602
Subscribers
No data24 hours
-57 days
-1230 days
Posts Archive
602
አንድ ሰው ጥሩ መሪ (Leader) ለመሆን ሊኖሩት የሚገቡ 20 ባህሪያት።
====================================
1. ድፍረት
ብዙ ሰዎች በጀግኖች ይሳባሉ በፈሪዎች ደግሞ ይቅለሸለሻሉ። ደፈር ሰዎችን ሰንመለከት እኛ የምንፈልገውን ነገር በእነርሱ ውስጥ እናያለን። ድፍረት የሰውን አቅም ያሰፋል ። አቅም ሲያንሰ አንደዚሁ ሰኬት ላይ የመድረሰ ተሰፋም ያንሳል። ፍርሃት ችሎታን ይገድባል። ሰለዚህ መሪዎች የማያልቅ ምኞተቸውን ሲከተሉ ደፈር መሆን አለባቸው። አሌክስ ዘ ግሬት ጀግና ባይሆን ኖሮ 200,000 የፐርዢያን ወታደሮች በ 35,000 ሰዎች ድል አያደርግም ነበር።
2. ታማኝነት
መሪ የቃሉን ያህል ዎጋ አለው። የትኛውም ንግድ፣ ድርጀት ወይም ሀገር መነሻው ታማኝነት ከሌለው ከፍ ባለ አቅም መነቃነቅ አይችልም። ሠዎች ለሚያምኑት ሰው ሲሉ አሰቸጋሪ በሆነ ነገር ውሰጥ ያልፋሉ። በዛ ሰው ላይ አምነት ከሌላቸው ግን በአለም ሁሉንም ሊሰጣቸው ቃል ቢገባላቸው እንኳ ስለእርሱ አንድ እርምጃ አይሄድም።ለታማኝነት ትልቅ ምሳሌ እየሱስ ክርስቶስ ነው። ተከታዮቹ እርሱ ከሞተ ቡኋላ አንኳን ስለእርሱ ሊሞቱ ፍቃደኞች ነበሩ ። ምክንያቱ ደግሞ በቃል ኪዳኑ ታማኝነት እምነት ስላላቸው ነው።
3. ጥልቅ ስሜት
የሚወዱትን ነገር ሲስሩ ሰራዎ ጥራትን ያሳያል ። ደስ በማይሰኙበት ሰራ ላይ መለቅ አይቻልም። ጥልቅ ስሜት በፍርሀት፣ በችግር፣ በትችት ውሰጥ እንድንቀጥል የማድርግ ሃይል ነው። ልክ አንደዚሁ ፍቅርም በምድር ላይ ትልቅ ሀይል ነው። በድሮና በአሁን ፈላስፈዎች አይን አግዚአብሔር ፍቅር ነው፣ ፍቅር አግዚአብሔር ነው። መሪ የሚሠራውን ሲወድ፣ የሚወደው ሲስራ ትልቅ ሰኬት ይጠብቃል። ማክል አንጀሎ ለቅርፃቅርፅ ያለው ጥልቅ ስሜት በመስኩ ላይ መሪ አድጎታል። ለስራው ጥልቅ ፍቅር ሰለነበረው በእይታው እና አንገቱ ላይ ጉዳት ከደረሰበት ብኋላ እንኳን በሲሲቲን ቻፕል ስራውን ቀጥሎል።
4. የፈጠራ ችሎታ
ዋና (የመጀመሪያ) ሃሳብ ከሌለን አዲሰን ነገር ለመፍጠር ይከብዳል። ሰለዚህም ንግዶች፣ ድርጅቶች አዳዲስ ሀሳብን ማፍለቅ ሲያቆሙ ትልቅ ወይም ትንሸ አዳዲስ ኩባንያዎች ቦታቸውን ይወሰዳሉ ። ለየት ብለው የሚታዮ መሪዎች ከፍተኛ የመፍጠር ችሎታ አላቸው። ብልሃት በትንሽ ነገር ብዙ እንዲሠሩ እና ችግሮችን በጊዜ እንዲፈቱ ያደርጋል ። ስቲቭ ጆብ ልዮ የፈጠራ አሰተሳሰብን ያሳየ መሪ ነው። በዚሁ በፈጠራ ችሎታ አመራሩ በ1997 የአፐል ኩባንያን ሲረከብ ከውድቀት አድኖታል። ምርትን በቀላሉ የቀን ተቀን ልምምድ ወሰጥ በመክተት አፐል ባሁኑ ጊዜ ይህ ነው የማይባል ትልቅ ዋጋ አለው።
5. ብሩህ አመለካከት
የመሪ ስራ ሰዎች ሲወድቁ ማንሳት ከቆሙም ከፍ ብለው አንዲቆሙ ማድረግ ነው። ይህን ለማድረግ መሪ ያለማቋረጥ አዎንታዊ መሆን አለበት ። አንድ ሰው የሌለውን ሊሰጥ አይችልም። ከዘላቂ ተሰፋቸው የተነሳ ትልልቅ አደጋ ሊያመጣ የሚችሉ እርምጆዎችን ይወስዳሉ፣ ሌሎችን አንዲወሰድ ያበረታታሉ ። ይህም ለትላልቅ መከናወኖች መሰረት ነው።
6. ትህትና
ትሁት መሪ ከእርሱ ከሚበልጡና ከሚያንሱ ሰዎች ይማራል ። ብዙ ጊዜ እውቀት ካልጠበቅናቸው ሰውና ቦታ ይገኛል ሰለዚህ መሪ ትሁት በሆነ ቁጥር ብዙ ይማራ በልዮነትም ይቆማል። ጥሩ ስሜት ከሚፈጥሩብን ጋር እንጂ እኛን ከሚያሳንሱ ሰዎች ጋር መሆን አንፈልግም ። ለዚህም ነው በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሠዎች ዛሬም ለኔንሰን ማንዴላ አክብሮት ያላቸው - ድሀ ሆነህ ሰታበቃ አንደ ልዑል የሚያዋራህ። ትህትና የጀነራል በሰይፍ ሊማርክ ከሚችለው በላይ ብዙ ተከታዮችን ይሰባል።
7. የማወቅ ጉጉት
አብዛኛው የአለም ድንቅ ግኝቶች የማወቅ ጉጉት ባለቸው ሰዎች ተገኝተዋል ። ለማወቅ የሚሻ ማንነት ሌሎች ያላወቁትን ለማወቅ ያበረታታል፣ አዲስን ነገር ለማወቅ አጋጣሚን ይፈጥራል። የማወቅ ጉጉት ድመቷን ገደላት የሚባል አባባል ቢኖርም ግን ይህ የማወቅ ጉጉት ዋጋ አለዉ። የራይት ወንድምአማቾች በሰማይ ላይ ሰለመብረር ማወቅ የማወቅ ጉጉት ባይኖራቸው ኖሮ ዛሬ አውሮፕላን አይኖርም ነበር ።
8. ርህራሄ
ርህራሄ አንደ ሽቶ ሠዎችን ይስባል። እውነተኛ እንክብካቤ ወይም ግድ አላቸው ብለን ለምናሰባቸው የልባችን እና ነፍሳችን ሁሉ እናፈሳለን። ተከታዮች ያላቸውን ሁሉ በመሪያቸው ህልምና ተስፈ ላይ ከማፍሠሳቸው በፊት መሪያቸው በእነርሱ ነገር የተሠጠ መሆኑን መተማመን አለባቸው። ለዚህም ነው ማዘር ቴሬዛ ምንም መኖክሴ ቢሆኑም ብዙ ሰራ ሰርተዋል። ለድሃ ያላቸው ርህራሄ ማንም የማይቆቆማቸው አድርጎዋቸዋል ። በ1997 ከዚህ አለም በሞት ሲለዮ የህንድ ጠቅላይ ሚኒሰቴር ሰለእርሳቸው ሲናገሩ ” ለብዙዎች የብርሃንና የተሰፋ ምልክት የሆኑት ከህይወታችን ሄደዋል” ።
9. መላመድ
በዚህ ምድር ላይ ህይወት ለመተንበይ የሚቻል አይደለም። የአየር ሁኔታ አንደሚለዋወጥ ግትር የሆነ መሪ በተልኮ ይወድቃል። ንፋስ ሲነፍስ ዛፎች ያጎነብሳሉ አሰደናቂ መሪም ያልታሰበ ነገር ሲያጋጥመው አንደዛ ነው። ታላቁ ሳይረሰ የማይደፈረውን የባቢሎን ምሽግን ድል ለመንሳት ተስማሚ የጦር ቴክኒኮች ባይጠቀም በታሪክ መፀህፍት ላይ አይገኝም ነበር።
. ቁርጠኝነት
ትልልቅ ነገር ለማከናወን ትልቅ መሰዋትነት ይጠይቃል። ትልቅ መሰዋትነት ደግሞ ያለቁርጠኝነት ማግኝት አይቻልም።የዳቨንቺ ሞናሊዛ ለመጨረሰ አራት አመት ወሰዶል ፣ ቶማስ ኤድሰን የብርሃን አምፓል ከመሰራቱ በፊት 1.000 ያልተሳካ ሙከራዎች አድርጎዋል። የድንቅ ሰዎች ሰራ ለመፈጠር የማይናወጥ ቁርጠኝነት ካስፈለገ እንደዛው የቀጠሩዋቸውን ለመምራት ያሰፈልጎታል።
11. የመቋቋም ችሎታ
ታላላቅ ነገሮች የሠሩ መሪዎች ትልቅ ፅናት አላቸው። ለምሳሌ ፒራሚድ የቆመው መንፈሰ ጠንካራነት ምን መስራት እንደሚችል የሚመሰክር ነው። ህልማቸውን ለማየት ባላቸው ቆራጥነት ፈርኣኖቹ ከሞቱ ሺ አመት ቡኋላ አንኳን አልተረሱም። የመሪ ስኬት ከፅናቱ ጋር ተመጣጣኝ ነው።ለዚህም ነው በየትኛውም ውጊያ አሸናፊ የሚሆነው መጨረሻ የቀረው ነው አንጂ በጭራሸ ብልሁ አይደለም።
12. ጥበብ
ጥበብ የእውቀት ትክክለኛ መተግበሪያ ነው። ታላቅ ጥበብ የያዘ መሪ የበለጠ ያከናውናል። ማሰተዋል አንድን መሪ ሌሎች ያላዮት እንዲያይ ይረዳዋል። ይህም ሌሎች መሰራት ያልቻሉትን እንዲሰራ በተጨማሪም ተቃዋሚዎቹን በብልጠት አጋሮቹን በብልሀት እንዲይዝ ያደርገዋል። የማሰብ ችሎታ የመሪን ዋጋ እጥፍ ያደርገዋል፣ ጥበብ ደግሞ ሶስት እጥፍ። ጠቢብ ሠለሞን ለዚህ ትልቅ ምሳሌ ነው - ምንም እንኳን በጠላት መንግስት የተከበበች ትንሽ ከተማ ቢመራም ብልህ እና በፍርድ አዋቂነት የተካነ ሰለነበር ከእርሱ ጋር የሚወዳደሩትን ገዢዎች ሁሉ እያሸነፈ በመጨረሻም ከነበረው እጅግ የሚልቅ ግዛት ገዛ።
13. ልግስና
ለየት ያሉ መሪዎች በገንዘባቸው ፣ በሰአታቸው፣ በእውቀታቸው፣ በችሎታቸው ለጋሶች ናቸው። እንድ ሠው የሚቀበለው ሳይሆን የሚሠጠው ትልቅ ያደርገዋል። መሰጠት ገልብጦ መቀበል ነው። ሰለዚህ መሪዎች በሰጡ ቁጥር በደንብ ይቀበላሉ እናም ተለይተው ይታያሉ።
14. አነቃቂነት
602
Repost from GMTV.ጂኤም ቲቪ HEAD OFFIC ETHIOPIA
መሃተመ ጋንዲ ፥ አብረሃም ሊንከን ፥ኦፕራ ዊንፍሪ የህይወታቸውን ጉልህ ክፍል ሰዋችን ሲያነቃቁ ቆይተዋል። ህይወት ለሁሉ ከባድ ነው፣ ማንም ከሰቃይ፥ ከመከራ ፥ከሀዘን አያመልጥም።ለዚህም ነው ብዙዎች በታላላቅ መሪ የሚሳቡት፣ ምክንያቱም ከወደቁበት ያነሱዋቸዋል። አንድ ሰው ከወደቀበት ብናነሳው እሱ እንዲከተለን ጠመንጃ ወይም ሰይፍ አያሰፈልገንም በፍቃደኝነት ይከተለናል። ከሺ አመት ብኋላ ናፖሊን ቦንፓሪት አንዲህ በማለት ተናገረ “አንድ ሰው አውቃለው ፣ እነግራቹሃለው እየሱስ ክርሰቶስ እንዲሁ ሠው አይደለም። በእርሱ እና በማንኛው ሠው መካከል ምንም ውድድር የለውም። አሌክሳንደር ፥ቄሳር፥ ቻርልሜንሁ እና አኔ ግዛቶችን ፈልገን አግኝተናል። ግን ሰለዚህ ድንቅ ሠው ፍጥረት በምን ላይ እናርፋለን? እየሱስ ክርስቶሰ ግዛቱን የመሠረተው በፍቅር እንጂ በሃይል አይደለም። በዘመኑም ብዙዎች ለእርሱ ይሞታሉ።
15. ተጠያቂነት
ነገሮች ጥሩ ሲሆኑ መሪዋች ይሞገሳሉ ሲበላሽ ግን ይተቻሉ። በልዮነት የሚቆሙ መሪዎ ምስጋናን ያጋራሉ ለጥፋት ግን ለብቻቸው ሀላፊነትን ይወስዳሉ። ለጥፋቱ ሌሎችን ተጠያቂ የሚያደርግ ሠው አይሻሻልም። የማይሻሻል ደግሞ መሪ ሊሆን አይችልም ።ሠው እራሱን ሳያሻሽል ሌላውን እንዴት ያሻሽላል። የመሪ ተጠያቂነት ከፍ ሲል መኳንትነቱ ከፍ ይላል።
16. የተፈጥሮ እውቀት (ደመነፍስ)
ደመነፍስ ሰሜት ምንም ምክኒያታዊ ማብራሪያ የሌለው ሰለ አንድ ነገር ወይም ሰው በዉስጣችን የሚሰማን ስሜት ነው። በየትኛውም ስርእት ፈጣን ማሰተዋል የሚሳካለትን ከሚወድቀው ይለያል ። ስኬት ላይ የሚወጡት ሰዎች ብዙ ጊዜ በጣም ብልጥ አይደሉም ነገር ግን በጣም በተፈጥሮ እውቀት የሚመሩ ናቸው። ሁለት ሰዎች ተመሳሳይ አውቀት ሊኖራቸው ይችላል አንድ ግን በተፈጥሮ እውቀት ላይ ተሞርክዞ የተለየ ውሳኔ ሊሰጥ ይችላል። መቼ መያዝና ፥መቼ ማጠፍ አና መቼ መጫወት ጎበዝ ካርታ ተጫዋችን ከተራ ተጫዋች ይለየዋል።
17. መግባባት
ከሌሎች ምን እደሚፈልጉ ካላሳወቁ፣ እነርሱም ፍላጉትዎን አያሟሉሎትም። መሪ ከበታች ካሉት ጋር ያለው መግባባት ውጤተማ በሆነ መንገድ እንዴት እንደሚሰሩ ይወስናል። ዊንስተን ቸርችል የቃላትን ሀይል ሰለተረዳ ለሁለት ቀን የሚናገረውን ንግግር ይለማመዳል ። በተፈጥሮም ቢሆን በመግባባት ባይሆን ኖሮ እንስሶች አብረው አያድኑም ነበር ወይም ወፎቼ ፍፁም በሆነ ሁኔታ አብረው አይበሩም።
18. ልህቀት
መሪ በልዮነት የሚወጣው ከእርሱ በታች የሆኑትን በልዮነት እንዲወጡ ሲረዳ ነው ። መሪ ይህን ሊያደርግ የሚችለው እራሱ ልህቀትን ሲለማመድ ነው ። በትንሽ ነገር ላይ መትጋት ትልቅ ሽልማት አለው። በትልቅ ነገር ላይ መትጋት ደግሞ ያልተለመደ ሽልማትን ያመጣል። የመሪ ሽልማት ከአመራር ጥራቱ ጋር የተመጠነ ነው።
19. ግርማ ሞገሰ
መሪነት ተፅኖ ያመጣል ። ሰለዚህ ጥሩ መሪ ለመሆን ትልቅ ቁጥር ያለውን ሰዎችን መሳብ አለበት። መሪ ግርማ ሞገስ ሊኖረው ይገባል ። ማንም ደስ የማይለወን ሰው አይከተልም። ሰዎች ለሚወዷቸው ለመሞት ፍቃደኛ ናቸው ለሚጠሉዎቸው ደግሞ በድንጋይ ለመደብደብ። መሪ በግርማ ሞገሱ ወደ እርሱ የሚስባቸው ሰዎች ቁጥር ብዙ ናቸው። ግርማ ሞገስ ሀይል ነው፣ እነ አብረሃም ሊንከን ፤ማርቲን ሉተር ኪንግ አለምን የለወጡበት ትልቅ ሀይል ግርማ ሞገስ ነው።
20. መንፈሳዊነት
ሰዎች በአካል ቤት ውስጥ ያሉ መንፈሳዊ ፍጥረቶች ናቸው። ነብሳቸውን ከነኩ ስለእርሶ ይሞታሉ። ያልተለመደ ነገር ለማድረግ የሚፈልግ መሪ መንፋሳዊ መሆን አለበት። ሰው ከውስጡ ትላላቅ ስራዎችን ይፈጥራል። ማንም ለቢል ጌት አይሞትም። ግን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ለ እየሱስ ክርሰቶስም፣ ለቡድሀ፣ ለክርሽና ከሁለት ሺ አመት በፊት ሞተዋል።
እወዳችኋለሁ❤❤❤❤
602
Repost from GMTV.ጂኤም ቲቪ HEAD OFFIC ETHIOPIA
አንድ ሰው ጥሩ መሪ (Leader) ለመሆን ሊኖሩት የሚገቡ 20 ባህሪያት።
====================================
1. ድፍረት
ብዙ ሰዎች በጀግኖች ይሳባሉ በፈሪዎች ደግሞ ይቅለሸለሻሉ። ደፈር ሰዎችን ሰንመለከት እኛ የምንፈልገውን ነገር በእነርሱ ውስጥ እናያለን። ድፍረት የሰውን አቅም ያሰፋል ። አቅም ሲያንሰ አንደዚሁ ሰኬት ላይ የመድረሰ ተሰፋም ያንሳል። ፍርሃት ችሎታን ይገድባል። ሰለዚህ መሪዎች የማያልቅ ምኞተቸውን ሲከተሉ ደፈር መሆን አለባቸው። አሌክስ ዘ ግሬት ጀግና ባይሆን ኖሮ 200,000 የፐርዢያን ወታደሮች በ 35,000 ሰዎች ድል አያደርግም ነበር።
2. ታማኝነት
መሪ የቃሉን ያህል ዎጋ አለው። የትኛውም ንግድ፣ ድርጀት ወይም ሀገር መነሻው ታማኝነት ከሌለው ከፍ ባለ አቅም መነቃነቅ አይችልም። ሠዎች ለሚያምኑት ሰው ሲሉ አሰቸጋሪ በሆነ ነገር ውሰጥ ያልፋሉ። በዛ ሰው ላይ አምነት ከሌላቸው ግን በአለም ሁሉንም ሊሰጣቸው ቃል ቢገባላቸው እንኳ ስለእርሱ አንድ እርምጃ አይሄድም።ለታማኝነት ትልቅ ምሳሌ እየሱስ ክርስቶስ ነው። ተከታዮቹ እርሱ ከሞተ ቡኋላ አንኳን ስለእርሱ ሊሞቱ ፍቃደኞች ነበሩ ። ምክንያቱ ደግሞ በቃል ኪዳኑ ታማኝነት እምነት ስላላቸው ነው።
3. ጥልቅ ስሜት
የሚወዱትን ነገር ሲስሩ ሰራዎ ጥራትን ያሳያል ። ደስ በማይሰኙበት ሰራ ላይ መለቅ አይቻልም። ጥልቅ ስሜት በፍርሀት፣ በችግር፣ በትችት ውሰጥ እንድንቀጥል የማድርግ ሃይል ነው። ልክ አንደዚሁ ፍቅርም በምድር ላይ ትልቅ ሀይል ነው። በድሮና በአሁን ፈላስፈዎች አይን አግዚአብሔር ፍቅር ነው፣ ፍቅር አግዚአብሔር ነው። መሪ የሚሠራውን ሲወድ፣ የሚወደው ሲስራ ትልቅ ሰኬት ይጠብቃል። ማክል አንጀሎ ለቅርፃቅርፅ ያለው ጥልቅ ስሜት በመስኩ ላይ መሪ አድጎታል። ለስራው ጥልቅ ፍቅር ሰለነበረው በእይታው እና አንገቱ ላይ ጉዳት ከደረሰበት ብኋላ እንኳን በሲሲቲን ቻፕል ስራውን ቀጥሎል።
4. የፈጠራ ችሎታ
ዋና (የመጀመሪያ) ሃሳብ ከሌለን አዲሰን ነገር ለመፍጠር ይከብዳል። ሰለዚህም ንግዶች፣ ድርጅቶች አዳዲስ ሀሳብን ማፍለቅ ሲያቆሙ ትልቅ ወይም ትንሸ አዳዲስ ኩባንያዎች ቦታቸውን ይወሰዳሉ ። ለየት ብለው የሚታዮ መሪዎች ከፍተኛ የመፍጠር ችሎታ አላቸው። ብልሃት በትንሽ ነገር ብዙ እንዲሠሩ እና ችግሮችን በጊዜ እንዲፈቱ ያደርጋል ። ስቲቭ ጆብ ልዮ የፈጠራ አሰተሳሰብን ያሳየ መሪ ነው። በዚሁ በፈጠራ ችሎታ አመራሩ በ1997 የአፐል ኩባንያን ሲረከብ ከውድቀት አድኖታል። ምርትን በቀላሉ የቀን ተቀን ልምምድ ወሰጥ በመክተት አፐል ባሁኑ ጊዜ ይህ ነው የማይባል ትልቅ ዋጋ አለው።
5. ብሩህ አመለካከት
የመሪ ስራ ሰዎች ሲወድቁ ማንሳት ከቆሙም ከፍ ብለው አንዲቆሙ ማድረግ ነው። ይህን ለማድረግ መሪ ያለማቋረጥ አዎንታዊ መሆን አለበት ። አንድ ሰው የሌለውን ሊሰጥ አይችልም። ከዘላቂ ተሰፋቸው የተነሳ ትልልቅ አደጋ ሊያመጣ የሚችሉ እርምጆዎችን ይወስዳሉ፣ ሌሎችን አንዲወሰድ ያበረታታሉ ። ይህም ለትላልቅ መከናወኖች መሰረት ነው።
6. ትህትና
ትሁት መሪ ከእርሱ ከሚበልጡና ከሚያንሱ ሰዎች ይማራል ። ብዙ ጊዜ እውቀት ካልጠበቅናቸው ሰውና ቦታ ይገኛል ሰለዚህ መሪ ትሁት በሆነ ቁጥር ብዙ ይማራ በልዮነትም ይቆማል። ጥሩ ስሜት ከሚፈጥሩብን ጋር እንጂ እኛን ከሚያሳንሱ ሰዎች ጋር መሆን አንፈልግም ። ለዚህም ነው በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሠዎች ዛሬም ለኔንሰን ማንዴላ አክብሮት ያላቸው - ድሀ ሆነህ ሰታበቃ አንደ ልዑል የሚያዋራህ። ትህትና የጀነራል በሰይፍ ሊማርክ ከሚችለው በላይ ብዙ ተከታዮችን ይሰባል።
7. የማወቅ ጉጉት
አብዛኛው የአለም ድንቅ ግኝቶች የማወቅ ጉጉት ባለቸው ሰዎች ተገኝተዋል ። ለማወቅ የሚሻ ማንነት ሌሎች ያላወቁትን ለማወቅ ያበረታታል፣ አዲስን ነገር ለማወቅ አጋጣሚን ይፈጥራል። የማወቅ ጉጉት ድመቷን ገደላት የሚባል አባባል ቢኖርም ግን ይህ የማወቅ ጉጉት ዋጋ አለዉ። የራይት ወንድምአማቾች በሰማይ ላይ ሰለመብረር ማወቅ የማወቅ ጉጉት ባይኖራቸው ኖሮ ዛሬ አውሮፕላን አይኖርም ነበር ።
8. ርህራሄ
ርህራሄ አንደ ሽቶ ሠዎችን ይስባል። እውነተኛ እንክብካቤ ወይም ግድ አላቸው ብለን ለምናሰባቸው የልባችን እና ነፍሳችን ሁሉ እናፈሳለን። ተከታዮች ያላቸውን ሁሉ በመሪያቸው ህልምና ተስፈ ላይ ከማፍሠሳቸው በፊት መሪያቸው በእነርሱ ነገር የተሠጠ መሆኑን መተማመን አለባቸው። ለዚህም ነው ማዘር ቴሬዛ ምንም መኖክሴ ቢሆኑም ብዙ ሰራ ሰርተዋል። ለድሃ ያላቸው ርህራሄ ማንም የማይቆቆማቸው አድርጎዋቸዋል ። በ1997 ከዚህ አለም በሞት ሲለዮ የህንድ ጠቅላይ ሚኒሰቴር ሰለእርሳቸው ሲናገሩ ” ለብዙዎች የብርሃንና የተሰፋ ምልክት የሆኑት ከህይወታችን ሄደዋል” ።
9. መላመድ
በዚህ ምድር ላይ ህይወት ለመተንበይ የሚቻል አይደለም። የአየር ሁኔታ አንደሚለዋወጥ ግትር የሆነ መሪ በተልኮ ይወድቃል። ንፋስ ሲነፍስ ዛፎች ያጎነብሳሉ አሰደናቂ መሪም ያልታሰበ ነገር ሲያጋጥመው አንደዛ ነው። ታላቁ ሳይረሰ የማይደፈረውን የባቢሎን ምሽግን ድል ለመንሳት ተስማሚ የጦር ቴክኒኮች ባይጠቀም በታሪክ መፀህፍት ላይ አይገኝም ነበር።
10. ቁርጠኝነት
ትልልቅ ነገር ለማከናወን ትልቅ መሰዋትነት ይጠይቃል። ትልቅ መሰዋትነት ደግሞ ያለቁርጠኝነት ማግኝት አይቻልም።የዳቨንቺ ሞናሊዛ ለመጨረሰ አራት አመት ወሰዶል ፣ ቶማስ ኤድሰን የብርሃን አምፓል ከመሰራቱ በፊት 1.000 ያልተሳካ ሙከራዎች አድርጎዋል። የድንቅ ሰዎች ሰራ ለመፈጠር የማይናወጥ ቁርጠኝነት ካስፈለገ እንደዛው የቀጠሩዋቸውን ለመምራት ያሰፈልጎታል።
11. የመቋቋም ችሎታ
ታላላቅ ነገሮች የሠሩ መሪዎች ትልቅ ፅናት አላቸው። ለምሳሌ ፒራሚድ የቆመው መንፈሰ ጠንካራነት ምን መስራት እንደሚችል የሚመሰክር ነው። ህልማቸውን ለማየት ባላቸው ቆራጥነት ፈርኣኖቹ ከሞቱ ሺ አመት ቡኋላ አንኳን አልተረሱም። የመሪ ስኬት ከፅናቱ ጋር ተመጣጣኝ ነው።ለዚህም ነው በየትኛውም ውጊያ አሸናፊ የሚሆነው መጨረሻ የቀረው ነው አንጂ በጭራሸ ብልሁ አይደለም።
12. ጥበብ
ጥበብ የእውቀት ትክክለኛ መተግበሪያ ነው። ታላቅ ጥበብ የያዘ መሪ የበለጠ ያከናውናል። ማሰተዋል አንድን መሪ ሌሎች ያላዮት እንዲያይ ይረዳዋል። ይህም ሌሎች መሰራት ያልቻሉትን እንዲሰራ በተጨማሪም ተቃዋሚዎቹን በብልጠት አጋሮቹን በብልሀት እንዲይዝ ያደርገዋል። የማሰብ ችሎታ የመሪን ዋጋ እጥፍ ያደርገዋል፣ ጥበብ ደግሞ ሶስት እጥፍ። ጠቢብ ሠለሞን ለዚህ ትልቅ ምሳሌ ነው - ምንም እንኳን በጠላት መንግስት የተከበበች ትንሽ ከተማ ቢመራም ብልህ እና በፍርድ አዋቂነት የተካነ ሰለነበር ከእርሱ ጋር የሚወዳደሩትን ገዢዎች ሁሉ እያሸነፈ በመጨረሻም ከነበረው እጅግ የሚልቅ ግዛት ገዛ።
13. ልግስና
ለየት ያሉ መሪዎች በገንዘባቸው ፣ በሰአታቸው፣ በእውቀታቸው፣ በችሎታቸው ለጋሶች ናቸው። እንድ ሠው የሚቀበለው ሳይሆን የሚሠጠው ትልቅ ያደርገዋል። መሰጠት ገልብጦ መቀበል ነው። ሰለዚህ መሪዎች በሰጡ ቁጥር በደንብ ይቀበላሉ እናም ተለይተው ይታያሉ።
14. አነቃቂነት
602
መንፈሳዊ ሰው or በውስጥ ማንነቱ የጠነከረ ሰው ሀሳቡ ሁሉ ኢየሱስ ነው ።
መንፈሳዊ ሰው or በውስጥ ማንነቱ የጠነከረ ሰው በፍቅር ይመላለሳል ።
መንፈሳዊ ሰው or በውስጥ ማንነቱ የጠነከረ ሰው የተወደደበት ፍቅር ያውቃል።
ኤፌሶን 3 (Ephesians)
14-15፤ ስለዚህ ምክንያት በሰማይና በምድር ያለ አባትነት ሁሉ ከሚሰየምበት ከአብ ፊት እንበረከካለሁ፤
16-17፤ በመንፈሱ በውስጥ ሰውነታችሁ በኃይል እንድትጠነክሩ ክርስቶስም በልባችሁ በእምነት እንዲኖር እንደ ክብሩ ባለ ጠግነት መጠን ይስጣችሁ፤ የእናንተ ሥርና መሠረት በፍቅር ይጸና ዘንድ፥
18-19፤ ከቅዱሳን ሁሉ ጋር ስፋቱና ርዝመቱ ከፍታውም ጥልቅነቱም ምን ያህል መሆኑን ለማስተዋል፥ ከመታወቅም የሚያልፈውን የክርስቶስን ፍቅር ለማወቅ ትበረቱ ዘንድ፥ እስከ እግዚአብሔርም ፍጹም ሙላት ደርሳችሁ ትሞሉ ዘንድ።
602
03 Addisalem assefa // አዲስአለም አሠፋ
Hekemenaye // ህክምናዬ
አዲስአለም አሠፋ New album
sʜᴀʀᴇ ◈sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ
👀 Video Watch
✅ ማርከን ዜማ @Markenzema_bot
በዚህ ቻናል የማይደመጥ መዝሙር የለም ብቻ ምን አለፋችሁ join ይበሉ
➡️ https://t.me/+S2wsmZMSQp3vcGxp
➡️ https://t.me/+S2wsmZMSQp3vcGxp
602
ስልኬ ሲሞላ አንዳንድ ነገሮችን አልቀበል ይላል አና አንዳንድ ነገሮችን ዲሌት አደርጋለው ከዛ ይቀበላል ፣እንደውም አንዳንድ ሀሳቦችን ከህይዎታችን ዲሌት መድረግ አለብን የእግዚአብሔር ሀሳብ ለመቀበል።
2 ቆሮንቶስ 10 (2 Corinthians)
5፤ የሰውንም አሳብ በእግዚአብሔርም እውቀት ላይ የሚነሣውን ከፍ ያለውን ነገር ሁሉ እናፈርሳለን ለክርስቶስም ለመታዘዝ አእምሮን ሁሉ እንማርካለን፥
602
🔥ርዕስ: "የተከፈተ ሰማይ/Sammii Banama"
በወንድም ኬፋ ፈዬ
🔥የተከፈተ ሰማይ ማለት የእግዚአብሔር ልዩና መለኮታዊ ጉብኝት ማለት ነው(God Special and divine Visitations)
✍️ሕዝቅኤል 1:1-3
"በሠላሳኛው ዓመት በአራተኛው ወር ከወሩም በአምስተኛው ቀን በኮቦር ወንዝ በምርኮኞች መካከል ሳለሁ ሰማያት ተከፈቱ፥ የእግዚአብሔርንም ራእይ አየሁ። ንጉሡ ዮአኪን በተማረከ በአምስተኛው ዓመት ከወሩም በአምስተኛው ቀን የእግዚአብሔር ቃል በከለዳውያን አገር በኮቦር ወንዝ ወደ ቡዝ ልጅ ወደ ካህኑ ወደ ሕዝቅኤል መጣ። የእግዚአብሔርም እጅ በዚያ በእኔ ላይ ሆነች"
✍️ማቴዎስ 3:16-17
"ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያው ከውኃ ወጣ፤ እነሆም፥ ሰማያት ተከፈቱ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንደ ርግብ ሲወርድ በእርሱ ላይም ሲመጣ አየ፤ እነሆም፥ ድምፅ ከሰማያት መጥቶ፡ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፡ አለ"
✍️ሐዋርያት 7:55-56
"መንፈስ ቅዱስንም ተሞልቶ ወደ ሰማይ ትኵር ብሎ ሲመለከት የእግዚአብሔርን ክብር ኢየሱስንም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አየና።
እነሆ፥ ሰማያት ተከፍተው የሰው ልጅም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አያለሁ፡ አለ"
✍️ሐዋርያት 10:11-15
" ሰማይም ተከፍቶ በአራት ማዕዘን የተያዘ ታላቅ ሸማ የሚመስል ዕቃ ወደ ምድር ሲወርድ አየ፤ በዚያውም አራት እግር ያላቸው ሁሉ አራዊትም በምድርም የሚንቀሳቀሱት የሰማይ ወፎችም ነበሩበት። ጴጥሮስ ሆይ፥ ተነሣና አርደህ ብላ የሚልም ድምፅ ወደ እርሱ መጣ። ጴጥሮስ ግን፡ ጌታ ሆይ፥ አይሆንም፤ አንዳች ርኵስ የሚያስጸይፍም ከቶ በልቼ አላውቅምና፡ አለ። ደግሞም ሁለተኛ፡ እግዚአብሔር ያነጻውን አንተ አታርክሰው፥ የሚል ድምፅ ወደ እርሱ መጣ"
🔥ሰማይ ሲከፈት የሚሆነው ነገር (Sammiin yeroo nurratti banamuu ta'aan)፦
👉. የእግዚአብሔርን ራዕይ ማየት ይሆናል(ሕዝቅኤል 1:1)=> Mul'ata Waaqayyoo ni argita.
👉. እግዚአብሔር ቃል ወይም መልዕክት ወደ አንተ/ቺ ይመጣል(እግዚአብሔር በቃሉ የልቡን ሀሳብ ይናገራል)(ሕዝቅኤል 1:3)=> Dubbiin Waaqayyoo gara kee in dhufa.
👉. የእግዚአብሔር እጅ በአንተ/ቺ ላይ ይሆናል(ሕዝቅኤል 1:3)=> Harkii Waaqayyoo sii gargaaruu sirratti dhufa.
👉. የእግዚአብሔር መንፈስ በሀይል ይወርድብሃል(ማቴ 3:15-16)=> Haffurii Waaqayyoo sirra buufata.
👉. የእግዚአብሔር ክብር ኢየሱስ ክርስቶስን በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ ማየት ይሆናል (ሐዋርያት 7:55-56)=> Ulfina Waaqayyoo kan ta'ee Yesusiin Mirga Abbaasaatti nii argita.
👉. የእግዚአብሔር ድምፅ ይመጣል(ማቴ 3:17; ሐዋርያት 10:15)=> Sagaleen Waaqayyoo gara kee in dhufa.
🔥ሰማይን የሚያስከፍት(Dhimmoota Sammii sirratti bansiisan keessaa)፦
👉1.የንስሐ ሕይወት ሰማይን ያስከፍታል(Jireenya Qalbii jijjirachuu qabaachuu):- ንስሐ የእግዚአብሔርን ፍርድ ሊያስቀይር የሚችል ኃይል አለው። ዮሐንስ በኃይለኛና ትልቅ ድፍረት ንስሐ እንዲገቡ ይናገር ነበር።
- ንስሐ በእግዚአብሔር ፊት ራስን ማዋረድ ነው።
- ንስሐ ማለት መጸጸት ነው
- ንስሐ ፍሬ አለው። ዮሐንስ ለዚህ ነው የንስሐ ፍሬ አድርጉ ያለው።
👉2. ኢየሱስ ሲሰበክ ሰማይ ይከፈታል (Yesus Kristoos Yeroo Lallabnuu)፦ ምንም እንኳ ዮሐንስ ከኢየሱስ የስድስት ወር ታላቅ ቢሆንም ዮሐንስ ኢየሱስን ሲሰብክ ሰማይ ተከፈተ። እስጢፋኖስ ኢየሱስ ሲሰብክ ሰማይ ተከፈተ። ምንም እንኳን አምላክ ቢሆንም በአንተ እጠመቃለሁ አለው።
=> ሐዋርያት 7:1-56
=> ማቴዎስ 3:1-17
👉3. መከባበርና መፈቃቀር(Walkabajuu fi waljaalachuun yoo jiraatee) ሲኖር ሰማይ ይከፈታል።
=> አለመከባበር ሰማይን ያዘጋል። ሁሉን ሰው ማክበር ይገባል።
🔥በኢየሱስ ክርስቶስነ ስም በሕይወት ዘመናችን ሁሉ ሰማይ በአንጻራችን የተከፈተ ይሁን።
🔥በሕዝቅኤል ላይ የተከፈተው ሰማይ፤ በአንተ/ቺ (በእኛ) ላይ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይከፈት።
🔥በጴጥሮስ ላይ የተከፈተው ሰማይ በአንተ/ቺ (እኛ) ላይ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም የተከፈተ ይሁን።
🔥 በእስጢፋኖስ ላይ የተከፈተው ሰማይ በአንተ/ቺ (እኛ) ላይ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም የተከፈተ ይሁን ።
🔥በኢየሱስ ላይ የተከፈተው ሰማይ በአንተ/ቺ(እኛ) ላይ የተከፈተ ይሁን።
602
ርዕስ: እግዚአብሔርን መፍራት እና የሚያስገኘው ጥቅሞች
(Waaqayyoon Sodaachuu fi Faayidaasaa)
እግዚአብሔርን መፍራት ምን ማለት ነው?
በምድር ላይ ተቋቁሞ ለማለፍ እንዲሁም ከማንኛውንም ክፋት ለመዳን እግዚአብሄርን መፍራት በጣም ወሳኝ ነው፡፡
እግዚአብሄርን መፍራት ማለት፦
እግዚአብሄርን እንደ እግዚአብሄርነቱ መጠን ማክበር እና መስማት ማለት ነው፡፡
ለእግዚአብሄር ፈጣሪነትና አምላክነት እውቅና መስጠት ማለት ነው፡፡
እኛ የእግዚአብሄር ፍጥረት እንደሆንን ለራሱ ለክብሩም እንደፈጠረን መረዳት ማለት ነው፡፡
እግዚአብሄርን አለመፍራት ማለት፦
በሃሳባችን ፣ በንግግራችንና በድርጊታችን ለእርሱ ፈቃድ ቦታ አለመስጠት ማለት ነው፡፡
በህይወታችን ለእርሱ ሀሳብ ቅድሚያ አለመስጠት ማለት ነው፡፡
ፍላጎቱን ከቁጥር አለማስገባት ማለት ነው፡፡
ስለዚህም እግዚአብሔርን እያወቁ እንደ እግዚአብሔርነቱ መጠን ስላላከበሩትና ስላላመሰገኑት የሚያመካኙት አጡ ( ሮሜ 1፥20-21)
ለማያምኑት:
እግዚአብሔርን መፍራት የእግዚአብሔር ፍርድን መፍራት እና የዘለአለም ሞት ይህም ዘላለማዊ ከእግዚአብሔር መለየት ነው (ሉቃስ 12፡5, ዕብ 10:31) ፡፡
ለአአማኞች:
እግዚአብሔርን መፍራት በጣም የተለየ ነገር ነው፤ የአምልኮ ፍርሃት እግዚአብሔርን ማክበር ነው::
(ዕብ 12: 28-29)’’ ስለዚህ የማይናወጥን መንግሥት ስለምንቀበል በማክበርና በፍርሃት እግዚአብሔርን ደስ እያሰኘን የምናመልክበትን ጸጋ እንያዝ፤አምላካችን በእውነት የሚያጠፋ እሳት ነውና።’’ መጽሐፍ ቅዱሳዊው ፍርሃት ለአማኝ እግዚአብሔር ኃጢአትን እንደሚጠላ እና በኃጢአተኛው ላይ ያለውን ፍርድ በመፍራት በአማኝ ሕይወት ውስጥ መፍራትንም ይጨምራል፡፡
ዘዳግም 10፡12; 20-21 እንዲህ ይላል- ‹‹እስራኤል ሆይ፥ አሁንስ አምላክህን እግዚአብሔርን ትፈራ ዘንድ፥ በመንገዱም ሁሉ ትሄድ ዘንድ፥ አምላክህንም እግዚአብሔርን ትወድድ ዘንድ፥ በፍጹምም ልብህ በፍጹምም ነፍስህ ታመልከው ዘንድ፥ መልካምም እንዲሆንልህ ዛሬ ለአንተ የማዝዘውን የእግዚአብሔርን ትእዛዝና ሥርዓት ትጠብቅ ዘንድ ነው እንጂ አምላክህ እግዚአብሔር ከአንተ የሚፈልገው ምንድር ነው?አምላክህን እግዚአብሔርን ፍራ፥ እርሱንም አምልክ ከእርሱም ተጣበቅ፥ በስሙም ማል።ዓይኖችህ ያዩትን እነዚህን ታላላቆች የሚያስፈሩትንም ነገሮች ያደረገልህ እርሱ ክብርህ ነው፥ እርሱም አምላክህ ነው።››
እግዚአብሔርን መፍራት በመንገዱ ለመጓዝ እርሱን ለማገልገል እና እርሱን ለመውደድ መሰረት ነው፡፡
እግዚአብሔርን መፍራት የሚያስገኘው ጥቅሞች
ሰው ለእግዚአብሄር ክብር ስለተፈጠረ እግዚአብሄርን እንደ እግዚአብሄርነቱ ካላከበረው ህይወቱ ይወሳሰባል፡፡ ሰው እግዚአብሄርን ካልፈራ ምንም ነገሩ ሊቃና አይችልም፡፡
ሰው እግዚአብሄርን ከፈራ ደግሞ በህይወቱ ሁሉም ነገሩ መስራትና መሳካት ይችላል፡፡ ሰው እግዚአብሄርን ከፈራ ሌላ ሁሉ ነገሩ ትክክለኛ ቦታውን ይይዛል፡፡
1. እግዚአብሔርን መፍራት ጥበበኛ ያደርጋል።
እግዚአብሄርን የሚፈራ ሰው ጥበበኛ ነው፡፡ እግዚአብሄርን የሚፈራ ሰው ለህይወቱ ያውቅበታል፡፡ እግዚአብሄርን የሚፈራ ሰው ከሰማይና ከምድር ፈጣሪ ጋር እንዴት እንደሚኖር
የሚያውቅ አስተዋይ ነው፡፡
የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው (ምሳሌ 1፡7)
የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው፥ ለሚያደርጓትም ሁሉ ደኅና ማስተዋል አላቸው፤ ምስጋናውም ለዘላለም ይኖራል (መዝሙር 111፡10)
2. እግዚአብሔርን መፍራት ምስጉን ያደርጋል።
እግዚአብሄርን የሚፈራ ሰው የተመሰገነ ነው፡፡ እግዚአብሄርን የሚፈራ ሰው የሚደነቅ ሰው ነው፡፡
ውበት ሐሰት ነው፥ ደም ግባትም ከንቱ ነው፤ እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን እርስዋ ትመሰገናለች (ምሳሌ 31፡30)
3. እግዚአብሔርን መፍራት ለመልካምነት ያበቃል።
እግዚአብሄርን የሚፈራ ሰው መልካም ከሚባል ምንም ነገር አይጎድልም፡፡
የሚፈሩት አንዳችን አያጡምና ቅዱሳኑ ሁሉ፥ እግዚአብሔርን ፍሩት (መዝሙር 34፡9)
4. እግዚአብሔርን መፍራት ፀሎት እንድሰማና ምኞት እንድፈጽም ያደርጋል።
እግዚአብሄር የሚፈሩትን ፀሎታቸውን ይሰማል ምኞታቸውንም ያደርጋል፡፡
ለሚፈሩት ምኞታቸውን ያደርጋል፥ ልመናቸውንም ይሰማል ያድናቸዋልም(መዝሙር 145፡19)
5. እግዚአብሔርን መፍራት ዕድሜን ያራዝማል።
የሚፈሩት ሰዎች ይበልጥ ረጅም እድሜ እንዲኖሩ እግዚአብሄር ይፈልጋል፡፡
እግዚአብሔርን መፍራት ዘመንን ታረዝማለች፤ የኀጥኣን ዕድሜ ግን ታጥራለች (ምሳሌ 10፡27)
6. እግዚአብሔርን መፍራት ሕይወትን ያስገኛል።
እግዚአብሄርን መፍራት ገንዘብና ንብረት ከማያስጥለንን አደጋ ያስጥለናል፡፡
ሰው ከሞት ወጥመድ ያመልጥ ዘንድ እግዚአብሔርን መፍራት የሕይወት ምንጭ ነው (ምሳሌ 14፥27)
7. እግዚአብሔርን መፍራት እግዚአብሔርን ያስደስታል
የሚፈሩ ሰዎች እግዚአብሄርን ያስደስቱታል፡፡
እግዚአብሔር በሚፈሩት፥ በምሕረቱም በሚታመኑት ይደሰታል (መዝሙር 147፡11)
8. እግዚአብሔርን መፍራት ከእግዚአብሔር ዘንድ ጥበቃና ከለላ ያስገኛል።
እግዚአብሄርን የሚፈሩ ሰዎች እግዚአብሄር በመላክቱ ይጠብቃቸዋል ያድናቸውማል፡፡
የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል (መዝሙር 34፡7)
9. እግዚአብሄር በሚፈሩትን ሰዎች ፋንታ ሃይሉን ይገልፃል፡፡ ራሱን እና ቃልኪዳኑን ይገልጥላቸዋል፡፡
እግዚአብሔር ለሚፈሩት ኃይላቸው ነው፥ ቃል ኪዳኑንም ያስታውቃቸዋል (መዝሙር 25፡14)
10. እግዚአብሄርን የሚፈራ ሰው ከራሱ አልፎ ለትውልዱ ጠንካራ መታመኛን ያዘጋጃል፡፡
እግዚአብሔርን ለሚፈራ ጠንካራ መታመን አለው፥ ለልጆቹም መጠጊያ ይኖራል(ምሳሌ 14፡26)
11. ልጅ ለአባቱ እንደሚራራ እግዚአብሄር ለሚፈሩት ይራራል፡፡
አባት ለልጆቹ እንደሚራራ እንዲሁ እግዚአብሔር ለሚፈሩት ይራራል (መዝሙር 103፡13)
12. እግዚአብሔርን መፍራት ወደ ሕይወት ያመራል።
እግዚአብሄርን ፈርቶ የሚስት ሰው የለም፡፡ ሰው እግዚአብሄርን በመፍራቱ ወደ ህይወት ይመራል፡፡
እግዚአብሔርን መፍራት ወደ ሕይወት ይመራል፤ የሚፈራውም ጠግቦ ይኖራል፥ ክፉ ነገርም አያገኘውም(ምሳሌ 19፥23)
602
ሮሜ 5 (Romans)
17፤ በአንዱም በደል ሞት በአንዱ በኩል ከነገሠ፥ ይልቁን የጸጋን ብዛትና የጽድቅን ስጦታ ብዛት የሚቀበሉ በአንዱ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በሕይወት ይነግሣሉ።
602
ትጠቀማለህ አንብበው !!!
እንደ እባብ ልባሞች ሁኑ
ማቴዎስ 10 (Matthew)
16፤ እነሆ፥ እኔ እንደ በጎች በተኵላዎች መካከል እልካችኋለሁ፤ ስለዚህ እንደ እባብ ልባሞች እንደ ርግብም የዋሆች ሁኑ።
እባብ በማንኛውም ሆኔታ ውስጥ መኖር ይችላል ፣በሰራ ውስ መኖር ይችላል ፣በድንጋይ ውስጥ መኖር የችላል ፣በዛፍ ላይ መኖር ይችላል ወዘተ በብዙ ነገር ውስጥ መኖር ይችላል ሆኔታውን ለራሱ እንዲመች ይደረጋል እንጂ እሱ እንደ እስስት አይለዋወጥም እባብ ልባም ነው መኖር ይችላል ራሱን እያደሰ ፣ክርሰቲያንም እነዲው ነው በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ የመኖር አቅም አለው ሆኔታውን ይለውጣል እንጂ ሆኔታው እሱን እየለወጠውም ፣ እንደ እባብ ልባሞች ሁኑ ሁኔታውን ለውጡት እንጂ እንደ እስስት ከሁኔታው ጋር ኣትለዋጡ ፣እባብ በተራራ በሸለቆም በዘፍም ቢሰራም መኖር ይችላል necharun ሰያለውጥ ፣በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ እንዳ ክርስቲያን መኖር ያሁንልን ።
እንደ እባብ ልባሞች እንሁን ።
602
Repost from Rohobot
ዮሐንስ 10 (John)
10፤ ሌባው ሊሰርቅና ሊያርድ ሊያጠፋም እንጂ ስለ ሌላ አይመጣም፤ እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ።
እሁድ 30/2/2018
live ይኖረናል በህይወት መንገስ በሚል ራእስ sher Sher አድርጉ
https://t.me/robhot
https://t.me/robhot
602
ያንን ጠያፉን ሕይወት
ዉበትን ጨምሮበት
ሳላውቅ ባለማመን ስላደረኩት
አገኘሁ ምህረት (2*)
ምንም ብሆን ጌታዬ ምሮኝ
ምንም ብሆን ቃሉ አሳምሮኝ
ምንም ብሆን ደሙ አሳምሮኝ
ደጉ ኢየሱስ ደርሶልኛል
ከሰይጣን አፍ አውጥቶኛል
ደጉ ኢየሱስ ደርሶልኛል
ከጉድ ከአፍረት አውጥቶኛል🙌🙌
ምንም ብሆን Sofia Shibabaw
sʜᴀʀᴇ ◈sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀ
በዚህ ቻናል የማይደመጥ መዝሙር የለም ብቻ ምን አለፋችሁ join ይበሉ
