cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

አቡ መርየም አዳማ

هدفنا الذب عن السنة..................... ትክክለኛው እስላማዊ አስተምህሮ ከቁርአንና ከሐዲስ ከደጋግ ቀደምቶች አረዳድ ከታማኝ ዑለሞች የሚሰራጭበት ቻናል ነው። በተጨማሪም ተውሂድንና ሽርክን እንዲሁም ሱናንና ቢድአን እንዲሁም የቢድአ ሰዎችን ለሰዎች በፁሁፍና በሙሀደራ መልክ ግልፅ ማድረግ https://telegram.me/abumerymadama

Show more
Advertising posts
743
Subscribers
-324 hours
-27 days
+630 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

الغرباء هم الذين يتمسكون بالسنة ويدعون إليها ويحذرون من ضدها وهم أقلّ الناس -
الشيخ العلامة الدكتور محمد بن هادي المدخلي حفظه الله https://t.me/DrMMadkhali/3995 الدال على الخير كفاعله
Show all...
sh-mohammad-hadi-m22022018_002.mp31.31 MB
« وَاتَّقُوا فِتْنَةً لَّا تُصِيبَنَّ الَّذِينَ ظَلَمُوا مِنكُمْ خَاصَّةً ۖ وَاعْلَمُوا أَنَّ اللَّهَ شَدِيدُ الْعِقَابِ » " ከናንተም ውስጥ እነዚያን የበደሉትን ብቻ ለይታ የማትነካን ፈተና ተጠንቀቁ ፡፡ አላህም ቅጣቱ ብርቱ መኾኑን እወቁ ፡፡ " የአላህ መልእክተኛ የዘረኝነት አስከፊነትና የከረፋ ጥንብ መሆኑን እንዲሁም አንዱ ሙስሊም በሌላው ላይ ያለው ሐቅ ምን እንደሆነና መግደሉ ኩፍር መስደቡ ፊስቅ መሆኑን የተናገራባቸው ሐዲሶች አንድ መፅሀፍ ይወጣቸዋል ። ነገር ግን የሰው ልጅ ልቦና በወንጀል ከታወረ ማየትም መስማትም አይችልምና ከልቦና መታወር ጠብቀኝ ብሎ አላህን መለመን ያስፈልጋል ። አላህ አላዋቂዎች በሚሰሩት ግፍ ምክንያት ከሚመጣ መቅሰፍትና ፈተና ይጠብቀን ። የሰውም የአጋንንትም ሸይጣኖችን የስራቸውን ሰጥቶ የወንድሞቻችንን ደም ይጠብቅልን ። https://t.me/bahruteka
Show all...
ባህሩ ተካ - Bahiru Teka

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته قناة رسمية لمحاضرات ودروس الأستاذ بحرو تكا (أبو عبيدة) الدعوة السلفية በአላህ ፈቃድ በዚህ ቻናል የአማርኛ ትምህርቶችን እንዲሁም አጫጭር የአረብኛና የአማርኛ ፁሁፎችን እንለቃለን ከዚህ ቻናል ውጪ ከሌላ ቦታ ተወስደው ለሚለቀቁ ኦዲዮዎች እውቅና አልሰጥም

https://telegram.me/bahruteka

👉 የማንም ብሄር ሆኖ መፈጠር ወንጀል አይደለም ። ይድረስ በሳውዲና በየትኛውም የዐለማችን ክፍል ለምትኖሩ ኢትዮዽያዊያን ሙስሊሞች ። የትም ኑሩ የትም ተፈጠሩ የየትኛውም ብሄር ወይም ጎሳ አባል ሁኑ ይህ በማናችሁም ላይ ወንጀል ሊሆን አይገባም ። ምክንያቱም ማንም ከዚህ ብሄር ( ጎሳ ) መፈጠር እፈልጋለሁ ብሎ አላህ ዘንድ ማመልከቻ አስገብቶ የተፈጠረ የለም ። ለምን ኦሮሞ ሆንክ ለምን አማራ ሆንክ ብሎ ሰውን መግደል ፣ አካል ማጉደል ፣ ደም ማፍሰስ የተከበረውን የሰው ልጅ ከፈጠረው አምላክ ጋር መዋጋት ነው ። በየትኛውም መመዘኛ ተቀባይነት የሌለው ነብዩ ከመላካቸው በፊት የነበሩት የመሀይማን ህዝቦች ተግባር ነው ። እንደዚህ አይነቱ ተግባር በተለይ በሙስሊሞች ሲፈፀም በጣም ያሳዝናል ። በአላህና በመጨረሻ ቀን ያመነ ሙስሊም ፣ ነገ ራቁቱን አላህ ፊት የሚቆም መሆኑን ያመነ ሙስሊም ። እንዴት ወንድሙን ከዚህ ብሄር ነው የተፈጠርከው ስለዚህ ሞት ይገባሀል ብሎ ይገድላል ? ‼ አሳፋሪ ነው ። ኢስላም አላህ የሰውን ልጅ በብሄርና በጎሳ ከፋፍሎ የፈጠረው ሊተዋወቁበት እንጂ ሊፎካከሩበት ፣ እኔ እበልጥ እኔ እበልጥ ሊባባሉበት እንዳልሆነ በሑጅራት ምእራፍ 13ኛው አንቀፅ እንዲህ በማለት ይነግረናል : – « يَا أَيُّهَا النَّاسُ إِنَّا خَلَقْنَاكُم مِّن ذَكَرٍ وَأُنثَىٰ وَجَعَلْنَاكُمْ شُعُوبًا وَقَبَائِلَ لِتَعَارَفُوا ۚ إِنَّ أَكْرَمَكُمْ عِندَ اللَّهِ أَتْقَاكُمْ ۚ إِنَّ اللَّهَ عَلِيمٌ خَبِيرٌ » " እናንተ ሰዎች ሆይ! እኛ ከወንድና ከሴት ፈጠርናችሁ ፡፡ እንድትተዋወቁም ጎሳዎችና ነገዶች አደረግናችሁ ፡፡ አላህ ዘንድ በላጫችሁ በጣም አላህን ፈሪያችሁ ነው፡፡ አላህ ግልጽን ዐዋቂ ውስጥንም ዐዋቂ ነው ፡፡" በዚህ መለኮታዊ የአላህ ቃል አላህ የሰውን ልጅ ከወንድና ከሴት በጎሳና በነገድ ከፋፍሎ የፈጠረው ለመተዋወቅ እንደሆነና ከዚህ ውጪ ትርጉም የሌለው መሆኑን ነው ። በዚህ መለኮታዊ የአላህ ቃል የሚያምን ሙስሊም በምን መመዘኛ አንዱን ከዚህ ጎሳ መፈጠር አልነበረብህም ወይም ሆነህ በመፈጠርህ ወንጀለኛ ያደርግሀል ብሎ አባሮ አድኖ ይገድለዋል ? ‼ እስኪ መልሱን ይንገሩን ። ይህ ማለት ጦርነቱ ከአላህ ጋር ነው ማለት ነው ። እንዴት እገሌን አማራ ወይም ኦሮሞ አድርገህ ፈጠርክ ብሎ ጠርነት መክፈት ነው ። በጣም አሳፋሪ ተግባር መሆኑ ብቻ ሳይሆን በምድር ላይ ጥፋት እንዲሰፍን መቅሰፍት እንዲመጣ የሚያደርግ ነው ። የዚህ አይነቱን ተግባር የማያወግዝ ትውልድ መቆሚያ የሌለው በላእ ለመቀበል ራሱን ያዘጋጅ ። እንዲህ አይነቱን ድርጊት ማስቆም የማይችል መንግስት በመከራና ሰቆቃ የሚኖር ሀገርን ለመምራት ራሱን ያዘጋጅ ። አላህ የሰው ልጆች የሚሰሩት ሀጢያት በምድር ላይ ጥፋት እንዲንሰራፋ ምክንያት የሚሆን መሆኑን ሲነግረን በሩም ምእራፍ በ41 ኛው አንቀፅ እንዲህ ይለናል : – « ظَهَرَ الْفَسَادُ فِي الْبَرِّ وَالْبَحْرِ بِمَا كَسَبَتْ أَيْدِي النَّاسِ لِيُذِيقَهُم بَعْضَ الَّذِي عَمِلُوا لَعَلَّهُمْ يَرْجِعُونَ » " የሰዎች እጆች በሠሩት ኃጢኣት ምክንያት የዚያን የሠሩትን ከፊሉን ያቀምሳቸው ዘንድ መከራው በየብስና በባሕር ተገለጠ ፤ (ተሰራጨ) ፡፡ እነርሱ ሊመለሱ ይከጀላልና ፡፡ " በዚህ አንቀፅ አላህ እንደሚነግረን የሰው ልጆች በሚሰሩት ግፍ ምክንያት በምድርና በባህር ላይ መከራ እንደሚንሰራፋ ( አላህ መቅሰፍት የሚያመጣ ) መሆኑን የመቅሰፍቱ መምጣት ሰዎቹ ከግፋቸውና ከበደላቸው ይመለሱ ዘንድ ተፈልጎ መሆኑን ነው ። ይህ ማለት ሰዎች በሰው ሲመከሩ አሻፈረኝ ካሉ የሚመክራቸው መከራ መምጣቱን ነው ። ነገር ግን መከራም መጥቶ ላይመከሩ ይችላሉ ። እንከን የሌለው የኢስላም አስተምሮ አንድ ሰው ሌላውን ያለ ወንጀሉ በግፍ ከገደለ የሰውን ዘር በሙሉ እንደገደለ መሆኑን በተቃራኒው አንዲትን ነፍስ ከሞት ለመትትረፍ ምክንያት የሆነም የሰውን ዘር ባጠቃላይ ከሞት ለመትረፍ ሰበብ እነደሆነ ነው የሚነግረን ። ይህ የመጠቀ መርህ በማኢዳ ምእራፍ በ32 ኛው አንቀፅ አላህ እንዲህ ብሎ ይነግረናል : – « مِنْ أَجْلِ ذَٰلِكَ كَتَبْنَا عَلَىٰ بَنِي إِسْرَائِيلَ أَنَّهُ مَن قَتَلَ نَفْسًا بِغَيْرِ نَفْسٍ أَوْ فَسَادٍ فِي الْأَرْضِ فَكَأَنَّمَا قَتَلَ النَّاسَ جَمِيعًا وَمَنْ أَحْيَاهَا فَكَأَنَّمَا أَحْيَا النَّاسَ جَمِيعًا ۚ وَلَقَدْ جَاءَتْهُمْ رُسُلُنَا بِالْبَيِّنَاتِ ثُمَّ إِنَّ كَثِيرًا مِّنْهُم بَعْدَ ذَٰلِكَ فِي الْأَرْضِ لَمُسْرِفُونَ » " በዚህ ምክንያት በእስራኤል ልጆች ላይ እነሆ ያለ ነፍስ (መግደል) ወይም በምድር ላይ ያለማጥፋት (ካልሆነ በስተቀር) ነፍስን የገደለ ሰው ሰዎቹን ሁሉ እንደገደለ ነው ፤ ሕያው ያደረጋትም ሰው ሰዎቹን ሁሉ ሕያው እንዳደረገ ነው ማለትን ጻፍን ፡፡ መልክተኞቻችንም በግልጽ ተዓምራት በእርግጥ መጡዋቸው ፡፡ ከዚያም ከዚህ በኋላ ከእነሱ ብዙዎቹ በምድር ላይ ወሰንን አላፊዎች ናቸው ፡፡ " የእነዚህ ረቂቅ መርሆችና አስተምሮዎች ባለቤት የሆነ ሙስሊም ወንድሙን በግፍ እንዴት እንደ ከብት አስተኝቶ ያርዳል ?‼ ነው ወይስ ለሸይጣናዊ አመለካከት ዲኑን ሽጦ ከአላህ ጋር መገናኘት የሚባል ነገር የለም ብሎ በመጪው ዐለም ክዶ ነው ? ይከብዳል ።!!!!! እባካችሁ ሙስሊሞች ከእንቅልፋችሁ ንቁ አኼራን አስታውሱ ካልነበራችሁበት ያስገኛችሁን እሱ ፊት ራቁታችሁ የምትቆሙት አላህን ፍሩ ። ወደራሳችሁ ተመለሱ ሀገራችሁንና ህዝባችሁን ከመከራ አድኑ ። በሰው ልጆች ደምና መከራ ለሚከብሩ በሰው አምሳል ለተፈጠሩ ሰው በላ አውሬዮች ሸቀጥ አትሁኑ ። በጣም የሚያሳዝነውና የሚያሳፍረው በአሁኑ ጊዜ ቁርኣን በወረደበት ፣ ጅብሪል በተመላለሰበት ፣ ነብዩ አውስና ኸዝረጅን ከ50 አመት የእርስ በርስ የመሀይምነት እልቂት በኋላ በላ ኢላሃ ኢልለላህ ( በኢስላም) አንድ ባደረጉበት ሀገር ሳውዲ ላይ የዚህ አይነቱ አሳፋሪ ተግባር በሀገራችን ሙስሊሞች መካከል መፈፀሙ ነው ። ውድ በሳውዲ የምትኖሩ የሀገራች ሙስሊሞች ዛሬ ነገ ሳትሉ ካላችሁበት የዘረኝት ስካር ወጥታችሁ ወደ አላህ ተመልሳችሁ ተውበት አድርጉ ። ውድ የኦሮሞና አማራ መሻኢኽና ዑለሞች እንዲሁም ዱዓቶች አላህ የጣለባችሁን አደራ ከምን ጊዜውም በላይ የምትወጡበት ጊዜ አሁን ነውና በመልካም በማዘዝና ከመጥፎ በመከልከል ድርሻችሁን ተወጡ ካልሆነ የሚመጣውን ፊትና ለመቀበለደ ተዘጋጁ ። ‼ አላህ በምድር ላይ ጥፋት ተንሰራፍቶ ግፍ ሲበዛ ግፈኞቹን ብቻ ለይቶ የማይነካ ፈተና የሚመጣ መሆኑንና እንድንጠነቀቅ በአንፋል ምእራፍ በ25ኛው አንቀፅ እንዲህ ብሎ ይነግረናል : –
Show all...
የሰለፎችን ጎዳና የተቃረነ ሰው... 📝 በታላቁ ሊቅ ሸይኽ ፈውዛን አላህ ይጠብቃቸው ⁉️ በሰለፍ መንሐጅ ላይ የተቃረነ አካል ከአህለል ቢድዓ ይቆጠራል ወይም ከአህለሱና መጠሪያነት ይወጣል ወይስ አይወጣም?  ✅ የሰለፎችን መዝሀብ የተቃረነ ከአህለሱና ወልጀማዓህ አይደለም፡፡ ይልቁንም ከኸለፎች (ወደኋላ መጠው በዲኑ ላይ ከዘባረቁት) ነው፡፡ የሰለፎችን መዝሐብ ከተቃረነ በሰለፍ መንሐጅ ሊሆን አይችልም፡፡ በእርግጥ ጥመቱ በተቃርኖው መጠን ሊሆን ይችላል፡፡ ምክንያቱም ሰዎች በተቃርኖ ይበላለጣሉ፡፡ በመሆኑም እንደተቃርኗቸው የሚሰጣቸውም ብይን በዚያው መጠን ይለያያል፡፡ 💼 ከሸይኽ ዩሱፍ አላህ ይጠብቃቸው ▵▮▱▰▱▰▱▰▱▰▱▰▯▴ ⚙ 📝 أَبُـــو عِـمْــرَان ❨𝕒𝕓𝕦 𝕚𝕞𝕣𝕒𝕟❩ 🏝 ••⇣⇣.  🏖   ••⇣⇣  ╰𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞.   ╰𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞 🖥️ በ 𝐓𝐞𝐥𝐞𝐠𝐫𝐚𝐦~𝐂𝐡𝐚𝐧𝐧𝐞𝐥 🏝 ⇣⇣⇣🍭⇣⇣⇣📲 ⇣⇣⇣↙️ https://t.me/AbuImranAselefy/8875 https://t.me/AbuImranAselefy https://t.me/AbuImranAselefy ሀሳብ  ካለዎ  ⤵️⤵️⤵️⤵️ https://t.me/AbuImranAselefybot
Show all...
Abu Imran Muhammed Mekonn

ዝም አንልም እኛ በህይወት እስካለን፤ ባለችው አቅማችን እንፋለማለን፤ ያበጠው ይፈንዳ ሲፈልግ ይተርተር፤ እውነት ይነገራል ቢጣፍጥም ቢመር። ያለወትን ሀሳብ 💡 ➢ @AbuImranAselefybot በሚለው ያድርሱኝ ⤵ ↪ እቀበላለሁ ↩ ⤴ ➻ በተለይ ስህተት ካዩ በፍጥነት ይጠቁሙኝ

↪️ የጁመዓ ኹጥባ (ምክር) ↩️ خطبة الجمعة؛ ➴➴➴➴➴ ==================== ✅ ርዕስ፦ ➴➷➘ "«እስልምና ለሴት ልጅ የሰጠው ክብር» በሚል አንገብጋቢ  ወቅታዊ ርዕስ ♻️عنوان" التكريم الإسلام للمرءة " موضوع ملح حاليًا ➴➴➴➴➴ ==================== 🎙በተከበሩ ሸይኽ ዩሱፍ አህመድ(አቡዓብዱልዓዚዝ) ሀፊዘሁሏህ 🎙 لفضيلة الشيخ يسوف بن آحمد (ابوعبد العزيز) -حفظه الله- 🗓 ሰኔ ‐28  ‐ 10- 2016 E.C 🕌 ባህር ዳር ከተማ መስጅደል ቡኻሪ 🕌 بمدينة بحردار [إثيوبيا]؛ في مسجد البخاري ➴➴➴➴➴ ==================== ሙስሊም አሏህን የምትፈራ ሴት ከባሏ ጋር ሊኖራት የሚገባ ኢስላማዊ ህግጋትን በተመለከተ ሰፋ ያለ ወሳኝ ምክርና ኢስላም ለሴቶች የሰጠው ክብርና ደረጃ ምን እነደሆነ እጅግ በጣም ደስ በሚል አገላለፅ የተብራራበት ምክር ነው። ➴➴➴➴➴ ==================== 🎙ሴቶችም ወንዶችም ይህንን ምክር በትክክል በማዳመጥ እየተሰሩ ያሉ ስህተቶችን/ጥፋቶችን ልንርቅ ይገባል፣ ➴➴➴➴➴ ==================== ከዑማው መስተካከል ትልቅ ባለድርሻዋ ሚስት፣እህት፣እናት የሆነችዋ ሴት ናትና እባካችሁ ሴቶች አሏህን ፈርታችሁ ተስተካክላችሁ ዑማውም እንዲስተካከል አሏህ በአዘዛችሁ ላይ ቀጥ በሉ። ➴➴➴➴➴ ==================== ዝርዝሩን ገብታችሁ ይ ደ መ ጥ share/ሼር/አድርጉ ባረከሏሁ ፊኩም። ➴➴➴➴➴ ==================== #size መጠን 09.03MB #length 34:13.58min 🕌መስጅድ:-አል-ቡኻሪ 🌎ባህር ዳር፣ ኢትዮጲያ የባህር ዳር አህለሱና መሻይኾች ገፅ https://t.me/alateriqilhaq كن على بصيرة
Show all...
AudioCutter_ሼኽ_ዩሱፍ_አህመድ_ጁሙዓ_ኹጥባcompressed_$cutted.mp38.61 MB
👉 ከነብዩላሂ ኢብራሂም ታሪክ ውስጥ በጥቂቱ የተዳሰሰበትን ፁሑፍ ወንድሜ አቡ ኢምራን ለአንባቢ እንዲመች አድርጎ ወደ pdf ቀይሮ አቅርበታል ። አላህ ልፋቱን በመልካም ስራ መዝገቡ ላይ ያስፍርለት ። እኔንም እሱንም የሱና ወንድምና እህቶቻችንንም በሐቅ ላይ ፅናቱን ይስጠን ። https://t.me/bahruteka
Show all...
የነብዩላህ ኢብራሒም ታሪክ.pdf3.43 MB
👉 የሙሐረም ወርና ሙስሊሞች የሙሐረም ወር ከሂጅሪያ ወሮች የመጀመሪያውና አላህ ለይቶ ካላቃቸው አራቱ ወራቶች አንዱ ነው ። ይህ ወር የሂጅሪያ ወር መጀመሪያ ቢሆንም ሙስሊሞች የዘመን መለወጫ ብለው በዚህ ወር መግቢያ ላይ የተለየ የሚሰሩት ነገር የለም ። ይልቁንም ሙስሊሞቸው ህይወታቸው የሰከንዶች ሽርፍራፊ ጥርቅም መሆኑንና እየአንዳንዱ ሽርፍራፊ በተቀነሰ ቁጥር ከእድሜያቸው እየተቀነሰና ወደ ቀብር እየተጠጉ መሆናቸውን ነው የሚያውቁት ። በመሆኑም በየትኛውም ዘመን ፣ አመት ፣ ወር ፣ ሳምንት ፣ ሳአት ፣ ደቂቃና ሰከንድ ለሚቀጥለው ዐለም መዘጋጀት እንዳለባቸው ያውቃሉ ። ከዚህ ዝግጅታቸው አንዱ ምንዳና ቱሩፋት አለባቸው በተባሉ ቦታና ጊዜያቶች የታዘዙትን መልካም ስራዎች መስራት ነው ። በመሆኑም በሙሐረም ወር ውስጥ የታዘዙ የአምልኮ አይነቶችን ይፈፅማሉ ምንዳውንም ከጌታቸው ይጠብቃሉ ። የሙሐረም ወር ከአራቱ የተከበሩ ወራቶች ለመሆኑ በመልእክተኛው ሐዲስ የተረጋገጠ ሲሆን ከ12ቱ አራቱ የተከበሩ መሆናቸው ደግሞ አላህ በተከበረው ቃሉ በተውባ ምእራፍ 36ው አንቀፅ እንዲ ብሎ ይነግረናል : – « إِنَّ عِدَّةَ الشُّهُورِ عِندَ اللَّهِ اثْنَا عَشَرَ شَهْرًا فِي كِتَابِ اللَّهِ يَوْمَ خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ مِنْهَا أَرْبَعَةٌ حُرُمٌ ۚ ذَٰلِكَ الدِّينُ الْقَيِّمُ ۚ فَلَا تَظْلِمُوا فِيهِنَّ أَنفُسَكُمْ ۚ وَقَاتِلُوا الْمُشْرِكِينَ كَافَّةً كَمَا يُقَاتِلُونَكُمْ كَافَّةً ۚ وَاعْلَمُوا أَنَّ اللَّهَ مَعَ الْمُتَّقِينَ » " የወሮች ቁጥር አላህ ዘንድ በአላህ መጽሐፍ ውስጥ ሰማያትንና ምድርን በፈጠረበት ቀን ዐሥራ ሁለት ወር ነው ፡፡ ከእነሱ አራቱ የተከበሩ ናቸው ፡፡ ይህ ቀጥተኛው ሃይማኖት ነው ፡፡ በእነርሱ ውስጥም ነፍሶቻችሁን አትበድሉ ፡፡ አጋሪዎችንም በአንድ ላይ ኾነው እንደሚዋጉዋችሁ በአንድ ላይ ኾናችሁ ተጋደሉዋቸው ፡፡ አላህም ከሚፈሩት ጋር መኾኑን ዕወቁ ፡፡" የአላህ መልእክተኛ – ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም – የተከበሩት ወራት የተኞቹ እንደሆኑ በሚከተለው በሐዲሳቸው ነገረውናል : – عن أَبي بَكْرَةَ رضي الله عنه عَنْ النَّبِيِّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ أنه قَالَ :  " إنَّ الزَّمَانَ قَدْ اسْتَدَارَ كَهَيْئَتِهِ يَوْمَ خَلَقَ اللَّهُ السَّمَوَاتِ وَالأَرْضَ السَّنَةُ اثْنَا عَشَرَ شَهْرًا مِنْهَا أَرْبَعَةٌ حُرُمٌ ثَلاثٌ مُتَوَالِيَاتٌ ذُو الْقَعْدَةِ وَذُو الْحِجَّةِ وَالْمُحَرَّمُ وَرَجَبُ مُضَرَ الَّذِي بَيْنَ جُمَادَى وَشَعْبَانَ " متفق عليه አቡ በክረተ የተባለ ሶሐብይ እንዳወራው የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል ይላል : – " ዘመን አላህ ሰማይና ምድር ሲፈጥር ወደ ነበረበት ተመልሷል ። ( የሐጅ ወር አላህ በዙል ሒጃ አድርጎታል ። መሀይማኖች የቀየሩት ውድቅ ሆኖ ወደዛው ተመልሷልና ይህን ያዙ ) ። አመት አስራ ሁለት ወር ነው ። ከእነሱ ውስጥ አራቱ የተከበሩ ናቸው ። ሶስቱ ተከታታዮች ናቸው ። ዙል ቀዕዳ ፣ ዙል ሒጃ ፣ ሙሐረም , ረጀብ ደግሞ በጁማደ ሳኒና በሻዕባን መካከል ነው ። " ከእነዚህ ከአራቱ ደግሞ ሙሐረም ይበልጥ የተከበረ ወር መሆኑን ሲነግሩን የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ይላሉ : – عن أبي ذر رضي الله عنه قال :  سألت النبي – صلى الله عليه وسلم – : أي الليل خير وأي الأشهر أفضل؟ فقال : " خير الليل جوفه وأفضل الأشهر شهر الله الذي تدعونه المحرم " አቡ ዘር የተባለ ሶሐብይ – ረዲየላሁ ዐንሁ – የአላህ መልእክተኛን የትኛው ለይል ይበልጣል ? የትኛውስ ወር በላጭ ነው ብዬ ጠየቋቸው ። እሳቸውም እንዲ አሉ : – " ከለሊቱ ውስጥ በላጩ ድቅድቁ ( ከመካከለኛው በኋላ) ያለው ነው ። ከወሮች ደግሞ እናንተ ሙሐረም ብላችሁ የምትጠሩት ነው ። " በዚህ ወር ውስጥ ተወዳጅ የሆው መልካም ስራ ደግሞ ፆም ነው ። ይህንንም መልእክተኛው እንዲህ በማለት ይነግሩናል : –  عن أبي هريرة أن النبي صلى الله عليه وسلم قال :  " أفضل الصيام بعد شهر رمضان شهر الله الذي تدعونه المحرم وأفضل الصلاة بعد الفريضة قيام الليل " . رواه مسلم አቡ ሁረይራ ባወሩትና ኢማሙ ሙስሊም በዘገቡት ሐዲስ ነብዩ እንዲህ ብለዋል : – " ከፆሞች ሁሉ በላጩ ከረመዳን ወር በኋላ ሙሐረም ብላችሁ የምትጠሩት ወር ( መፆም ነው) ከሶላት ሁሉ በላጩ ከፈርድ ሶላት በኋላ የለይል ሶላት ነው ። " የአላህ መልእክተኛ በሙሐረም ወር መፆም ( የቻሉትን ማለት ነው) ከረመዳን ወር ፆም ቀጥሎ የተወደደ መሆኑን እየነገሩን ነው ። በመሆኑም አንድ ሰው በሙሐረም ወር ውስጥ የቻለውን ያክል ቢፆም በጣም ተወዳጅ ነው ። እዚህ ጋር መታወቅ ያለበት ከረመዳን ውጪ ወሩን ሙሉ መፆም እንደማይቻል ነው ። በዚህ በሙሐረም ወር የዐስረኛውን ቀን መፆም ያለፈውን አመት ወንጀል የሚያስምር መሆኑን መልእክተኛው በሚቀጥለው ሐዲሳቸው ነግረውናል ። عن أبي قَتادة رضي الله تعالى عنه ، عن الرّسول - صلّى الله عليه وسلّم - قال : " صوم عاشوراء يكفِّر السّنة الماضية " رواه النسائي አቡ ቀታዳ የተባለ ሶሐብይ የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል ይላል : – " የዓሹራእ ቀንን መፆም ያለፈው አመት ወንጀል ያስምራል ። " ከእነዚህ መረጃዎች በመነሳት ሙስሊሞች በሙሐረም ወር ከፆም የበለጠ የተወደደ ስራ አለመኖሩን ያውቃሉ ። በቻሉት አቅም በፆም ወደ አላህ ይቃረባሉ ከዚህ ውጪ አላስፈላጊ አመለካከትና እምነት ከኢስላም አንፃር ቦታ የለውም ። አላህ ከተጠቃሚዮች ያድረገን ። https://t.me/bahruteka
Show all...
ባህሩ ተካ - Bahiru Teka

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته قناة رسمية لمحاضرات ودروس الأستاذ بحرو تكا (أبو عبيدة) الدعوة السلفية በአላህ ፈቃድ በዚህ ቻናል የአማርኛ ትምህርቶችን እንዲሁም አጫጭር የአረብኛና የአማርኛ ፁሁፎችን እንለቃለን ከዚህ ቻናል ውጪ ከሌላ ቦታ ተወስደው ለሚለቀቁ ኦዲዮዎች እውቅና አልሰጥም

https://telegram.me/bahruteka

ሙስሊም፣ ሙስሊም ወንድሙን ይቅርና ሌላውንም መበደል አይፈቀድለትም!! ————— አላህ መበዳደልን በእጅጉ እርም አድርጓል!!። ሙስሊሙንም ሆነ ሙስሊም ያልሆነን አካል መበደል አምላካችን አላህ በእጅጉ የከለከለው ተግባር ሲሆን ሙስሊም ከሙስሊም ሲሆን ደግሞ ይበልጥ የከበደ ነው!!። አላህ እንዲህ አለ:- وَوَقَعَ الْقَوْلُ عَلَيْهِم بِمَا ظَلَمُوا فَهُمْ لَا يَنطِقُونَ «በመበደላቸውም በእነርሱ ላይ ቃሉ ይፈጸምባቸዋል፡፡ እነርሱም አይናገሩም፡፡» አን-ነምል 85 በምንወደውም ሆነ በምንጠላው ሰው ላይ ፍትሃዊ እንድንሆንና ከበደል እንድንርቅ እንዲህ በማለት ነግሮናል:- يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا كُونُوا قَوَّامِينَ لِلَّهِ شُهَدَاءَ بِالْقِسْطِ ۖ وَلَا يَجْرِمَنَّكُمْ شَنَآنُ قَوْمٍ عَلَىٰ أَلَّا تَعْدِلُوا ۚ اعْدِلُوا هُوَ أَقْرَبُ لِلتَّقْوَىٰ ۖ وَاتَّقُوا اللَّهَ ۚ إِنَّ اللَّهَ خَبِيرٌ بِمَا تَعْمَلُونَ «እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ለአላህ ቀጥተኞች በትክክል መስካሪዎች ሁኑ፡፡ ሕዝቦችንም መጥላት ባለማስተካከል ላይ አይገፋፋችሁ፡፡ አስተካክሉ፡፡ እርሱ (ማስተካከል) ለአላህ ፍራቻ በጣም የቀረበ ነው፡፡ አላህንም ፍሩ፡፡ አላህ በምትሠሩት ሁሉ ውስጠ አዋቂ ነው፡፡» አል-ማኢዳ 8 የቅርብን ሰውም ሆነ የሩቅ ሰው፣ ሙስሊምም ሆነ ሌላን አካል መበደል በእስልምናችን በእጅጉ የተወገዘ ሀራም ተግባር ነው!። መበዳደልን የሚከለክሉ ሌሎች በርካታ የቁርኣን አንቀፆችም አሉ። አላህ በሀዲሰ'ል ቁድስ መበዳደልን እርም እንዳደረገ እንዲ በማለት ነግሮናል:- “ባሮቼ ሆይ! እኔ መበደልን በራሴ ላይ እርም አድርጌያለሁ፣ በመካከላችሁም እርም አድርጌያለሁና አትበዳደሉ።” [ሙስሊም 2577 ዘግበውታል።] ከኢበኑ ዑመር (ረዲየላሁ ዐንሁማ) ተይዞ የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል:- “ሙስሊም የሙስሊም ወንድም ነው። አይበድለውም፣ አያዋርደውም። ለወንድሙ ጉዳይ የቆመ (የሆነ) ሰው፣ አላህ ለርሱ ጉዳይ ይሆንለታል። ለአንድ ሙስሊም ከጭንቀቱ መውጫ ያበጀ (ያስተነፈሰ ሰው)፣ አላህ ለርሱ ከቂያማ ቀን ጭንቀቶች መውጫ ያበጅለታል። የሙስሊም ወንድሙን ነውር የሸፈነ ሰው አላህ በእለተ ትንሳዔ (ቂያማ) ቀን ነውሩን ይሸፍንለታል።” [ቡኻሪ 2442 ዘግበውታል] ከጃቢር ኢብን ዐብደላህ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ ነቢዩ እንዲህ ብለዋል:- “ወዮላችሁ በደልን ተጠንቀቁ! እሱ እኮ በእለተ ትንሳዔ ጭለማ ነው…” በሌላ ዘገባም እንዲህ ብለዋል:- “በደልን ፍሩ እርሱ እኮ የቂያማ ቀን ጭለማ ነው…” [አህመድ በሙስነዳቸው፣ ቡኻሪ በአደቡል ሙፍረድ፣ ሙስሊም በሶሂሃቸው ዘግበውታል] በደልን እንጠንቀቅ!! ውጤቱ የከፋ ነው!! የተበዳይ ዱዓም ግርዶሽ የለበትም!! በዳይ ከመሆን ተበዳይ መሆን ይሻላል!! ✍🏻ኢብን ሽፋ (t.me/ibnshifa) የተለያዩ ት/ቶችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችን ⤵️ #join በማድረግ ይቀላቀሉ https://telegram.me/IbnShifa https://telegram.me/IbnShifa
Show all...
[ኢብን ሽፋ - Ibn Shifa]

እራስህን ሁል ጊዜ ለቁርኣንና ለሀዲስ ተጎታች አድርግ! በአንድ ነገር ላይ ከቁርኣንና ከሀዲስ ማስረጃ ሳታገኝ አቋም አትያዝ! ሁሌም ለሰዎች መልካምን ተመኝ! ለሀቅ እንጂ ለሰዎች ወጋኝ አትሁን

ፋሽን ነው መሰለኝ 🔍🔎🔍🔎🔍🏝 አንድ ቃላት አለ ፋሽን ነው መሰለኝ ከሙብተዲዕ ሙሪድ ምላስ ላይ የሚገኝ ሱኑዮች ተናግረው ሰው ሲያስጠነቅቁ ያልገባቸው መስለው ሆነው ያላወቁ ሰው ያማሉ ብለው ሀቅን ነው ሚርቁ ✅🔍✅🔍✅🔍✅🔍✅🔍 ተዝኪያ ለመስጠት ለመደገፍ ሰውን               ያናግራቸዋል የማይባለውን          ረድ አንሰማም ሀሜት ነው እሱማ ሂስድም ነው ይላሉ አንዱ አንዱን ሊቀማ 📝🎙📝🎙📝🎙📝🎙📝 ሽርክን መሰባበር ተውሂድን ማስፋፋት            ቢድዓን አንቅሮ በሱና መተካት             ውሸትን አዋርዶ ለሀቅ መዋጋት መቼም ሆኖ አያውቅም አንድነትን ማጥፋት           ሊሆንም አይችልም ኡማን መለያየት 🔎🏝🔎🏝🔎🏝🔎🏝🔎🏝 የአንድነት መሰረት የመጥበቂያው ሽቦ     በተውሂድ  ሲኖር  ነው  በሱና ተውቦ ሱናን ለማዳከም የቻለውን ሲጥር ሀቀኛ ለመምሰል ቅጥፈትን ሲደውር ሰውን ለማሳመን ሲቀንስ ሲደምር ሲረማመድ ስታይ በኡለሞች ክብር ምን አርገህ      ቀረፅከው ይህን በእይታህ ስር? 🚦🕌🚦🕌🚦🕌🚦🕌🚦🕌 ሀሚትማ ነው ካልክ ያጠፋን መተቸት ስሙን  እየጠሩ  ቢድዓውን  መግታት ጥፋቱን መናገር  ችግሩ እንዲታወቅ ማንቂያ ደውል መስጠት ሰው እንዲጠነቀቅ ቢድዓን ርቆ ሱናውን እንዲያጠብቅ እስኪ የቱ ጋር ነው አንተ ምታውቀው ሀቅ? ሀሚታ ነው ያልከኝ ካጥፊዎች ማስጠንቀቅ? 📚💡📚💡📚💡📚💡📚💡 ሰው ግራ ሲጋባ ሙዳቸው ሲጠፋው ለባጢል ሲቋምጥ መስሎበት እውነታው የሚነግረው አጥቶ መንገዱን ሲስተው ቢድዓን ሲያደልብ ሀቅ እየመሰለው ለወንድሙ አዝኖለት ሀቅን ቢጠቁመው የዚህ ሰው ጥፋቱ ስህተቱ ምንድን ነው? 🏖💻🏖💻🏖💻🏖💻🏖💻 አይ አትንኩ ሸኬን አትጥሩ ስሙን             ያሻውን ይናገር የፈለገውን              ማለትህ ከሆነ ተናገር በይፋ ሰው ያማሉ ብለህ የሰው ስም አታጥፋ መወገን ለዲን ነው ጥርት ላለው ሀቅ ፍቱን መድኃኒት ነው ቢድዓን ለመራቅ ሰውን ቢያበጃጁት ቢያሸላልሙት ሀቅን እስካልያዘ  ይመራል  ከሬት ▵▮▱▰▱▰▱▰▱▰▱▰▯▴ 📝 በእህታችን ኡሙ ማሂር አላህ ይጠብቃት 🏝 ••⇣⇣.  🏖   ••⇣⇣  ╰𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞.   ╰𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞 🖥️ በ 𝐓𝐞𝐥𝐞𝐠𝐫𝐚𝐦~𝐂𝐡𝐚𝐧𝐧𝐞𝐥 🏝 ⇣⇣⇣🍭⇣⇣⇣📲 ⇣⇣⇣↙️ https://t.me/AbuImranAselefy https://t.me/AbuImranAselefy https://t.me/AbuImranAselefy ሀሳብ  ካለዎ  ⤵️⤵️⤵️⤵️ https://t.me/AbuImranAselefybot
Show all...
Abu Imran Muhammed Mekonn

ዝም አንልም እኛ በህይወት እስካለን፤ ባለችው አቅማችን እንፋለማለን፤ ያበጠው ይፈንዳ ሲፈልግ ይተርተር፤ እውነት ይነገራል ቢጣፍጥም ቢመር። ያለወትን ሀሳብ 💡 ➢ @AbuImranAselefybot በሚለው ያድርሱኝ ⤵ ↪ እቀበላለሁ ↩ ⤴ ➻ በተለይ ስህተት ካዩ በፍጥነት ይጠቁሙኝ

የጎንፎ ዳዕዋ ግብዢያ ለታ ርዕስ" ያአላህን ድንና የነብዩን መንገድ ጨምድደን እንያዝ ከተዳሰሱት ነጥቦች መካከል> አላህን በብቸኝነት ማምለክ ነጃ የመውጫ ጣፋጭና አዋጭ ነው ተውሂድ የነብያቶች ሁሉ ጥሪ ስለመሆኑ ከተለያዩ አንጃዎች ያስጠነቀቁበት ወሳኝ ምክር « መሰረታዊ፣አሳሳቢና ሁሌም ወቅታዊ  የሆነውን አሏህን ያዘዘውን በመታዘዝ እና የከለከለውን በመከልከል ተገቢውን ፍራቻ መፍራት በሚል መሰረታዊ እና ሁሌም በየትኛውም ሁኔታችን፣ቦታ፣ጊዜ  ልንዘነጋው የማይገባ ትልቅ ወስያ ዙሪያ የተሰጠ እጅግ ወሳኝ ምክር»በሚል 👉አሏህ ያዘዘውን በመታዘዝ እና የከለከለውን በመከልከል ተገቢውን ፍራቻ መፍራት 👉ነብያቶች ሳይቀሩ አሏህን እንዲፈሩ የታዘዙበት ስለመሆኑ 👉አሏህን መፍራት ና ውጤቱ ምን እንደሆነ 👉ሪዝቃችን በረካ ፣ሀገራችን ሰላም እንዲሆን ዋና ሰበቡ አላህን መፍራት ስለመሆኑ 👉አሏህን መፍራት ሙሉ ሰላም የሚገኝበት ስለመሆኑ 👉አሏህን በመፍራት ላይ ኢስቲቃማ ሊኖረን ይገባል 🎤 በሸይኽ ሙሐመድ ሃያት ከሃራ [ሃፊዘሁሏህ] 🕌መስጅደ ፉርቃን  ጎንፎ 🗓ሰኔ‐ 26‐ 10 - 2016E.c https://t.me/SheikMohmmedHyatHara
Show all...
ሸይኽ ሙሀመድ ሀያት ጎንፎ.mp38.54 MB
Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.