የስንኝ ቋጠሮ
Open in Telegram
የዚህ ቻናል ዋና አላማ የተለያዩ ወጣቶች የግጥም ችሎታቸውን የሚዳብሩበት እና የሚያወጡበት ቻናል ነው። ግጥሞችን ለመላክ @mogea ይጠቀሙ መልሰን ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል!!
Show more2 046
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
2 046
Ysfen:
እኔምን አገባኝ
ዘገንኩላት ቆሎ የሰጠችኝ እሷ
ምንም አልሰሰተች ጨክና ለራሷ
እኔ ምን አገባኝ...
ቀልቤንገፎት ያ ፈገግታ
ልቤን ገዝቶት ያ ዝምታ
እኔ ምን አገባኝ..
በፈገግታበዝምታ በአርምሞ ተከብቤ
ተለያይቶ ተጠፋፍቶ እጅግ እርቆ ከእኔልቤ
ሁኔታዎች ሲቀየሩ ዛሬ በትናንት ሲተካ
ፈልጌ ፈልጌ ያጣሁት ልቤን ሰርቀሽዋል ለካ፡፡
እኔ ምን አገባኝ...
በውበትሽተማርኮ ልቤ ጥሎኝ ከጠፋ
በዚህ በውሸት አለም ብርሀንዋ በጠፋ
""ፍቅርወዴት አለሽ""እያልኩ ጊዜዬን አላጥፋ።
እግዜሮ ከላይ ወርዶ ልብናኩላሊትን ሲመረምር
አንዱ ብቻውን እኔዘንድ እንዳይቀር
ወይ ልቤን መልሺልኝ
ወይ ኩላሊቴን ውሰጂልኝ።
እ
ኔ
ም
ን
አ
ገ
ባ
ኝ
፡፡
¥$f€n
@gitmv
@gitmv
2 046
✅ ሰላም ዉድ የጥበብ አፍቃሪያን ይህ ከላይ የምትመለከቷቸው እስራስ ✏️ ፣ እስክሪብቶ🖋 እና ወረቀት📃 ተገናኝተው የሰሩትን ጥበቦች ነው ።💯
✅ይህንንና ሌሎችም የስዕል(የጥበብ) ስራዎችን እኛ ጋር ያገኛሉ። የፈለጉትን ፎቶ ማሰራት ይችላሉ ይዘዙን በተመጣጣኝ ዋጋ እና በአጭር ግዜ ውስጥ ሰርተን እናስረክቦታለን። 🔹 ለስጦታ - ለሰርግ (weeding)
- ለምርቃት (graduation)
- ለልደት (Birthday)
ለተለያዩ ፕሮግራሞች አሪፍ አማራጭ!!!
🔶👇ከታች ያለውን ቻናል ይቀላቀሉ👇
t.me/beyaART
👉ይዘዙን @beyadani
ስልክ:- 0964037827📲
2 046
ሰላም የ ስንኝ ቋጠሮ አባሎች
በዚህ ቻናል ፖስት የሚደረጉ ግጥሞች ምንም አይነት ሃሳብ ሊኖራቸው ይችላል ነገር ግን ትኩረት የምናደርገው በግጥሙ የመልክት ይዘት ብቻ ሳይሆን በ ግጥሙ የ አፃፃፍ ስልት መሆኑን አውቃችሁ በተለይ ጥበብን ለማጉላት እንደሆነ በመረዳት ግጥሞችን እንድታነቡ በትህትና እናሳስባለን።
ስለዚህ እኔ ሃይማኖቴ ምንም ቢሆን ዘሬ ምንም ቢሆን አመለካከቴ ምንም ቢሆን በ ግጥም የየሚተላለፈውን ጥበብ ስለማደንቅ በጣም ከልክ ያለፈ ባህላችንን የማይወክል ነውር ነገር ካልሆነ በቀር ከ አባሎቻችን የሚላኩ ግጥሞችን እንደ ክህሎቱ ጉልበት ፖስት የምናደርግ መሆኑን እንድታውቁ ይሁን ለማለት እፈልጋለሁ!!
2 046
N@ti ኢthio:
እርግጡንልንገርሽ ~አፈቅርሻለሁኝ
ህልሜን እንዳዋይሽ ህልምሽን ንገሪኝ
ህልም እንደ ፈቺው ነው እባክሽ አትፍሪኝ
ብዬ ባልኩሽ ጊዜ ህልምሽን ብትነግሪኝ
እንደዚህ ፈታሁት እ'ህ" ብለሽ ስሚኝ ።
፡
ህልምሽን ስፈታው ትርጉሙ ይኸው ነው
መጣላት ለሚለው በፍቅር መውደቅ ነው
ዕንባ ማለት ደግሞ ደስታና ፌሽታ ነው
ፈልገሽ ማጣትሽ እኔን ማግኘትሽ ነው ።
፡
ህልምሽን ነግረሽኝ እኔም ፈታሁልሽ
ህልሜን ደግሞ ስሚኝ እታለም ልንገርሽ ?!
፡
በነጭፈረስ ላይ አንቺ ተቀምጠሽ
እኔ ስከተልሽ እርቀሽኝ ሳለሽ
ብጣራ አትሰሚኝ ሰግረሽ ትሄጃለሽ
ምንድነው ትርጉሙ ንገሪኝ አስልተሽ ።
ህልምሽን ነገርሽኝ ህልሜንም ነገርኩሽ
ህልም እንደ ፈቺው ነው እውን ይሁን አልኩሽ
ግን .......
ግንግን - እታለሜ .....?
ህልምተተርጉሞ ህይወት እንዲዘራ
ነይና ልቀፍሽ አዝመራው ይዘራ
እሸት ሳለሽ ልብላሽ
እሸት ሳለው ብይኝ
እርግጡን ልንገርሽ - አፈቅርሻለሁኝ
✍✍ N@ti ኢthio
2 046
N@ti ኢthio:
---ለሷምንም አይደል---
፡
ለሷ ምንም አይደል፣
ብቻዬን ማውራቱ አልፎም ጨርቄን መጣል፣
በፍቅሯ ወላፈን ብኖርም ስቃጠል፣
እራሴን ላጠፋ ከእንጨት ብንጠለጠል፣
ከቁብም አትቆጥረው ለሷ ምንም አይደል፣
፡
በእንባ ብታጠር ሳቄ ለቅሶ ሆኖ፣
ወዜ ቢገረጣ እንደ አንዳች ተኖ፣
ልቤ ቁስል ቢሆን ባያቅ እንኳ ድኖ፣
ቀልቤም እሷን ቢለኝ ባይተዋት ጨክኖ፣
ከደጇ ባልጠፋ ቤተስኪያኔ ሆኖ፣
፡
ለሷ ምንም አይደል፣
ብቻዬን ማውራቱ አልፎም ጨርቄን መጣል፣
፡
በፊደላት ክምር፣
ነድፊያት በብዕር፣
ልክ እንደ ዳዊቱ ስደግማትም ብኖር፣
እልፋትን ባነባት ገድሏንም ብናገር፣
በእለተ ቀኖቼ ሳልሰለች ብዘክር፣
አንድ ያለኝን ልቤን ለፍቅሯ ብገብር፣
፡
ለሷ ምንም አይደል፣
፡
ባልተዜመ ዜማ ባልተቃኘ ቅኝት፣
ባልመሸ ማለዳ ባልጨለመ ፅልመት፣
እሷኑ እያሰብኩ እሷን ባልምበት፣
፡
ለሷ ምንም አይደል፣
፡
የእንባዬ ዘለላ ከአይኔ ሚፈሰው፣
ወተት መሳይ ጥርሴ መሳቅን ባያውቀው፣
ለሷ ምንም አይደል ጠባሳስ ለራሴው፣
፡
እሷን ጠቅም መስሎኝ ስለሷ ብለፋ፣
ምንም አይመስላትም ብኖርም ስከፋ፣
፡
ጊዜያት ሳይገቡኝ አልፈውኝ ቢጓዙ፣
የህወቴ ፋኖስ ባይሞላም መቅረዙ፣
ለሷ ምንም አይደል የኔ ድንግዝግዙ፣
፡
ለኔ ባይሸልማት እንጂ ባልታደል፣
ይሄ ሁሉ ነገር እንዴት ምኗም አይደል?፣
፡
በጥበብናበፍቅር እንኑር
✍✍N@ti ኢthio
2 046
የሌሊቷ ብርሀን
ፀሐዪ ሲደክማት ብርሀኗን ሰጥታ
ስራዋን ጨርሳ ጨለማን አንግታ።
ልትሄድ ወደ ሌላ ብርሀን አውሳ
የሌሊቷ ብርሀን ብርታትን ተውሳ
ይኸው ትታያለች ሰማዩ ላይ ነግሳ።
የዛሬው ይለያል በጣም ተውባለች
ለጥምቀት ምትወጣ ኮረዳ መስላለች ።
በደማቅ ብርሀኗ ልብን ታሞቃለች
ላኮረፈው ሰማይ ፈገግታን ሰጥታለች ።
በኮከቦች ጥለት ባማረው ቀሚሷ
ፈጣሪ ሸምኖ ባዘጋጅው ልብሷ።
ሰማዩ አይበቃትም ምድር ጠባታለች
በውብ አስተያየቷ ታሽኮረምማለች።
በተመስጦ ሆኜ እያስተዋልኳት ነው
ሀሳብ ሲበዛብኝ እሷን ማዋየው።
የተረጋጋች ናት ጆሮ የታደለች
ያሰብኩትን ሀሳብ ቶሎ ትረዳለች።
ዝም ብላ ስታየኝ ዝም ብዬ ሳያት
የአምሮዬ ጭንቀት አንድ በአንድ ሲገባት። የሆዴን ስነግራት የሆዷን ስትነግረኝ
በልብ ስንግባባ ሳልዋሻት ሳትዋሸኝ።
የሌሊቷ ብርሀን ሁሌም ቢሆን ያው ናት ይሁን እንጂ አንዳንዴ ተቀጣረን ሳጣት።
ብዙ አስባለሁ እንዴት ቀጥራኝ ቀረች ባይመቻት እንጂ በሀሷቧ ካልዋለች።
በእኔማ አትጨክንም ከልብ አቃታለሁ የሌሊት ብርሃኔን የወሰዳት ማነው ?
ዞራ እስክትመጣ እጠብቃታለሁ
ምንም ያህል ብትቆይ እኔ በተስፋ አለሁ ስትመጣ ምላትን ነገር እያሰብኩኝ ፈገግ እላለሁ ። አንድ ቀን ብትቀርም ነገ ተስፋዬ ነው
ነገንም ብትደግም እጠብቃታለሁ።
@josiahfadfam
@josiahfadfam
@josiahfadfam
2 046
N@ti ኢthio:
====አልወለድም===
ተይ አልወለድም
ምድርን አልፈልግም,,,,
ተወለድአትበይኝ
በፈጠረሽ ስሚኝ,,
:
ለአኬልዳማመሬት
በደም ልቆሽሽ
ሰውን ላበላሽ
የስው ዋጋ ጠፍቶ
ብሔር ከሰው በልጦ
ባለሽባት ሀገር
ተወለድ እያልሽኝ
ስላሜን አትንሽኝ,,,,
,,,,,አዎ
መፈናቀልየለ መደብደብ በዱላ
መንገድ አይዘጋ ከስው አልጣላ
ሆድሽ ኢትዬጵያ ናት መኖሪያ አለሜ
በፍቅር የኖርኩት ከእህት ከወንድሜ
,,,ዛሬብቻሽን ነሽ አውቃለሁ እናቴ
ወንድሜም ተገሏል የለችም እህቴ,,,
:
ስለዚህእናቴ
ተወለድ አትበይኝ
በፈጠረሽ ስሚኝ
በቃ ልኑርበት ከሰው ሳልጣላ
ኢትዬጵያ ናት ሆድሽ አልፈልግም ሌላ::
:
ላቤንጠብ አድርጌ ምንም ሀብት ባፈራ
ልጆችንም ብወልድ ትልቅ ቤት ብሠራ
በእልልታም ብትድሪኝ በሆታ ጭፈራ
ባፍንጫየ ይውጣ ሁሉም ሲያምረኝ ይቅር
ነገ ልፈናቀል ከኖርኩበት ሠፈር
ዘልየ ጨፍሬ ካደኩባት ሀገር
:
ስለዚህእናቴ.......
ልክእንደ ኢትዬጵያ እኔ የምወዳት
ቅንጣትም ሳልፈራ የምቀመጥባት
ጦር,,ጎራዴሳንጃ ምንም የሌለባት
ደስታ የበዛባት ሠላም የሞላባት
ኢትዬጵያ ሆድሽ ናት ተይኝ ልኑርባት
:
ግን,,,
መፈናቀልቀርቶ
ስው መግደል አብቅቶ
የፈጣሪም መንበር
መቃጠሏ ሲቀር
ሁሉም ኢትዬጵያዊ በፈለገው ሀገር
እንደልቡ ሠርቶ እንደልቡ ሲዞር,,ሳይቀዱሽየምልሽ
የዛኔግን ጥሪኝ
ና ተወለድ በይኝ...
:
,,እውነትነው
አንዳች የማልዋሽሽ ...
ሀኪሞች
ምጥ ሳላበዛብሽ
በተፈጠርኩበት በቤታችን አልጋ
እወለዳለሁኝ ጨለማው ሲነጋ::
✍✍N@ti ኢthio
2 046
ለፈገግታ…
Ysfen:
ሱሪእና ቀሚስ
እግዜር ቸርነቱ መስጠት ሳያልቅበት
ሄዋንን ከፈላት ካንዲት ክፋይ አጥንት።
ካንተው ላንተው ሰራት እርሱ አበጃጅቶ
ያንተው ጎዶሎህን ባዶነትክን አይቶ።
ሞጌ ልጠይቅህ ትዝ ካለህ ያኔ
ቅጠል ነበር ልብስህ ነበር የሄዋኔ።
ሞጌ ልጠይቅህ ትዝ ካለህ ሙሴ
ህግናፅላቱ ያ ባህርከፋዩ የህዝብ-እንደራሴ
ሴቷ ቀሚስ ትልበስ ወንዱም ሱሪ ይልበስ
ብሎ ነበር ያኔ
ላዳመ-ሄዋኔ።
አሁን ያንን ትዕዛዝ ህዝቡ እየረሳ
መከራና ችግር በዛበት አበሳ።
እናልህ ሞግዬ ሴቶቹን ሰብስበህ እንደምትልልን
ቀሚስን ልበሱ ብለዋል በልልን
ሱሪ እንድንለብስ ለእኛ እንዲተውልን።
የሱሪዎችን መብት ካላከበራቹ
ቀሚሶች አለቁ ተለበሰላቹ!!!!
ይስፈን✍
@gitmv
@gitmv
2 046
አድዋ
ቢገባህ ወንድሜ ቢገባሽ እህቴ
ላንተ ላንቺ ሲል ነው የሞተው አባቴ
ይቺን ውድ ሀገር ቅኝ ሳያስገዛ
ህይወቴ እንድትሆን ያላት ጣዕም ለዛ
የከሳው ፊታችን ባባታችን አጥንት ይኸው ዛሬ ወዛ
ለአንድ ወረቀት ለአንድ ውጫሌ ውል
ለኢትዮጵያ የቆመ ስንት ህዝብ አለቀ ምንም ሳይወላውል
ይህን ግጥም ዛሬ በፊደሌ የፃፍኩት
ይህን ግጥም ዛሬ ከፊታችሁ ቆሜ ለናንተ ያነበብኩት
አድዋ በሞተው ነው ባባቴ አጥንት
የዜግነት ክብር በኢትዮጵያችን ፀንቶ
ብዬ ምዘምረው በእኔ አይደለም ከቶ
አዎ ባባቴ ነው ለኔ ብሎ ሞቶ
አንገቴን ሳልደፋ እንድሄድ ሳልፈራ ማንንም
እውነት ነው ምላችሁ አለ የአባቴ ደም
ተፈጥሮን ማደንቀው የዚችን ውብ ሀገር
በአብዲሳ አጋ ነው በባዩ አልበገር
አፄ ሚኒሊክም ጀግና ነው ሲበዛ
ለቃሉ ታማኝ ነው አለው እኮ ለዛ
በማርያም ብለህ የሰበሰብከው
ጊዮርጊስ ከፊት መንገድ አሳየው
አንተ ብትኖር ነው አሉላ አባ ነጋ
ጨልሞ ያልቀረው የኢትዮጵያ ደመና ይኸው ዛሬ ነጋ
እቴጌ ጣይቱ የሴት ጀግናይቱ
ጦሩን አሳምራ መራችው ከፊቱ
አፄ ዮሀንስም እንደተናገረው
ኢትዮጵያ ማለት
አንደኛ እናትህ ናት፣ የእናት ፍቅር
ሁለተኛ ክብርህ ናት፣ የዘውድ ክብር
ሶስተኛ ሚስትህ ናት፣ የሚስት ደግነት
አራተኛ ልጅህ ናት፣ የልጅ ደስታ ህይወት
አምስተኛ ደግሞ ያው መቃብርህ ናት ሲል እንደሰማነው
ፈፅሞ አልዋሸም ስትሞት ማረፊያህ ነው
ስለዚህ ወንድሜ ስለዚህ እህቴ
እንደው ልያዛችሁ በሞተው አባቴ
እርስ በእርሳችሁ ቃታ አትማዘዙ ያባቴ ይበቃል የሱ መች አነሰ
እሱም ወዶ አይደለም ባገሩ መጥተው ነው ደሙን ያፈሰሰ
ጦርነት ካማረህ ከወገን አይደለም
ሽጉጥ መማዘዝም ካገር ልጅ አይደለም
ይህ ካማረህ ደግሞ ቃታ ሚሳብበት መቼ ከአለም ጠፋ
ግብፅ እና አሜሪካም አለ እየደነፋ
ጉልበትን ማሳየት ወንድም ላይ አይደለም
ወንድ ነኝ ካልከኝም ሂዳ ግብፅን ግጠም
አለዚያማ ታዲያ መጋደል ከወንድም
ወንድነት አይደለም ጀግና አያስብልም
ስለዚህ እህቴ ደግሜ ልንገርሽ
ከሁሉ በፊትም ፀብ አይቅደምብሽ
ስለዚህ ወንድሜ ደግሜ ልንገርህ
በምንሽር ሳይሆን ይምበርከክ በፍቅርህ
ተፃፈ በ መስከረም በፍቃዱ
በ 14 / 06 / 13
@gitmv
@gitmv
2 046
የፈጣሪ ስራ🌍
እንከን የሌለበት የፈጣሪ ፍጥረት
ሰማይና ምድር በውስጧ ሚኖሩት
ውበት የሆኑት የሰማያት ድምቀት
ጨረቃና ፀሀይ እንዲሁም ከዋክብት
ባህርና ወንዞች ተራሮች ኮረብቶች
ልብን ሚማርኩ የአምላክ በረከቶች
ማዕበል ነፋሱ የሚታዘዙለት
ይሁን ባለው ቃሉ ሁሉ የሆነለት
ሰውን ግን በመልኩ በአምሳሉ ፈጥሮ
እንዲኖርበት በዚ ውብ ተፈጥሮ
ገዢም አደረገው በቃሉ ተናግሮ
ቃላት ብደረደር ለፈጣሪ ስራ
ባህር ቀለም ቢሆን ቢፃፍ በየተራ
ከቶ አይገልፀውም ዘለአለም ቢወራ
...............................የፈጣሪ ስራ
✍ ቤዛ
@gitmv
@gitmv
2 046
Bob marley🎸♍:
ሀገር ማለት ለኔ
ሀገር ማለት ለኔ መሬቱ አይደለም
ሀገር የሚለው ቃል ለኔ የሚሰጠኝ አለው ብዙ ትርጉም
ሜዳው እና መስኩ በእርግጥ እሱ አይደለም ሀገር የሚያስብለው
ሀገር አንለውም ከጀምበሯ መውጫ ቢገተር ተራራው
ከአድማስ ወዲያ ማዶ ዛፍ እና ቅጠሉ ለምልሞ ቢታይም
ታዲያ ምን ዋጋ አለው ብቻውን ባዶ ነው ሀገር አይባልም
ወንዙ ቢንቆረቆር ከአጥናፍ እስከ አጥናፍ
ቀን እና ለሊትም ቢዘምሩ አዕዋፍ
ውብ ነገር ቢኖርም ሰሜን እና ደቡብ
ተፈጥሮው ቢያማልል ያለው ምስራቅ ምዕራብ
ብቻውን ከንቱ ነው ያለ ሰው ያለ ህዝብ
እኛ ስንኖር ነው ሀገር ምናሰኘው ምድሪቷ ምታብብ
እንዲያው ለተመልካች የእኛ ልዩነት ጎልቶ ቢታያቸው
ለባለቅኔው ግን ቅኔ ለሚፈታው አንድነት አላቸው
እስቲ እኔም ባቅሜ እንዲ አርጌ ልፍታው
ሰሙ=ልዩነቱ ከላይ ያለው ሲሆን ውቡ ቀለማቸው
ወርቁስ?ካላችሁኝ እሱንም ለማግኘት ሲበዛ ቀላል ነው
በዚህ በውብ ቀለም በልዩነታችን ነው የተቀመረው
ታዲያ የዚህ ቀመር ውጤቱ ምንድነው?
ይህንን ለማወቅ ቀለም ቀቢ መሆን ፈፅሞ አያሻውም
ሒሳብ መምህርም አያስፈልገውም
ይህንን ለማወቅ እርቀት ሳንጓዝ ሰው መሆን በቂ ነው
የቀመሩ ስሌት:-80 ብሄሮች የሚሰጡን ቀለም የኛ የሆነውን=ኢትዮጵያችንን ነው!!!
ተፃፈ በመስከረም በፍቃዱ
በ 03 / 06 / 13
