የስንኝ ቋጠሮ
Open in Telegram
የዚህ ቻናል ዋና አላማ የተለያዩ ወጣቶች የግጥም ችሎታቸውን የሚዳብሩበት እና የሚያወጡበት ቻናል ነው። ግጥሞችን ለመላክ @mogea ይጠቀሙ መልሰን ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል!!
Show more2 046
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
2 046
ሰዎች እንደተቀየርክባቸዉ ያወራሉ፤ በእነርሱ ምክንያት እንደተቀየርክ ግን አይገባቸዉም…ስለዚህ ሲወዱህ የሚወድ ሲጠሉህ የማይጨነቅ ብርቱና ቅን ልብ ይኑርህ ፤ በኑሮህ ሁሉ የምታዉቀዉን ሁሉ መናገር ላይጠበቅብህ ይችላል፤ የምትናገረዉን ሁሉ ግን ማወቅ አለብህና! ግለ ኑሮህን በአስተዉሎት ኑር። በዚህ ምድር ሰዉ መሆን ነዉ እንጂ፤ ሰዉ መምሰል ቀላል ነዉ፤ እንዲሉ በፍጹም ራስ ተማመን፣ ሁሌም ራስህንም ሁን፤ በዙሪያህ ላሉ ጩኸቶች ሁሉ ጆሮህን አትስጥ። ሀይቅ ዳር ተሰብስበዉ እንቁራሪቶች አብዝተዉ ስለጮሁ ሀይቁ የእንቁራሪቶች ነዉ ማለት አይደለም:: ለክብራቸዉ ሲሉ ዝም ያሉ ብዙ ዓሳዎች በሀይቁ ዉስጥ አሉና።
©ሎሬት ፀጋዬ_ገብረመድህን
@gitmv
@gitmv
@gitmv
2 046
አልፏል ላይመለስ አዲስ ያልኩት አመት፣
እኔም ትቼዋለሁ ዳግም ላልኖርበት፣
፡
በምድር እንድኖር እድሜን ከሰጠኸኝ፣
ልክ እንደወራቱ እኔንም ለውጠኝ፣
፡
#አሜን ...
happy new year 2013
2 046
ዛሬውኑ የሚቀጥለውን ዓመት ግብህን ግልጽ አድርግ!
ነገ ወደ አዲስ አመት ከመግባትህ በፊት አንድ ነገር ላስታውስህ፡- በሚቀጥለው ዓመት ያለህን ግብ በሚገባ ሳታውቅ ወደ አዲስ አመት መግባት ማለት እጅግ አክሳሪ ጉዳይ ነው፡፡ ግብህን ግልጽ አድርገህ ያልጀመርከው ነገር ብዙ ከሄድክ በኋላ እንደገና እንድትመለስና ብዙ ከጠመጠምክ በኋላ እንደገና እንድትፈታ ያደርግሃል፡፡
ዓልመህ ተነሳ እንጂ ዓላማህን እግረ-መንገድህን እየፈጠርከው አትሂድ፡፡ የምትደርስበትን ሁኔታ ቀድመህ አይተህ ተነሳ እንጂ የደረስክበት ቦታ ደስ ስላለህ ብቻ ዓላማህ እንደሆነ አድርገህ አትቀበለው፡፡ ግብህን አውቀህ ደስ ብሎህ ተነሳ እንጂ አንድ ደስ የሚል ነገር እስከሚያጋጥምህ ድረስ እያዘገምክ አትሂድ፡፡ የውስጥ ደስታህንና እርካታህን በየእለቱ ከሚገጥምህ ገጠመኝ ጋር አታገናኘው፡፡ በዚያ ምትክ ዓላማን በማወቅ፣ ግብን በማውጣትና እዚያ ጥግ ለመድረስ ጉዞን በመጀመርህ ምክንያት ደስተኛ ሁን፡፡ ከዚያም ጉዞህን ቀጥል፡፡
ወደ የት መሄድና መድረስ እንደሚፈልግ የማያውቅ ሰው ያለበትን ደረጃ እያየ ከማዘን ያለፈ ነገር ማድረግን በፍጹም አይችልም፡፡ ሃዘንና ለራስ ከንፈርን መምጠጥ ማንንም የትም አድርሶ ስለማያውቅ፣ የት መድረስ እንደምትፈልግ ግልጽ የሆነ ንድፍ ሊኖርህ ይገባል፡፡ ያንን ካደረግህ በኋላ የሚቀጥለውን አመት ግህን አስመልክቶ ያለህ እቅድ መቼ ተከናውኖ ማየት እንደምትፈልግ የጊዜን ገደብ በግልጽ ማስቀመጥ ተገቢ ነው፡፡ የቀን ገደብ ወይም ቀጠሮ ያላስቀመጥክለት ነገር የመከናወኑ ነገር አጠራጣሪ ነው፡፡
የቀን ገደብ ማውጣት መነሳሳትን በውስጥህ ከመፍጠሩ ባሻገር የግምገማ ነጥብን እንድታስቀምጥ ይረዳሃል፡፡ ይህ መነሳሳት በየቀኑ፣ በየሳምንቱ፣ በየወሩና በየዓመቱ፣ ማከናወን ያለብህን ነገሮች እንድታስብ ይጋብዝሃል፡፡ ይህንን ከግብ አንጻር የሆነ መነሳሳት ይዘህ ስትራመድ አንዳንድ ጊዜ አቅምህ አናሳ እንደሆነ ማየትህ የማይቀር ነው፡፡ ንድፍህን እንዴት ተግባራዊ ለማድረግ እንደምትችል ማሰብ የምትጀምረው ያን ጊዜ ነው፡፡ ምናልባት ራስህን ማሻሻል የሚያስፈልግህን ሁኔታ ትደርስበት ይሆናል፡፡ ምናልባትም ደግሞ ድጋፍ ሊሰጥህ የሚችልን ሰው ማሰብና ማነጋገር ሊኖርብህ ይችላል፡፡
ግብ ማለት መጨረሻ ላይ ስኬታማ እንደሆንን የምናውቅበትና ለማየት የምንፈልገው ስእል ሲሆን፣ እቅድ ማለት እዚያ ግብ ለመድረስ መውሰድ የሚገቡን እርምጃዎች ጥርት ባለ መልኩ ሲቀመጡና ስናያቸው ማለት ነው፡፡ ተግባር ማለት ደግሞ ያንን ለመውሰድ የወሰንነውን እርምጃ ተግባራዊ የምናደርግባቸው ጥቃቅን እንቅስቃሴዎች ናቸው፡፡ ስለዚህም፣ ግብን፣ እቅድንና የየእለት ተግባርን ስኬታማ በሆነ መልኩ በመያዝ በገንዘብ መበልጸግን ከፈለክ በግብ አወጣጥ ዘዴ፣ ግቡን ተግባራዊ ለማድረግ እቅድን በማውጣት ብልሃትና የተግባር ሰው በመሆን ቆራጥነት ማደግ የግድ ነው፡፡ ፍላጎትህ ምኞት ሆኖ እንዳይቀር ግብን አውጣ፡፡ ግብህ ከንቱ ሆኖ እንዳይቀር ግልጽ የሆነና ቀን ገደብ ያለው የእንቅስቃሴ እቅድ አውጣ፡፡ እቅድህ ከንቱ እንዳይሆን ደግሞ መተግበር ጀምር፡፡ ይህንን መስመር መከተል ስትጀምር ብዙም ሳትቆይ የስኬትን ጣእም ማጣጣም ትጀምራለህ፡፡
መልካም አዲስ አመት ለምወዳችሁ የሃገሬ ሰዎች በሙሉ!
Dr Eyob M.
2 046
🙏 ሰላም ለእናንተ ይሁን እንዴት አደራችሁ🙏
✍ እሰቲ ሰው ፈልጉ✍
📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖
አንደበተ ርቱእ - ቋንቋው ቀጥተኛ፣
ለሌላው አሳቢ - ያልሆነ ምቀኛ፤
፡
ከሸር ካሉባልታ - ከክፋት የራቀ፣
ጉራና ትምክህትን - በፍፁም የናቀ፣
አውቃለሁኝ ብሎ - ያልተመፃደቀ፤
፡
ሁሉንም አክባሪ - በሰው የማይኮራ፣
ለፍርድ የማይቸኩል - ቃሉ የተገራ፤
፡
ፍቅር ቁምነገሩ - ከወረት የፀዳ፣
በመከራ ሰዓት - ወዳጁን ያልከዳ፤
፡
ፈጣሪን አመስጋኝ - የሚኖር በወጉ፤
እርሱ ነው ሰው ማለት - እስቲ ሰው ፈልጉ፡፡
@gitmv
@gitmv
@gitmv
2 046
🌻ሰዎች ስለወቀሱን የማይርድ፤ ስለኮነኑን የማይወድቅ፤ ስለፈረዱብን የማይሞት፤ ስለጠሉን የማይፈራ፤ ስለተዉን የማይደክም መንፈስ በውስጣችን ሊኖር ግድ ይለናል።
🌻 ከፈጣሪ የተሰጠን እውነተኛው ማንነታች ይህ ነው። ብዙዎቻችን ደካማ ስለተባልን ደክመናል፤ ሃጥያተኛ ስለተባልን ቆሽሸናል፤ ወንጀለኛ ስለተባልን ታስረናል።
🌻የሌሎች ሰዎች አስተያየትና መስፈርት ከእውነተኛው ማንነታችን አርቆናል፤ ሰላም ካለበት ስፍራ አውጥቶ የይሉኝታ ሰፈር ኗሪ አድርጎናል።
፨፨፨፨፨፨፨መልካም አዲስ አመት፨፨፨፨፨፨፨
2 046
“ እውነታው ሰዎች ሊያወድሱህ ከፈለጉ ከፈጣሪ ታናሽ ያደርጉሃል ። ሊዘልፉህ ከፈለጉ ደግሞ ሳጥናኤል የሚቀናበት ክፉ ያደርጉሃል ።
ከሰማሃቸው ደግሞ ራስህን የመሆን እድል አይሰጡህም ። ሁሉም በፈለጉት መንገድ ሊቀርፁህ መጥረቢያ ይስላሉ ።
ልብህን ከከፈትክላቸው የየድርሻቸውን ጠርበው ቅርፅ አልባ ያደርጉሃል።
እኔና አንተ አንድ ቦታ ላይ በተለያየ አቅጣጫ ፊታችንን አዙረን ብንቆም የእኔ ቀኝ ያንተ ግራ ነው። 'ቀኝ ይሄ ነው ወይም ግራ ይሄ ነው' ብዬ ብከራከርህ ቂል ነኝ ።
እንዳንተ አቋቋም ያንተ እውነት ይሆናል ። እንደ እኔ አቋቋም ደግሞ የእኔ እውነት ይሆናል ። ባንተ እውነት ለማመን ያንተን ጫማ መዋስ አለብኝ። የቆምኩበት ሆኜ ለስህተትህ ሒሳብ እየሰራሁ ስዳኝህ እቀሽማለሁ። "
" ጠበኛ እውነቶች " ከተሰኘው የሜሪ ፈለቀ መጽሐፍ የተቀነጨበ ::
ይቀላቀሉን
👇👇👇
@bamatub
@bamatub
@bamatub
2 046
✍️አንተን የበላ
*****************
የአባት መና ፣ ሕያው እንጀራ
ዳግም ላታስርብ ፣ የምትበላ
የሕይወት መጠጥ ፣ የዘልአለም
አንተን ጠጥቶ ፣ መጠማት የለም
ሁሉ አንተ ነህ ፣ በሁሉም አንተ
ስለሞትክለት ፣ ላንተ የሞተ
ሳይጥር ሳይለፋ ፣ ላቡን ሳይዘራ
እንዴት ይራበው ፣ አንተን በላና
ያ ስጋ እንጀራህ ፣ የተቆረሰው
ለኔ ነው ብሎ ፣ ያመነብህ ሰው
ልሙት ቢል እንኳን ፣ አይሆንለትም
አንተን የበላ ፣ ሞት የለበትም
2 046
#ግጥም
ልቤ ዝቅ ብሏል?
📝Beemnet tilahun
SUBSCRIBE
https://www.youtube.com/channel/UC3n0W0ebq_vRF_dwmWF_3xg
@DAILY_PICTURES1
2 046
✍እንጀራ እና ውሀ
*****************
ወይ እግዚአብሔር ላይሆን ፣ ወይ በልቶ ላይጠግብ
በድያብሎስ ስብከት ፣ "እንደ" ብሎ ሲያስብ
አዳም በበደለ ፣ ቃል እንዲሞት ታዞ
ፍቅር የሕይወት ምንጭ ፣ ከአብ ልብ ፈሶ
ሰው በልቶ እንዲጠግብ ፣ ጠጥቶ እንዳይጠማው
እንጀራ ተራበ ፣ ውሀን ውሀ ጠማው
✍የሕይወት እንጀራ ♥ኢየሱስ♥ የሕይወት ውሀ!!
#ሄኖክ_አሸብር
2 046
ለስሙ ነው እንጂ
አንዱ ከአንዱ ጋር ተመሳስሎ ሲኖር
ቃልህን ሳይፈፅም አንተን ሳያከብር
እኛ ያንተ ልጆች የተባልን ሁሉ
እንደቃልህ መኖር ልክ እንደሀሳብህ
መኖር ካቃተን ለዳንበት ክብርህ፡
ከዚች አለም ጣጣ ከተመሳሰልን፡
ለስሙ ነው እንጂ ኧረ መቼ ዳንን!
ሲሰድቡን ተሳድበን ሲረግሙን ተራግመን፡
መኖር ከጀመርን መለየት አቅቶን
ለስሙ ነው እንጂ እረ መቼ ዳንን!
ቃልህን ለመፈፀም የልብህን መሻት
ካልተሯሯጥን ሁልጊዜ ቀን ከሌት
ከዚች አለም ጣጣ ከክፉ ምኞቷ
አጥፍቶ ጠፊ ስር መሠረቷ
ተለይተን ካልኖርን ክርስቶስን መስለን
ለስሙ ነው እንጂ እረ መቼ ዳንን!
ተመሳስለን እኖርን በስም ክርስትና
ከህወታችን ጠፍቶ የአንተ ህልውና
አንተ ስትመጣ በክብር ታጂበህ
በመለአክት አጀብ እጂጉኑ ከብረህ
ያንጊዜ እንዳናጣ ከአንተ ተቀባይነት
እንድህ ልለምንህ አባዬ የኔ አባት
መኖር ከተባለ ክርስትና ህይወት
ቀንከሌትእንትጋ አንተን ለማስደሰት።
ኑሮአችን ይሁን ለሰማዩ ስራ
ልጆቼ ብለህ በእኛ እንዲትኮራ።
እባክህ እርዳን አግዘን በፀጋህ
ኑሮአችን እንዲሆንለዳንበት ክብርህ።
ወተንም እንኑር ከአስመሳይነት ኑሮ
እንኑር ለአንተ ስምህ በእኛ ከብሮ
እንኑር ለአንተ ስምህ በእኛ ከብሮ።
ከሰላም ጌታቸው
@bamatub
@bamatub
ከ daily pic የተወሰደ
2 046
" የአባቴ ብልጠት"
አንድ ቀን ወደ ትምህርት ቤት እየሄድኩኝ መንገድ ላይ አስገራሚና አስተማሪ ነገር ገጠመኝ ለሊቱን ዘንቦ ስለ ነበረ(የድሬ ዝናብ) መሬቱ አሸዋማ ቢሆንም አልፎ አልፎ ከጭቃ ጋር እየታገልኩ ስሄድ ሁለት ጎልማሳ ሰዎች ከፊት ለፊቴ ይሄዱ ነበር ። አንደኛው ሁለት ትንንሽ ልጆች ይዛል ልጆቹም ከፊት እየሮጡ አስቸገሩ አባታቸው "ተው ትወድቃላችሁ እኔ ልያዛችሁ" ቢላቸውም አሻፈረኝ አሉ ከዚያ አባትየው ትንሽ አሰላስሎ ለጋደኛው "አሁን እንዴት እደምይዛቸው ተመልከት" አለው ከዚያ አባትየው እየተንገዳገደ "ልወድቅ ነው ልጆቼ ያዙኝ" ብሎ ጭኸ ልጆቹም በፍጥነት አንዱ የግራ እጁን ሌላኛው የቀኝ እጁን ያዙት እርሱም ጠበቅ አርጎ ያዛቸውና ልጆቼ እንዳልወድቅ እጄን አትልቀቁኝ አላቸው እነርሱም እሺ አባዬ አሉት ይሄኔ አባትየው ዞር ብሎ ለጓደኛው አየህ እንዴት እንደያዝኩቸው ትወድቃላችሁ ልያዛችሁ ብላቸው አንወድቅም ብለው ይወድቃሉ ያዙኝ ብላቸው ግን እንይዘዋለን ብለው ይያዛሉ አለው ልያዛችሁ ብዬ ከማልይዛቸው ያዙን ብዬ ብይዛቸው ይሻልል አለው።
በጣም ገረመኝ የአባትየው ብልጠት የሰማዩ አባቴን አስታወሰኝ የልጆቹ መረዳት አባታቸውን መያዛቸው ነው እውነቱ ግን እነሱ በአባታቸው መያዛቸው ነው። አገልግሉኝ ያለን ለካ ሊያገለግለን ፈልጎ ነው! ዘምሩልኝ ያለን ለካ ሊባርከን ፈለጎ ነው! ስጡኝ ያለን ለካ ሊሰጠን ፈልጎ ነው! እንጂማ የትኛውን ጉድለቱን ልንሟላ የትኛውን ደካሙን ለናግዝ " እርሱም ሕይወትንና እስትንፋስን ሁሉንም ለሁሉ ይሰጣልና አንዳች እንደሚጎድለው በሰው እጅ አይገለገልም።"
(የሐዋርያት ሥራ 17:25) ለካ የሳምራዊቷን ሴት ውሃ አጠጪን ያላት እንደተጠማች አውቆ የህይወትን ውሀ ሊያጠጣት ነው ለካ "ውሀ አጠጪን ብሎ ውሃ የሚጠጣ የአባት ብልጠት" " ኢየሱስ መልሶ።... ውኃ አጠጪኝ የሚልሽ ማን መሆኑንስ ብታውቂ፥ አንቺ ትለምኚው ነበርሽ የሕይወትም ውኃ ይሰጥሽ ነበር አላት።"
(የዮሐንስ ወንጌል 4:10) እሷማ ምንታርግ ምድራዊ ውሃ የሚለምን ሰማያዊ ውሃ ያጠጣኛል ብላ እንዴት ትጠርጥር የአባቷ ብልጠት አልገባትም "ሊያጠጣ ሲፈልጎ አጠጡኝ እንደሚል "
እግዚአብሔር አምላክ ሕዝቡን ከባርነት ቤት ሲያወጣ ያለውን ተመልከቱ " እግዚአብሔርም ሙሴን ተናገረው። ወደ ፈርዖን ግባ እንዲህም በለው። እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። ያገለግለኝ ዘንድ ሕዝቤን ልቀቅ።"(ኦሪት ዘጸአት 8:1) የእውነት ግን እስራኤል ነው እግዚአብሔርን ያገለገለው ወይስ እግዚአብሔር ነው የእስራኤልን ያገለገለው? ማነው መና ከሰማይ ያወረደው? ማነው ደመና ጋርዶ የእሳት አምድ ዘርግቶ ያገለገለው? ማነው በምድረ በዳ ከነክፉ አመላቸው እንደ ንስር በክንፍ የተሸከማቸው? እግዚአብሔር ነው። እነሱማ አስመረሩት እንኩዋን ሊያገለግሉት። ታገለግሉኛላችሁ ብሎ አውጥጦ እራሱ አገለገላቸው ።
የአባቴ ብልጠት አገልግሉኝ እያለ ማገልገሉ፤ አክብሩኝ ያለ ማክበሩ፤ ስጡኝ እያለ መስጠቱ ነው። እኔ በአባቴ ብልጠት ተገርሚያለሁ እናንተስ?
@bamatub
@bamatub
@bamatub
