HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Open in Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Show more2 276
Subscribers
+524 hours
+117 days
+3430 days
Posts Archive
በጭንቀትና በመከራ ውስጥ ስትሆኑ ይኼንን ብትጸልዩ ብዙ ታተርፋላችሁ!! እህታችን መልክአ ኡራኤልን ዘወትር በመጸለይ የሆነውን ተመልከቱ! https://youtu.be/eVh0vsTk7Lw?si=cdFaFkDOOqlqkfmN
#በተሸለመበት_የፍዝክስ_መጽሐፍ_መተት_አሰርተው_ልጁን_አሳበዱት!! ቅዱስ ቁርባን ባሕሪን ይገራል እውቀትን ይሰጣል ልጆችን ያረጋጋል!! #ethiopia #ጸሎት https://youtu.be/s9vLWJERLfU
«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!»
+++ ሄሮድስም ከሞተ በኋላ፥ እነሆ፥ የጌታ መልአክ በግብፅ ለዮሴፍ በሕልም ታይቶ። የሕፃኑን ነፍስ የፈለጉት ሞተዋልና ተነሣ፥ ሕፃኑን እናቱንም ይዘህ ወደ እስራኤል አገር ሂድ አለ። እርሱም ተነሥቶ ሕፃኑንና እናቱን ያዘና ወደ እስራኤል አገር ገባ። በአባቱም በሄሮድስ ፈንታ አርኬላዎስ በይሁዳ እንደ ነገሠ በሰማ ጊዜ፥ ወደዚያ መሄድን ፈራ፤ በሕልምም ተረድቶ ወደ ገሊላ አገር ሄደ፤ በነቢያት። ናዝራዊ ይባላል የተባለው ይፈጸም ዘንድ፥ ናዝሬት ወደምትባል ከተማ መጥቶ ኖረ። (የማቴ.2፡19-23)
5ቱ የመተት መታደስን ለማስቆም የሚረዱ የጸሎት ክፍሎች! መታቹንና አስመታቹን ክፉኛ የሚቀጡ የጸሎት ክፍሎች! https://youtu.be/DrMTMXVfupc?si=fIf6Zo3wskZvC8qi
የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!
+++ የአስቆሮቱ ያይደለ ይሁዳ። ጌታ ሆይ፥ ለዓለም ሳይሆን ራስህን ለእኛ ልትገልጥ ያለህ እንዴት ነው? አለው። ኢየሱስም መለሰ አለውም። የሚወደኝ ቢኖር ቃሌን ይጠብቃል፤ አባቴም ይወደዋል ወደ እርሱም እንመጣለን በእርሱም ዘንድ መኖሪያ እናደርጋለን።
የማይወደኝ ቃሌን አይጠብቅም፤ የምትሰሙትም ቃል የላከኝ የአብ ነው እንጂ የእኔ አይደለም። ከእናንተ ዘንድ ስኖር ይህን ነግሬአችኋለሁ፤ አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል። ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም። ልባችሁ አይታወክ አይፍራም። እኔ እሄዳለሁ ወደ እናንተም እመጣለሁ እንዳልኋችሁ ሰማችሁ። የምትወዱኝስ ብትሆኑ ከእኔ አብ ይበልጣልና ወደ አብ በመሄዴ ደስ ባላችሁ ነበር።
ከሆነም በኋላ ታምኑ ዘንድ አሁን አስቀድሞ ሳይሆን። ነግሬአችኋለሁ። ከእንግዲህ ወዲህ ከእናንተ ጋር ብዙ አልናገርም፥ የዚህ ዓለም ገዥ ይመጣልና፤ በእኔ ላይም አንዳች የለውም፤ ነገር ግን አብን እንድወድ ዓለም ሊያውቅ፥ አብም እንዳዘዘኝ፥ እንዲሁ አደርጋለሁ። ተነሡ፤ ከዚህ እንሂድ።
(የዮሐንስ ወንጌል 14፡22-መጨረሻው)
ሰኔ ፲፭ /15/በዚች ቀን የሰማይ ጭፍራ የተባለ የቅዱስ ሚናስ ቤተ ክርስቲያኑ መርዩጥ በተባለ አገር የከበረችበት ነው። ከዚህ አስቀድሞ የቅዱስ ሚናስ ሥጋ ተሠውሮ ይኖር ነበር። ጌታችንም ሊገልጠው በወደደ ጊዜ ምክንያት አደረገ ይኸውም እንዲህ ነው ፥ የቅዱስ ሚናስ ሥጋው ተደፍኖ በሚኖርበት ኮረብታ አቅራቢያ በጎችን የሚያረባ አንድ ሰው በጎቹን እየጠበቀ ይኖር ነበር። ከዚያ እረኛ በጎች ውስጥ ደዌ ያለበት አንዱ በግ በዚያ በኮረብታው አጠገብ ባለ የጉድጓድ ውኃ ተጠምቆ ወዲያውኑ ከደዌው ዳነ። እረኛውም አይቶ አደነቀ ሌሎችንም ደዌ ያለባቸውን አመጣ በዚያ ውኃም በታጠቡ ጊዜ ሁሉም ዳኑ። ከዚህም በኋላ ይህ በቦታው ሁሉ ታወቀ፡ ደዌ ያለባቸውም ሁሉ እየመጡ አፈሩን ከውኃው ጋር አንድ አድርገው ለውሰው በመቀባት ወዲያውኑ ይድኑ ነበሩ ምክንያቱን ግን አላወቁም። በዚያ ውኃና በአፈሩ በሽተኞችን እንደሚያድን የዚያ በግ ጠባቂ ወሬው በሮሙ ንጉሥ ዘንድ ተሰማ። ለንጉሡም የቁስል ደዌ የታመመች ልጅ ነበረችው። ወደ በግ ጠባቂውም ላካት እርሱም በጎቹን እንደ አዳናቸው አዳናት። እርሷም በተፈወሰች ጊዜ በዚያ ቦታ ፈውስ የሚደረግበትን ምክንያት ታውቅ ዘንድ ወደደች። ከዚህ በኋላ ቅዱስ ሚናስ በሕልም ተገለጸላትና ሥጋዬ በዚህ ቦታ ተደፍኖ ስለሚኖርእነሆ አስቆፍረሽ ታወጪው ዘንድ እግዚአብሔር አዞሻል አላት። ከእንቅልፍዋም በነቃች ጊዜ ቅዱስ ሚናስ እንዳዘዛት አደረገች። የከበረ ሥጋውንም አወጣች በዚያም ውብ የሆነች ቤተ ክርስቲያን ሠራችለት ንጉሡም በዚያ ቦታ ከተማ እንዲሠሩ መኳንንቱንና ሹሞቹን አዘዛቸው ታላቅ ከተማም ተሠራች ሰሟም መርዩጥ ተባለች። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239
በትዳራቸው ከሚማግጡ ሰዎች ጀርባ ያለው የአጋንንት ሴራና ተንኮል! ሴቶችን ወንዳወንድ አድርጎ የሚያሳይ የወንድ ዛር አጋንንት! ጭፈራ ቤት ገብተን የምንሸምተው የአጋንንት ሠራዊት!
https://youtu.be/vGDK2907kQs?si=P5yYMZ68Gn006rCP
#መምህር_ግርማ_ጋር_ሄጄ_ከተፈወስኩ_በኋላ_ጤናውና_በረከቱ_ተመለሰልኝ!! እግዚአብሔር የATM ማሽን የሚመስለው ብዙ ሰው አለ!! #hailegebriel #ጸሎት https://youtu.be/b5D5DC1x2vs
የዕለቱን ወንጌል አንብቡት!
+++ ከዚህም ሁሉ በፊት እጃቸውን በላያችሁ ይጭናሉ ያሳድዱአችሁማል፤ ስለ ስሜም ወደ ምኵራብና ወደ ወኅኒ አሳልፈው ይሰጡአችኋል፥ ወደ ነገሥታትና ወደ ገዥዎችም ይወስዱአችኋል፤ ይህም ለምስክርነት ይሆንላችኋል። ሰለዚህ እንዴት እንድትመልሱ አስቀድማችሁ እንዳታስቡ በልባችሁ አኑሩት፤ (የሉቃስ ወንጌል 21፡12-14)
ሰኔ ፲፬ /14/በዚች ቀን ቅዱሳን አባ አክራና፣ ዮሐንስ፣ አብጥልማና ፊልጶስ በሰማዕትነት ሞቱ። ይህም ቅዱስ አክራ ከግብጽ ደቡብ ይምንሑር ከሚባል አገር ሰዎች ወገን ነው ስሙ ፊልጶስ የሚባል ወንድም ነበረው እነርሱም ባለጸጎች ነበሩ ስማቸው ዮሐንስና፣ አብጥልማ ከሚባል ሁለት ቀሳውስት ጋራ ሰማዕታት ይሆኑ ዘንድ ተስማሙ አራቱም ቀርጥስ ወደሚባል አገር ሔዱ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በመኰንኑ ፊት ታመኑ። መኰንኑም በቀስቶች እንዲነድፏቸው አዘዘ ግን ቀስቶች አልነኳቸውም። ሁለተኛም እሳትን አንድደው በሚነድ የእሳት ምድጃ ውስጥ ይጨምሩአቸው ዘንድ አዘዘ እንዲሁም አደረጉባቸው ጌታም መልአኩን ልኮ አዳናቸው። ከዚህም በኋላ በፈረስ ጅራት ላይ አሥረው ከቀርጥስ ከተማ እስከ ይምንሑር አገርድረስ ይጐትቷቸው ዘንድ አዘዘና ይህንንም አድረጉባቸው ግን ምንም ምን ጉዳት አልደረሰባቸውም። ከዚህም በኋላ ራሶቻቸውን በሰይፍ እንዲቆርጧችው አዘዘ ከይምንሑር ከተማም አውጥተው ራሶቻቸውን ቆረጡአቸው። ፃ ከሚባል አገር ሰዎች መጥተው የቅዱስ አባ አክራን ሥጋውን ወሰዱ ውብ የሆነች ቤተ ክርስቲያንም ሠርተው ሥጋውን በውስጧ አኖሩ ከእርሱም ታላላቅ ድንቆችና ተአምራት በብዛት ተገለጡ። እንዲሁም የእነዚያን የሦስቱን ቅዳሳን የፊልጶስን፣ ለአብጥልማንና የዮሐንስን ሥጋቸውን ከይምንሑር ከተማ ሰዎች መጥተው ወሰዱ በመልካም ልብሶችም ገነዙአቸው ጥሩ ቤተ ክርስቲያንም ሠርተው ሥጋቸውን በውስጧ አኖሩ ከእነርሳቸውም ቁጥር የሌለው ድንቅ ተአምርተገለጠ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239
በመምህር ተስፋዬና በሊቃውንቱ መካከል የተፈጠረው ምንድነው? ያልተጠመቁ አጥማቂያን የሚሉ የመናፍስት ውጊያ ያልገባቸው ሊቃውንቶች! https://youtu.be/QgJfrNQDMhg?si=j3LTDxPkt0P2dz8r
+++ አባታችን መምህር ግርማ ያስተማሩን ልናዳምጠው የሚገባ ወሳኝ መልዕክት! የሚጸልይ ነገር ግን የማይማር ሰው ትዕብተኛ ነው!! በጠባቡ በር ለመግባት ምን እናድርግ? https://www.youtube.com/watch?v=YlhlRvUYDTY&pp=ygUNaGFpbGUgZ2VicmllbA%3D%3D
+++ ከማስተዋል መንገድ የሚሳሳት ሰው በሙታን ጉባኤ ያርፋል። ተድላ የሚወድድ ድሀ ይሆናል፥ የወይን ጠጅንና ዘይትንም የሚወድድ ባለጠጋ አይሆንም። ኀጥእ የጻድቅ ቤዛ ነው፤ በደለኛም የቅን ሰው ቤዛ ነው። ከጠበኛና ከቍጡ ሴት ጋር ከመቀመጥ በምድረ በዳ መቀመጥ ይሻላል። የከበረ መዝገብና ዘይት በጠቢብ ሰው ቤት ይኖራል። አእምሮ የሌለው ሰው ግን ይውጠዋል። ጽድቅንና ምሕረትን የሚከተል ሕይወትንና ጽድቅን ክብርንም ያገኛል። ጠቢብ የኃያላንን ከተማ ይገባባታል፥ የሚታመኑበትንም ኃይል ያፈርሳል። አፉንና ምላሱን የሚጠብቅ ነፍሱን ከመከራ ይጠብቃል። ኵሩና ተጓዳጅ ሰው ፌዘኛ ይባላል፤ እርሱም በትዕቢት ቍጣ ያደርጋል። ታካችን ምኞቱ ትገድለዋለች፥ እጆቹ ይሠሩ ዘንድ አይፈቅዱምና። (ምሳሌ፡21፡16-25)
ቅዱስ ሚካኤል የአመቱ ሰው ይበለን። ትላንት በነበረን ነዝክርና የበረከት ሥራ መርሃ ገብር በጎሮ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ተካሂዷል። በመጨረሻም የአባቶች ምርቃት ይሄንን ይመስላል ይደረሳችሁ። አሜን በሉ ሁላችሁም። 🙏
የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!
+++ ከአለቆችም አንዱ። ቸር መምህር፥ የዘላለምን ሕይወት እንድወርስ ምን ላድርግ? ብሎ ጠየቀው። ኢየሱስም። ስለ ምን ቸር ትለኛለህ? ከአንዱ ከእግዚአብሔር በቀር ቸር ማንም የለም። ትእዛዛቱን ታውቃለህ፥ አታመንዝር፥ አትግደል፥ አትስረቅ፥ በሐሰት አትመስክር፥ አባትህንና እናትህን አክብር አለው። እርሱም። ይህን ሁሉ ከሕፃንናቴ ጀምሬ ጠብቄአለሁ አለ። ኢየሱስም ይህን ሰምቶ። አንዲት ገና ቀርታሃለች፤ ያለህን ሁሉ ሽጠህ ለድሆች ስጥ፥ በሰማይም መዝገብ ታገኛለህ፥ መጥተህም ተከተለኝ አለው። እርሱ ግን ይህን ሰምቶ እጅግ ባለ ጠጋ ነበርና ብዙ አዘነ። (የሉቃስ ወንጌል 18፡18-23)
+5
በድጋሚ እንኳን ለቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። ዛሬ በጎሮ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን እግዚአብሔር ፈቅዱ እዚህ አክብረናል። እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን። 🙏
+9
«ከኃያሉ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል በቀር ማንም የሚያጸናኝ የለም። ዳን ፲፥፳፩» እንኳን ለቅዱስ ሚካኤል አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። ቅዱስ ሚካኤል አማላጅነቱ፣ ረድኤት በረከት፣ ቃልኪዳኑ ከሁላችን ጋር ይሁን። በርቱ፣ ጠንክሩ! አምላከ ቅዱስ ሚካኤል ስለ ቅዱስ ሚካኤል ብሎ ይማረን፣ ይቅር ይበለን።
#የመናፍስት_ውጊያ_ትምህርት_በዘመናችን_ለምን_ጭቅጭቅና_ተቃውሞ_ገጠመው?? ለድምጽና ለአብነት ብለው መናፍስትን የሚዋረሱ ሰዎች መጨረሻቸው!! #ebs #seifu https://youtu.be/FX8rchJhdWE
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
