uz
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Kanalga Telegram’da o‘tish

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት analitikasi

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 368 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 5 620-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 191-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 368 obunachiga ega bo‘ldi.

22 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -33 ga, so‘nggi 24 soatda esa -2 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 22.71% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 7.98% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 489 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 226 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 22 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 23 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 368
Obunachilar
-224 soatlar
+317 kunlar
-3330 kunlar
Postlar arxiv
፪ኛው ዙር ፥ ዝክረ አበው ዘደብረሰላም 2015 ዓ.ም ዓርብ ጠዋት ፤ ሚያዝያ 27 ።
፪ኛው ዙር ፥ ዝክረ አበው ዘደብረሰላም 2015 ዓ.ም ዓርብ ጠዋት ፤ ሚያዝያ 27 ።

✞ #እሑድ፤ #ዳግም ትንሣኤ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡ ‹‹ይትነሣእ እግዚአብሔር ወይዘረው ፀሩ ወይጕየዩ ጸላዕቱ እምቅድመ ገጽ ከመ የሐልቅ ጢስ ከማሁ የሐልቁ ›› መዝ ፷፯፥፩ እንኳን ለበዓለ ዳግም ትንሣኤ እና #ሚያዝያ_23_በዓለ_ክላሌሁ_ለሊቀ_ሰማዕታት_ቅዱስ_ጊዮርጊስ በሰላም አደረሳቹህ  #ሥርዓተ_ማኀሌቱን ሰሙነ ፋሲካ  ስለሆን  እንደ #የደብሩ_ይትባህል እያጣቀሳቹህ እንድጠጠቀሙ የበዓለ #ትንሣኤን እና #የቅዱስ_ጊዮርጊስን  ሥርዓተ ማኀሌት እነሆ ብለናን፡፡  #እስከ_ዳግም_ትንሣዔ_ድረስ_መልክ_አይደረስም!  https://t.me/medihanaelem/6274 #ሊቀ_ሰማዕታት_ቅዱስ_ጊዮርጊስ፡፡ ※እናቱ ቴዎብስታ ስትባል አባቱ  እንጣስዮስ ይባላል፡፡ አባቱ ባረፈ ጊዜ መስፋን ነበርና የእርሱን ሹመትን ሊቀበል  ወደ ንጉሥ ዱድያኖስ ሄደ፤ ሰዎችን ጣዖት አቁም በግድ እንደሚየስመልክ ባየ ጊዜ ፤ ባሮቹን ነጻ አውጥቶ ገንዘቡንም ለምስኪኖችና ለድኀች ሰጠ ንጉሡም ከእርሱ ጋር እንዲተባብር ቢያባብለው እና ቃል ኪዳን ቢገባለት ቅዱስ ጊየርጊስ አልተቀበለውም ፡፡ ※ለመስማት የሚያስጨንቅ መከራን እና ስቃይን አደረሰበት ጌታችን  ግን መልሶ ያጸናዋል ቊስሉንም ያድንለት ነበር ፡፡ ※ጌታችን ለቅዱስ ጊየርጊስ 3 ጊዜ  እንደሚሞት እርሱም እንደሚያስነሳው በአራተኛውም የምስክርነት አክሊልን እንደሚቀበል ነገረው ፤ ስሙ በዓለም ሁሉ የተገለጠ ይሆን ዘንድ በተጋድሎና መከራ በመቀበልም ጽኑዕ በሆነ ሥቃይም ሰባት ዓመት እንደሚኖር መላእክትም እንደሚያገለግሉት ነገርው  ፤ ቃል ኪዳንንም ሰጠው ፡፡ ※ ንጉሡ አትናስዮስ በሚባል ታላቅ ሥረየኛ መርዘ አስበጥብጦ እና ክፉ አስማትን አስርቶ ቢሰጠው ቅዱስ ጊያርጊስን ምንም ሳያገኝው ቀረ ፤ ሥርየኛውም ይህን አይቶ በኢየሱስ ክርስቶስ አሞኖ ሰማዕትነትን ተቀብሎ ሞቷል፡፡ከእርሱም ጋር #ሠላሳ ሺህ የሚሆኑ ሰዎች አብረው የሕይወት አክሊልን ተቀብለው በሰማዕትነትን ዐረፈዋል፡፡ ※ በሰባ ነገሥታት ፊት በቆመ ጊዜ የተቀመጡባቸውን የእንጨት ወንበሮች እንዲአብቡና እንዲበቅሉ  አድርግ ቢሉት በጾሎቱ አድርጎ አሳያችው ይህንንም አይተው እጅግ ብዙ አህዛብ በአምላካችን አምነዋል፡፡ ※ ብዙ መከራንም አደረሱበት በጐድጓዳ በረት ምጣድ ውስጥ አኑርው አበሰሉት ፤ እቃ ጥለው አሳርረው ሥጋውንና ዐጥንቱን ፈጭተው አመድ አድረገው በተኑት ፡፡ ጌታችንም ነፍሱን ከሥጋው መልሶ ዳግም አስነሳው ወደ እነርሱም ተመልሶ በጌታችን ስም ሰበካቸው ይህንንም አይተው ቁጥር የሌላቸው አሕዛብ በጌታችን አምነው ሰማዕታት ሆኑ፡፡ ※ ነገሥታቱም ሙታኖችን ብታስነሳ በአምላክህ እናምናለን አሉ ፤በጸሎቱ ሙታኖችም አስነሳላቸው በጌታቸንም ስም አምነው በእርሱ ስም አስተማሩ ጥምቀትንም ተቀበሉ ፡፡የቀሩት ነገሥታት ግን ሰይጣናትን  ነው ያሳየኸን ብለው ተከራከሩ ፡፡ ※ ከአንዲት እምበለት ቤት ተቀምጦ ምግብ ልትፈልግለት ሄዳ በተመለሰች ጊዜ ቤቷ ላይ ተአምር አየች ፤ የክርስቲያኖች አምላክ በሰው ተመስሎ እኔ ጋር መጣ ብትል ቅዱስ ጊየርጊስም  #_እኔ_አምላክ_አይደለሁም_የአምላክ_ባርያ_ነኝ እነጂ አላት፡፡ የአምላክ አገልጋይ ከሆንክ ቸርነትህ እንድትደርሰኝ እለምናለሁ አለችው ልጇንም በመስቀል ምልክት አማትቦበት ከዕውርነት አድኖታል ፡ ※ ንጉሡም ተአምር ማድረጉን በሰማ ጊዜ በመንኰራኵርም ፈጨው ከከተማ ውጪ ወስደው ጣሉት ከሞትም ተነሣ ተመለሶም ወደ ነገሥታቱ ሄደ ፡፡ንጉሡም አድንቆ ይለምንው ጀመር በመንግሥቱ ላይ ሁለተኛ ያደርገው  ዘንድ ቃል ገባለት ቅዱስ ጊዮርጊስ እየዘበት ነገ ጠዋት ለአማልክቶች እሰዋለሁ ብሎት አደረ ፡፡ በሚጸልይበትም ጊዜ የንጉሡ ሚስት ሰምታ ጠየቀችው እርሱም ስለ ጌታችን አስተምራት አመነች  ፡፡ በማግሥቱም ንጉሡ ሰውን ሰብስቦ እንደሚጠብቀውና እውነት መስሎ በታያት  ጊዜ አዘነች ፡፡እርሱም ልጅሽን በምድር ላይ አኑሪው አላት ከዚያም ወደ አጵሎን (ጣዖቱ) ሂድ ወደ እኔም እንዲመጣ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እዘዘው አለው ፡፡ ልጁም ድኖ ቅዱሱ እንዳለው ሄዶ  አዘዘው ፡፡ በጣዖቱም የነበረው እርኩስ መንፈስ  ወጥቶ እኔ ሰውን የማስት እንጅ አምላክ አይደለሁም አለው ፡፡  ቅዱስ ጊዮርጊስም ምድር ትውጠው ዘንድ አዘዛት ወዲያውኑ ዋጠችው ጣዖቱንም ከአገልጋዮቻቸው ጋር አጠፋቸውን ንጉሡም ከወገኖቹ ጋር አፈረ፡፡ ※ ንጉሡም ሚስቱ በጌታችን እንዳመነች ባወቀ ጊዜ በመጋዝ አሰነጠቃት የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለች፡፡ ※ ነገሥታቱ ኀፍረት እንዳይጨመርባቸው ለንጉሡ በሰይፋ እንቁረጠው ብለው ጻፉለት እርሱም አዘዘ ፡፡ ድል አድራጊው ጊዮርጊስም   ከሰማይ እሳት ወርዶ ሰባውን ነገሥታት ያቃጥላቸው ዘንድ መከራውም ከክርስቲያን ወገኖች ጸጥ ይል ዘንድ ለመነ ፤ አሣቱም መጥቶ ወዲያውኑ አጠፋቸው፡፡ ※ጌታችን ተገልጾለት እጅግ ብዙ ቃል ኪዳንን ሰጠው ፤ መታሰቢያህን የሚያደርግ  ኃጢያቱን እደመስሳለሁ በመከራ ውስጥም ያለ በባሕርም ሆነ በየብስ በደዌም ሆነ በሕማም ያለ በስምህ የሚለምነኘን እኔ ፈጥኜ ከመከራው አድነዋለው ይህንንም ጌታችን ተናግሮ በክብር ወደ ሰማይ ወጣ፡፡ ※ በስተ መጨረሻም ራሱን ዘንበል አድርጎ በሰይፍ ቆረጡት በመንግሥተ ሰማያትም አክሊላትን ተቀበለ ፡፡ አገልጋዮቹም የቀረውን ሥጋውን ወስደው በልብስ ጠቀልልው ወደ ሀገሩ ልዳ ወሰዱት ፡፡ ቤተ ክርስቲያንንም ሰርተው በውስጥዋ አኖሩት ከእርሱም ቊጥር የሌላቸው ብዙዎዋች ተአምራቶች ተገለጡ፡፡ የቅዱስ ጊዮርጊስ ምልጃ አይለየን ——— #ኮከበ ክብር፥ *ሊቀ ሰማዕታት፥ *መክብበ ሰማዕታት፥ *የፋርስና የቤሩት ኮከብ፥ *የልዳ ፀሐይ፥ *የኢትዮጵያ ገበዝ፥ *ባለ ፀዓዳ ፈረስ፥ *፸ ነገሥታትን ድል ያደረገ፥ *በሕይወቱ ክርስትናን ያስፋፋ፥ በዕረፍቱ ክርስቶስን የሰበከ፥ ከዕረፍቱ በኋላ ዛሬን ጨምሮ ፈጥኖ የሚራዳ፥ *፫ት ጊዜ ሞቶ ፫ት ጊዜ የተነሣ፥ *፯ት አክሊላትን የተቀናጀ፤ *እመቤታችንን በጣም ስለሚወድ ስሙ ከስሟ፥ ዝክሩ ከዝክሯ፥ ፍልሰቱ ከፍልሰቷ ጋር የተባበረ እንዲኾን ያደረገችለት፤ #ኀያል መስተጋድል ኀያል ኮከበ ክብር፤ ኀያል ገባሬ ተአምር፤ ጊዮርጊስ ቅዱስ ለእግዚአብሔር፡፡ #በእንተ ጊዮርጊስ ፍቁርከ (ሰማዕትከ፥ ምዕመንከ)፤ ምህላነ ስማዕ በዕዝንከ፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ፤    ትምሕርት ዋና ክፍል ፥ ንዑስ ክፍል /ሕትመት እና ሚዲያ/  የተዘጋጀ ::    #share Contact: https://t.me/finotehiwot1927 .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .Telegram...  https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot      www.finotehiwotsundayschool.com  YouTube    https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram (https://t.me/finotehiwot1927) ——

✞  የሰሙነ ፋሲካ የመዠመርያው #ዐርብ፤ #ቅድስት ቤተክርስቲያን ይባላል፡- በክርስቶስ ደም ተዋጅታ በተመሠረተችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታላቅ መታሰቢያ በመሆኗ በሰሙነ ፋሲካው ያለችው ዐርብ «ቤተ ክርስቲያን» ተብላ ትጠራለች፡፡ ማቴ. 26 ÷ 26-29 የሐ. ሥራ. 20-28 በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ፤    .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w, .      www.finotehiwotsundayschool.com