en
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Open in Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 368 subscribers, ranking 5 620 in the Religion & Spirituality category and 2 191 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 368 subscribers.

According to the latest data from 22 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -33 over the last 30 days and by -2 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 22.71%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 7.98% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 489 views. Within the first day, a publication typically gains 1 226 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 22.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 23 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 368
Subscribers
-224 hours
+317 days
-3330 days
Posts Archive
፪ኛው ዙር ፥ ዝክረ አበው ዘደብረሰላም 2015 ዓ.ም ዓርብ ጠዋት ፤ ሚያዝያ 27 ።
፪ኛው ዙር ፥ ዝክረ አበው ዘደብረሰላም 2015 ዓ.ም ዓርብ ጠዋት ፤ ሚያዝያ 27 ።

✞ #እሑድ፤ #ዳግም ትንሣኤ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡ ‹‹ይትነሣእ እግዚአብሔር ወይዘረው ፀሩ ወይጕየዩ ጸላዕቱ እምቅድመ ገጽ ከመ የሐልቅ ጢስ ከማሁ የሐልቁ ›› መዝ ፷፯፥፩ እንኳን ለበዓለ ዳግም ትንሣኤ እና #ሚያዝያ_23_በዓለ_ክላሌሁ_ለሊቀ_ሰማዕታት_ቅዱስ_ጊዮርጊስ በሰላም አደረሳቹህ  #ሥርዓተ_ማኀሌቱን ሰሙነ ፋሲካ  ስለሆን  እንደ #የደብሩ_ይትባህል እያጣቀሳቹህ እንድጠጠቀሙ የበዓለ #ትንሣኤን እና #የቅዱስ_ጊዮርጊስን  ሥርዓተ ማኀሌት እነሆ ብለናን፡፡  #እስከ_ዳግም_ትንሣዔ_ድረስ_መልክ_አይደረስም!  https://t.me/medihanaelem/6274 #ሊቀ_ሰማዕታት_ቅዱስ_ጊዮርጊስ፡፡ ※እናቱ ቴዎብስታ ስትባል አባቱ  እንጣስዮስ ይባላል፡፡ አባቱ ባረፈ ጊዜ መስፋን ነበርና የእርሱን ሹመትን ሊቀበል  ወደ ንጉሥ ዱድያኖስ ሄደ፤ ሰዎችን ጣዖት አቁም በግድ እንደሚየስመልክ ባየ ጊዜ ፤ ባሮቹን ነጻ አውጥቶ ገንዘቡንም ለምስኪኖችና ለድኀች ሰጠ ንጉሡም ከእርሱ ጋር እንዲተባብር ቢያባብለው እና ቃል ኪዳን ቢገባለት ቅዱስ ጊየርጊስ አልተቀበለውም ፡፡ ※ለመስማት የሚያስጨንቅ መከራን እና ስቃይን አደረሰበት ጌታችን  ግን መልሶ ያጸናዋል ቊስሉንም ያድንለት ነበር ፡፡ ※ጌታችን ለቅዱስ ጊየርጊስ 3 ጊዜ  እንደሚሞት እርሱም እንደሚያስነሳው በአራተኛውም የምስክርነት አክሊልን እንደሚቀበል ነገረው ፤ ስሙ በዓለም ሁሉ የተገለጠ ይሆን ዘንድ በተጋድሎና መከራ በመቀበልም ጽኑዕ በሆነ ሥቃይም ሰባት ዓመት እንደሚኖር መላእክትም እንደሚያገለግሉት ነገርው  ፤ ቃል ኪዳንንም ሰጠው ፡፡ ※ ንጉሡ አትናስዮስ በሚባል ታላቅ ሥረየኛ መርዘ አስበጥብጦ እና ክፉ አስማትን አስርቶ ቢሰጠው ቅዱስ ጊያርጊስን ምንም ሳያገኝው ቀረ ፤ ሥርየኛውም ይህን አይቶ በኢየሱስ ክርስቶስ አሞኖ ሰማዕትነትን ተቀብሎ ሞቷል፡፡ከእርሱም ጋር #ሠላሳ ሺህ የሚሆኑ ሰዎች አብረው የሕይወት አክሊልን ተቀብለው በሰማዕትነትን ዐረፈዋል፡፡ ※ በሰባ ነገሥታት ፊት በቆመ ጊዜ የተቀመጡባቸውን የእንጨት ወንበሮች እንዲአብቡና እንዲበቅሉ  አድርግ ቢሉት በጾሎቱ አድርጎ አሳያችው ይህንንም አይተው እጅግ ብዙ አህዛብ በአምላካችን አምነዋል፡፡ ※ ብዙ መከራንም አደረሱበት በጐድጓዳ በረት ምጣድ ውስጥ አኑርው አበሰሉት ፤ እቃ ጥለው አሳርረው ሥጋውንና ዐጥንቱን ፈጭተው አመድ አድረገው በተኑት ፡፡ ጌታችንም ነፍሱን ከሥጋው መልሶ ዳግም አስነሳው ወደ እነርሱም ተመልሶ በጌታችን ስም ሰበካቸው ይህንንም አይተው ቁጥር የሌላቸው አሕዛብ በጌታችን አምነው ሰማዕታት ሆኑ፡፡ ※ ነገሥታቱም ሙታኖችን ብታስነሳ በአምላክህ እናምናለን አሉ ፤በጸሎቱ ሙታኖችም አስነሳላቸው በጌታቸንም ስም አምነው በእርሱ ስም አስተማሩ ጥምቀትንም ተቀበሉ ፡፡የቀሩት ነገሥታት ግን ሰይጣናትን  ነው ያሳየኸን ብለው ተከራከሩ ፡፡ ※ ከአንዲት እምበለት ቤት ተቀምጦ ምግብ ልትፈልግለት ሄዳ በተመለሰች ጊዜ ቤቷ ላይ ተአምር አየች ፤ የክርስቲያኖች አምላክ በሰው ተመስሎ እኔ ጋር መጣ ብትል ቅዱስ ጊየርጊስም  #_እኔ_አምላክ_አይደለሁም_የአምላክ_ባርያ_ነኝ እነጂ አላት፡፡ የአምላክ አገልጋይ ከሆንክ ቸርነትህ እንድትደርሰኝ እለምናለሁ አለችው ልጇንም በመስቀል ምልክት አማትቦበት ከዕውርነት አድኖታል ፡ ※ ንጉሡም ተአምር ማድረጉን በሰማ ጊዜ በመንኰራኵርም ፈጨው ከከተማ ውጪ ወስደው ጣሉት ከሞትም ተነሣ ተመለሶም ወደ ነገሥታቱ ሄደ ፡፡ንጉሡም አድንቆ ይለምንው ጀመር በመንግሥቱ ላይ ሁለተኛ ያደርገው  ዘንድ ቃል ገባለት ቅዱስ ጊዮርጊስ እየዘበት ነገ ጠዋት ለአማልክቶች እሰዋለሁ ብሎት አደረ ፡፡ በሚጸልይበትም ጊዜ የንጉሡ ሚስት ሰምታ ጠየቀችው እርሱም ስለ ጌታችን አስተምራት አመነች  ፡፡ በማግሥቱም ንጉሡ ሰውን ሰብስቦ እንደሚጠብቀውና እውነት መስሎ በታያት  ጊዜ አዘነች ፡፡እርሱም ልጅሽን በምድር ላይ አኑሪው አላት ከዚያም ወደ አጵሎን (ጣዖቱ) ሂድ ወደ እኔም እንዲመጣ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እዘዘው አለው ፡፡ ልጁም ድኖ ቅዱሱ እንዳለው ሄዶ  አዘዘው ፡፡ በጣዖቱም የነበረው እርኩስ መንፈስ  ወጥቶ እኔ ሰውን የማስት እንጅ አምላክ አይደለሁም አለው ፡፡  ቅዱስ ጊዮርጊስም ምድር ትውጠው ዘንድ አዘዛት ወዲያውኑ ዋጠችው ጣዖቱንም ከአገልጋዮቻቸው ጋር አጠፋቸውን ንጉሡም ከወገኖቹ ጋር አፈረ፡፡ ※ ንጉሡም ሚስቱ በጌታችን እንዳመነች ባወቀ ጊዜ በመጋዝ አሰነጠቃት የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለች፡፡ ※ ነገሥታቱ ኀፍረት እንዳይጨመርባቸው ለንጉሡ በሰይፋ እንቁረጠው ብለው ጻፉለት እርሱም አዘዘ ፡፡ ድል አድራጊው ጊዮርጊስም   ከሰማይ እሳት ወርዶ ሰባውን ነገሥታት ያቃጥላቸው ዘንድ መከራውም ከክርስቲያን ወገኖች ጸጥ ይል ዘንድ ለመነ ፤ አሣቱም መጥቶ ወዲያውኑ አጠፋቸው፡፡ ※ጌታችን ተገልጾለት እጅግ ብዙ ቃል ኪዳንን ሰጠው ፤ መታሰቢያህን የሚያደርግ  ኃጢያቱን እደመስሳለሁ በመከራ ውስጥም ያለ በባሕርም ሆነ በየብስ በደዌም ሆነ በሕማም ያለ በስምህ የሚለምነኘን እኔ ፈጥኜ ከመከራው አድነዋለው ይህንንም ጌታችን ተናግሮ በክብር ወደ ሰማይ ወጣ፡፡ ※ በስተ መጨረሻም ራሱን ዘንበል አድርጎ በሰይፍ ቆረጡት በመንግሥተ ሰማያትም አክሊላትን ተቀበለ ፡፡ አገልጋዮቹም የቀረውን ሥጋውን ወስደው በልብስ ጠቀልልው ወደ ሀገሩ ልዳ ወሰዱት ፡፡ ቤተ ክርስቲያንንም ሰርተው በውስጥዋ አኖሩት ከእርሱም ቊጥር የሌላቸው ብዙዎዋች ተአምራቶች ተገለጡ፡፡ የቅዱስ ጊዮርጊስ ምልጃ አይለየን ——— #ኮከበ ክብር፥ *ሊቀ ሰማዕታት፥ *መክብበ ሰማዕታት፥ *የፋርስና የቤሩት ኮከብ፥ *የልዳ ፀሐይ፥ *የኢትዮጵያ ገበዝ፥ *ባለ ፀዓዳ ፈረስ፥ *፸ ነገሥታትን ድል ያደረገ፥ *በሕይወቱ ክርስትናን ያስፋፋ፥ በዕረፍቱ ክርስቶስን የሰበከ፥ ከዕረፍቱ በኋላ ዛሬን ጨምሮ ፈጥኖ የሚራዳ፥ *፫ት ጊዜ ሞቶ ፫ት ጊዜ የተነሣ፥ *፯ት አክሊላትን የተቀናጀ፤ *እመቤታችንን በጣም ስለሚወድ ስሙ ከስሟ፥ ዝክሩ ከዝክሯ፥ ፍልሰቱ ከፍልሰቷ ጋር የተባበረ እንዲኾን ያደረገችለት፤ #ኀያል መስተጋድል ኀያል ኮከበ ክብር፤ ኀያል ገባሬ ተአምር፤ ጊዮርጊስ ቅዱስ ለእግዚአብሔር፡፡ #በእንተ ጊዮርጊስ ፍቁርከ (ሰማዕትከ፥ ምዕመንከ)፤ ምህላነ ስማዕ በዕዝንከ፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ፤    ትምሕርት ዋና ክፍል ፥ ንዑስ ክፍል /ሕትመት እና ሚዲያ/  የተዘጋጀ ::    #share Contact: https://t.me/finotehiwot1927 .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .Telegram...  https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot      www.finotehiwotsundayschool.com  YouTube    https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram (https://t.me/finotehiwot1927) ——

✞  የሰሙነ ፋሲካ የመዠመርያው #ዐርብ፤ #ቅድስት ቤተክርስቲያን ይባላል፡- በክርስቶስ ደም ተዋጅታ በተመሠረተችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታላቅ መታሰቢያ በመሆኗ በሰሙነ ፋሲካው ያለችው ዐርብ «ቤተ ክርስቲያን» ተብላ ትጠራለች፡፡ ማቴ. 26 ÷ 26-29 የሐ. ሥራ. 20-28 በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ፤    .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w, .      www.finotehiwotsundayschool.com