የስንኝ ቋጠሮ
Open in Telegram
የዚህ ቻናል ዋና አላማ የተለያዩ ወጣቶች የግጥም ችሎታቸውን የሚዳብሩበት እና የሚያወጡበት ቻናል ነው። ግጥሞችን ለመላክ @mogea ይጠቀሙ መልሰን ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል!!
Show more2 046
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
2 046
የስሜቴ ግዞት
ሆዴ ይረበሻል ሀሳቤ ይበተናል
የማላውቅ ስሜት ግዞቱ
አድርጎ እኔንስ አስሮኛል
ምን እንደሚሠማኝ ለራሴ ጨንቆኛል
ይለፈልፍ ጀመር የማላውቅ ነገር
በድንገት ከውስጤ
አወያየው ጀመር ይረዳኝ አስቤ
ይቀባጥር ጀመር የባጥ የቆጡን
ልረዳው አልቻልኩም የሚያወራውን
የጠየኩት ሌላ የመለሠው ግራ
ያወራ ጀመረ ሌላኛው በተራ
እኔ ሳላስበው ክርክሩ ጦፎ
በነሡ ክርክር የኔ ነብስ ታፍኖ።
እንዳስቆማቸው ከአቅሜ በላይ ነው
እንዳልረዳቸው አይገባ ወሬአቸው
እኔስ ተቸገርኩኝ ሆነብኝ ግራ
የሚነግረኝ የለ ኢሄን ሚያብራራ።
አእምሮ ና ልቤን አልኩ አልረዳቸው
ኢኸው እኔም አለውግራ እንደተጋባው ።
ምናልባት አንድ ቀን ኢሄን
ስሜት አይቶ
ከስሜቴ ግዞት ፈልቅቆ አውጥቶ
ነፃ ያደርገኛል ኢሄን ቅኔ ፈቶ።።
@gitmv
@gitmv
2 046
ሰው_መሆን_ከንቱ🛐🛐🛐
💝 አንዲት ከልጅነቷ ጀምራ ዓይነ-ስውር የነበረች ልጅ ነበረች፡፡ በዓይነ-ስውርነቷም የተነሳ ራሷን ጣም ትጠላ ነበር፡ ሰውም አትቀርብም ከባድ የመንፈስ ጭንቀትም ነበረባት፡ በዚህ ሁኔታ እድሜዋ ወደ ሃያዎቹ ይጠጋል፡ በዚህ ጊዜ ታዲያ አንድ ሰው ትተዋወቃለች፡፡
💝 ይህም ሰው ብልህና አፍቃሪ ስለነበር ያደረባትን የመንፈስ ጭንቀት ፍቅር በመስጠትና ጥበባዊ ምክሮቹ ይፈውሳታል፡ በጊዜ ሂደትም በጣም የሚፋቀሩ ፍቅረኛሞች ይሆናሉ፡፡ ፍቅራቸውም በጣም የሚያስቀና ነበር፡፡
💝 አንድ ቀን ታዲያ አፍቃሪ ጓደኛዋ እንዲታገባው ይጠይቃታል፡፡
"የዓለምን ብርሃን በዓይኔ እስካላየሁ ድረስ ማግባት አልፈልግም" ነበር መልሷ፡፡
ከጥቂት ቀናት በሇላ በልገሳ በተገኙ የአይን ብሌኖች ቀዶ ጥገና ተደርጎላት ማየት ቻለች፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ ፍቅረኛውን እንዳየችው ይህንን ጥያቄ እያቀረበላት ነበር፡፡
💝 "እሺ አሁን የዓለምን ብርሃን አየሽ ታገቢኛለሽ?" ይህን እንዳላት እሷ በድንጋጤና በመገረም የምትለው ይጠፋታል፦
ምክንያቱም ፍቅረኛዋ ዓይነ-ስውር ነው!
ትንሽ ቆይታም መልስ ሰጠችው፡
"ዓይነ-ስውር ማግባት አልፈልግም!" የሚል፦
እርሱም በማዘን ይሄን አጭር ማስታወሻ ፅፎ ጥሏት ሄደ!
"የዓለምን ብርሃን እንዲታዪ ሁለት ዓይኖቼን መለገሴ አይፀፅተኝም ምክንያቱም ዘለዓለም አፈቅርሻለሁ!" 💓💗
#በቅንነት_ሸር_ያድርጉት 👇👇👇
@gitmv @gitmv
@gitmv @gitmv
2 046
#It_is_my_WiFi
(#በእውቀቱ_ስዩም)
ጎረቤቴ ቺስታ ግብፃዊ ነው፤ ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድቡን ከገነባች እንግዲህ ተስፋ የለንም ብሎ አሜሪካ ውስጥ ጥገኝነት ጠይቆ በመኖር ላይ ይገኛል ! እኔ ከወራት በፊት “ግድቡ ተሽጧል” እሚለውን ቀደዳ አምኜ ጥገኝነት መጠየቄን የሰማ አይመስለኝም፡:
ኑሮየ ለክፉ እሚሰጥ አይደለም፤ አውቶብስ እነዳለሁ፤ በተረፈው ጊዜየ ዲሽ አጥባለሁ፤ የናሳውን ሳተላይት ዲሽ ማለቴ ነው፤ ግብጡ ግን መና-እጢ ደሃ ነው፤(by the way “ መናጢ ድሃ” ማለት በጣም ከማጣቱ የተነሳ እጢ ሳይቀር የሚቸግረው ድሃ ማለት መሆኑን ስንቶቻቸን እናውቃለን? ) ስላሳዘነኝ እኔ በወር ሰማንያ ዶላር እምከፍልበትን ዋይፋይ እንዲጠቀም ፓስወርዱን ሰጠሁት ፤ አንባቢ ሆይ! ለዚህ ደግነቴ ያገኘሁት ምላሽ ምን ይመስልሃል? ባለፈው መንገድ ላይ አግኝቶኝ እሳት ጎርሶ እሳት ለብሶ ባረብኛ “ኢንቲ አዩኒ” ብሎ ባረቀብኝ ! የዛሬ አመት ወደ አሜሪካ ስበርር ለትራንዚት ዱባይ አምስት ሰአት ሰለተቀመጥሁ አረብኛ በመጠኑ እሰማለሁ፤ ምን ማለቱ መሰላችሁ : “ ፊልም ላይ ተጥደህ እየዋልክ ኔትዎርኩን ስሎው እያደረግህብኝ ነው! “ ማለቱ ነው ! እረ ገለስ! ውፈር ተበገስ it is my Wi-Fi ‘ ብየ ቀወጥኩት!
(በግብጽ የኢትዮጵያ አምባሳደር እንዳጫወቱኝ ግብፆች “ ጀ“ የሚል ቃል የላቸውም፤ ገማል ይላሉ እንጂ ጀማል አይሉም! ለዛ ነው” ጀለስ “ ማለት ሲገባኝ “ገለስ “ የሚለውን ቃል የተጠቀምኩኝ ! ለምሳሌ፤ ባህር ዳርቻ አሸዋ ላይ በጀርባህ ተንጋለህ ተኝተህ፤ ደረትህን ለጸሀይ፥ ጉያህ ላይ ያለውን ፎጣ ደግሞ ለነፋስ ሰጥተህ ዘና ስትል ፤ አንዲት ግብፃዊ “ገላህ ያምራል ካለችህ” ሙገሳ አይደለም፤ ሃራስመንት ነው!
በምነዳው አውቶብስ ውስጥ እንደ ወያላ ሆኖ የሚሰራ ፈረንጅ አለ፤ ትናንት የተቃውሞ ሰልፈኞችን ኒውዮርክ አራግፈን ስንመለስ ያባይ ነገር ተነሳና “ግብጻውያን በፍቅር ዘፈን ውስጥ ሳይቀር ስለ ናይል እንደሚዘፍኑ ታቃለህ? “ አለኝ “ አንተ በዚህ ትገረማለህ? የእኛ ዘፋኞችማ ግድቡ ከመሰራቱ ሃያ አመት አስቀድሞ ስለግድቡ ሲዘፍኑ ኖረዋል “ ብየ መልሰኩለት ፤ የነገርኩትን ሰምቶ አማትቦ ዞር ይላል ብየ ሳስብ “እስቲ እንዱን ዝፈንልኝ “ ብሎ አያፋጥጠኝም? ዞር ዞር ብየ አውቶብሱ ውስጥ አበሻ አለመኖሩን ካረጋገጥኩ በሁዋላ የንዋይ ደበበን ዘፈን ተረርር ር አደረኩለት ፤
“ገዳም የፍቅር ገ-Dam
ልቤ አንቺን አይከ-dam”
በነገራችን ላይ ፤ ግድቡን ትተን ስለባልቦላው ማውራት የምንጀምርበትን ጊዜ አልናፈቃችሁም?! እንደኔ እንደኔ፤ ግድቡ ስራ ሲጀምር ለአንድ አመት ያህል ህዝቡ ለመብራት መክፈል የለበትም! እንዲያውም በጊዜ መብራት አጥፍቶ የተኛ ሰው በወንጀል ቢጠየቅ ደስ ይለኛል !
የሰይጣን ጆሮ ይደፈንና ግድቡ ተርባይኑን ማንቀሳቀስ ቢያቀተው ወይም ተርባይኑን ለጥቂት ቢስተውስ ? ወይ ደግሞ የግልገል ጊቤን አርአያ ተከትሎ ቢገግምስ? እኔ ጣጣ ያለው አይመስለኝም ፤ ሌላው ቢቀር ሳልመን እናረባበታለን፤ በነገራቸን ላይ ሳለመን የፈረንጅ ሞጃ እሚበላው ምርጥ ያሳ አይነት ነው ፤ በአሳ በሎች ግምገማ እንደሀረር ሰንጋ ይቆጠራል፤ ሳልመን የበላ ትውልድ ጭንቅላቱ ይሰራል ፤ ጭንቅላቱ ከሰራ አጥብቆ ይመራመራል፤ ኤሌክትሪክ የሚያመነጭ ኒውክልየር ይፈጥራል ፤
ይህ በአንዲህ እያለ፤ አባይ በተነሳ ቁጥር “ አባይ ማደርያ የለው ግንድ ይዞ ይዞራል “ የሚለው እጅ እጅ እሚል ተረት መጠቀሱ የማይቀር ነው ፤ የሆነው ሆኖ ፤ከግድቡ ሙሌት በሁዋላ ግንዱ ለማን ይደርሳል ? ዶክተር አቢይ;-ሶስት ቦታ ተቆርጦ እንደ ቅርጫ እንካፈለው እንደማይል ተስፋ አለኝ! እዛው ግብፅ ፈልጣ ሩዝ ትቀቅልበት!
ከአበዛሁት አትፍረዱብኝ ! _የአገር_ፍቅር ሲበዛ #ካቲካላ_ነው! አናት ላይ ይወጣል!
@gitmv @gitmv
@gitmv @gutmv
2 046
ከቀናት በፊት የእድሜ መሃላ ውስጥ ነበርን። በቃል ውበት የሰከርን፣ በእምነት ጌጥ ያጌጥን፣ ያለንበትን ቀናት በሺህ እጥፍ ተጉዘን፤ ክንዳችን እንደተጣመረ፣ ልባችን እንደተቋለፈ፣ ከንፈራችን በአንድ እንደተጠረዘ፣ በደመና ተጭነን አርገን ነበረ።
የኛ ደሴት እዚህ እንዳልሆነ ይሰማናል። ማንም የኛን ያህል ፍቅርን እንደማያውቀው ያመነው ልብችን በትምክህት ከአምላኩ ቀምቶ ከሰባቱ ሰማያት በአንዱ ገዢ ነበር።
[ምን ያደርጋል?!] ፍቅር ብቻ እንደ ማለዳ ወፍ የሚቀኛው አንደበታችን ዛሬ ተራገመ፣ እንደ ናርዶስ ሽቶ ያወደው ላባችን፤ ዛሬ የመኝታችንን እድፍ አጋለጠ፣ በስስት ሚፈላለጉ ዐይኖች ዛሬ ሽሽት ገቡ።
የረከሰ ቤተመቅደስ ማን ይፈለገዋ? ቀዳሽ የለውም፣ አጣኝ የለውም፡ ሳሚ ተሳላሚ የለውም።
ያለ ቦታው የወደቀ ቤተመንግስት ጠባቂ የለውም፣ ታሪክ ሆነ ግርማ የለውም፣ ማንም እየመጣ ውዳቂውን ይጥልበታል። ማንም እየመጣ የቤቱን አመል ያራግፍበታል። የአላፊ አግዳሚው እዳሪ አስተናጋጅ ይሆናል።
እንደዛ ተሰማኝ። ቀፈፈኝ! እኔን ብቻ የሚያቅፉ እጆች ዛሬ ለሌላ ተዘረጉ፣ እኔ ብቻ የሚቀምሱ ከንፈሮች፤ ዛሬ እንደ ሰፈር እድር ወጥ ቀማሽ ከስንቱ ተናከሰ። በአንድ ቀን እምነቴ ፈረሰ። ለሺህ አመት የገነባሁት በጥቂት ሰዓታት ተናደ።
ማሃላ ለካ ክብደቱ በሰዓቱ ነው፣ ቃል ጥንካሬና ውበቱ በቦታው ነው። ቀን የጣለ እለት፣ ማይጋፈጡት እውነት የደረሰ የመጣ እለት፣ ምንም ነው። ለእድሜ ልክ የገባውላት ቃል አሁን ረከሰ። ለሺህ አመት ትንቢት የማልኩት መሃላ በዛሬ የሎስ ቀን ተሸነፈ።
ፍቅር ነብይ ያደርጋል። ድፍረትን እንደ እቴጌቱ ሸማ አልብሶ፤ በኩራት የአምላክን የሕይወት ድርሰት መነባንቦች እኔ ካልከተብኳቸው ያሰኛል። ዛሬ ላይ ሆነን እስከሞት በራሳችን መሻት የራሳችንን መቼት እንደርሳለን። ትላንትን ማለፋችን እምነት ሆኖን፤ ዛሬን ብቻ ሳይሆን እስከ እልፍ ትውልድ በግጥም ስንኞች መኖራችንን እንቀኛለን።
መንገዳችንን ከነመሰናክሉ ከነ ጓዳ ጎድጓዳው ሳይሆን በተደላደለ የደመና ሰረገላ ላይ በፍላጎት ሃሳባችን እንጭነዋለን። ድንገት ግን ከደመናው ላይ የሚያራግፈን፣ ጎትቶ ሚያስለቅቀን፣ ገፍቶ የሚጥለን የንፋስ ጦረኛ ዝናር ታጥቆ ጦሩን ሰብቆ ይወራናል። ያንግዜ አለም የምጥ ሰዓት ሆናብን እናነባለን፤ ማሸነፍ ስለማይሆንልን!
ዛሬ ለኔ የምጥ ቀን ነው። ማልጋፈጠው እውነት መጣ፣ ማልዘለው መሰናክል፣ ማልደበቀው ፀሃይ፣ ማልከልለው ብርሃን እረታኝ፤ በሰፊ ባህር ውስጥ እየጎተተ የሚያሰምጠኝ መንፈስ ወረረኝ። የሚዋኙ እጆቼን፣ የሚንፈራገጡ እግሮቼን ሰለባቸው።
ሃሳብ ቀድሞ የሞተ እለት፤ ስጋ ኑዋሪ አልባ ጎጆ ነብስ የግዞት ስደተኛ ናቸው።
ምንም ቢመጣ አልተውሽም ያልኳትን ከምንም በላይ መጣና ልተዋት ተነሳው። ሞትም አይለየን ያልኳትን ከመቃብር የገዘፈ የቁም ሞት ከፈለን። አንድነት ጠወለገ አብሮነት ከሰመ። አንገቷን እንደ ደፋች አበባ፣ እንደደረቀ ቅጠል፣ እንደበሰበሰ ቅርንጫፍ ከመሬት ሊወድቅ ማንም ሊረግጠው አንድ ሐሙስ ቀረው። -አንድነት።
ከአልጋዬ ተነሳው። የታገልኩትን የሃሳብ ልክፍት እንደማላሸንፍ ሳውቅ እጅ ሰጠው፣ ይቅርታ የሚያደርግ ብርቱ ልብ እንደሌለኝ ተረዳው፤ ልብሴን ይዤ ወጣው።
ምንም አላለችኝም። ማልቀስ ጀመረች ከአልጋዋ ተነስታ አትሂድ አላለችም። እንባዋ ግን ህመሟን ይናገራል። ፀፀቷ ያማል፤ ይሰማል። ይቅር ማለት ግን ማንን ገደለ? እንጃ ልቤ ደነደነ።
የትላንት እንባዋ የራሄል ነበረ የአምላክን ልብ የሚፈትን፤ ዛሬ ግን ባዶ ሆነበኝ። -አቅም አነሰው። መልስ የሌለው ጥያቄ፣ ክብደት የሌለው ሸክም፣ ለዛ የሌለው ቅላፄ፤ ስበት የሌለው ደምግባት ሆነ።
ምንም ብቻን ያዘለ የኔን ልብ መፈተን የከዳው ባዶ። እርሷ በምሬት እንባ ቃል ሳታወጣ ትማፀናለች። እኔ አይኗ እንዳይረታኝ እንደ ሎጥ ሚስት እንዳልቀር ሽሽቴን እንዳታሸንፈው ሳልዞር ሳላያት ወጣው [አይኖቿን አውቃቸዋለውና]። ወዴት አላውቅም ብቻ ሽሽት!
✍fanuel a.
@zikiretibeb
@zikiretibeb
2 046
⚜ ምሳሌያዊ ንግግሮች⚜
🔱 ሀ ባሉ ተዝካር በሉ።
🔱 ሬሳ በምን ከበደ? ሀሳቡን በሰው ላይ ጥሎ።
🔱 ሳይታገል ጣይ ሳይወጋ ገዳይ።
🔱 ማን ያውቃል ባላገር ማን ይጠብቃል ማገር።
🔱 በሁለት በትር አይማቱ በሁለት ዳኛ አይሟገቱ።
🔱 አሞራና ቅል ተጋቡ አሞራው በረረ ቅሉም ተሰበረ።
🔱 ብዙዎች ለብዙ ሲያውቁ የራሳቸውን አይጠነቀቁ።
(የአማርኛ ምሳሌያዊ ንግግሮቾ)
ከሚለው መፀሀፍ የተቀነጨበ!
https://telegram.me/manbabemulusewyaderegal
2 046
ያጋጣሚ ገጣሚ
እንደ ተናደደ ቀለም ጨበጠና
እንደ ተናደደ ሉኩን ቀደደና
እንደ ተናደደ ጎንበስ ቀና አለና
እንደ ተናደደ ሀሳብ ሲመጣለት አቀረቀረና
እንደ ተናደደ ስለ ፍቅሩ አሰበ
እንደ ተናደደ በራሱ ሀሳብ ውስጥ እራሱን ሰለበ
እንደ ተናደደ ከራሱ ተለየ
እንደ ተናደደ ፍዝዝ ብሎ ቆየ
እንደ ተናደደ ያጠፋችውን ሁሉ
እንደ ተናደደ በደሏን በሙሉ
እንደ ተናደደ ማብክሰክ ጀመረ
እንደ ተናደደ ቃላት አዋቀረ
እንደ ተናደደ ስንኙን ሰደረ
የመክዳት አጋጣሚ
ግጥም አጣጣሚ
ቃላት ለቃቃሚ
አረገው ገጣሚ
✍🏽ቧኂት [የአሊዬ ልጅ]
`@yetibebmenge
@yetibebmenge
