረግ ታዬ 👇👇👇 ክርስትና ቢሉ ክርስቶስ ነው ክርስቲያን ነኝ ካሉ መኖር ነው የት ነው ያለው ክርስትና አድራሻው ወዴትነው የልጁን መልክ እንድንመስል ነው የተጠራነው ታዲያ ሚታየው ምንድነው ታዲያ ሚሆነው ምንድነው የመዝሙር ግብዣችን ነው ተባረኩበት❤️❤️❤️ sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ ማርከን ዜማ @Markenzema_bot በዚህ ቻናል የማይደመጥ መዝሙር የለም ብቻ ምን አለፋችሁ join ይበሉ  👇 https://t.me/+S2wsmZMSQp3vcGxp https://t.me/+S2wsmZMSQp3vcGxp

.   ሉዓላዊ || በረከት ደጀኔ New Worship ♡ ㅤ  ⎙ㅤ  ⌲        ✉️    ˡᶦᵏᵉ    ˢᵃᵛᵉ    ˢʰᵃʳᵉ   ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ

Never forget this formula--- In the beginning God

photo content

Here is the e-book of እንደገና በህይወት መኖር /ሪቫይቫል ለኢትዮጵያ/ Read and share it to brothers and sisters “እግዚአብሔርም ለእስራኤል ቤት እንዲህ ይላልና፦ እኔን ፈልጉ፥ በሕይወትም ትኖራላችሁ፤”   — አሞጽ 5፥4 All the praise be to our great God

#የቤተክርስቲያን_ገጽታዎች   የቤተክርስቲያን ገጽታዎች • ቤተክርስቲያን ስንል በምድር ላይ የክርስቶስ ወኪል የሆነች አካልን የሚያመለክት ሲሆን ተፈጥሯዊ ገጽታዋም በሁለት መልከ ይብራራል። 1. ሁሉን አቀፍ ቤተክርስቲያን • ሁሉን አቀፍ ቤተክርስቲያን(ዓለም አቀፍ ቤተክርስቲያን) በክርስቶስ ኢየሱስ ምድራዊ አገልግሎት ዘመን ጀምሮ የተጠሩትንና መንፈስ ቅዱስ ከወረደበት ከጴንጤ ቆስጤ ቀን ጀምሮ በክርስቶስ አምነው የእግዚአብሔር ቤተሰብ የሆኑትን ማለትም በክርስቶስ ሆነው ያንቀላፉትንና በሕይወት ያሉትን ሁሉ ያቀፈች ስትሆን እጅግ ብዙ ቁጥር ያላትና በቦታ ያልተወሰነች ናት። 2. አጥቢያ ቤተክርስቲያን • ሁሉን አቀፍ ቤተክርስቲያን አንድ ስትሆን አጥቢያ ቤተክርስቲያን ግን በስፍራና በአካባቢ የተወሰኑ ብዙ አብያተክርስቲያናትን ያመለክታል (ሮሜ 16:5፣ 1ኛ ቆሮ 1:2፣ ቆላ 4፡15)። አማኞች የአንዲት አጥቢያ ቤተክርስቲያን አባል ለመሆን የሚጠበቅባቸው በክርስቶስ ማመን ብቻ ነው። ይሁን እንጂ አጥቢያ ቤተክርስቲያን በክርስቶስ አምነው ከዳኑ ሰዎች በተጨማሪ ልባቸውን ለጌታ ያልሰጠ ወይም ያልዳነ ሰዎችን ልታቅፍ ትችላለች ማቴ 12፡20)። እነዚህ ሰዎች እንዲሁ ሲታዩ የቤተክርስቲያኒቱ አባል ቢመስሉም የእግዚአብሔር ቤተሰብ ሊሆኑ አይችሉም (ሐዋ 8፡1)። አጥቢያ ቤተክርስቲያን ተልዕኮዋን ለመፈጸም ማለትም ለአምልኮ፣ ለወንጌል ስርጭት፣ ደቀመዛሙርትን ለማፍራት እንዲሁም ለአንድነት መዋቅራዊ አስተዳደር የሚያስፈልጋት ሲሆን በተለያየ መልኩ ልትታይ ትችላለች።

🌿ወጣትነት ማለት...✍ ወጣትነት ፋሽን ተከታይ ዘናጭ ተሽቀርቃሪ መሆን ማለት አይደለም! ወጣትነት ራስን በሱሶች ማጠር ማለት አይደለም! ወጣትነት በምክንያታዊነት ሳይሆን በስሜታዊነት እየተነዱ ራስንና ሌላውን አደጋ ውስጥ መዝፈቅ ማለት አይደለም! ወጣትነት ብዙ ጃንቦ የጠጣ ጀግና ማን ነው መባባል ማለት አይደለም! ወጣትነት ብረት ገፍቶ ደረትን ማሳበጥ ማለት አይደለም! ወጣትነት ሺሻ ቤት ተቀምጦ ጭስ ማቡነን ማለት አይደለም! ✍ወጣትነት በወሲብ ሱስ ከዚህም ከዚያችም ጋር በዝሙት ተወጥሮ መልከስከስ ማለት አይደለም! ወጣትነት በጥላቻ እና በዘረኝነት ተሞልቶ መታወር፣ መደባደብ እና መነታረክ ማለት አይደለም! ወጣትነት ተመልሶ የማይመጣውን ተፈጥሮ የሰጠችንን ታላቅ ሃይል በማይረባው ነገር ጊዜን ማቃጠል ማለት አይደለም! ወጣትነት ግዜያዊ ስሜትን ብቻ እያዳመጡ እንደፈረስ ጋሪ መነዳት ብቻ አይደለም! ወጣትነት በሀሜት፣ በአሉባልታ፣ በወሬ ሱስ፣ በአቃቂር፣ በተንኳሽነት፣ በቧልት መሞላት ማለት አይደለም! ✍ወጣትነት ይሄንንም ያንንም ይቺንም ያቺንም መጀንጀን መጀናጀን ማጀናጀን ማለት አይደለም! ወጣትነት በባዶ ጭንቅላት ምርጥ አልባሳትን ለብሶ እየተጀነኑ በባዶ ኩራት ተወጥሮ መሬትን ለመርገጥ እየተጸየፉ መራመድ ማለት አይደለም! ወጣትነት በግዴለሽነት፣ በተስፋ መቁረጥ፣ ከነፈሰው ጋር መንፈስ ማለት አይደለም! ወጣትነት በራስ ወዳድነት መንፈስ መወጠር እና እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል ማለት አይደለም! ወጣትነት በማይረባው በቀበሌኛው አመለካከት መታጠር ማለት አይደለም! ወጣትነት ቁንጫ የምታክል እውቀት በመያዝ ይቺ እውቀት ብቻ ትበቃኛለች እያሉ አጉል መመጻደቅ ማለት አይደለም... ✍ወጣትነት ባህር ነው። ወጣትነት ውቂያኖስ ነው። ወጣትነት አድማሰ ሰፊነት ነው። ወጣትነት እውቀትን ለማስፋት የምንጋደልበት ሰአት ነው። ወጣትነት በማስተዋል ብርሃን መሞላት ነው። ወጣትነት ችግር ፈጣሪነት ሳይሆን ችግር ፈቺነት ነው። ወጣትነት በዘረኝነት ተሞልቶ አማራ፣ ትግሬ፣ ኦሮሞ፣ ወላይታ...ቅብርጥሶ እየተባባሉ ቡድን በመስራት ስለ ቀበሌኛ አስተሳሰብ መስበክ ሳይሆን ወጣትነት ስለ ኢትዮጵያዊነት ከተቻለም አለም አቀፋዊ እይታን ማስፋት ነው። ✍ወጣትነት ፍቅርን እና አንድነትን መስበክ ነው። ወጣትነት በዝሙት ባህር መንቦራጨቅ ሳይሆን ስሜትን የመግዛት ጥበብ ማዳበር መቻል ነው። ወጣትነት ብርሃን ነው። ወጣትነት ተስፋ አለመቁረጥ ነው። ወጣትነት በቀናነት መሞላት ነው! ወጣትነት እስከመጨረሻው ጠብታ ህልምን ለማሳካት መፍጨርጨር ነው። ወጣትነት ማንበብ ነው ። ወጣትነት መጠየቅ ነው ። ወጣትነት ስለዓለም፣ ስለ ህይወት፣ ስለ ጥበብ፣ ስለ እውቀት ብዙ ለማወቅ መጠማት ነው ። ወጣትነት ለሌሎች መኖር ነው። ወጣትነት ለአገሬ ምን ልስራላት ብሎ ራስን መጠየቅ ነው። ወጣትነት ስለነገ ትልቅ ህልም እና እቅድ መሰነቅ ነው። ወጣትነት እሳት ነው። ወጣትነት ቤንዚል ነው። ወጣትነት ቅጠል ነው። ወጣትነት ጤዛ ነው። ወጣትነት ታክሲ ነው። ወጣትነት ምርጫ ነው። ወጣትነት በባህር ላይ ያለች ጀልባ መሆን ነው። ወጣትነት የመቶ ሜትር ሩጫ ያህል ነው። ወጣትነት ውስጥን ፈተናን ለማለፍ ማጀገን ነው። ወጣትነት ከፍርሃት፣ አልችልም እና አይሳካልኝም የሚለውን እስር በጣጥሶ ማለፍ ነው። ወጣትነት ለአንዳች ስኬት በኩራት እና በሞራል መራመድ ነው ...።

የኢየሱስ ሞት እጅግ ዝነኛ ሞት ነው። በዓለም ላይ እንደዚህ የተነገረለት ሞት የለም። በዚህ ደረጃ የታወቀ፣ የበርካታ የሥነ ጥበብ መስኮች (ሥዕል፣ ሙዚቃ፣ ቲአትር፣ ፊልም፣ ቅርጻ ቅርጽ፣ ወዘተ.) ጭ
የኢየሱስ ሞት እጅግ ዝነኛ ሞት ነው። በዓለም ላይ እንደዚህ የተነገረለት ሞት የለም። በዚህ ደረጃ የታወቀ፣ የበርካታ የሥነ ጥበብ መስኮች (ሥዕል፣ ሙዚቃ፣ ቲአትር፣ ፊልም፣ ቅርጻ ቅርጽ፣ ወዘተ.) ጭብጥ እና እጅግ መወያያ የሆነ ሞት የለም። ስፍር ቍጥር የሌላቸው መጻሕፍትም ተጽፈውበታል። ይህን መስቀል ልዩ የሚያደርገው በዚያ ላይ የተሰቀለው ሰው ማንነት ነው። አምላክ በሥጋ የተሰቀለበት መሆኑ። እርሱን የሚመስል ሰው ኖሮ አያውቅም። በምድር ላይ እንደ እርሱ ንጹሕ፣ እንደ እርሱ ቅዱስ፣ እንደ እርሱ ደግ፣ እንደ እርሱ ትሑት፣ እንደ እርሱ ጻድቅ፣ እንደ እርሱ ቸር ሰው ኖሮ አያውቅም። ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ እንደ እርሱ ዐይነት መልካም ኖሮ አያውቅም። ሊሰቀል ያልተገባው ቅዱስ ሰው ነው የተሰቀለው። "የተሰቀለው" ገጽ 12። የፊታችን ታህሳስ 12 ይመረቃል።

👉ለተጠማ የህይወት ውሃ...ኢየሱስ ❤
“በእኔ የሚያምን መጽሐፍ እንዳለ፥ የሕይወት ውኃ ወንዝ ከሆዱ ይፈልቃል ብሎ ጮኸ።”   — ዮሐንስ 7፥38
👉ለተራበ የህይወት እንጀራ...ኢየሱስ
“የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ።”   — ዮሐንስ 6፥48
👉መንገድ_ለጠፋው :መንገድ...ኢየሱስ
“ኢየሱስም፦ እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።”   — ዮሐንስ 14፥6
👉ለጨለመበት ብርሃን... ኢየሱስ
“ደግሞም ኢየሱስ፦ እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ፤ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም ብሎ ተናገራቸው።”   — ዮሐንስ 8፥12
👉ለተቅበዘበዘው መልካም እረኛ... ኢየሱስ
“መልካም እረኛ እኔ ነኝ። መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል።”   — ዮሐንስ 10፥11

እረኛ ነበርኩኝ የበጎች ጠባቂ፤ አንተ ነህ ያረከኝ አስተዋይ አዋቂ፤ ተዋጊ እንድሆን ድፍረት የሰጠኸኝ፤ እራሴን አንተ ነህ በዘይት የቀባኸኝ። እኔ ማነኝ - ተደሰ እሸቴ Full Album▸ Albastros.com @Yedestaye_Elilta

📔ርዕስ፦ እውነተኛ አምልኮ 👤ጸሐፊ፦ ዶ/ር አለሙ ቢፍቱ 💾መጠን፦2.8MB የገጽ ብዛት፦106 __ የደራሲው ሌሎች ስራዎች፦ * እሳቱ እንዳይጠፋ * በአገልግሎትና በራእዪ ማደግ * የትዳር ሚስጥር __

መሃተመ ጋንዲ ፥ አብረሃም ሊንከን ፥ኦፕራ ዊንፍሪ የህይወታቸውን ጉልህ ክፍል ሰዋችን ሲያነቃቁ ቆይተዋል። ህይወት ለሁሉ ከባድ ነው፣ ማንም ከሰቃይ፥ ከመከራ ፥ከሀዘን አያመልጥም።ለዚህም ነው ብዙዎች በታላላቅ መሪ የሚሳቡት፣ ምክንያቱም ከወደቁበት ያነሱዋቸዋል። አንድ ሰው ከወደቀበት ብናነሳው እሱ እንዲከተለን ጠመንጃ ወይም ሰይፍ አያሰፈልገንም በፍቃደኝነት ይከተለናል። ከሺ አመት ብኋላ ናፖሊን ቦንፓሪት አንዲህ በማለት ተናገረ “አንድ ሰው አውቃለው ፣ እነግራቹሃለው እየሱስ ክርሰቶስ እንዲሁ ሠው አይደለም። በእርሱ እና በማንኛው ሠው መካከል ምንም ውድድር የለውም። አሌክሳንደር ፥ቄሳር፥ ቻርልሜንሁ እና አኔ ግዛቶችን ፈልገን አግኝተናል። ግን ሰለዚህ ድንቅ ሠው ፍጥረት በምን ላይ እናርፋለን? እየሱስ ክርስቶሰ ግዛቱን የመሠረተው በፍቅር እንጂ በሃይል አይደለም። በዘመኑም ብዙዎች ለእርሱ ይሞታሉ። 15. ተጠያቂነት ነገሮች ጥሩ ሲሆኑ መሪዋች ይሞገሳሉ ሲበላሽ ግን ይተቻሉ። በልዮነት የሚቆሙ መሪዎ ምስጋናን ያጋራሉ ለጥፋት ግን ለብቻቸው ሀላፊነትን ይወስዳሉ። ለጥፋቱ ሌሎችን ተጠያቂ የሚያደርግ ሠው አይሻሻልም። የማይሻሻል ደግሞ መሪ ሊሆን አይችልም ።ሠው እራሱን ሳያሻሽል ሌላውን እንዴት ያሻሽላል። የመሪ ተጠያቂነት ከፍ ሲል መኳንትነቱ ከፍ ይላል። 16. የተፈጥሮ እውቀት (ደመነፍስ) ደመነፍስ ሰሜት ምንም ምክኒያታዊ ማብራሪያ የሌለው ሰለ አንድ ነገር ወይም ሰው በዉስጣችን የሚሰማን ስሜት ነው። በየትኛውም ስርእት ፈጣን ማሰተዋል የሚሳካለትን ከሚወድቀው ይለያል ። ስኬት ላይ የሚወጡት ሰዎች ብዙ ጊዜ በጣም ብልጥ አይደሉም ነገር ግን በጣም በተፈጥሮ እውቀት የሚመሩ ናቸው። ሁለት ሰዎች ተመሳሳይ አውቀት ሊኖራቸው ይችላል አንድ ግን በተፈጥሮ እውቀት ላይ ተሞርክዞ የተለየ ውሳኔ ሊሰጥ ይችላል። መቼ መያዝና ፥መቼ ማጠፍ አና መቼ መጫወት ጎበዝ ካርታ ተጫዋችን ከተራ ተጫዋች ይለየዋል። 17. መግባባት ከሌሎች ምን እደሚፈልጉ ካላሳወቁ፣ እነርሱም ፍላጉትዎን አያሟሉሎትም። መሪ ከበታች ካሉት ጋር ያለው መግባባት ውጤተማ በሆነ መንገድ እንዴት እንደሚሰሩ ይወስናል። ዊንስተን ቸርችል የቃላትን ሀይል ሰለተረዳ ለሁለት ቀን የሚናገረውን ንግግር ይለማመዳል ። በተፈጥሮም ቢሆን በመግባባት ባይሆን ኖሮ እንስሶች አብረው አያድኑም ነበር ወይም ወፎቼ ፍፁም በሆነ ሁኔታ አብረው አይበሩም። 18. ልህቀት መሪ በልዮነት የሚወጣው ከእርሱ በታች የሆኑትን በልዮነት እንዲወጡ ሲረዳ ነው ። መሪ ይህን ሊያደርግ የሚችለው እራሱ ልህቀትን ሲለማመድ ነው ። በትንሽ ነገር ላይ መትጋት ትልቅ ሽልማት አለው። በትልቅ ነገር ላይ መትጋት ደግሞ ያልተለመደ ሽልማትን ያመጣል። የመሪ ሽልማት ከአመራር ጥራቱ ጋር የተመጠነ ነው። 19. ግርማ ሞገሰ መሪነት ተፅኖ ያመጣል ። ሰለዚህ ጥሩ መሪ ለመሆን ትልቅ ቁጥር ያለውን ሰዎችን መሳብ አለበት። መሪ ግርማ ሞገስ ሊኖረው ይገባል ። ማንም ደስ የማይለወን ሰው አይከተልም። ሰዎች ለሚወዷቸው ለመሞት ፍቃደኛ ናቸው ለሚጠሉዎቸው ደግሞ በድንጋይ ለመደብደብ። መሪ በግርማ ሞገሱ ወደ እርሱ የሚስባቸው ሰዎች ቁጥር ብዙ ናቸው። ግርማ ሞገስ ሀይል ነው፣ እነ አብረሃም ሊንከን ፤ማርቲን ሉተር ኪንግ አለምን የለወጡበት ትልቅ ሀይል ግርማ ሞገስ ነው። 20. መንፈሳዊነት ሰዎች በአካል ቤት ውስጥ ያሉ መንፈሳዊ ፍጥረቶች ናቸው። ነብሳቸውን ከነኩ ስለእርሶ ይሞታሉ። ያልተለመደ ነገር ለማድረግ የሚፈልግ መሪ መንፋሳዊ መሆን አለበት። ሰው ከውስጡ ትላላቅ ስራዎችን ይፈጥራል። ማንም ለቢል ጌት አይሞትም። ግን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ለ እየሱስ ክርሰቶስም፣ ለቡድሀ፣ ለክርሽና ከሁለት ሺ አመት በፊት ሞተዋል። እወዳችኋለሁ❤❤❤❤

ቁርጠኝነት ትልልቅ ነገር ለማከናወን ትልቅ መሰዋትነት ይጠይቃል። ትልቅ መሰዋትነት ደግሞ ያለቁርጠኝነት ማግኝት አይቻልም።የዳቨንቺ ሞናሊዛ ለመጨረሰ አራት አመት ወሰዶል ፣ ቶማስ ኤድሰን የብርሃን አምፓል ከመሰራቱ በፊት 1.000 ያልተሳካ ሙከራዎች አድርጎዋል። የድንቅ ሰዎች ሰራ ለመፈጠር የማይናወጥ ቁርጠኝነት ካስፈለገ እንደዛው የቀጠሩዋቸውን ለመምራት ያሰፈልጎታል። 11. የመቋቋም ችሎታ ታላላቅ ነገሮች የሠሩ መሪዎች ትልቅ ፅናት አላቸው። ለምሳሌ ፒራሚድ የቆመው መንፈሰ ጠንካራነት ምን መስራት እንደሚችል የሚመሰክር ነው። ህልማቸውን ለማየት ባላቸው ቆራጥነት ፈርኣኖቹ ከሞቱ ሺ አመት ቡኋላ አንኳን አልተረሱም። የመሪ ስኬት ከፅናቱ ጋር ተመጣጣኝ ነው።ለዚህም ነው በየትኛውም ውጊያ አሸናፊ የሚሆነው መጨረሻ የቀረው ነው አንጂ በጭራሸ ብልሁ አይደለም።