en
Feedback
ኢንፋቅ የልማትና መረዳጃ ማህበር /ደሴ/

ኢንፋቅ የልማትና መረዳጃ ማህበር /ደሴ/

Open in Telegram

ይህ የኢንፋቅ ልማትና መረዳጃ ማህበር Official የቴሌግራም ቻናል ነዉ። . የእርሶ ትንሽ እጅ ለሌሎች ምርኩዝ ናት! .

Show more
1 404
Subscribers
-124 hours
-97 days
-1030 days
Posts Archive
......የሄዱ እለት መዲናይቱ በቀን ፀሀይ ስትጨልም፣ ሀዘን ወርሷት ዞላም ከቧት ስትል እልም፣ ሶሀበቶች ክው ሲሉ ውስጥ ነዶ፣ ሰይፍ ሳቡ ያ ኡመር ማመን ገዶ። የሄዱ እለት የመዲናው የኑር አምባ፣ ሞላት ሀዘን ሂጃዚቱን እያደባ፣ ቀምቶ አዛን ቅላፄውን ውቡን ቃና፣ አባረረው ያንን ቢላል ከመዲና። በአንቱ መምጣት የተዋበው ያ ጎዳና፣ የሄዱ እለት ሀዘን ቃኘው እንደገና፣ የአንቱ መምጣት ከፍ ያረጋት መዲናይቱ፣ የሄዱ እለት ከብዷት ታዬ መፅናናቱ። ወዳጄዋ ምኞቴ ነው የጧት ማታ፣ መጎራበት ከአንቱ ቅጥር በዚያ ቦታ፣ የሞትኩ እለት ሲዘጋጋ ሙላው ሁላ፣ ወዳጅ ሁኑኝ አማላጄ ለእኔው መላ። اَللّٰهُــمَّ صَــلِّ عَلَـــى سَيِّــدِنَا مُحَــمَّــدْ ገጣሚ ▻ ፈትሁዲን_ዑመር 1448 ዐ.ሂ

ወዳጄዋ ምኞቴ ነው የጧት ማታ፣ መጎራበት ከአንቱ ቅጥር በዚያ ቦታ፣ የሞትኩ እለት ሲዘጋጋ ሙላው ሁላ፣ ወዳጅ ሁኑኝ አማላጄ ለእኔው መላ። ገጣሚ▻ ፈትሁዲን_ዑመር #የኸሚስ_ብዕሮች #ኢንፋቅ_ሚዲያ #ኢ
ወዳጄዋ ምኞቴ ነው የጧት ማታ፣ መጎራበት ከአንቱ ቅጥር በዚያ ቦታ፣ የሞትኩ እለት ሲዘጋጋ ሙላው ሁላ፣ ወዳጅ ሁኑኝ አማላጄ ለእኔው መላ። ገጣሚ▻ ፈትሁዲን_ዑመር #የኸሚስ_ብዕሮች #ኢንፋቅ_ሚዲያ #ኢንፋቅ

♦️የአዲስ አባላት ትውውቅ ፕሮግራም♦️ 💭 ለኢንፋቅ ለመስራት በቅርቡ የተመዘጋችሁ አዳዲስ አባላት በሙሉ የፊታችን #እሁድ ነሀሴ 24 የትውውቅ ፕሮግራም ስለሚኖረን ሁላችሁም እንድትገኙ ለማለት እንወ
♦️የአዲስ አባላት ትውውቅ ፕሮግራም♦️ 💭 ለኢንፋቅ ለመስራት በቅርቡ የተመዘጋችሁ አዳዲስ አባላት በሙሉ የፊታችን #እሁድ ነሀሴ 24 የትውውቅ ፕሮግራም ስለሚኖረን ሁላችሁም እንድትገኙ ለማለት እንወዳለን❗ 🗓 እሁድ ነሀሴ 24 🕑 ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ 📍 ፒያሳ ሰይድ ያሲን ህንፃ 5ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 516 📃

አፍሬ ነው አፍሬ ነው ሆዴ አንቱ የኔ መውደድ፣ ስራዬ ከስራሁ እርቆ ቢንጋደድ፤ አስቀረኝ መሰለኝ የራሴው ስንክሳር፣ ላፍታ መጣ ብዬ ወዳአንቱ እንዳልሀድር። አፍሬ ነው አፍሬ ነው ቀና ማልል፣ አቀርቅሬ የቀረሁት ብጎዳድል፣ ብሞላማ የአንቱን ሱና ብራመደው፣ ባልተከዘ ሰውነቴም ባላፈረው። አንተ ሀጁ ተሳፋሪው ተመዲና፣ የሰራሁት ያረከሰኝ ያመፅኩበት ያሳነሰኝ ያደፍኩበት ዝቅ ያረገኝ እስኪሸሸኝ፤ ይህ አንገቴ እስኪቃና እስኪያነሳኝ፣ ለወዳጄ ሰላምታዬን አድርስልኝ። اَللّٰهُــمَّ صَــلِّ عَلَـــى سَيِّــدِنَا مُحَــمَّــدْ ተፃፈ-በፈትሁዲን ዑመር 1447 ዐ.ሂ . #ኢንፋቅ_ሚዲያ #ኢንፋቅ

በረቢዕ ነውና... የረቢዕ ስጦታ ፈንታም እጣዬ ነሁ፣ የሺ አምስት ኡመትሁ ሀበሻ ላይ ያለሁ፣ ስከትብ ስላንቱ በማውቀው በአጀሙ፣ ስልዎት አለሁኝ አንቱ ሙከረሙ። በረቢዕ ነው እና     ጀምበር መገለጡ፣ በረቢዕ ነው እና     ከዞላም ማምለጡ፣ አናውን ዳናውን ንጉሱን ከአልከሶ፣ ዊላዳሁ ሞሸረው ቀለም አስፈስሶ። ውልደትዎ ወልዶ እዝነት ከደግነት፣ ዞላም ሊገረሰስ ኑር በኑሩ ሊመረት፣ አሚና አዝልቃወት ቀኑ ደረሰና፣ አለማት ተቸሩ ሸረፍ ከልቅና። ዳና የዘነበው የሸህ ሚስባሁ ቃና፣ በጫሌ ላይ ቢጎርፍ የውልደትሁ ዜና፣ በርዘንጅ የፈሰሰው በሙላው ነውና፣ ገሌ ገሌ አንልም ሰምጠን ያለ ዋና። ይሄ ወራት እማ እጅግ ሰው ቢያዘልቅ፣ የኪስራን ጉልላት ፈራርሶ ሲወድቅ፣ የሺ አመት እሳቱ ክፋቱ ሲላቀቅ፣ ደርቆ የሰዋ ሀይቅ ኢብሊስም ሲያንቧርቅ፣ ታዬ በውልደትሁ ነቢይ በአንቱ መዝለቅ። ከአሚና ማህፀን ኑር ፈሶ ሻም ደርሶ፣ ፅልመት ወገግ አለ ብርሀን ደግሶ፣ እኔም አንቱን ብዬ ከመስመሩ ሳርቅ፣ ሁሌ አረሳዎትም ረቢዕ ሲዘልቅ። 
#በፈትሁዲን_ዑመር 1448 ዐ.ሂ

በረቢዕ ነውና... የረቢዕ ስጦታ ፈንታም እጣዬ ነሁ፣ የሺ አምስት ኡመትሁ ሀበሻ ላይ ያለሁ፣ ስከትብ ስላንቱ በማውቀው በአጀሙ፣ ስልዎት አለሁኝ አንቱ ሙከረሙ። በረቢዕ ነው እና ጀምበር መገለጡ፣ በረ
በረቢዕ ነውና... የረቢዕ ስጦታ ፈንታም እጣዬ ነሁ፣ የሺ አምስት ኡመትሁ ሀበሻ ላይ ያለሁ፣ ስከትብ ስላንቱ በማውቀው በአጀሙ፣ ስልዎት አለሁኝ አንቱ ሙከረሙ። በረቢዕ ነው እና     ጀምበር መገለጡ፣ በረቢዕ ነው እና     ከዞላም ማምለጡ፣ አናውን ዳናውን ንጉሱን ከአልከሶ፣ ዊላዳሁ ሞሸረው ቀለም አስፈስሶ። ውልደትዎ ወልዶ እዝነት ከደግነት፣ ዞላም ሊገረሰስ ኑር በኑሩ ሊመረት፣ አሚና አዝልቃወት ቀኑ ደረሰና፣ አለማት ተቸሩ ሸረፍ ከልቅና። ዳና የዘነበው የሸህ ሚስባሁ ቃና፣ በጫሌ ላይ ቢጎርፍ የውልደትሁ ዜና፣ በርዘንጅ የፈሰሰው በሙላው ነውና፣ ገሌ ገሌ አንልም ሰምጠን ያለ ዋና። ይሄ ወራት እማ እጅግ ሰው ቢያዘልቅ፣ የኪስራን ጉልላት ፈራርሶ ሲወድቅ፣ የሺ አመት እሳቱ ክፋቱ ሲላቀቅ፣ ደርቆ የሰዋ ሀይቅ ኢብሊስም ሲያንቧርቅ፣ ታዬ በውልደትሁ ነቢይ በአንቱ መዝለቅ። ከአሚና ማህፀን ኑር ፈሶ ሻም ደርሶ፣ ፅልመት ወገግ አለ ብርሀን ደግሶ፣ እኔም አንቱን ብዬ ከመስመሩ ሳርቅ፣ ሁሌ አረሳዎትም ረቢዕ ሲዘልቅ። 
#በፈትሁዲን_ዑመር 1448 ዐ.ሂ
#የኸሚስ_ብዕሮች #ኢንፋቅ_ሚዲያ #ኢንፋቅ

ረሱል (ሰ.0.ወ) አቡ ሁረይራ (ረ.0) ባስተላለፉት ሀዲስ እንዲህ ብለዋል : "ፀሐይ ከምትወጣባቸው ቀናት ሁሉ በላጩ የጁምዓ ቀን ነው"። (ሙስሊም ዘግበውታል) የተዋበ ጁምዓ! #መልካም_ጁምዓ #ኢን
ረሱል (ሰ.0.ወ) አቡ ሁረይራ (ረ.0) ባስተላለፉት ሀዲስ እንዲህ ብለዋል : "ፀሐይ ከምትወጣባቸው ቀናት ሁሉ በላጩ የጁምዓ ቀን ነው"።  (ሙስሊም ዘግበውታል) የተዋበ ጁምዓ! #መልካም_ጁምዓ #ኢንፋቅ_ሚዲያ #ኢንፋቅ

ውበቱ ባይማርክ የፊቱ ገፅታ፣ ምንም ከመልኩ ላይ ባይገባም ከእይታ፣ ግና ኑር ነበረ ኑርን የወደደ፣ የልቡ ላይ ሁቡ ነቢይን የሰነደ። ምንም ደሀ ቢሆን ባይኖረው ቆጠሮ፣ ምንም በአይን ቢታይ ከቁመቱ አጥሮ፣ የዚያ ዘመን ሰዎች ዘር ግንዱን እያዩ አድልተው ለውበት፣ አገለሉት አሉ ክብር እንደመስጠት። ጁለይቢይ መች አጣ የሚወደው ከቶ፣ ከአላህም ከረሱል ውዴታ ተሰቶ፣ ጁለይቢይ ከእኔ ነው እኔም ከእሱ ነኝ፣ ብለው አወደሱት መልከ መልካሙ አዛኝ። ጥሪት ከቆጠሮ ባይኖረው ከጓዳ፣ ከመልኩ ቢደብስ ቁመቱ ባይፀዳ፣ ለትዳር ፍለጋ ባይወጣም ከሜዳ፣ ግና ነቢይ ዳሩት መልካሟን ኮረዳ። ስሙ ባይታወቅ በዙሪያው ነዋሪ፣ ዘነጋው ከቦታው የእገሌው ተጣሪ፣ ጁለይቢይን አጣሁት ፈልጉልኝ እማ፣ ብለው አወደሱት የአለሙ ራህማ። ባለ 7 ታሪክ ክንደ ብርቱው ያ ሰው፣ ከጀሀድ ሜዳ ላይ ሂዶ የወደቀው፣ 7 ወዲያ ጥሎ ዲኑን ሲል የሞተው፣ በነብዩ እጅ ላይ ለህድ የተንተራሰው።

ውበቱ ባይማርክ የፊቱ ገፅታ፣ ምንም ከመልኩ ላይ ባይገባም ከእይታ፣ ግና ኑር ነበረ ኑርን የወደደ፣ የልቡ ላይ ሁቡ ነቢይን የሰነደ። ምንም ደሀ ቢሆን ባይኖረው ቆጠሮ፣ ምንም በአይን ቢታይ ከቁመቱ አ
ውበቱ ባይማርክ የፊቱ ገፅታ፣ ምንም ከመልኩ ላይ ባይገባም ከእይታ፣ ግና ኑር ነበረ ኑርን የወደደ፣ የልቡ ላይ ሁቡ ነቢይን የሰነደ። ምንም ደሀ ቢሆን ባይኖረው ቆጠሮ፣ ምንም በአይን ቢታይ ከቁመቱ አጥሮ፣ የዚያ ዘመን ሰዎች ዘር ግንዱን እያዩ አድልተው ለውበት፣ አገለሉት አሉ ክብር እንደመስጠት። ጁለይቢይ መች አጣ የሚወደው ከቶ፣ ከአላህም ከረሱል ውዴታ ተሰቶ፣ ጁለይቢይ ከእኔ ነው እኔም ከእሱ ነኝ፣ ብለው አወደሱት መልከ መልካሙ አዛኝ። ጥሪት ከቆጠሮ ባይኖረው ከጓዳ፣ ከመልኩ ቢደብስ ቁመቱ ባይፀዳ፣ ለትዳር ፍለጋ ባይወጣም ከሜዳ፣ ግና ነቢይ ዳሩት መልካሟን ኮረዳ። ስሙ ባይታወቅ በዙሪያው ነዋሪ፣ ዘነጋው ከቦታው የእገሌው ተጣሪ፣ ጁለይቢይን አጣሁት ፈልጉልኝ እማ፣ ብለው አወደሱት የአለሙ ራህማ። ባለ 7 ታሪክ ክንደ ብርቱው ያ ሰው፣ ከጀሀድ ሜዳ ላይ ሂዶ የወደቀው፣ 7 ወዲያ ጥሎ ዲኑን ሲል የሞተው፣ በነብዩ እጅ ነው ለህድ የተንተራሰው።

#ለኢንፋቅ #በቅርብ_ቀን #ኢንፋቅ_ሚዲያ "የእርስዎ ትንሽ እጅ ለሌሎች ምርኩዝ ናት"
#ለኢንፋቅ #በቅርብ_ቀን #ኢንፋቅ_ሚዲያ "የእርስዎ ትንሽ እጅ ለሌሎች ምርኩዝ ናት"

#መልካም_ጁምዓ #ኢንፋቅ_ሚዲያ #ኢንፋቅ
#መልካም_ጁምዓ #ኢንፋቅ_ሚዲያ #ኢንፋቅ

#የኸሚስ_ብዕሮች ረሱለል አሚን...ﷺ እርሶ ላይ አርፈው ልብሶች ተዋቡ፣ አማረባቸው ሞገስ ደረቡ! አይኖ ስር ሆኖ ኩሉም ደመቀ፣ ሰርክ ተመቸው ፍካት ሰነቀ! ሲዋኩ ፀዳ ጥርሶን አጊኝቶ፣ ፈገገ ሳቀ እጅግ ተደስቶ! አለሟን አየች መሬትን ደላት፣ ደስታ ቦረቀች ሲራመዱባት!💚 ✍አፍራህ ሁሴን . . . #ኢንፋቅ_ሚዲያ #ኢንፋቅ #የኸሚስ_ብዕሮች

ኑ አብረን በኸይር ስራ እንዋል! . ነገ #እሁድ_ጠዋት ከ2:00 ጀምሮ በኢንፋቅ የዚያራ ዘርፍ የተዘጋጀ የ #ልብስ_አጠባ በመርከዝ ዳረል አርቀም (ፔፕሲ) ስለሚኖር እርሶም የዚህ ኸይር ስራ አካል በ
ኑ አብረን በኸይር ስራ እንዋል! . ነገ #እሁድ_ጠዋት ከ2:00 ጀምሮ በኢንፋቅ የዚያራ ዘርፍ የተዘጋጀ የ #ልብስ_አጠባ በመርከዝ ዳረል አርቀም (ፔፕሲ) ስለሚኖር እርሶም የዚህ ኸይር ስራ አካል በመሆን የአጅር ተካፋይ ይሁኑ። . ኑ አብረን በኸይር ስራ እንዋል! . #ኢንፋቅ_ዚያራ #መልካም_ቀን

#ለኸሚሳችን 55 . . . `````አርግዛዎት ጉድ ታዬ አሉ ለጉድ ሚከብድ፣ ከጅምሩ በእርግዝና በአሚና ሆድ። ውሀ ኩሬው የሚርቀው እታች ሆኖ፣ ከፍ አለ አሉ ለአሚናቱ ተመጥኖ፣ ያ ደመናው ለፀተይዋ መጋረጃ፣ ተንሳፈፈ ከአሚና ራስ ለማብረጃ። አርግዛዎት ያንን ኑር ቅብ የተዋቡ፣ መለክ መቶ ሲያባሽራት ሊሉ አርሂቡ፣ አንቢያውስ መቼ ቀርቶ ከሷ ዘንዳ፣ ሆነው እዝነት ዘለቁልን ሙሀመዳ። መርዬምም አኢሻ መተው የዛ ለታ፣ በዊላዳሁ ጎጉቶ መህሉቁ ሲምታታ፣ ተኩለው ቢዘልቁ ተውበው በጠና፣ አሚናን ገረማት የልጇ ኑር ፋና። ተቆርጦ እትብታቸው በጣሙን ተውበው፣ ታዩ አሉ ቢመጡ ጨረቃን አስንቀው፣ ምጡም ገር ነበረ ላአሚናም አልጠና፣ እንደሌላዋ ሴት አልነበሩም እና። ብቅ ያሉ ለታማ አሚና ጉድ አየች፣ ኑር ሻምን-ሶሪያ ሲያበራ አየሁ አለች፣ ልቅናወት ቀድሞ ቢሰፍርም በአርሹ፣ ግን ዱኒያም ላይ ታዬ ስምሁ መንበሽበሹ። የጠራው ጌታዬ ከሁሉም ክጀላ፣ አንቱን ቢልክልን የከውናቱን መላ፣ ይኸው ሰው ሆንና እርቀን ከሽርኩ፣ ለአንድ አላህ ብቻ ነው ሱጁድ መንበርከኩ። የመጡ ለታ ነው እሳቱ መጥፋቱ፣ የመጡ ለታ ነው ቢወድቅ ጉልላቱ፣ የመጡ ለት ዘይኔ ሴትም ነጃ ወጣች፣ ከአፈር መውደቅ ቀርቶ በቁም ተከበረች። በአንቱ የተገኘው ፈዲላው በዛና፣ ለቀለም ከበደ ቢፃፍ ለምጠና፣ ሁሉ በአንቱ አማረ አዱኒያም ዲናችን፣ በውልደትሁ ጠራ የልብ እድፋችን። ሶሊ ወሰሊሙ በማለቂያው ነቢይ፣ በእኒያ በተኳሉት በሆኑት ሙረቢይ፣ በጎድም በዘመድ በሙላው ጠቅላላ፣ ሰለዋቱ ይንጎድ ሳይል ወደ ሆላ።
ተፃፈ-በፈትሁዲን-ዑመር 1448ዐ.ሂ  / ሰኔ-2018 ዐ.ል
. . . #ኢንፋቅ_ሚዲያ #ኢንፋቅ