en
Feedback
የስንኝ ቋጠሮ

የስንኝ ቋጠሮ

Open in Telegram

የዚህ ቻናል ዋና አላማ የተለያዩ ወጣቶች የግጥም ችሎታቸውን የሚዳብሩበት እና የሚያወጡበት ቻናል ነው። ግጥሞችን ለመላክ @mogea ይጠቀሙ መልሰን ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል!!

Show more
2 046
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
3:00 Lay Wddrun Enjemralen

በተላኩልን ግጥሞች ዛሬ ማታ 3:00 ላይ ውድድሩን እንጀምራለን!! ተወዳዳሪዎች እስከ ምሽት 3:00 ድረስ ለጓደኞቻችሁ ሊንኩን በመላክ join እንዲያደርጉ የማድረግ ሃላፊነት አለባችሁ!! ሽልማቱ 👉 አንደኛ ለወጣ የ15 ብር ካርድ እና ለ አንድ ቀን በቻናሉ ላይ ፎቶውን እንለጥፋለን 👉ሁለተኛ ለወጣ የ 10 ብር ካርድ 👉ሶስተኛ ለሚወጣ 7 ብር ካርድ ልብ ይበሉ አንድ ተወዳዳሪ ለማሸነፍ 65 like ማምጣት አለበት!! መልካም እድል!!

እስካሁን አምስት ተወዳዳሪዎች በተሰጣቸው ርዕሰ ግጥሞቻቸውን ልከውልናል እናመሰግናለን ከዚህ በኋላ አንድ ተወዳዳሪ ብቻ ከላከልን ቀጥታ ወደ ውድድሩ እንሄዳለን!! @gitmv ሽልማቱ እንደቀድሞው MB አይደለም ከፍ ያለ ሽልማት ነው!! 65 like ቀድሞ ያመጣ ትወዳዳሪ ያሸንፋል!!

አራት ተወዳዳሪዎች ልከውልናል !!

እባካችሁ ተወዳዳሪዎች ግጥሞቻችሁን ላኩልን ጊዜ በሚል ርዕሰ እንድትፅፉ ማስታወቂያ ላይ ተለጥፎ ሶስት ሰዎች ብቻ ናቸው የላኩልን አሁንም እንጠብቃለን ስለዚህ ይህ የመጨረሻው ውድድር ነው

እስካሁን ድረስ ከዘጠኝ ተወዳዳሪዎች ሁለቱ ብቻ ናቸው ግጥም የላኩልን ስለዚህ ዛሬ ማወዳደር አልተቻለም!! ሌሎች ተወዳዳሪዎች ግጥሞቻቸውን እስኪልኩልን ድረስ እንጠብቃለን የላካችሁልን በትግስት ጠብቁን!! ቢያንስ ስድስት ተወዳዳሪዎች እስኪልኩልን እንጠብቃለን ምናልባት ፖስት የተደረገውን አላዩትም ይሆናል!!

ግጥሞቻችሁን የምትልኩበት እና አስተያየት መስጫ ሊንክ @mogea

ሰላም ይብዛላችሁ የቻናላችን አባሎች በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውን የ አምስተኛውን ዙር ውድድር ዛሬ ማታ እንጀምራለን!! ተወዳዳሪዎችቻችን 👉"ጊዜ"👈 በሚል ርዕሰ ከ አምስት ስንኝ ያልበለጠ ግጥም ፃፉ!! እና ላኩልኝ!! ላልሰሙ ተወዳዳሪዎች ሼር አድርጉላቸው!! ተወዳዳሪዎች ግጥማችሁን ልካችሁ ስታበቁ ውድድሩን እንጀምራለን!! ዛሬ ማታ እንጀምር 👍 ዛሬ ማታ ይቅርብን 👎

ከኔ ላ'ንተ ተለጉሟል አፌ ጽሞና አይሠለቸው ከሠው መደበቁ ብቸኝነቱ እንደው ለርሡም ህይወት ሆኗል ዝምታው ቅኔ ነው። አልናገርም እንጂ አልናገርም እንጂ እያየውህ ስቴድ የእንባ ጭጋግ አይኔን ክፉኛ ጋ'ርዶት ደብዝዞ እይታዬ ሰላንተ ስዋትት እንስፍስፏ ልቤ ገና በጨቅላ እድሜ ስላንተ ስትቃትት ማነው የተረዳኝ ማንስ ነው የገባው? ወዶ የማጣት ምስጢር ደርሶበት የጎዳው? ኧረ እኔስ አሞኛል አንተ እንዴት አርጎሀል? አፍቅሮ ማጣቱ አንተንስ ሠብሮሀል? ወይንስ እንደፊቱ ሠዎች እንደሚሉህ ሁሉንም እረስተህ ህይወት ጀምረሀል? ዝም ልበል እንጂ ዝም ልበል እንጂ ውስጤ እያረረ ተናግሮስ ማን ተርፏል ከናፍቆት ከሀዘን እሪ ባይ በከንቱ ያለቅጥ መብከንከን ትዝታን በጋሪ ታሪክን በፈረስ አያመላለሡ የሇሊት መኖር ነው ፍቅር እንደው ሡሡ። Mahlet melese, 2013E.C

እስካሁን ባሉ አራት ውድድሮች ከ አንድ እስከ ሶስት የወጡ ተወዳዳሪዎች ከታች ስማቸው ተዘርዝሯል፨ 1.Blue Fish 2.Gosaye Fike 3.Addis Kidan 4.Kal'ab Mesfin 5.Fisiha 6.Kassahun 7.Chernet 8.Abebaw 9.Halid በጣም ድንቅ ውድድር እያሳያችሁ የተወዳደራችሁ ተወዳዳሪዎች ነበራችሁ በጣም እናመሰግናለን!! አሁን ከላይ ስማችሁ የተጠቀሰ የግጥም ርዕስ እንሰጣችኋለን በዛ የግጥም ርዕስ ትወዳደራላችሁ!! ማንኛውም አስተያየት ጥያቄ ካላችሁ 👉 @mogea ላይ ላኩልን!!

sticker.webp0.16 KB

ተወዳዳሪዎችን ሸልመናቸዋል ከዚህ ቀጥሎ አምስተኛው ዙር ውድድር መቼ እንደሚጀምር እና እስካሁን ድረስ ከ አንድ እስከ ሶስት የወጡትን ተወዳዳሪዎች በማስታወቂያ እናሳውቃችዋለን የሚፅፉበትን የ ግጥም ርዕስ እንሰጣቸዋለን በዚህ መልኩ እናወዳድራለን!! @gitmv @gitmv @gitmv

አራተኛው ዙር ውድድር በድል ተጠናቀቀ !!!! 1⃣ በምን ልግለጽልሽ በ አበባው 2⃣ ፍቅር በ ቸርነት 3⃣ ትመጪያለሽ ብዬ በ ሃሊድ አሁን ከ አንድ እስከ ሶስት የወጣችሁ ተወዳዳሪዎች ስልካችሁን በውስጥ መስመር ላኩልን !! @gitmv @gitmv

//ትመጪያለሽ ብዬ// ትመጭያለሽ ብዬ አንዲው ተንጋልዬ ከ ትንሿልጋዬ አይኖቼን ካምፖሉ ሳልነቅል ተክዬ ተስፋንም ሰንቄ አንቺን ብጠብቅም ከሄድሽበት ቀረሽ እንዳልሽ እልም ድርግም ቻርጄም እያለቀ ባትሪ ሎው እያለ ነው አሁን ይሄን ግጥም በምን ልልከው ነው? .................................... @halid_o ነኝ ከ ቴሌግራም

እባክ አቤቱ ፈጣር ኃይልን አንቴ ስጠን ወድቀን እንዳንቀር ፊቅርህ ይደግፈን። ኃጥያትና በቀል እንደ ጀብድ ስቆጠር እዉነት እየጠፋ ሐሰት በእጅግ ስከብር። አንተ ተመልከተን ከዚህ በላይ ጠፍተን ከፊትህ ከአንተ ጋር ራሳችን ሰዉረን። የኖርንም መስሎን በክፍት ስንሰምጥ ላንወጣ ወደ ላይ እጃችንን ስንሰጥ። እኮ እየጠፍን ኔን አንቴ ተመልከተን ከዚህ አዘቅጥ ህወት ሰላም ከነፈገን። ሰዉ ከሰዉ ተቆጥሮ እንሰሳ ከሆነ ይሄዉ ወራት አልፎ ዓመት ተቆጠሬ። ጀግና ነን እያልን በእጅጉን ፎክረን እንኳን ለመጀገን ለመኖር ስያቅተን ላናሸንፍ ስንጥር ጥፋት ላሌማመን። ከዝንጀሮ መጣን ተብሎ ስነገር ከአፈር አበጅተ ቃልህም ስቀየር። ዛሬ ያ ልታመን ጥቅት ቀርቷልና ስራችን ስመራን በጥፋት ጎዳና። ያ እኮ ነዉ ያስባለን ከእንስሳ የመጣ ከጭቃማ ብሆን ከዛ ብንወጣ። እንድህ አንጨክንም እንድህ አናደርግም ብሄር እየለየን ሰዉን አንገልም። እባክህ ፈጣር አሁን ተመልከተን ትርጉሙ የገባዉ የ እዉነት ሰዉ አርገን። ✍essey

ንግስናየ ይቅር ዘውዴን ከራሴ ላይ ከእናቴ ከቀሙኝ መማሬ ለምን ነው እሷን ከነጠቁኝ ለይስሙላ ብቻ ሳያት እያፈርኩኝ ንግስናየ ይቅር ዘውዴን መልሱልኝ ልቤን ፍራች ፍራች ደርሶ እየተሰማው ከራሴ ስትወልቂ ልቤን ቅር ካለው ታዲያ እንዴት አድርጌ ልቤን ላሳምነው ልቤስ ንጉሥ ነበር በመላ አካላቴ ዘውዴ ስትወልቅ ደከመ ጉልበቴ ከነሐስ ከወርቁ ነበር ያሰራሗት ጊዜው አጉል ሆኖ ከራሴ አወለቅሗት ንግስናየን ትቼ ንግስቴ አደረግሗት ታዲያ ወንድሞች ምኑ ነው ጥፋቴ ከመንበር ወርጄ ባረግሗት ንግስቴ ዘመኑ ከፋ እና ከዙፋን ቢያወርደኝ የእኔ ነሽ የምላት ዘውዴም ከፋችብኝ ሽማግሌም ብልክ ራስህ ና አለችኝ ከዙፋኔ ጋራ ልቤንም ቀምታኝ ታዲያ እንዴት አድርጌ ከፊቷ እኔ ልገኝ አሁንም እላለሁ ንግስናየ ይቅር አንችን ለእኔ ካለሽ ልብሽ ካለው ፍቅር ኧረ ዘውዴን ዘውዴን የራስ አክሊሌን ያለሷ እኮ አያምርም ስጀምር ቀኔን ሰው ከማይፈትሸው ጥሩ ቦታ መርጠሽ ሌላ እንዳይገባበት በፓስወርድ ቆልፈሽ እባክሽ ክፈችው ሚስጥሩን ተናግረሽ ለእኔም አስቢልኝ ለእውነተኛ አፍቃሪሽ ስንቱ እየደረሰ ልቤን ቢያንኳኩትም ለመግባት አልቻሉም አልተገኘ ቁልፉም ቀን በውኔ ሳይሽ ሌሊት ደግሞ በህልሜ ስትዞሪብኝ አድረሽ ለፍርድ ፊትሽ ቆሜ ምን ይሆን ውሳኔሽ በፍቅርሽ ታምሜ ተይ አትጨክኝብኝ ልኑር አንችን ስሜ ከራሴ ላይ ወርደሽ በልቤ ተደፋሽ ሰው ከማይደርስበት ሰውር ቦታ መርጠሽ እኔ በአንች አልፈርድም ጊዜው ነው ያሰወደደሽ ከሰው ሁሉ መርጦ ንግስቴ አደረገሽ ካልጠፋ ቀለበት ካልጠፋ ጉትቻ ለምን አስወደደኝ እንደው ዘውዴን ብቻ

#እያፈቀርኩሽ ልጥላሽ ውስጤ ፍቅር ኖሮ የምር እየወደድኩሽ አይወደኝም እሱ እያሾፈብኝ ነው አልሽ ከራስሽም አልፎ ነገርሽው ለልብሽ በ አይወደኝም ግምት እራስሽን አሳመንሽ ፊትሽን አጥቁረሽ በፈጣሪ እየማልሽ አትወደኝም አንተ የውሸትህን ነው አልሽ እኔም ያንቺ ግምት ከሚሆን የውሸት እያፈቀርኩሽም ልለይሽ የእውነት በፈጣሪ ምለሽ አታፈቅረኝም ካልሽ ላንቺ እውነት ብዬ #እያፈቀርኩሽ ልጥላሽ 😔😔😔😔😔 join us 👉gitmv ✍@Abelaxu94 Code #4

መልክት አድርሱልኝ በሉ እስቲ ንገሯት ትመልሰው ልቤን እደቀልድ ሰጥቻት አጣሁ እኔነቴን እናንተኑ ሰምታ ቀልቤን ባትመልሰም አደራ ግን በሏት እዳጥይው የትም ደግሞ እደምትሏት :- ሲአፈቅረሽ ተጎድቶ መተው ቢጀምርም መናፈቅ ጀምሮ መርሳት ግን አልቻለም የሚወድሽ ልቤ መቼም አይረሳሽም ብሎሻል በሉልኝ ወይ እዛችኋት ኑ እኔ እነግራታለሁ ፍቅሬን በየቀኑ!! ጓደኞቼ! ግን ከሁሉም በፊት በኔ መወደዷን መገሷን ንገሯት ይህን ስትሰማ መግደርደሩ ቢአምራት ማነው ካለቻችሁ የጓጃሙ ፋኖ # ፍስሃ ነው በሏት ኧረ እንዲያውም ተውት እራሴ እሄዳለሁ የሆነውን ሁሉ እኔ እነግራታለሁ ላፍቅርሽ ነው እጂ ልማርክሽ አላልኳት ለምን እፈራለሁ ሁላችሁም ተውት እራሴ ልሄድ ነው ለትብብራችሁ በፍቅር አምላክ ስም አመሠግናለሁ!! ✍ፍስሃ join us 👉 gitmv Code #3

#ግጥመ-ቸርነት !!! ፍቅር ? !!! ፍቅር ፍቅር ፣ግን ፍቅር ምንድር ነው? ፍቅር የተባለ ስሙ የገነነ ቆይ እሱ ግንማነው? እራስን ቀንኖ ለሰው ገኖ መኖር በሞፈር አፈር ፊት በማነቆ ቀንበር ስለ ወንድም ስቃይ በሬ ሆኖ መኖር ሌሎች በገመዱት በጨካኞች ጅራፍ ስለ አዳም ቁስል ሲል ስለሱ መገረፍ ፍቅር ግን ምንድር ነው? የትልቅ ዋርካ ዛፍ የቅርንጫፍ ሲሳይ የታች ተሸካሚ የለት ምግብ አብሳይ ለዛፍ ፍሬ አበባ ለወንድም ምህዋሩ መሰረት ቁም ነገር የሚታይ ያይደለ ድብቅ ከታች ስሩ ፍቅር ግን ምንድር ነው? 📝በቸርነት ተፃፈ ከለታት በአንዱ 2013ዓ.ም Join Us 👉 @gitmv Code #2

በምን ልግለጽልሽ ድርሰቱን አንዳልደርስ........ ...... እንዴት ብዬ ልድረስ? በጥዑም ቃል ውበት አኔ አንችን ላወድስ!? ግጥም እንዳልሞነጭር በሰባራው ብዕሬ..... የት ሆኖልኝ ችዬ- ቃላት አንጠርጥሬ ቅኔም እንዳለዘርፍልሽ..... የት ሄጄ ተምሬ ቀለሙን ቆጥሬ? ምንም ስለማልችል ደግሞ .. ለመናገር ቃላትን ዘርዝሬ... ዝምታዬም ቃል ነው እንዲገባሽ ፍቅሬ💋 ❤️❤️❤️አቢ ያንችው ግዳይ❤️❤️❤️💋 Join us 👉 @gitmv Code #1