የስንኝ ቋጠሮ
Open in Telegram
የዚህ ቻናል ዋና አላማ የተለያዩ ወጣቶች የግጥም ችሎታቸውን የሚዳብሩበት እና የሚያወጡበት ቻናል ነው። ግጥሞችን ለመላክ @mogea ይጠቀሙ መልሰን ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል!!
Show more2 046
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
2 046
....ነግሬሽ ነበረ....
ሴት ክብሯን ረስታ ፣ ጭኗን እንዳታምነው
ሁሉን ያጣል ብዬ ፣ የሁሉም የሆነው!!!
ነግሬሽ ነበረ
ውበት ደም ግባትሽ ፣ ሁሉን እንደሚስብ
የወንድ ልጅን ዐይን..
ከተበተነበት ፣ እንደሚሰበስብ
ነግሬሽ ነበረ...
ትንሽ ስትዘነጊኝ ፣ ብዙ እንደማስብ!!!
ነግሬሽ ነበረ... ባትሰሚኝም እንኳ
ሳሙና ነው ብዬ ፣ የቆንጆ ሴት መልኳ
እድፋም ስሜቶችን...
አሽታ ስታነፃ ፣ ያበቃል ታሪኳ!!!
ነግሬሽ ነበረ
ሴት ልጅ ስታማርጥ ፣ ለራሷ ምራጭ ናት
በክብር ነው እንጂ...
በመውለድ አይደለም ፣ የሚኮነው እናት፡፡
ክብረ ቢስ ህይወቶች ፣ ጣፍጠው አይቀጥሉም
የወለዱ ሁሉ እናቶች አይደሉም
ነግሬሽ ነበረ
እናትነት ስሟ
ከክብሯ ነው እንጂ ፣ ከልጇ እንዳልመጣ
ወልዳም ምንም ነች ፣ ሴት ክብሯን ስታጣ።
ነግሬሽ ነበረ...
ሴት ክብሯን ስትጥል ፣ እድሜዋ ይሔዳል
የወንድ ልጅ ቤቱ...
የሴትልጅ ውበት ነው ፣ ካየበት ይለምዳል፡፡
ነግሬሽ ነበረ...
ጭንሽ ሴትነትን ፣ ከቶ እንደማይበልጠው
ቁንጅናም ይረክሳል!
ብቻውን እንዲቀር ፣ ሁሉም ከመረጠው!
ብነግርሽ ብነግርሽ ፣ ባትሰሚኝም ቅሉ
"ሰደበኝ" በማለት ፣ ታወሪያለሽ አሉ
ልክ ነሽ አንዳንዴ
እውነቶች ውሸት ፊት ፣ ስድብ ይመሥላሉ።
ሞኝ ሰው ሲመክሩት
ሞኝ ሰው ሲነግሩት
የቀኑበት መስሎት ፣ በከንቱ ቢታበይ
ግን እነግርሻለሁ!
ነግሪያት ነበር ስል
ቀንቶ ተናገረኝ ፣ ወይም ሰደበኝ በይ።
ግን እነግርሻለሁ
ግን እመክርሻለሁ
ሴት ልጅ ክብሯ ሲጎድል ፣ ውበቷ አይመችም
ሁሉም ይመኟታል ፣ ከአንዱም ልብ የለችም!!!
✍✍N@ti ኢthio
2 046
Selam Bishaw:
♥️💗ሁሉም ሰው ማጣት ማይፈልጋቸው ብዙ ነገሮች አሉ እኔም እንደዛው ማጣት ማልፈልገው ብዙ ነገር አለ ከሁሉም ይበልጥ ግን እናቴን ማጣት አልፈልግም!!💗💞♥️
እስኪ እናቱን የሚወድ ❤️
SHARE ...For more
💮 🇯 🇴 🇮 🇳 👇 🇺 🇸
@learneachother
━━━━━━━✦🌹✿🌹
2 046
Fellow Alien👽:
All kind of psychology facts and inspirational qoutes.
Send your feedbacks
@Psychologyfactsbot
https://t.me/psycologically
2 046
በእናቶች እንባ በአባቶች ፀሎት
ባትቆም ይቺ ሀገር
እንደኛ ዳንኪራ እንደ ክፋታችን
ልክ እንደ ሎጥ ዘመን በዲን አልቀን ነበር
እናቶችን አባቶችን ያቆይልን…………!!!!!!!!!!!
✍ኢትዔል
2 046
በእናቶች እንባ በአባቶች ፀሎት
ባትቆም ይቺ ሀገር
እንደኛ ዳንኪራ እንደ ክፋታችን
ልክ እንደ ሎጥ ዘመን በዲን አልቀን ነበር
እናቶችን አባቶችን ያቆይልን…………!!!!!!!!!!!
እቴኤል✍
2 046
።።።።።።ዕድር።።።።።።
(በ ብርሃን_ዘኢትዮጵያ)
ሞቱን የሚኖር ሰው
መቼ ኖሮ ያውቃል
ኑሮዉ እየከፋ
ሞቱ ግን ይደምቃል።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
፲፯/፲/፳፻፱
@tibebnBeMasho
@tibebnBeMasho
2 046
ነገ 😅😠😒😣
ነገ . . .
ነገዬን አላውቅም።
ዛሬ ደመና ነው ሰማዩ አርግዟል፣
ነፋሱ አይጣል ነው ለጉድ ይጋረፋል፣
የውሽንፍሩ ሃይል ልብ ያስደነግጣል፣
መብረቁም ከባድ ነው የምር ሆድ ያስብሳል፣
እንጃ ግን አላውቅም ሆዴን ባር ባር አለኝ፣
የነገ ዋዜማ ደረሰ መሰለኝ፣
ዛሬዬን አልኖርኩም ትላንትም እንዲያው ነው፣
ታዲያ ለነገዬ ተስፋ ለምንድን ነው?!
ደስታ ይኑር አይኑር ፍቅር ወይ ጥላቻ፣
ሰቅዞ የሚይዝ የነገ ፍራቻ፣
የትላንት ጠባሳ የዛሬ እንቅፋት ፣
ነገን አለማወቅ ባሳደረው ብሶት፣
ሁሉ ህልመኛ ሆነ ሁሉ ባለራእይ፣
ቅዠት እና ህልምን በደንብ እንኳ ሳይለይ።
ህልምስ ጥሩ ነበር የሚፈታው ጠፋ እንጂ፣
ትርጉም የሌለው ህልም ቅዠት ነው አይበጅ፣
" ትናንት ታሪክ ነበር ነገ ብሩህ አለም "
ይላሉ . . .
ዛሬ ድልድይ ናት ወደ ብሩህ አለም የምትጋልብባት።
እኔ ግና የትናንት ጠባሳ ዛሬም እያመመኝ
ወደ ብሩህ አለም ማያዬን ጋረደኝ፣
ድልድዩም ረግቧል አላስጋልብ አለኝ።
ፍርሃት የተባለ ሰቅዞ የያዘኝ፣
ስንፍናን ጨምሮ ይባስ አሳመመኝ።
አሁን ጎብጫለሁ፣
ግና አልወደኩም።
በጣም ታምሜያለሁ ፣
ግን አለሁ አልሞትኩም።
የነገ ፍራቻ በሚባለው ህመም፣
ትርጉም በማትሰጠው በማትገባው አለም፣
ይኽው እጽፋለሁ ከቀለለኝ ብዬ፣
ትርጉም እየፈለኩ ለውዷ ሂዊዬ።
.
ገጣሚ እዮሲያስ መላኩ
2 046
Ysfen:
...አማረኝ...
ሆዴንባር ባር አለኝ ማያውቀውን ወዶ:
ልቤምአመረረ፥
እግሬም አሰመረ፥
አይኔም አማተረ÷ ካድማስ ወዲያ ማዶ::
""ወይፈረንጅ ጠብሼ
እንደማይክልጃክሰን ፊቴን አስቦርሼ
ይህም ካልተሳካ የኢሉምናቲ ታቶ ተነቅሼ
በብሔር በጎሳ በዘር ከምደራጅ
መሆን ነው ያማረኝ ከጥቁሮች ፈረንጅ፡፡""
ብዬ አሰብኩና÷
ሆኖ አገኘሁት መቃዠት ሆነና።
ወይ ኢትዮጵያዊነት ወይ ሀበሻነቴ!!!
ጊዜማይቀይረው መጠለያ ቤቴ
ኢ ት ዮ ጵ ያ ዊ ነ ቴ፡፡
ኢትዮጵያዊነትን ጊዜ ካልቀየረው እራሴን ልቀይር
ትውልድ ይዳን በኔ ይብቃ!ከስህተቴ ልማር!!
እንዳይሆንብኝእንደ በእጅ-ያለ-ወርቅ
ከመዳብ ሳልቆጥረው ዋጋውን ልጠይቅ
አማረኝ በቃ አማረኝ፡
ኢትዮጵያዊነቴን ማወቅም ማሳወቅ፡፡
¥$f€n
2 046
Rahel Berhanu:
✍ምኑንተገጠመ
*********
የዘማሪው መዝሙር ፣ የገጣሚው ግጥም
ሊናገር ካልቻለ ፣ የክርስቶስን ስም
ማዜሙም መግጠሙም ፣ ለጌታ ካልዋለ
ጥበብ ለጠቢቡ ፣ ለኢየሱስ ካልሆነ
ምን ዋጋ አለው ዜማ
ምን ዋጋ አለው ቅኔ
ምን ዋጋ አለው ስንኝ
ምን ዋጋ አለው ቃሌ
ለኢየሱስ ተገጥሞ ፣ ለ'ሱ ካልተዜመ
ምኑን ተገጠመ ፣ ምኑንስ ተዜመ
የቋጠረው ስንኝ ፣ ኢየሱስ ከሌለው
የገጣሚው ግጥም ፣ ንፋስ ተከታይ ነው
ለኢየሱስ ካልሆነ ፣ ቢሰደር እልፍ ቃል
ግጥም ሁሉ ቤቱን ፣ በከንቱ ይመታል
#ሄኖክ_አሸብር
2 046
Blûê fíßh🐟🐟:
❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤
ድምፃውያንበድምፃቸው ጠላትን ሲገሉ
ጠብ ጫሪዎች የተቃቃሩት ሲሸመግሉ
አይቼ
የዚህ ዘመን ልጆች ድምፃቸው መትረይስ
ሰውን ብቻ ሳይሆን እንሰሳትን የሚጨርስ
እያልኩኝ ሲራገም ስሳደብ ከርሜ
ዛሬ በድምፅሽ ተፈወስኩ ስልሽ ከህመሜ
ልብሽ አላምን ብሎ ቢጠራጠር
አይንሽም አላምን ብሎ ቢቀር
እውነት እምልልሻለሁ ሂዋኔ
በድምፅሽ ተፈውሻለሁ እኔ
❤❤❤❤❤
ዛሬም ደውይልኝ 🙏🙏
ተፃፈ # Blue fish
