en
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Open in Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Show more
2 276
Subscribers
+324 hours
+137 days
+3830 days
Posts Archive
«ግብዝነት» ግብዝ ሰው (አስመሳይ ሰው) በድብቅ እግዚአብሔር የለም ብሎ የሚያምን ነው፤ እግዚአብሔር አለ ብሎ የሚያምን ቢኾን ኖሮ፣ እርሱን ፊት ለፊት ለማታለል ባልደፈረ ነበር። በሕይወታችን አስመሳይነትን ለብሰን የምንኖር ከኾነ አኗኗራችን ድራማ ይኾንብናል። የሚኾነውና እንዲኾን የምንፈልገው እርስ በእርሱ ይምታታብናል። መልካም መባል እጅግ የምንፈልግና በሰዎች ዘንድም እንደዛ እንድንባል የሚያደርጉ ነገሮችን በማስመሰል የምንተውን፡ ከእውነተኛ የመልካምነት ሕይወት ግን ፈጽሞ ራቅ ያልን ጥቂት ሰዎች አይደለንም። ግብዝነት ተግባራዊ የኾነ የመጠራጠር ሕይወት ነው። እግዚአብሔርን በአንደበታችን ላንክደው እንችላለን፣ በሕይወታችን ውስጥ ሰዎች እርሱን የምናመልክ አድርገው እንዲያስቡ አድርገን ልንተውን እንችላለን፡ በድብቅ ወይም በስውር በውስጣችን ያለው ግን ድፍረትና ትዕቢት፡ ራስን ማክበር ስለ ኾነ እግዚአብሔር ከሚፈቅደው ውጪ ኾነን እንገኛለን። የዚህ ኹሉ መነሻው ከእውነት መንገድ መውጣትና እውነትን በተግባራዊ የሕይወት ክፍላችን ውስጥ መግፋታችን ነው። ለዚህም ነው ሕይወታችን ከጥፍጥና ይልቅ ምሬት እንዲስማማው ያደረግነው። መልካም የኾነው እርሱ በአርአያውና በአምሳሉ ፈጠረን እኛ ግን በፈቃዳችን ጥመት ምክንያት ሌላ አርአያን ተላበስን። ውስጣችንን በዚህ ዓለም ፍቅር አሰከርናት፥ የእግዚአብሔር የኾነውን በጎ ነገር ከተግባራዊ ሕይወታችን አራቅነው፥ ራሳችን ላይ በክፉ ዝንባሌያችን ምክንያት የዝሙትን እሳት አነደድን። ራሳችንም ባነደድነው የዝሙት እሳት ተቃጠልን፣ ረከስን፣ ቆሸሽንም፤ ኾኖም በሰዎች ዘንድ ንጹሕ አድርገን ራሳችንን በማሳየት ጻድቅ ተሰኘን፥ ይህ በእጅጉ አስገራሚ ነው። ግብዝነታችን ከማደጉ የተነሣም፥ ግብዝ መኾናችንም ተረሳን፥ ውስጣችን በከንቱ ውዳሴ፥ በዚህ ዓለም ክብር ገነነች። ሰዎችን ከሰዎች አበላለጥን፥ ፍትሐዊነትን ከአእምሮችን በግብዝነታችን ብሩሽ አጠብናት፥ ፍትሕ ርትዕ የምትመስል ሌላ አዲስ ነገር አበጃጀን። ስለዚህም የማንሰማ፥ የማናስተውል፥ አፍቅሮተ ሰብእ የሌለን፥ በራስ ወዳድነት ጽናት የታጠርን፥ ከእግዚአብሔር ይልቅ ለዓለም የተመቸን፥ በውስጣችን ፈጽሞ የረከስን፥ ወደ እውነተኛ ሕይወት የመመለስ ፍላጎትና ወኔያችን የሞተብን ስንት ነን? እጅግ ብዙ! እግዚአብሔር በቸርነቱ ዓይነ ልቡናችንን ያብራል። ዮሐንስ ዘሰዋስው እንዲህ ይላል፦ "አንዳንድ ወጣት ሴቶች (ልጃገረዶች) መጥፎ የኾነውን ያለ ሓፍረት ይፈጽማሉ፤ ሌሎች ደግሞ በታላቅ ጭምትነት እየታዩ ኾኖም በድብቅ ከመጀመሪያዎቹ ይልቅ የባሰውን ይፈጽማሉ፤ ይህም አሳፋሪ ከኾኑ ፈቃዳት ጋር የሚመሳሰል ነው። እንደ መመጻደቅ፣ ክፋት፣ ጥልቅ ኀዘን፣ ሮሜ 1፥ 26 ጉዳቶችን ማሰብ፣ በልብ በሌሎች ላይ መዘበትን የመሰሉ ያልታመኑ (አስመሳይ የኾኑ) ብዙ ደንገጡሮች (ገረዶች) አሉ። አንድ ነገር በማሳየት ብቅ ይላሉ፣ ኾኖም ግን ከሚታየው ሌላ ተቃራኒ ኹኔታ አላቸው።" እንዲል። (ሳሙኤል ፍቃዱ (ተርጓሚ)፣ ምዕራግና ድርሳን፣ የመጀመርያ ዕትም 2011 ዓም ገጽ 168)። ይህ ሴቶችን ብቻ የሚመለከት ሳይኾን ወንዶችንም የሚመለከት ጉዳይ ነው። ውጫዊ ድርጊታችን ከጥልቅ ውስጣችን ጋር እጅግ ተቃራኒ የኾነብን ጥቂት አይደለንምና! ጥሩ መባልን የምንሻ፣ ነገር ግን በድርጊት ተቃራኒ የኾን፣ የምንቆረቆር የምንመስል ነገር ግን ከቤተ ክርስቲያን ሕግ ፈጽሞ የራቅን ስንት ግብዞች አለን! ሰዎች በውጭ የምናሳየውን ነገር አይተው እርሱማ ጎበዝ ነው፣ እርሷማ ጎበዝ ናት ብለው ያደናነቁን ፍሬ ቢስ አስመሳዮች ብዙ ነን። ይሄ የኃጢአትን ጣዕም ከመውደዳችን የተነሣ የመጣብን ፅኑ ሕማም መኾኑን ልብ እንበል። ከግብዝነት ሕይወት እንውጣ፤ ክርስቲያናዊውን ሕይወት በተግባር እንግለጥ። ክርስትና እንደ እግር ኳስ ጫዎታ 11 ሰዎችን አስገብቶ ከውጪ መጮኸ አይደለም። የደጋፊነት ሕይወት ሳይኾን በተግባር የሚገለጥ ሕይወት ነው። የብዙዎቻችን ችግር ከተግባር ውጪ ኾነን በተግባር ውስጥ በጥሩ ኹኔታ ያለን አስመስለን መተወናችን ነው። መፍትሔውም ወደ እውነት ለመመለስ ኹል ጊዜ ሳያቋርጡ መትጋት ነው። እውነት የምትሽሞደሞድ አይደለችም፥ በግል ስሜት የምትሠራም አይደለችም፥ ይልቅስ ከእግዚአብሔር ጋር ባለን አንድነት የምትረዳ ልዩ ሀብት ናት። ጌታ ራሱ "እኔ መንገድ እውነትና ሕይወት ነኝ" እንዳለ፥ እርሱ ባሳየን የአርአያነት ተግባራዊ የኾነ የእርስ በእርስ ፍቅር መንገድነት፥ እውነት የኾነውን የእርሱን ቃል አክብረን፥ ወደ ሕይወት መግባት አለብን። መንገዱን ካላገኘን እውነትን ሕይወትንም ማግኘት አንችልም። ስለዚህ ከግብዝነት ለመውጣት ስለ እውነት በእውነት መኖር መጀመር አለብን። በእውነተኛ የሕይወት ጎዳና ውስጥ እውነተኛ ፍቅር እና እውነተኛ ጣዕም ያለው ሕይወት አለና። ቆም ብለን አኗኗራችንን እንመርምር፥ የገፋናትን እውነት እንመልሳት፥ የጠላናትን አንድነት እንፈልጋት፥ ይህን ጊዜ የምናመልከው አምላክ ከግብዝነት እሳት ያድነናል። ይህ እሳካልኾነ ግብዝነታችንና ተመጻድቋችን ለማናስበው ትልቅ ችግር ይዳርገናል። ማስመሰላችንም ሕይወታችንን መራራና ርባና ቢስ ያደርግብናል፥ የሕይወት ብርሃንም ይነሣብናል። ይህን ኹሌም በማስተዋል ወደየ ልቡናችን እንመለስ! "አቤቱ ጌታችን ሆይ የኃጢአታችን ክምር የሰናዖርን ግንብ አኽሏል፤ የዐመፃችን ጽናትም ከፈርኦን ብሷል፤ ለምሕረት የላክከውን ሙሴን በትዕቢታችን አልቀበል ብለናል፤ በራሳችን ፈቃድ ለክፉ ሐሳብ ባርያ ኾነናል፤ ካንተ ይልቅ ተድላ ዓለምን መርጠናል፤ በማስመሰልና በግብዝነት ሕይወት ውስጥ ሰጥመን ገብተናል። ስለዚህ አምላካችን ሆይ ወደ እውነት እንመለስ ዘንድ ንጹሕ ልብን ፍጠርልን! ሕሊናችንን ያቆሳሰሉብንን የዚህ ዓለም ጫጫታዎችን አርቅልን። አቤቱ ሆይ በምሕረት ዓይኖችህ ተመልክተኸን ስለ ቸርነትህ ማረን! #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

#በልጅነቱ_እናቱ_ለጠንቋይና_ቃሊቻ_የገበረችው_ወጣት_አሳዛኝ_ታርክ!! ተገፍቼ ሃይማኖተን ቀየርኩ የምትሉ አዳምጡ!! ለንስሐ አባታችን መናገር የሌሉብን ነገሮች! https://youtu.be/Ne96tvnSMs0

«አቤቱ ጌታ ሆይ የምንራበው አንተን ነውና አንተነትህን ስጠን፤ የምንኖረው ከአንተ አፍ በሚወጣው በእያንዳንዱ ጣፋጭ ቃል ነውና እነዚህን ቃላትህን አድለን።» ብጹዕ አቡነ ሺኖዳ

#በሰሞነ_ሕማማትና_በዐቢይ_ጾም_ወቅት_የሚሰገድ_የንስሐ_ስግደት_በተግባር!! የንስሐ ስግደት እንዴት እንስገድ?? የዐቢይ ጾም ወቅት የሚሰገድ የንስሐ ስግደት!! https://youtu.be/njygiHkfbNA

#አጋንንትና_ስይጣን_በሦስት_ምክንያት_ከእኛ_አይወጣም!! ሚስት ለባሏ ትገዛ ማለት ምን ማለት ነው?? አጋንንት ውስጣችን ሲያደፍጡ ብዙ ነገር ያበላሻሉ!! https://youtu.be/TgMxZCubyjI

ሞርሞር የመቃብር መንፈስና ልጆችን ኦቲስቲክ የሚያደርገው የዛር መንፈስ https://youtu.be/H47RXvYFhn0?si=wik-wMF5f6QjUUnu

"ቁጡ ሰው ከመኾን ገር ሰው ወደ መኾን ከተለወጥህ፣ ጨካኝ ሰው ከመኾን ቸር ሰው ወደ መኾን ከተቀየርህ በተግባር አሳየኝ እንጂ 'ለአያሌ ቀናት ጾምሁ፤ ይህን ወይም ያን አልበላሁም፤ ወይን አልቀመስሁም፤ መሻቴን ገትቻለሁ' እያልህ አትንገረኝ፡፡ እስከ አሁን ቁጣን የተሞላህ ከኾነ ለምን ሥጋህን ታስጨንቃለህ?  ቂምና በቀል በልቡናህ ውስጥ ካሉ፥ ወይንን ሳይኾን ውኃ የምትጠጣው ለምንድን ነው?  ረብ ጥቅም የሌለውን ጾም አትጹም፤ ጾም ብቻዋን ወደ ላይ አታርግምና፡፡" (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ- የክርስቲያን መከራ ገጽ 71)

«ብፁዕ አቡነ አረጋዊ በሕመም ምክንያት በሀገር ውስጥ እና በውጪ ሀገር በሕክምና ሲረዱ ቆይተው መጋቢት 12 ቀን 2015 ዓ.ም በተወለዱ በ54 ዓመታቸው ከእዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። የብፁዕ አባታች
«ብፁዕ አቡነ አረጋዊ በሕመም ምክንያት በሀገር ውስጥ እና በውጪ ሀገር በሕክምና ሲረዱ ቆይተው መጋቢት 12 ቀን 2015 ዓ.ም በተወለዱ በ54 ዓመታቸው ከእዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። የብፁዕ አባታችን በረከታቸው ይደርብን አሜን!!!»

መምህር ተስፋዬ Live ላይ እያለ የተላከበት የደብተራ መንፈስና ሴራው!! መናፍስትን መልሶ ወደ መታቹ እንዴት መላክ ይቻላል?? የጥላወጊ መንፈስና ጥፋቱ!! https://youtu.be/am2JtLN5j-k

በመምህር ተስፋዬና በአባ ገብረኪዳን መካከል ምንድነው የተፈጠረው?? የጬሌና የዛር መንፈሶችን ለመላቀቅ መንገዱ!! ለምንድነው የመናፍስት ሴራ አልገባ ያለን?? https://youtu.be/7ldreHGm_hk

"ነገሮችን የምሸከምበት ጥንካሬን እንዲሰጠኝ እግዚአብሔርን ለምኜው ነበር። እርሱ ግን በእርሱ ላይ እንድደገፍበት የሚያደርገኝን ድካም ሰጠኝ።" => በራሱ ትግል ከሚታመን ኅያል ይልቅ፣ እግዚአብሔርን ጉልበት የሚያደርግ ደካማ ይበረታል። እግዚአብሔርን ከሚያስረሳ ጥንካሬ ይልቅ፣ እርሱ ላይ የሚያስደግፍ ድካም ይሻላል። "ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ"

#ስለ_እርሱ_አንብቡ እግዚአብሔር በአሳባችሁ ውስጥ እንዲኖር ስለ እርሱ አብዝታችሁ #አንብቡ። እርሱን ለማወቅ ስለ እርሱ #አንብቡ። እርሱን ካላወቃችሁት እንዴት እርሱን ልትወዱት ትችላላችሁ? ስለ እርሱ #አንብቡ፤ ስታነቡ ግን በሳይንሳዊ ወይም በፍልስፍና ጠባይ አታንብቡ ወይም ደግሞ ስለ እርሱ ጥናታዊ ጽሑፍ ወይም ትምህርት ለመስጠት አታንብቡ። ነገር ግን ወደ እርሱ ጥልቀት ለመግባት ወይም እርሱ ወደ እናንተ ጥልቀት እንዲገባ #አንብቡ። ለነፍሳችሁ ውድ የሆኑትን የእርሱን ባሕርያት ለማወቅ ስትሉ #አንብቡ ይህ እውቀት አሳባችሁ ከእርሱ ጋር እንዲጣበቅና ፍቅሩ ከእናንተ ልብ ጋር እንዲቀናጅ ያደርግላችኋልና። ስለ ስምምነቱ ስትሉም #አንብቡ። ከወደዱት ሰዎች ጋር ስላለው ግንኙነት በጠላቶቹ ላይ ስላለው አቋም ስትሉ #አንብቡ! እግዚአብሔር ቸር እንደ ሆነ ቀምሳችሁ ታዩ ዘንድ ስለ እርሱ #አንብቡ። ታዲያ ንባባችሁ ለልባችሁ ምግብ እንዲሆን እንጂ እንዲሁ ተራ ንባብ እንዲሆን አትፍቀዱ። ስለ እግዚአብሔር ብዙ ካነበባችሁ በእርሱ ዘንድ ያለውን ፍጹምነት በሙሉ ታገኛላችሁ። ከወደዳችሁት ስለ እርሱ ማንበባችሁን ትቀጥላላችሁ። እግዚአብሔር ስለ እርሱ የሚያነቡትን ስለ እርሱ ዜና የሚጠይቁትን ከእርሱ ታሪኮች መካከል አንዱን ለማወቅ የሚናፍቁትንና እርሱን የሚያደንቁትን ሰዎች ይወዳቸዋል። ስለ እርሱ ከመጽሐፍ ቅዱስ ወይም ከአባቶች ብሒሎች ወይም ከቤተክርስቲያንና ከቅዱሳን ታሪክ ልታነቡ ትችላላችሁ። በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ የእግዚአብሔር እጅ ለመዳሰስ ስትሞክሩ በጥበቡ በኃይሉና በርኅራኄው ውስጥ እንደምትወዱት ታውቃላችሁ። #አቡነ_ሺኖዳ_ሳልሳዊ

#ጸሎተ_ማሪያም_በአጋንንት_ላይ_ያለው_የበላይነትና_ጥቅሞቹ!! የሹክሹክታ መናፍስቶችና ሚስጥራዊ ጉዳቶች!! የመናፍስት ሹክሹክታ ምንድነው? ደብተራ ምንድነው? https://youtu.be/W9c0MNdczQg

«መጨመርና መሙላት ሁለም ከእግዚአብሔር ነው፤ ማጉደልና ማፍዘዝ ደግሞ የዓለም፣ የሰይጣንና የክፉ ሰዎች ሥራ ነው። ስለዚህ ዘመኑን እንዋጅ፣ እንንቃም ጭምር»

#እውቀታችን_ገንዘባችን_ጤናችን_በአጋንንትና_መተት_እንዳይወሰድ_ይኼንን_እናድርግ!! https://youtu.be/O7tUyT2yrrY

#በእሷ_እውቀት_ዕድልና_ትምህርት_ብዙዎች_ተጠቅመዋል!! አብረውን የሚወለዱ ክፉ መንፈሶች!! https://youtu.be/hVXQi5UYYJ8

#የመኪና_ሹፌሮችን_ማዕከል_ያደረጉ_የመናፍት_ጥቃቶችና_ጉዳቶች!! ለሹፌሮች የተላለፈ ጥብቅ መልዕክት!! https://youtu.be/g0WNXdLMOG4

#ተጨማሪ_ዘወትር_የሚሰገድ_የአምልኮት_ስግደት_በተግባር_ይኼው!! https://youtu.be/FS1Yn3K21uA

#እፎይ_የክርስቶስ_ባሪያ_አደረገኝ_እውነቱ_ይኼ_ነው!! #የሦስቱ_ወንድሞች_ምስክርነት!! https://youtu.be/C7_AAdXYhA4?si=InSrC7rFcT8n2yYV

#ይኼንን_ምልክት_ካያችሁ_በትክክል_መተት_ተደርጎባችኋል!! https://youtu.be/8YYffeEVen8?si=ftsHUoKBpf9UFHC5