en
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Open in Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Show more
2 276
Subscribers
+524 hours
+117 days
+3430 days
Posts Archive
#የመናፍስት_ውጊያ_ትምህርት_በዘመናችን_ለምን_ጭቅጭቅና_ተቃውሞ_ገጠመው?? ለድምጽና ለአብነት ብለው መናፍስትን የሚዋረሱ ሰዎች መጨረሻቸው!! #ebs #seifu https://youtu.be/FX8rchJhdWE

ሰኔ ፲፩ /11/ በዚችው ቀን በጦርነት ድል አድራጊው ከቤተ መንግሥት ወገን የሆነ የመላእክት አርአያ ያለው የከበረ ሰማዕት ገላውዴዎስ የተጋድሎው ፍጻሜ ነው። ይህ ቅዱስ ምድራዊ መንግሥትንና የዚህን
ሰኔ ፲፩ /11/
በዚችው ቀን በጦርነት ድል አድራጊው ከቤተ መንግሥት ወገን የሆነ የመላእክት አርአያ ያለው የከበረ ሰማዕት ገላውዴዎስ የተጋድሎው ፍጻሜ ነው። ይህ ቅዱስ ምድራዊ መንግሥትንና የዚህን ዓለም ክብር የናቀ ነበረ መልካም ገድልንም ተጋደለ። የማይጠፋ ሰማያዊ መንግሥትንና የማያልቅ ክብርንም ወረሰ። የዚህም ቅዱስ የአባቱ ስም አብጥልዎስ ነው እርሱም ለሮም ንጉሥ ለኑማርያኖስ ወንድሙ ነው መልኩም እንደ እስራኤል ያዕቆብ ልጅ እንደ ዮሴፍ እጅግ ውብ ነበር። ዲዮቅልጢአኖስም ሊሸነግለው ቢሞክር አልደሳካለትም በመጨረሻም ከወዳጁ ፊቅጦር ጋር ወደ ግብፅ ንጉስ እንዲሸነግላቸው ላካቸው። ወደ እንዴናው ገዥ ወደ አርያኖስም በደረሰ ጊዜ አርያኖስ አይቶ ደነገጠ ተነሥቶም እጁን ሳመው እንዲህም ብሎ ለመነው። ጌታዬ ገላውዴዎስ ሆይ ይህን ሥራ አትሥራ የንጉሥንም ትዕዛዝ አትተላለፍ። ቅዱስ ገላውዴዎስም እንዲህ ሲል መለሰለት ንጉሥ ያዘዘህን ልትፈፅም እንጂ በነገርህ ልታስተኝ አልተላክሁም አለው። መኰንኑም እስከሚቆጣ ድረስ እንዲህ እርስበርሳቸው ይነጋገሩ ነበር በመኰንኑም እጅ ጦር ነበረ ቅዱስ ገላውዴዎስንም ወጋው ነፍሱንም ክብርይግባውና በጌታችን እጅ ሰጠ በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!!» +++ በምትገቡባትም በማናቸይቱም ከተማ ወይም መንደር፥ በዚያ የሚገባው ማን እንደ ሆነ በጥንቃቄ መርምሩ፤ እስክትወጡም ድረስ በዚያ ተቀመጡ። ወደ ቤትም ስትገቡ ሰላምታ ስጡ፤ ቤቱም የሚገባው ቢሆን ሰላማችሁ ይድረስለት፤ ባይገባው ግን ሰላማችሁ ይመለስላችሁ። ከማይቀበላችሁም ቃላችሁንም ከማይሰሙ ሁሉ፥ ከዚያ ቤት ወይም ከዚያች ከተማ ስትወጡ የእግራችሁን ትቢያ አራግፉ። እውነት እላችኋለሁ፥ በፍርድ ቀን ከዚያች ከተማ ይልቅ ለሰዶምና ለገሞራ አገር ይቀልላቸዋል። እነሆ፥ እኔ እንደ በጎች በተኵላዎች መካከል እልካችኋለሁ፤ ስለዚህ እንደ እባብ ልባሞች እንደ ርግብም የዋሆች ሁኑ። ነገር ግን ወደ ሸንጎ አሳልፈው ይሰጡአችኋል፥ በምኩራቦቻቸውም ይገርፉአችኋልና ከሰዎች ተጠበቁ፤ ለእነርሱና ለአሕዛብም ምስክር እንዲሆን፥ ስለ እኔ ወደ ገዥዎች ወደ ነገሥታትም ትወሰዳላችሁ። አሳልፈውም ሲሰጡአችሁ፥ የምትናገሩት በዚያች ሰዓት ይሰጣችኋልና እንዴት ወይስ ምን እንድትናገሩ አትጨነቁ፤ በእናንተ የሚናገር የአባታችሁ መንፈስ ነው እንጂ፥ የምትናገሩ እናንተ አይደላችሁምና። ወንድምም ወንድሙን፥ አባትም ልጁን ለሞት አሳልፎ ይሰጣል፥ ልጆችም በወላጆቻቸው ላይ ይነሣሉ ይገድሉአቸውማል። በሁሉም ስለ ስሜ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ፤ እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል። በአንዲቱ ከተማም መከራ ቢያሳዩአችሁ ወደ ሌላይቱ ሽሹ፤ እውነት እላችኋለሁና፥ የሰው ልጅ እስኪመጣ ድረስ የእስራኤልን ከተማዎች አትዘልቁም። ደቀ መዝሙር ከመምህሩ፥ ባሪያም ከጌታው አይበልጥም። ደቀ መዝሙር እንደ መምህሩ፥ ባሪያም እንደ ጌታው መሆኑ ይበቃዋል። ባለቤቱን ብዔል ዜቡል ካሉት፥ ቤተሰዎቹንማ እንዴት አብዝተው አይሉአቸው! እንግዲህ አትፍሩአቸው፤ የማይገለጥ የተከደነ፥ የማይታወቅም የተሰወረ ምንም የለምና። በጨለማ የምነግራችሁን በብርሃን ተናገሩ፤ በጆሮም የምትሰሙትን በሰገነት ላይ ስበኩ። ሥጋንም የሚገድሉትን ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ፤ ይልቅስ ነፍስንም ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ የሚቻለውን ፍሩ። ሁለት ድንቢጦች በአምስት ሳንቲም ይሸጡ የለምን? ከእነርሱም አንዲቱ ያለ አባታችሁ ፈቃድ በምድር ላይ አትወድቅም። የእናንተስ የራሳችሁ ጠጉር ሁሉ እንኳ ተቈጥሮአል። እንግዲህ አትፍሩ ከብዙ ድንቢጦች እናንተ ትበልጣላችሁ። ስለዚህ በሰው ፊት ለሚመሰክርልኝ ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እመሰክርለታለሁ፤ በሰው ፊትም የሚክደኝን ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እክደዋለሁ። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

#ከሞት_የተነሳችው_ልጅ_ያጋለጠችው_ከባድ_ምስጢር!! ከኦርቶዶክስ ለምን ወደ እስልምና ሄደች? ዲያብሎስ ክርስትና እንድጠላና እንድሰደብ ያደርገውን ተመልከቱ!! https://youtu.be/l0HmTcKag_U?si=f1zviqtVfmlsPZWl

#ምስጢር_ሳናወጣ_ቶሎ_ሸኘን_አፍዝዘን_አደንዝዘን_ቁጭ_አደረግናት!! ዕድላችን በመተትና ዓይነጥላ ከታሰረ እንዲህ ይሆናል! የእርግማን ትውልድ ምልክቶች! #ጸሎት https://youtu.be/t-n9Cmb7cQ0

ሰኔ ፲ /10/ በዚች ዕለት ለክርስቲያን ወገኖች በዓለሙ ሁሉ ታላቅ ደስታ ሆነ መላእክትም በሰማያት ደስ ተሰኙባት። በዚች ቀን ዕውነተኛ ምእመን ከሆነ ከንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ዘንድ የጣዖት ቤቶች እንዲዘ
ሰኔ ፲ /10/
በዚች ዕለት ለክርስቲያን ወገኖች በዓለሙ ሁሉ ታላቅ ደስታ ሆነ መላእክትም በሰማያት ደስ ተሰኙባት። በዚች ቀን ዕውነተኛ ምእመን ከሆነ ከንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ዘንድ የጣዖት ቤቶች እንዲዘጉ አብያተ ክርስቲያናትም እንዲከፈቱ ትእዛዝ ወጥቷልና። ደስታን የተመላች ያች መልእክት ወደ እስክንድርያ ከተማ እንደ በዛሬዋ ቀን በደረሰች ጊዜ ፈጽሞ ደስ ተሰኙ ወደ ግብጽ አውራጃዎችም ሁሉ ላኳት ምእመናን ሁሉ ስለ ቤተ ክርስቲያን ክብር ከፍ ከፍ ማለት ደስ አላቸው። የጣዖታት ቤቶችንም ዘጓቸው አብያተ ክርስቲያናትንም ከፈቱአቸው እንደ ዛሬም በዚች ዕለት በዓል አደረጉ ይኸውም ቈስጠንጢኖስ በነገሠ በዐሥራ አንድ ዓመቱ ነበር እለእስክንድሮስም ሊቀ ጵጵስና በተሾመባት በመጀመሪያ ዓመት ነበር። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በእኛ ላይም ይቅርታውና ቸርነቱ ይደረግልን ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

#መንፈስ_የሌብኝም_እኔን_አይነካኝም_ብላችሁ_ግግም_የምትሉ ይኼንን አዳምጡ!! በሕይወት ያለ ውሻ ለድግምት የሚቀብሩ መተተኞች! ጠልሰም ይዞብን የመጣው መዘዝ!! https://youtu.be/hM1xiztNmXE?si=Ji-AY_iVeH_LB0Xu

«ጸሎት» +++ ሁሉም ነገር ለፍቃድህ የሚገዛልህና የሚታዘዝልህ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፡ ያደረግሁትን ነገር ሁሉ ይቅር በለኝ፡ ኃጢአተኛ የሆንኩትን እኔን ከአሁን በኃላ እንዳልበድል አድርገኝ። ጌታ ሆይ፡ የማይገባኝ መሆነን ባውቅም ከኃጢአቴ ሁሉ ልታነጻኝ ትችላለህ። ጌታ ሆይ፡ ሰው ፊትን እንደሚያይ፡ አንተ ግን ልብን እንደሚታይ አውቃለሁ። ቅዱስ መንፈስህን ወደ ውስጤ ጥልቅ ላክልኝ፡ ነፍሴንና ሥጋዬን ይኖርበትና ገንዘቡ ያደርገው ዘንድ። ያለ አንተ ልድን አልችልም፡ በምትጠብቀኝ በአንተ ግን ማዳንህን እናፍቃለሁ። እናም አሁን አንተን ማዳንህን እለምንሃለሁ። የአንተን ጠብብ እሻለሁ፡ የሚረዳኝንና የሚጠብቀኝን ታላቁን ደግነትህንና ቸርነትህን እማጸናለሁ። ሁሉን ቻይ ታላቅ አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፡ በቀንና በሌሊት የአንተን መኖር አስታውስና አንተን ሁል ጊዜ በፊቴ አደርግህ ዘንድ ልቤን ምራልኝ። + አሜን +

«ተወዳጆች! እግዚአብሔር ከእኛ ከደካሞች ጋር እንደሆነ ዲያብሎስ ጠንቂቆ ያውቃል እኛ ግን አናውቅም። ታዲያ አስተውሉ! እግዚአብሔር ሁለም ከእኛ ጋር ነው ቤተሰቦቼ!»

እናት አባቶቻችሁ እንዲቆርቡ ከፈለጋችሁ በቅድሚያ ይኼንን አድርጉ!! በመስተፋቅር ተጋብተው የተወለዱ ልጆች ጸባይና አመል! https://youtu.be/n-cTxJWV3q4?si=7_zyj1585QJEXzsR

ሰላም ውድ ቤተሰቦቼ እንዴት ናችሁ። ሰንበት እንዴት ነበር? ቤተሰቦቼ ለቅዱስ ሚካኤል ለሰኔ 12 ዓመታዊ ክብረ በዓል ለዝክር መሳተፍ የምትፈልጉ ብዬ በጠየኩት መሠረት (37,000) ብር ሰብስበናል እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን። በእውነት በዚህ የበረከት ሥራ የተሳተፋችሁ እህታችን ወለተ ሚካኤልና ቤተሰቦቿ፣ ገብረ ጻድቅና ቤተሰቦቹ እግዚአብሔር ያክብርልኝ በወጣ ይተካላችሉ። ወለተ ሚካኤልና ቤተሰቦቿ (30,000) እንዲሁ ወንድማችን ገብረጻድቅና ቤተሰቦቹ (7000) በአጠቃላይ 37,000 ብር ዛሬ ለዝክሩ ማህበር ካህናት አባቶች ባሉበት አስረክበናል በዛሬው ዕለት። እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን። ደግሞ መሳተፍ ፈልጋችሁ በተለያዬ ምክንያት ያልሆነላችሁ ቅዱስ ሚካኤል አሳባችሁን ይሙላላችሁ። ገንዘብ መስጠት ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔር ማሰባችንንም ይቆጥረዋልና እግዚአብሔር አሳባችሁን መሻታችሁን ሞልቶላችሁ ደግሞ በሌላ የበረከት ሥራ እንገናኛለን። በርቱ እላለሁኝ። 🙏 እግዚአብሔር ለዕለቱ በሰላም በጤና ያድርሰን። በዛን ዕለት ያለውን ነገር ደግሞ የምናጋራችሁ ይሆናል። 🙏 ሰላም ሁኑ! በርቱ

#ከወንድም_ከሴትም_ጋር_እተኛለሁ_የዘመኑ_ሰዎች_አሳፋሪ_ንግግር! የሉሲፈር መንፈስ የአያያዝ ስልቱና ጥፋቱ! መተት በጸጉራችን ሲደረግ ይኼንን ምልክት ታያላችሁ! https://youtu.be/b_wXcMJCtew?si=jVknpCOOxw4CjN6I

ሰኔ ፰ /8/ በዚች ቀን አምላክን የወለደች በሁለት ወገን ድንግል የሆነች የእመቤታችን ማርያም የታወቀችው በውኃ ምንጭ ዘንድ ያለች የቤተ ክርስቲያንዋ ቅዳሴ ነው። እርሱም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየ
ሰኔ ፰ /8/
በዚች ቀን አምላክን የወለደች በሁለት ወገን ድንግል የሆነች የእመቤታችን ማርያም የታወቀችው በውኃ ምንጭ ዘንድ ያለች የቤተ ክርስቲያንዋ ቅዳሴ ነው። እርሱም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእርሷ ጋር ወደ ግብጽ አገር ተሰዶ ሲመለስ ያፈለቀው የተባረከ መታጠቢያ ነው። ይህም እንዲህ ነው ለጻድቁ ዮሴፍ የእግዚአብሔር መልአክ በሕልም ተገልጾለት ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ግብጽ አገር ሒድ አለው። ዮሴፍም ነቅቶ ተነሣ ክብር ይግባውና ሕፃኑን ጌታችንን እናቱንና እኅቷ ሰሎሜን ይዞ ወደ ግብጽ አገር ሔዱ በዚያም በውስጧ ባሉ በብዙ አገሮች እየዞሩ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር ኖሩ። ሄሮድስም ከሞተ በኋላ የእግዚአብሔር መልአክ ለዮሴፍ ሁለተኛ ተገለጠለት ወደ እስራኤልም አገር ሕፃኑንና እናቱን ይዞ እንዲመለስ አዘዘው። በሚመለሱም ጊዜ ወደ መዓልቃ ደረሱ ከዚያም ወደ መጣርያ አገር ደረሱ ይቺም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ውኃ ያፈለቀባትና የመታጠቢያ ቦታ የሆነች ናት እርሷም እስከ ዛሬ አለች ሰዎችም ከአገሩ ሁሉ ከየነገዱ ሁሉ መጥተው አምላክን ወደ ወለደችና በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ ወደ ጸናች ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያም ይለምናሉ ከተባረከውም የውኃ ምንጭ ታጥበው ከደዌያቸው ሁሉ ይድናሉ በዛሬዪቱ ቀን ከከበረች ቤተ ክርስቲያንም ይባረካሉ። እርሷን እመቤታችንን ለመረጣትና ለወደዳት በሥጋም እናቱ ላደረጋት ስለርሷም ዘመድ ለሆነንና ወደርሱ ላቀረበን ወራሾቹም ላደረገን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

አሳፋሪው የቢንያም ሽታዬ ንግግርና ዳግም ቁልቁል የመውረድ ጉዳይ!! https://youtu.be/c8eawHLq8is?si=T27YnVCtA-Aw8Y2o

#ቤታችን_በአጋንንት_የመያዙና_የመጠቃቱ_ምልክቶችና_መፍትሔዎቹ!! ቤታችን ጸሎትና ስግደት ማድረግ ለምን ከበደን? #hailegebrielreacts19 #ጸሎት https://youtu.be/K08lLCp4ZQM

ሰኔ ፯ /7/ አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሰኔ ሰባት በዚች ቀን አምላክን የወለደች የእመቤታችን የድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን የተከፈተችበትና የከበረችበት ነው። እርሷም
ሰኔ ፯ /7/
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሰኔ ሰባት በዚች ቀን አምላክን የወለደች የእመቤታችን የድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን የተከፈተችበትና የከበረችበት ነው። እርሷም ዌላ በሚባል አደባባይ ያለች ሦስት ዓመት ከስድስት ወር ተዘግታ የኖረች ነበረች። ይኸውም በአንድ ሽህ ሃያ ዓመተ ሰማዕታት ነው። ከእመቤታችን ድንግል ማርያም ሰው ለሆነ ሕይወትና መድኃኒት አድርጎ እርሷን ለሰጠን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር

በመዝሙረ ዳዊት ጸሎት በውሻ የተደገመባትን መተትና ክፉ መንፈስ ያሸነፈች ጀግና!! ከሰዎች ሥጦታ ስንቀበል ልናደርግ የሚገቡ ጥንቃቄዎች!! Haile Gebriel Reacts19 https://youtu.be/ROHsNWyRrNA?si=7AFVb2zfcYgc6cEo

#የሰውን_ልጅ_የክፋት_ጥግ_ተመልከቱ_ሕጻኗን_በመተት_አፍዝዘው_አደንግዘው_ቁራኛ_አደረጓት!! ፖርኖግራፊ በዓይን የሚገባ ርኩሰትና ክፋት! #የሮፍናን_ኮንሰርት! https://youtu.be/jq6tvRBnOO8

#የዕለቱ_ወንጌል_አንብቡት! +++ አንተ ታናሽ መንጋ፥ መንግሥትን ሊሰጣችሁ የአባታችሁ በጎ ፈቃድ ነውና አትፍሩ። ያላችሁን ሽጡ ምጽዋትም ስጡ፤ ሌባ በማይቀርብበት ብልም በማያጠፋበት በሰማያት የማያል
#የዕለቱ_ወንጌል_አንብቡት! +++ አንተ ታናሽ መንጋ፥ መንግሥትን ሊሰጣችሁ የአባታችሁ በጎ ፈቃድ ነውና አትፍሩ። ያላችሁን ሽጡ ምጽዋትም ስጡ፤ ሌባ በማይቀርብበት ብልም በማያጠፋበት በሰማያት የማያልቅ መዝገብ የሚሆኑትን የማያረጁትንም ኮረጆዎች ለራሳችሁ አድርጉ፤ መዝገባችሁ ባለበት ልባችሁ ደግሞ በዚያ ይሆናልና። ወገባችሁ የታጠቀ መብራታችሁም የበራ ይሁን፤ እናንተም ጌታቸው መጥቶ ደጁን ሲያንኳኳ ወዲያው እንዲከፍቱለት ከሰርግ እስኪመለስ ድረስ የሚጠብቁ ሰዎችን ምሰሉ ጌታቸው በመጣ ጊዜ ሲተጉ የሚያገኛቸው እነዚያ ባሪያዎች ብፁዓን ናቸው፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ታጥቆ በማዕድ ያስቀምጣቸዋል ቀርቦም ያገለግላቸዋል። ከሌሊቱም በሁለተኛው ወይም በሦስተኛው ክፍል መጥቶ እንዲሁ ቢያገኛቸው፥ እነዚያ ባሪያዎች ብፁዓን ናቸው። ይህን ግን እወቁ ባለቤት በምን ሰዓት ሌባ እንዲመጣ ቢያውቅ ኖሮ፥ በነቃ፥ ቤቱም እንዲቆፈር ባልፈቀደም ነበር። እናንተ ደግሞ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ፥ የሰው ልጅ በማታስቡበት ሰዓት ይመጣልና። ጴጥሮስም። ጌታ ሆይ፥ ይህን ምሳሌ ለእኛ ወይስ ደግሞ ለሁሉ ትናገራለህን? አለው። ጌታም አለ። እንኪያስ ምግባቸውን በጊዜው ይሰጣቸው ዘንድ ጌታው በቤተ ሰዎቹ ላይ የሚሾመው ታማኝና ልባም መጋቢ ማን ነው? ጌታው መጥቶ እንዲህ ሲያደርግ የሚያገኘው ያ ባሪያ ብፁዕ ነው። እውነት እላችኋለሁ፥ ባለው ሁሉ ላይ ይሾመዋል። (የሉቃስ ወንጌል 12፡32-44) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

«በመንገድ እየሄድህ ሳለ በድልድይ ስር ስታልፍ ድንገት ከላይ የሚንጠባጠብ የቆሸሸ ውኃ ቢነካህ ሁኔታው ሊያናድድህ ይችላል። ነገር ግን ያ ቦታ እንደሚያፈስ እያወቅህ ተመላልሰህበት ከበሰበስህ ግን ጥፋቱ የአንተ እንጂ የማንም አይደለም። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደሚለው አንዳንዴ ልክ እንደዚያ ጠብታ ሰይጣን ወደ ኅሊናህ ሊያስገባ የሚሞክረው ነፍስህን የሚያቆሽሽ ክፉ ሐሳብ ይኖራል። አንዴ የነካህ ክፉ ሐሳብ ግን ተመላልሶ እንዲያቆሽሽህ ከፈቀድህ ተወቃሹ አንተ እንጂ ሰይጣን አይሆንም።» #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239