fa
Feedback
ኢንፋቅ የልማትና መረዳጃ ማህበር /ደሴ/

ኢንፋቅ የልማትና መረዳጃ ማህበር /ደሴ/

رفتن به کانال در Telegram

ይህ የኢንፋቅ ልማትና መረዳጃ ማህበር Official የቴሌግራም ቻናል ነዉ። . የእርሶ ትንሽ እጅ ለሌሎች ምርኩዝ ናት! .

نمایش بیشتر
1 451
مشترکین
-224 ساعت
-87 روز
-4630 روز
آرشیو پست ها
ወደ ሆላ ተጉዘን ከስንኞቻችን ማህደር ስንጨልፍ ''እንዴት ነሁ'' ብለን በትንሻ ቆጭተናል! እንዴት ኖት አልኩና ዳግም እንደገና፣ መዲናን አቀናሁ በመናብ ጎዳና። ሶሉ አለ ነቢይ ﷺ .
ግጥም-ፈትሁዲን ዑመር

#ለኸሚሳችን 53 . . . ---------------ትናገር ትናገር አኢሻ የደጉን ሰው ውበት የደጉን ሰው እዝነት የደጉን ሰው አህላቅ ትናገርም ታውጋ የፊቶን አሳሳቅ። የግንባርዎ ኑር የአካልዎ ብርሀን፣ ዞላም ማባረሩን አኢሸቱ ታውጋን፣ መርፌ ተደብቃ ጠፍታ ወድቃ ያኔ፣ ተገኘ ትላለች ብቅ ቢሉ ዘይኔ። ፀባዬ ቁርአን ተራማጅ በመንገድ ፣ እንዴት ነሁ በጠና እንዴት ነሁ ሙሀመድ። ጫማዎን ጠግነው ታይተዋል ሙስጦፋ፣ ልብስዎን በመርፌ ሰፍተዋል በይፋ፣ ቤትዎን ሲያፀዱ ሲወጡ ሲወርዱ፣ በእጅግ መተናነስ ታዩ ሙሀመዱ። ከአፋቸው ለአንድ ቀን መጥፎ መቼ ፈልቃ፣ በመልካም ላይ ኖሩ ሀያት እስኪያበቃ፣ እንዲህ እንዲህ ብላ ብትነግረን አኢሻ፣ ነፍሳችንን ፈተሽን ብትሆነን ወጌሻ። ስለ ውበትዎ ደግሞ ስታወራ፣ ፈገግ ያሉ ለታ የእኛ ኸይረል ወራ፣ እንደ ቁራጭ ቀመር ነበረ ትላለች ፊትዎ ሲያበራ። ደግሞ እንዲህ ትላለች አኢሻ ሚስታቸው፣ እኒያ ወይዛዝርቶች ዩስፍን ቢያይዋቸው፤ ጣታቸውን ቆርጠው ቢደማም እጃቸው፤ ግና የእኔን ነቢይ በድንገት ቢያይዎት፣ ጣታቸውን ሳይሆን ልብ ነው ሚቆርጡት። ፅድት ያለ ውበት ልስልስ ነው ገላቸው፣ ከሚስክም በላይ ነው ነቢይ ጠረናቸው፣ ከላይ የሚያበሩት የኑሩ አውድማ፣ ውስጣቸውም ነበር የምግባሮች አርማ። ሰለዋቱ በዝቶ ናኝቶ በአለማቱ፣ መጉደል እየራቀው ጠርቶ ከጉድለቱ፣ በአንቱ ቤተ ዘመድ ደግሞም በጓድዎ፣ የአላህ ሰላት ሰላም ሁሌ አይለይዎ።
ተፃፈ-በፈትሁዲን ዑመር 1448ዐ.ሂ/2018ዐ.ል
. . . #ኢንፋቅ_ሚዲያ #ኢንፋቅ

#ለኸሚሳችን 52 . . . ...........አንቱን ስል እንኳን ሰው መሆንን ግመል አስከብሮል፣ የአንቱ መሆን ነቢይ ስንቱን ሰው ሞሽሮል። ካልቀበሩኝ በቀር እሩህ ከእኔ ሸሽቶ፣ ካልዛለ በስተቀር ይህ ክንዴ ተረቶ፣ ካልከፈኑኝ በጨርቅ አይኔ ካልተዘጋ፣ ስላንቱ እከትባለሁ በቆላም በደጋ። እኔ ምን ቸገረኝ አንቱን ስል ቢጠሉኝ፣ ስድባቸው ምርቃን ጥፊያቸው አይጎዳኝ። አንቱን ስል ቢጠሉኝ አንቱን ስል ነብዬ፣ ግድ የለኝም ጭራሽ ቢያገሉኝ ውድዬ። እንኳን ጥየሁ ልሄድ ጓዞቼን ጠቅልዬ፣ እንኳንስ ልራመድ አንቱን ወዲያ ብዬ፣ ማሰብ ያሳመኛል በልቤ ማስታወስ፣ ታቅፌሁ እኖራለሁ እስከ ለህዴ ድረስ። አንቱን ስል ቢጠላኝ አንቱል ስል ቢጋፋ፣ አንቱን ስል የራቀኝ ከጎኔ ቢጠፋ፣ ግድ የለኝም እና አንቱን ስል ለሄደ፣ መታኮሱን ትቶ ይምጣ እየበረደ። ባያውቅሁ ነው እንጂ ያወቀሁ መች ሄዶ፣ አንቱን ሲል ይኖራል ቀለም ፊደል ሰዶ፣ የግንባርሁን ኑር መቶ ያየው ለታ፣ ሊሰድብሁ የመጣው ቀረ በዝምታ። አንቱን ስል ልሙተው ሳልጠፋ ከደጅሁ፣ ልመላለስበት ከሚያበራው ከስምሁ፣ አድሮ ከሚንረው ወዝቶ እየፈለቀ፣ ከስምሁ ልዋልል አይኔ እየሰበቀ። ወገግ ከሚለው ከስምሁ ዳርቻ፣ ኑርን ከሚያስንቀው ከመልክሁ መባቻ፣ መዝለቁ ቢገደን ቁመን ከዳር ዳሩ፣ መፃፉን ይዘናል እያልን ሙክታሩ። አንቱን ስል ከጠላኝ ከኢማኑ ጎሎ፣ አንቱን ስል ይውደደኝ ጥሉን ወዲያ ጥሎ፣ ከስሮ ከሚከስር ጎሎ እየጎደለ፣ ወዳጅሁን ይውደድ መውደድ እያከለ። ከምሎ በካሚል መጉደል እየራቀው፣ ማነሱ እየበዛ አንዳችም ሳይከላው፣ ሰለዋቱ በአንቱ በዘመድ الصحابة፣ አበደን ቀን ለይሉን ይውረድ እየረባ። ተፃፈ-በፈትሁዲን ዑመር ሙሀረም-1448 ዐ.ሂ /ሰኔ-2018 ዐ.ል . . . #ኢንፋቅ_ሚዲያ #ኢንፋቅ

#ለኸሚሳችን 51 . . . ..............አፍሬ ነው ተው ጀሰዴ ተው እባክህ አታክስረኝ መንገድ ለቀህ። ተይኝ ነፍሴ ተይ አድቢ፣ መልስ የለሽም ከስራሽ ዘንድ ስትቀርቢ። ምናለበት ባትረክሺ ባታረክሽኝ፣ ቀና እንዳልኩኝ ይህ አንገቴን ባታስደፊኝ። ተይኝ ነፍሴ አትራመጅ ወደ ዞላም፣ ተወዳጅቶ ከክፉ ዘንድ ቀኝ አይሰላም፣ የሄደ ሰው በአባሙራ በሱ መንገድ፣ ሆኖል ትርፉ በፀፀት ደጅ በእሳት መንደድ። አፍሬ ነው እንጂ መዲና ማልመኝ፣ እንጂ መች ጠላሁት ከወዳአንቱ ብገኝ፣ ከወዳአንቱ ቀዬ ከአረንጓዴው ቁባ፣ መገኘት መች ጠላሁ ሆንኩ እንጂ ማረባ። አፍሬ ነው እንጂ በምግባሬ ማነስ በውድቅ ማንነቴ፣ እንጂማ መች ጠላ አንቱን ሰውነቴ። የሚያሳዝን ቢሆን የርምጃዬ ነገር፣ ቢያድፍ ሰውነቴ በአጉል ስደናገር፣ ማነሴ እያነሰ ከጭላጭ ስር ብናኝ፣ ማፈሬ በረታ ከአንቱ እርቄ ብገኝ። አፍሬ ነው ሆዴ አንቱ የኔ መውደድ፣ ስራዬ ከስራሁ እርቆ ቢንጋደድ፤ አስቀረኝ መሰለኝ የራሴው ስንክሳር፣ ላፍታ መጣ ብዬ ወዳአንቱ እንዳልሀድር። አፍሬ ነው አፍሬ ነው ቀና ማልል፣ አቀርቅሬ የቀረሁት ብጎዳድል፣ ብሞላማ የአንቱን ሱና ብራመደው፣ ባልተከዘ ሰውነቴም ባላፈረው። አንተ ሀጁ ተሳፋሪው ተመዲና፣ የሰራሁት ያረከሰኝ ያመፅኩበት ያሳነሰኝ ያደፍኩበት ዝቅ ያረገኝ እስኪሸሸኝ፤ ይህ አንገቴ እስኪቃና እስኪያነሳኝ፣ ለወዳጄ ሰላምታዬን አድርስልኝ። ሶሊ ወሰሊሙ ዳኢመን በጠና፣ ተኩለው በመጡት በኑሮቹ ዋና፣ በቤተሰብ ጓዶዎ ሰርክ በምልልስ፣ ሰለዋቱ ይንጎድ ሁለዜም እንደ አዲስ። ተፃፈ-በፈትሁዲን ዑመር 1447 ዐ.ሂ . . . #ኢንፋቅ_ሚዲያ #ኢንፋቅ

#ለኸሚሳችን 50 . . . --------------መሰናበቻው በመሰናበቻው በንግግራቸው፣ አላውቅም እያሉ ለሚመጣው አመት ለመገኘታቸው፣ የለም የሚመጣ መልዕክተኛ ሆላ፣ ህዝብም የለም የሚፈጠር ከዚህ ሌላ። በመሰናበቻው በሀጁ ስንብት፣ በሀጀተል ወዳዕ በሚንበሩ መልዕክት፣ እናንተ ሰዎች ሆይ ብለዋል በአደራ፣ ስለ ሰው ልጅ ክብር በነቢይ ተወራ። ደግሞም ከልክለዋል አራጣን በጠና፣ ስለ ሴቶች መብት አስፍረው በዋና፣ ተናግረው በቃላት ስለ ዲኑ መምላት፣ በእኩልነት ሰብከው ኑሩ አሉ በአንድነት። መስክሩልኝ ብለው ስለ መልዕክት መድረስ ለሶሀበታቸው፣ ቢሉ ያንን ጊዜ ሶሀባው በቃላት መሰከሩላቸው፣ ከዚያም የአላሁ መስክርልኝ ብለው፣ ቆጩ ምክራቸውን ሊሄዱ ጠቅልለው። መቼም ያማል ይሄ ወጉ ላደመጠው፣ እንኳን በአካል በነበረው በሀደረው፣ በሌለው ሰው በዚያ ዘመን ባልተገኘው፣ ከአይኑ አፍስሶል ይኸ ኸበር የደረሰው። መዲናይቱ በቀን ፀሀይ ስትጨልም፣ ሀዘን ወርሷት ዞላም ከቧት ስትል እልም፣ ሶሀበቶች ክው ሲሉ ውስጥ ነዶ፣ ሰይፍ ሳቡ ያ ኡመር ማመን ገዶ። የሄዱ እለት የመዲናው የኑር አምባ፣ ሞላት ሀዘን ሂጃዚቱን እያደባ፣ ቀምቶ አዛን ቅላፄውን ውቡን ቃና፣ አባረረው ያንን ቢላል ከመዲና። በአንቱ መምጣት የተዋበው ያ ጎዳና፣ የሄዱ እለት ሀዘን ቃኘው እንደገና፣ የአንቱ መምጣት ከፍ ያረጋት መዲናይቱ፣ የሄዱ እለት ከብዷት ታዬ መፅናናቱ። ወዳጄዋ ምኞቴ ነው የጧት ማታ፣ መጎራበት ከአንቱ ቅጥር በዚያ ቦታ፣ የሞትኩ እለት ሲዘጋጋ ሙላው ሁላ፣ ወዳጅ ሁኑኝ አማላጄ ለእኔው መላ። ሶሊ ወሰሊሙ ዳኢመን አበዳ፣ በዚያ መልከ ውቡ በእኔው ሙሀመዳ፣ ይርከፍከፍ ዘላለም ይውረድ ያለ ፋታ፣ ይዋልልም ይዝነብ ያላንዳች ጋብታ።
ተፃፈ-በፈትሁዲን ኡመር 1447ዐ.ሂ_2018ዐ.ል
. . . #ኢንፋቅ_ሚዲያ #ኢንፋቅ

#ለኸሚሳችን 49 . . . .............-የምን ቅድስና . በውልደቴ ምድር በእኔ እትብት መርጊያ፣ ወዴት ልሂድ ጥዬ ምነው አጣህ ማያ። ቅድስት ናት አልከኝ አንተው አርክሰሀት በመጠጥ አረንቆ በአረቂ ገላሀት። ቅድስት ነሽ አልካት? የምን ቅድስና አንተው አርክለሀት ስሟን ጥለህ ሜዳ፣ ደሞ ትጋፋለህ እሷ ሙስሊም ወልዳ። በገዛ ሀገሬ ወዴት ልሂድ እኔ፣ ሞቼም የሄድኩ ቀን ወዴት ይረፍ ጎኔ፣ ምነው ለከት አጣ የጭካኔህ ወሰን፣ ቆሻሻ አስመሰልከኝ ቀብረህ እንደማዘን። የምን ቅድስና ለበድን ገላዬ አፈር ሆነህ ከልካይ፣ ቅድስት ነኝ ብትል አትሆንም የበላይ። ትውልድ ይወቅሰሀል በተራ በተራ፣ ዛሬ ወዲህ ሆነህ ለሰራሀው ስራ፣ ለሰራኸው በደል ለግፍህ አረንቋ፣ ነገ ይጠፋሀል መናገሪያ ቋንቋ። ዩሀንስ በዳግም በዘመን ሊደገም፣ ሲቃጣ እያዬሁት የማይሆን ሊቀለም፣ ለትውልድ ሊሻገር በብራና ሰፍሮ፣ ይኸው ተጎስሞል የበደል ከበሮ። አይበጅም ተመለስ ባለ ቅድስት ወጉ፣ ሙስሊም ጡሀራ ነው የስር ማዕረጉ። የምን ቅድስና ነጃሳ ታቅፎ፣ ራስ ማታለል ነው መጠጥ ተደግፎ። ይልቅ መቻቻልን ተክለህ ለትውልዱ፣ የመስጅዱ ቅያስ ተሰምሮ መንገዱ፣ ካስማው ተንሰራፍቶ ምሶሶው ተቃንቶ፣ አዛኑ ይሰማ ከህዋው ላይ ጎልቶ። አክሱም የጋራ ነች ልክ እንደ ሰመራ፣ አብላጫ እንኳ ቢሆን የእምነቱ ጎራ፣ መቻቻል ነው እንጂ የሚበጀው ለሰው፣ መቻል ለቅፅበት ነው ኖሪ እስከሚመረው። የምን ቅድስና ሽፍንፍኑን ገላ ይገለጥ እያሉ፣ እረክሰው ሊያረክሷት ወዲያ እያገለሉ። ቅድስት ነኝ አሉ!? አዛን ሳይሰማ መስጅድ ሳይሰራ፣ የመቃብር ቦታው ካሬው ሳይመራ፣ የሂጃቧ መብት በውል ሳይጣራ፣ ቅድስት ነኝ ማለት ሁኖል ለእኔ ተራ። . .
ተፃፈ-በፈትሁዲን ዑመር 1447ዐ.ሂ
. . . #ኢንፋቅ_ሚዲያ #ኢንፋቅ

#ለኸሚሳችን 48 . . . '''''''''''''''''''''''''''''-ሳይሰዬም መብረር መሄድ ልብ አያርፍም፣ መዲና ስር ሳይሰየም። ሳይሰየም ከአጥሩ ቅጥር አረፍ ብሎ፣ እንዴት ይርጋ የወዳጅ ልብ አዘንብሎ። ተጀሰዱ ባይገኝም ባህር ማዶ፣ የእግር ኮቴው ባይራመድ መዳፍ ሰዶ፣ አረፍ ባይል ከአንቱ አውራጃ ተቀምጦ፣ መናቡ ግን ሁሌ እዛ ነው አንቱን መርጦ። ሀቢበሏህ የአላህ ወዳጅ የእኔ አማላጅ፣ ከቶ ምነው እንዲህ መራቅ እስከምፈጅ። ምነው መቅረት ለጠባቂ ማርፈድዎ፣ ታዩት እንጂ ከስቶ አለቀ አንቱን ብሎዎ። አጉድዬ አማናዎን ስጠለፍ በወንጀል፣ ትላንት ደህና ሆኜ ዛሬ ደግሞ ስቀል፣ ስወድቅ ስነሳ ተው ባሉኝ ስራመድ፣ ሀፍረት ብቻ ሆነ መገን የኔስ መንገድ። ትቼዎት አልሄድም በእርግጥ አንቱን ጥዬ፣ በውድቀቴ ማግስት እላለሁ ነብዬ። ከሄድኩማ ጥዬሁ ስምሁን ወዲያ ብዬ፣ እኔው ነኝ የምከስር እኔው ነኝ አንቱዬ። አንቱማ ሙሉ ነሁ ማን መቶ ማን ቀርቶ፣ ካሚል መልከ ውቡ ከዩሱፉ ጎልቶ፣ ለእኔው እንጂ ክስረት ለራኩት ከሱና፣ አንቱማ አንቱ ነሁ መሙላትሁ የፀና። ሶሉ አለ ነቢይ በእኒያ በተኳሉት፣ መኳለዎ ቀድሞ በውልደት ባማሩት፣ በወዳጅ ቤተሰብ በሙላው ጠቅላላ። ይርከፍከፍ ሰለዋት በሊሳኑ ሁላ።
ተፃፈ-በፈትሁዲን ኡመር 1447ዐ.ሂ
. . . #ኢንፋቅ_ሚዲያ #ኢንፋቅ

#ለኸሚሳችን 47 . . . .............አላህ አሶድዶት . መህሉቁ ቢንጋጋ ካለፈም ከመጣው፣ በእኔም ኡምር ክርሚያ ስሄድ በሚመጣው፣ አምሳያሁ ላይገኝ በመልክም ባህሪ፣ አላህ አስወድዶት ሆነሆል ዘውታሪ። ወረቢ ለም ተሊድ ኒሳዕ በጠቅላላ፣ እንደ አሚናቱ ልጅ  እንደ ከውኑ መላ፣ የተዋጠን እንባ ገንፍሎ ሚያፈሰው፣ የአንቱ ፍቅር እንጅ አይደል የሌላ ሰው። አላህ አስዎድዶት ከቶ ማን ሊጠላሁ፣ ልጥላም ላለ ዞላም ኑር ነበረ ገላሁ፣ እንደከሳው ሰውባን እንደ ቢላል ስደት፣ ግንድንም እንሰሳ ሆኖል ጣር መለዬት። አቡበከር ሲዲቅ ከረሱል ሲሄዱ፣ ከፊት ከሆላቸው ቀኝ ግራ ሲርዱ፣ ፍቅር ግልቶ ሲታይ ከዋሻ እስኪደርሱ፣ ለነፍስም አልነበር ሆዱ መላወሱ። ታዲያ ከዋሻው ደጅ የደረሱ ጊዜ፣ ቀድሜ እስኪ ልየው ልዝለቅ ቆይ አንደዜ፣ ጎጅም ልጉዳ ካለ ቀድሞ እኔኑ ይጉዳ፤ ሀላቸው ነበረ እኔው ልሁን ፊዳ። ዘልቀው ከዋሻው ጋር ልብስዎትን ቀደው፣ ጉራንጉር ቀዳዳን ሁሉንም ሸፍነው፣ ለአንዲቱ ቢያጡላት መሸፈኛ ቅዳጅ፣ በግርዎ ዘጉና ገደም አሉ ወዳጅ። ታዲያ ጉድ ልንገርህ ስማኝ ደህኔ ላፍታ፣ የመውደድን ነገር የፍቅርን ከፍታ፣ ብትዘልቅ በግር መርዝ እባብ አውጥታ፣ ቻሉት ያ ሲዲቁ እስከ እንባ ጠብታ። በጉንጭዎ ዘልቃ ብትፈስ እንባይቱ፣ ነቁ ከተኙበት ያአለሙ ራህመቱ፣ የወዳጅን ገላ በሰበብ እበሳ፣ አሻሩት ሀኪሙ ህመሙም ተነሳ። አላህ አስዎድዶት በግዑዝ አቅለኛ፣ ለመግለፅ ተሳነው ስንቱ ብዕረኛ፣ እንደዘቡራ ልጅ ባይጠናም ብዕሬ፣ ላውሳሁ እንደ ቀድርበቀለም መትሬ። አላህ አሶዎድዶት ሊሳደብ የመጣው የቅኔ ዘራፊ፣ አወዳሽሁ ሆኖ ሆነ ተሰላፊ። አላህ አስዎድዶት በሚያምረው ፀባይሁ በዚያ በኑር ገላ፣ አለሙን ኳኳሉት እርቅ አለ የተጣላ። ሰለዋት ቀን ለይሉን ይዝነብ ያለ ፋታ፣ በኔው በአላህ ወዳጅ  በእኔው ድርሻ ፋንታ፣ በቤተሰብ ጎዶ በሙላው ሰርክ ይዞ፣ ይውረድ ዘላለሙን ሁለዜ ተጉዞ።
በፈትሁዲን ዑመር 1447ዐ.ሂ/2018ዐ.ል
. . . #ኢንፋቅ_ሚዲያ #ኢንፋቅ

ኑ አብረን በኸይር ስራ እንዋል! . ነገ #እሁድ_ጠዋት ከ2:00 ጀምሮ በኢንፋቅ የዚያራ ዘርፍ የተዘጋጀ የ #ልብስ_አጠባ በመርከዝ ዳረል አርቀም (ፔፕሲ) ስለሚኖር እርሶም የዚህ ኸይር ስራ አካል በ
ኑ አብረን በኸይር ስራ እንዋል! . ነገ #እሁድ_ጠዋት ከ2:00 ጀምሮ በኢንፋቅ የዚያራ ዘርፍ የተዘጋጀ የ #ልብስ_አጠባ በመርከዝ ዳረል አርቀም (ፔፕሲ) ስለሚኖር እርሶም የዚህ ኸይር ስራ አካል በመሆን የአጅር ተካፋይ ይሁኑ። . ኑ አብረን በኸይር ስራ እንዋል! . #ኢንፋቅ_ዚያራ #መልካም_ቀን

#አስቤዛ_ዚያራ . አሰላሙ አለይኩም ዛሬ ቅዳሜ ከሰአት 10:30 ጀምሮ አስቤዛ ዚያራ ስለምናደርግ መሳተፍ የምትፈልጉ ፒያሳ ሰይድ ያሲን ህንጻ 5ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 516 ይምጡ ወይም ከታች ባለው ስ
#አስቤዛ_ዚያራ . አሰላሙ አለይኩም ዛሬ ቅዳሜ ከሰአት 10:30 ጀምሮ አስቤዛ ዚያራ ስለምናደርግ መሳተፍ የምትፈልጉ ፒያሳ ሰይድ ያሲን ህንጻ 5ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 516 ይምጡ ወይም ከታች ባለው ስልክ ቁጥር ይደውሉ :- . 0973429397 . #አስቤዛ_ዚያራ #ቅዳሜ #ኢንፋቅ

#ለኸሚሳችን 46 . . . ...........ፍቅርዎት . አይሄድም እርቆ አይረሳም ጭራሽ፣ ወዳጁን አይንቅም ለቅፅበት ቢበላሽ፣ ያደፈን ማንነት የደበሰን ገላ፣ ገፍትሮም አልጣለ ደግፎል በመላ። ምን በአደፍ ብቀርብ በጥላሸት ገፄ፣ አንገት ቢያስደፋኝም የሚያስቆጭ አመፄ፣ ግና ሄጄ አልቀርም ከስምሁ ቆርጬ፣ መለስ እለዋለሁ ከቀለሜ እሩጬ። ሄዶ የቀረ ነው ከስሮ የከሰረ፣ ላተቅነጡ ብሎ እየተናገረ። ግና ትልቅ ወዶ ስለምን ይረከስ፣ ነፍስ ማስታወስ ነው ከማነስ እንዳታንስ። ወዳጄ ፍቅርዎት ምርኩዝ ነው ለልቤ፣ ወርቆ እንዳይረሳ ጠፍቶብኝ አዳቤ፣ የአንቱን ቀለም ይዤ ይመር እንጂ መልኬ፣ ያለዚያስ ቀረሁኝ በአጥፊ ተማርኬ። አዎ ስምሁ ይጠብቃል ካጉል መንገድ፣ የአንቱ ወዳጅ በኑር ኑር ነው የሚራመድ፣ እንደምን ነሁ ታዲያ ውዱ ያ ሙሀመድ፣ ይሄው አለሁ ናፍቆት ይዞኝ ስነክር መድ። ሀገርሁ እሩቅ ነው ባህር አለውና፣ ሀበሻ ላይ ቀረሁ ናፍቆቴ እንደጠና፣ እዘይርሆለሁ የቀና እንደሁ መንገድ፣ ቀርቤ ልሆለሁ እንዴት ነሁ ሙሀመድ። ዘይንዬ ደጉዬ ፀባዬ መልካሙ፣ ያላወቀሁ ከስሮል ወሮቶል ዞላሙ። ልቅና በወደደሁ በሱናሁ በዋለው፣ መውደድ በመከተል አንቱን በመሰለው። ፍቅርዎት አዋቶል እንደ እንደ አፍቃሪ ለይላ፣ ኡምርን መጨለጥ ነው አመንምኖ ገላ፣ እንዴት እንሁነው ቀርተን ተሀበሻ፣ ጉንጫችን መሰለው የቦይ ማፋሰሻ። ረሺ እንደረሳ አውሽም እንዳወሳ፣ በሁለቱም ቁጥር አደዱ ሳይሳሳ፣ ይውረድ ሰለዋቱ በሊሳኑ ሁላ፣ ገሌ ገሌ ሳንል በሙላው ጠቅላላ።
ተፃፈ-በፈትሁዲን ዑመር ሸዋል/1447ዐ.ሂ
. . . #ኢንፋቅ_ሚዲያ #ኢንፋቅ

#ለኸሚሳችን 45 . . . ...........የውዴታ ነገር . . ሰውባንን አክስቶት አደብዝዞት ታይቶ፣ መዲናን አስትቶ ቢላልን አዝምቶ፣ ደግሞ ግመሊቱን አይኖቾን ዘጋግቶ፣ ከሞት አደረሳት ውዴታሁ ማን ትቶ። ሰው አይለይ ከጉዕዝ ይዞ ያስለቀሰ፣ ለአጀብ እየጠና መግለፁ እያነሰ፣ የውዴታ ነገር ከእንቅልፉ ቀስቅሶ፣ ጦይባ ላይ መለሰው ቢላልን አስሶ። መገን ይሄ ቢላል ዚያራ መቶበት፣ በመናብ ከአይኑ ላይ ጥሪ ተወስቶበት፣ በእንባ እየዳከረ በናፍቆት አለንጋ፣ ሻምን ለቆ ሄደ ማልዶ ሌት ሲነጋ። ለትዝታ ቢርቅ ሸሽቶ ወዲያ ማዶ፣ ግና ግን ተጠራ ውዴታ ስር ሰዶ፣ ታዲያ ያያት ለታ ውቢቱን መዲና፣ አዝና ነው ያገኛት ለብቻ መንና። እንዴቱን አታዝን እንዴት ትሁን ደህና፣ ትተዋት ኮብልለው የውበቶ ፋና፣ ታዲያ ቢላል ሲታይ መቶ ሙነወራ፣ ጥያቄ መጣበት በል በአዛን ተጠራ። እንቢ ማለት ቢከብድ ሊሞክር ተነሳ፣ ግን ሙሀመድ ብሎ እንዴት ይጨርሳ፣ አቆርጦት ወደቀ እንባ ሆኖ ፊቱ፣ መዲናም የዛን ለት አዘነች በብርቱ። አሪህና የሚሉት ነቢይ የሉምና፣ ቢላል ሀዘን ወርሶት ሚም በእሱ ላይ ጠና፣ መርሀባ ቢል እንኳን የልጅ ልጅን አይቶ፣ ግና ተረታ አሉ የወዳጅ ፊት አቶ። የውዴታ ነገር እንዴቱን ይቻላል፣ ለአንዳንዱ እየጠና ለአንዳንዱ ይቀላል፣ አንዳንዱን ሲያሳዝን አንዳንዱን ሲያባባ፣ ሺ አራት አልፎ መቶም ፍቅርሁ መድ አስነባ። ለምን ትፈርዳለህ አይተህ በምልከታ፣ ሰው ግመልን ሳይል ግዑዝ ሲያንገላታ፣ የውዴታ ነገር የሳበ ለት ቃታ፣ አንተንም አይምርም ልብ ነው ሚመታ። ሶለዋት ቀን ለይል በሊሳኑ ሁላ፣ ይውረድብሁ ውዱ ሳይዘው ከለላ፣ ከደመና በዝቶ በዝናብ ጠብታ፣ በአንቱ ወዳጅ ዘመድ ይንጎድ ጠዋትም ማታ። 1447ዐ.ሂ ተፃፈ-በፈትሁዲን ዑመር . . . #ኢንፋቅ_ሚዲያ #ኢንፋቅ

(የቀጠለ...) . . . ያልሞተ ወጣት ያረጃል። እርጅና ሰፊ የጥሞና ጊዜ ነው። በልጅነት ያሳለፉትን ጨዋታ እያሰቡ በትዝታ የሚፈገገበት፣ በታዳጊነት የነበረን የሰላ ጭንቅላት፣ በወጣትነት የነበረን የጠነከረ ጉልበት እያነሱ <ወይኒቷ የእገሌ ልጅ! የዛሬውን አያድርገውና> እያሉ የሚብከነከኑበት ዘመን ነው ይኼኛው። እርጅና የ<Your battery is getting low> ዘመን ነው። ጊዜያችንም፣ ጉልበታችንም፣ ትውስታችንም የገዛ አካላቶቻችን ሳይቀሩ እስኪበቃህ ተጠቀምከኝ ብለው የሚከዱብን ዘመን ነው። ፈቅ ስንል ሞት ነው ያለው። ወቅቱን ያልጠበቀ ሞት ሳይነካን አላህ ወፍቆን ካረጀን ዱንያ ላይ የሚቀረን ብቸኛው ዕጣ ሞት ነው። በዚህኛው ዘመናችን የመጣ ረመዳን እንኳን ልንጠቀምበት ልንጾመውም ይከብደናል። ሸሪዓውም አግራርቶልናልና ምስኪኖችን እናበላበት እንደሆን እንጅ የወጣትነት ጉልበታችን ዳግም አይገኝም። ግን አሁንም ቢጠይቁን <እንደው አላህ ለከርሞ ቢያደርሰኝና እቺን እግሬን የያዘኝን፣ ጨጓራየን የሚያስቸግረኝን፣ ደምግፊቴ፣ ስኳሬ እና ቀኝ ታፋየን የመታኝ ንፋስ ቢተወኝ ኢንሻአላህ ቀጣዩን ረመዷን በደምብ እጠቀምበታለሁ ነው መልሳችን። ጣፋጩ ዘመናችሁ ላይ የምትገኙ ህጻናት ሆይ! ይህኛው ረመዳን ልክ እንደአዲስ ልሙጥ ወረቀት ከእነየዋህነታችሁና ፍልቅልቅታችሁ የምትገናኙት ብቸኛው ረመዷኗችሁ ነው። ጾም ግዴታ ያልሆነባት ነፍሳቸሁ ቀሪ ዘመኗን የምትራመድበትን መንገዷን የምትቀይስበት ዕድሏ ነው። ዛሬ ያልተለማመደችውን ጾም፣ ሶላት፣ ሶደቃ ከየትም አታመጣውም። ዛሬ ያልቀራችው ቁርዓን ነገ ከነአካቴው ትዝ አይላትም። ምናልባት ሞት ሳይቀድማት በደረሰችበት ቀጣዩ ረመዳንማ ልጅነት ይደበዝዛል። ከባባድ ሀላፊነቶች ይጫኗት ይጀምራሉ። ለቀሪ ዘመናችሁ የምትዘጋጁበት፣ ጊዜያችሁን በመማር ብቻ የምትጨርሱበት ረዥም ጊዜ ይመጣል። ያላችሁ ረመዷን ቀጣዩ አይደለም፤ ይኽኛው እንጅ! እናንተ ለእውነተኛው መራር የህይወት ትግል የምትዘጋጁ ታዳጊዎች ሆይ! ይህኛው ረመዳን ብዙ ሀላፊነቶች ከጫንቃችሁ ላይ ሳይጫኑባችሁ የምታገኙት ረመዷን ነው። ጉልበታችሁ እንደጠነከረ፣ አዕምሯችሁ እንደሰላ፣ ቀልባችሁ ለመስተካከል እንደገራች የምታገኙት ረመዷን ነው። ምናልባት ሞት ሳይቀድማቹህ በደረሰችሁበት ቀጣዩ ረመዷንማ ሀላፊነቶች ይደራረባሉ። ቁርዓንን ለመሐፈዝ፣ ለቂርዓት፣ እስከወዲያኛው ዓለም ህይወታችንን የሚያስተካክሉልንን ጠቃሚ ልማዶችን ለመገንባት ጊዜውም ትኩረቱም የማይኖርበት ዘመን ይመጣል። ያላችሁ ረመዷን ይህኛው እንጅ ቀጣዩ አይደለም። እናንተ ህይወታቸሁን መባዘን የመላው አሁንም ለአኼራ ለመትጋት ረዥም የመቶበቻ እድሜ ያላችሁ የሚመስላችሁ ወጣቶች ሆይ! ይህኛው ረመዳን ረዣዥም ሌሊቶችን መቆም የምትችሉበት፣ ያለምንም መቸገር ጾም የሚገራላችሁ፣ ከሌሎች ምንም ሳትጠብቁ ያላችሁን የምትቸሩበት ብቸኛው ረመዷናችሁ ነው። ስለስራ፣ ስለቤተሰብ፣ ስለስኬቶች እንደምታቅዱት ሁሉ ለአኼራችሁም በሰፊው ማቀድ የምትችሉበት ረመዳኗችሁ ነው። ምናልባት ሞት ሳይቀድማችሁ በደረሰባችሁበት ቀጣዩ ረመዳንማ ጉልበቶች ይዝላሉ፤ ተስፋዎችም ይጨልማሉ። ላለፉት ጊዜያት ተብከንክኖ ከመቆጨት ውጭ ያቃጠሉትን ጊዜ የሚክሱበት ወኔውም፣ አቅሙም፣ ቀሪ ሰፊ ዕድሜም የማይኖርበት ዕድሜ ነው የሚጠብቃችሁ። ያላችሁ ረመዷን ይህኛው እንጅ ቀጣዩ አይደለም። እናንተ የዕድሜ ባለጸጎች ሆይ! ይህኛው ረመዳን ካሁን በኋላ ልታገኟቸው ከምትችሏቸው ረመዷኖች ሁሉ በተሻለ በትንሹ ዕድሜያችሁ የምታገኙት ነው። ዕድሜ እንደኩንታል ተጭኖ ይብስኑ ያጎብጣል፣ ይባስኑ አቅምን ይነሳል እንጅ ጉብዝናን አይጨምርም። ምናልባት ያለፉት ረመዷኖች ይህንኛውን ረመዳን በመጠበቅ ውስጥ ይሆናል የባከኑት። አሁን ግን ጉልበታችሁ ደክሟል፣ ሰውነታችሁ አልታዘዛችሁ ብሏል፣ አቅማችሁን ነስቷችኋል፤ ቢሆንም ከነገው የተሻለ ጠንካሮች ናችሁ። ነገ መኖሩ ቃል የተገባለት ባይኖርም ምናልባት ሞት ሳይቀድማችሁ በደረሳችሁበት ቀጣዩ ረመዳንማ እርጅና ይበልጥ ይጫጫናቹሀል፣ ሌሎችን ማገዛችሁ ቀርቶ ለራሳችሁም አጋዥ ያስፈልጋቹሀል፣ የበለጠ ይደክማቹሀል፣ ሰውነታችሁም የበለጠ ይከዳቹሀል። ያላችሁ ረመዷን ይህኛው እንጅ ቀጣዩ አይደለም። አንቺ ነፍሴ ሆይ፤ የምርም ከረመዷን በረከቶች የምትጠቀሚው መቼ ነው? ያ በተስፋዎችሽና ህልሞችሽ ውስጥ ቀልጦ በሚቀረው ቀጣዩ ረመዷን፣ ወይስ ከደጅሽ ቆሞ በርሽን በሚያንኳኳው ያሁኑ ረመዷን? ዛሬ ነገ ማለት ከሸይጧን መሳሪያዎች አንዱ ነው። ከሞት አፋፍ ደርሰን በእጃችን ላይ አንድም ነገ እስካልቀረን ድረስ ሁሌም ነገ! ነገ! ነው የሚለን። አሁን ግን የጀነት በሮች የሚከፈቱበት፣ ለተውበትና ለለውጥ.... ነገሮች የተመቻቹበት ይህኛው ረመዷን በእጃችን ላይ ነው። አሁን ካልሆነ መቼ? በዚህኛው ረመዳን ካልሆነ በየትኛው? . . . #ኢንፋቅ_ሚዲያ #ኢንፋቅ

#ለኸሚሳችን 44 . . . ያለን ብቸኛ ረመዷን ይህኛው ብቻ ነው! (የለያሊ ኢንፋቅ መድረክ ዘጠኝ <የሂላል ምሽቶች 2፤ ለኔ ነው> ላይ የቀረበ ጽሑፍ) ጊዜ ሲጓዝ ልክ እንደሂላሏ ነው፤ በዝምታና በዝግታ። ለአፍታንኳ ለማናችንም አይቆምልንም። ቆርኪ ደርድረን የወረወርነው ተምች ገና አየር ላይ እንዳለ ነው፤ <ጨዋታው ፈርሷል ዳቦው ተቆርሷል ከእንግዲህ አደግክ የምን መራገጥ ነው> የተባልነው። ያቸፈቸፈ ጢማችን በቅጡ ሳያድግ ነው፤ ተው ሽበቱን አትንቀለው ይበዛል ያሉን። ሉጫ ጸጉራችንን በመስታወት አይተን ማበጠሪያችንን ከጭንቅላታችን ላይ ስናስቀምጥ ነው ከመላጣችን ጋ የተፋጠጥነው። ጊዜ በዝግታ ይጓዝ እንጅ 4, 5 ዙር አጥፎን ሄዷል። ስንሮጥ ኖረን... ደክመናል፣ ዝለናል። ከሩጫችን ላፍታ አስቆመው <ምነው መጣደፋችሁ?> ቢሉን መልስ የለንም። ነገን እንጓጓለን። አሁንም <ነገ ምናለ?> ቢሉን መልስ የለንም። በዚህ ሁሉ መሀል ረመዷን ቀኑን ጠብቆ እንደሚገኝ እንግዳ ይመጣል፤ ይሄዳል። ሁሌም ሲመላለስ ታላቅ ወር ነው፤ ሸይጣኖች የሚታሰሩበት፣ የጀሀነብ በሮች ተዘግተው የጀነት በሮች የሚከፈቱበት። እኛ ግን አምና እንዳገኘን ሆነን አንጠብቀውም። አንዳንዶቻችን ከደጃፉ የምንደርሰው ከነወጣትነት ጉልበታቸን ይሆናል። አንዳንዶቻችን እድሜ ተጭኖን ከአምናው ዝለንና ተዳክመን ይሆናል። ሌሎቻችን ደግሞ ጭራሽኑ ረመዳንን ድጋሚ ላናይ ከዱንያ ተሰናብተንም ይሆናል። የሂላል ምሽቶች በውብ ብርሃን የደመቁበት፣ የሚጠበሰው አሳምቡሳ ሽታ ቤታችንን ሞልቶት ያገኝንበት። ትናንሽ ዓይኖቻችን በደስታ የተንቦገቦጉበት፣ ትንንሽ እጆቻችን በወላጆቻችን መዳፍ ውስጥ ገብተው ወደተራዊህ ያመራንበት፣ ምናልባትም የሶላቱን ግማሽ ወይ በእንቅልፍ ወይ በጨዋታ የጨረስንበት። ምሳ በልቶ የወዛ ከንፈራችንን ጾመኛ ነኝ እንልበት ዘንድ ሙልጭ አድርገን የታጠብንበት ዘመን ነበር። በልጅነታችን የረመዷን ግዝፈቱ ባይገባንም፤ ደስ የሚለው መንፈስ የሚጋባብን፣ የወሩን መምጣት የምንወድበት፤ ደጋግመን የምንናፍቀበትም ዘመን ነበር። ልጅነትኮ ደስ ይላል። ያኔ ዘመን በቀስታ እንደሚወርድ ዥረት ነበር። <አዛን ብሏል አፍጥሩ>  ለማለት የመግሪብን አዛን የተጠባበቅንባቸው ቅጽበታት በትላልቅ ሰዎች ልኬት በዓመታት የሚመነዘሩ ነበሩ። ግማሽ ቀን ጾመን እንኳ ልባችን ደጋግሞ ጾም የጎበኛት ያህል ትደሰት ነበር። በየአቅጣጫው የቁርኣን  ድምጾችን ስንሰማ እንፈነድቅ ነበር። ምናል ቶሎ ባደግን፤ የምርም ጾመኞች በሆንን፤ ጊዜያችን በቁርዓን ቢያልፍ፣ እንደትላልቅ ሰዎች ሚስበሀዎቻችንን እየሳብን ዚክር ብናደርግ... እንል ነበር ያኔ። ስንጠየቅ ኢንሻአላህ ትልቅ ስንሆን ኢንሻአላህ ቀጣዩ ረመዷን ነው መልሳችን። አልሞትንምና አደግን። ህጻንነትና ልጅነት የሚንናፈቅ እንጂ የሚኖሩት ዘመን መሆኑ ቀረ። ዘመን ናፋቂን ብቻ ይወልድ ይመስለኛል። ወይ በትዝታ ትናንትን ስንናፍቅ እንኖራለን። ወይ በተስፋ ነገን ስንናፍቅ እንኖራለን።  እንደዚያ የናፈቅነው ነገ ዛሬ ሆነና አደግን። የምርም ጾመኞች ልንሆን፣ ጊዜያችንን በቁርዓን ልናሳልፍ፣ ትልቅ ነንና እንደትላልቅ ሰዎች ሚስበሀዎቻችንን እየሳብን ዚክር ልናደርግ፤ ድንቄም! ማደግ የሚናፍቁት ሳይሆን ዘወር ብሎ ጣፋጩን ልጅነትን የሚያስተዝት የሚያስናፍቅ ጊዜ ነው። ብዙዎቻችን በዚህኛው ዘመናችን ተማሪዎች ነን። በእጃችን አንድ አምፖል እንኳ መፍጠር ሳንችል የእድሜያችንን አያሌ አመታት አምፖልን የፈጠረው ኤዲሰን እንደሆነ ለመማር የምንገብርበት ዘመን ነው። ጊዜ የለንም፣ የረመዷን አጋማሽ ላይ የሆነኛው ፈተና ይጀምራል፣ አሳይመንት ይበዛል። በጉጉት እንጠብቀው የነበረውን ረመዷን በእጃችን ስንይዘው በጣቶቻችን መሀከል ሾልኮ ይጠፋናል፤ ልክ እንደ አሸዋ። ስንጠየቅ ኢንሻአላህ ጊዜ ሲኖረን ኢንሻአላህ ቀጣዩ ረመዷን ነው መልሳችን። አሁንም አልሞትንምና እናድጋለን። ከታዳጊዎች ጎራ ወጥተን ወጣቶች እንሰኛለን። በዚህኛው ዘመናችን ልክ እንደልጅነታችን የወደቀ ሽምብራው ፈሰሰ አይባልለትም፤ ያፈሰሰውን ሽምብራ ይለቅማታል። ያለቀሰ ቱ በል ልምታልህ አይባልም። ሽመልህን አንሳና ችግርህን ራስህ ተጋፈጥ ነው የሚባለው። የዱንያን እሾሆች እየነቀሉ ማለፍ፤ ካልሆነም እየተወጉ አይንን ጨፍኖ ዝም ማለትን ይፈልጋል፤ ወጣትነት። እንደታዳጊነታችን በቤተሰብ ስር ሆነን ለህይወት የምንዘጋጅበት እድሜም አይደለም። ወጣትነት የምርም መኖር የምንጀምርበት እድሜ ነው። ለገንዘብ መልፋት፣ ለእውቀት መትጋት፣ ራስን ማሻሻል ላይ መስራት... ብዙ መባዘኖችን ይዞ ይመጣል። ከዚህ የዱኒያ ዛዛታ ሊያስመልጠን፤ ከራቅነው ጌታችን ጋ እስከቀሪ ዘመናችን ሊያወዳጀን ታላቁ የለውጥ ወር፤ ረመዷን ይመጣል። ግን ወጣትነት መባዘን ነው፤ ጊዜን ይነጥቃል። ከራስ ጊዜ ተቀንሶ ለቤተሰብ የሚሰደቅበት፣ ባል ሆኖ ለሚስቱና ለልጁ የተሻለ ኑሮ ወገቡን ጠበቅ አድርጎ ከጊዜ የሚፋለምበት ዘመን ነው። ገና ሰማዩ በንጋት ወጋገን ሳይቀልም በፊት... ላብና ትዕግስቱን ለቤተሰቡ ቀለብ ሲል ወደሚገብርባት አለም የሚቀላቀልበት ጊዜው ነው። ለርሷም ሚስት ሆና ለባሏና ልጇ የሞቀ ጎጆ ስትል ብዙ ነገሯን አሳልፋ የምትሰጥበት። በሚቦካ ሊጥ ውስጥ፣ በተጣደ ጀበና ውስጥ፣ ፈገግ ባሉ ልጆቿ ነጫጭ ጥርስ ውስጥ የኢባዳ ቅጽበታቶች በውልብታ የሚያልፉባት ዘመን ነው። እርሱ ሪዝቅ ሲያባርር እርሷ ቤቷን ስታሟሙቅ ላፍታ ጋብ ብለው ከረመዳን በረከቶች ጥቂት እኖኳ ዘግነው እንዳያልፉ ፋታ አይሰጣቸውም፤ ወጣትነት። ቤትና መኪና ለመግዛት፣ ኑሮን ለማሻሻል አያሌ አስር አመታት እንደነገሩ የሚከሰከሱበት፤ ሩቅ ባሰቡ ቁጥር ዛሬን የሚነጥቅ ዘመን። ወጣትነት ሁለት አማራጮች ነው ያሉት። ነገ ቀና እንድትል ዛሬን አቀርቅር ካልሆነ ዛሬን ቀና በልና ነገን ታቀረቅራታለህ ነው ምርጫው። ጊዜ የተትረፈረፈበትን፣ ሁሉም ነገር ከጨዋታ እንጅ ከቁምነገር የማይቆጠርበትን ዘመን... ትተን፣ ለቁምነገር የምንዘጋጅበትን፣ የምንማር-የምናውቅበትን ዘመን ትተን... ሁሉም ቁምነገር ተደርጎ ለአኼራችን ጊዜ የምናጣበት ወጣትነት ላይ ደርሰናል። ወጣትነት የብዛኔ ዘመን ብቻ አይደለም። ገና ረዥም ጊዜ እንዳለን፤ ህይወታችንን ገና አጣጥመን እንዳልጨረስነው የምናስብበትም ዘመን ነው። ሰዓታት በእንቶፈንቶ የሚያልፉበት፣ ጨዋታና ቀልዱ የሚበዛበትም ጊዜ ነው። ረመዷን መጥቶ ባለፈን ቁጥር ረዥም የተውበት እድሜ ረዥም ለአኼራ ብቻ የመትጊያ እድሜ ያለን ይመስለናል። ስንጠየቅ ኢንሻአላህ ነገሮች ሲስተካከሉልኝ፣ ስራ እንዳሁኑ ባያጨናንቀኝ... ደግሞም ይህችን ደግማ የማትገኝ እድሜ ዘና ልበልባትና ኢንሻአላህ ቀጣዩ ረመዷን ነው መልሳችን።

#ረመዳን_9 . አላህ ይቀናል... . ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ “አላህ ይቀናል! አላህ የሚቀናው አንድ ሙእሚን ሐራም የተደረገበትን ነገር ሲሰራ ነው።” . #መልካም_ረመዳን #ኢንፋቅ
#ረመዳን_9 . አላህ ይቀናል... . ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ “አላህ ይቀናል! አላህ የሚቀናው አንድ ሙእሚን ሐራም የተደረገበትን ነገር  ሲሰራ ነው።” . #መልካም_ረመዳን #ኢንፋቅ

#ረመዳን_8 . ሪዝቅህ እንዲጨምር... . ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ “ሲሳዩ እንዲሰፋለት እና እድሜው እንዲረዝምለት የሚፈልግ ዝምድናውን ይቀጥል።” . #መልካም_ረመዳን #ኢንፋቅ
#ረመዳን_8 . ሪዝቅህ እንዲጨምር... . ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ “ሲሳዩ እንዲሰፋለት እና እድሜው እንዲረዝምለት የሚፈልግ ዝምድናውን ይቀጥል።” . #መልካም_ረመዳን #ኢንፋቅ

#ረመዳን_7 . በምናደርገዉ ጉዞ ሁሉ አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን። . "የእርሶ ትንሽ እጅ ለሌሎች ምርኩዝ ናት!" Visit us: www.charityinfaq.org . #ኢንፋቅ #ኢንፋቅ_ሚዲያ
#ረመዳን_7 . በምናደርገዉ ጉዞ ሁሉ አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን። . "የእርሶ ትንሽ እጅ ለሌሎች ምርኩዝ ናት!" Visit us: www.charityinfaq.org . #ኢንፋቅ #ኢንፋቅ_ሚዲያ #መልካም_ረመዳን

#ሸባቡ_ኢንፋቅ #የኢንፋቅ_ወጣቶች #እናመሰግናለን
+9
#ሸባቡ_ኢንፋቅ #የኢንፋቅ_ወጣቶች #እናመሰግናለን

#ሸባቡ_ኢንፋቅ #የኢንፋቅ_ወጣቶች . የኢንፋቅ ልማትና መረዳጃ ማህበር በየአመቱ በሚያደርገዉ የረመዷን አስቤዛ እደላ ከአመት አመት በትጋትና በቅንነት የእረፍት ቀኖቻችሁን ሰውታችሁ ደፋ ቀና ስትሉ ለ
+1
#ሸባቡ_ኢንፋቅ #የኢንፋቅ_ወጣቶች . የኢንፋቅ ልማትና መረዳጃ ማህበር በየአመቱ በሚያደርገዉ የረመዷን አስቤዛ እደላ ከአመት አመት በትጋትና በቅንነት የእረፍት ቀኖቻችሁን ሰውታችሁ ደፋ ቀና ስትሉ ለነበራችሁ አባላት አላህ ኸይር ስራችሁን ይቀበላችሁ። #እናመሰግናለን . . #ኢንፋቅ_ዚያራ

#ረመዳን_6 . አላህ ዘንድ ተወዳጅ ስራ! . ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ “አላህ ዘንድ ተወዳጅ ስራ ማለት በሙስሊም ወንድምህ ልብ ውስጥ ደስታን ማስገባት፣ ወይንም ከርሱ ያለበትን ጭንቅ ማስወገድ፣
#ረመዳን_6 . አላህ ዘንድ ተወዳጅ ስራ! . ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ “አላህ ዘንድ ተወዳጅ ስራ ማለት በሙስሊም ወንድምህ ልብ ውስጥ ደስታን ማስገባት፣ ወይንም ከርሱ ያለበትን ጭንቅ ማስወገድ፣ ወይንም ብድሩን መክፈል፣ ወይንም ረሀቡን ማባረር (ማስወገድ) ናቸው።” . #መልካም_ረመዳን #ኢንፋቅ