en
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Open in Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 413 subscribers, ranking 5 577 in the Religion & Spirituality category and 2 192 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 413 subscribers.

According to the latest data from 13 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 71 over the last 30 days and by -3 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.53%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 9.38% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 933 views. Within the first day, a publication typically gains 1 446 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 23.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 14 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 413
Subscribers
-324 hours
+357 days
+7130 days
Posts Archive
እንኳን ለእመቤታችን ከነልጇ ከ፫ ዓመት ከ፮ ወር ከስደት በኃዋላ ተመልሰው በደብረ ቁስቋም ላረፋበት ለበዓለ ቁስቋም ማርያም አደረሰን፨ ከሚከበርባቸው ቦታዎች ዐበይቶቹ፤ ፠ ረጠደብረ ቁስቋም (ግብፅ) ፠ ገዳመ ጽጌ ድንግል (ደቡብ ወሎ፥ ወግዲ ወረዳ) ፠ ደብረ ፀሐይ ቁስቋም ማርያም (ጎንደር ከተማ) ፠ እንጦጦ መንበረ ንግሥት ቁስቋም ማርያም (እንጦጦ፥ አዲስ አበባ) ፠ ቃሊቲ ቁስቋም ማርያም (ቃሊቲ፥ አዲስ አበባ) ፠ ሸጎሌ ኪዳነ ምሕረት /የቁስቋም ማርያም ታቦት በድርብነት አለ፤ (ጉለሌ፥ ጎጃም በር፥ አዲስ አበባ)

ንግሥተ ሰማያት ወምድር ማርያም ድንግል፤ (ኅብረ ሐመልሚል ቀይህ ወፀዓድዒድ) ተፈጸመ ናሁ ማኅሌተ ጽጌ፡፡ (የብር ዝንጕርጕር፣ የነጭና የቀይ ድብልቅ መልክ ያለው ንጹሕ ተዓምርሽ በወርቅ አምሳል የተዘጋጀ ነው፤ ሊቁ አባ ጽጌ ድንግል /ጽጌ ብርሃን/ የደረሰው እነሆ ያማረ የተወደደ ማኅሌተ ጽጌ የተባለ ምሥጋና መላ፥ ተፈጸመ፤ የሰማይና የምድር ንግሥት ማርያም ሆይ ልጅሽ ወዳጅሽ በእቅፍሽ ውስጥ እንዳለ ይህንንም የማኅሌተ ጽጌ ምሥጋናን ተቀበዪ፥ ወደ ሰማይ አሳርጊ፡፡)

ተሰአሎ ለአቡከ ወይነግረከ፤ ወለሊቃውንቲከ ይዜንዉከ፡፡ (አባትህን ጠይቅ ይነግርሃል፤ ሊቃውንትን ጠይቅ ያስታውቁህማል፡፡) የኹሉንም ሳምንታት ማኅሌተ ጽጌ ቀድሞ ከአባቶች ሲወርድ ሲዋረድ የመጣውን ዚቁን፤ ታላቁ ሊቅና ቅዱስ አባ ጽጌ ድንግል ከደረሰው ማኅሌተ ጽጌ ጋር እያስማሙ አቀናብረው ያቀረቡልን ዐበይት የላይ ቤትና የታች መምህራን፡፡ እነርሱም፤ ✤✤ የላይ ቤቱን፤ መምህር ተክለማርያምና ሊቀ ማዕምራን ወመጋቤ ሐዲስ ወ/ሰንበት ባይነሳኝ፤ (ሁለቱም የቀለም ቀንድ የኾኑ ሊቃውንት የመጻሕፍተ ሐዲሳት ዋና ምስክርና የመካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም ዋና አስተዳዳሪ የነበሩ ናቸው፡፡) ✤✤ የታች ቤቱን፤ መምህር ክፍሌ ወልደ ጻድቅ ና መጋቤ አእላፍ ሄኖክ ወልደሚካኤል /ሁለቱም ሊቃውንት የደብረ ኀይል ወደብረ ጥበብ በዓታ የአቋቋም ዋና ምስክርና የደብሩ አስተዳዳሪ የነበሩ ናቸው፡/

ታላቁ ገዳማችን አሰቦት ደብረ ወገግንና ደብረ ኪሩብን ለመሠረቱት ለአባታችን ለአቡነ ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ በዓለ ዕረፍት (ጥቅምት 29) በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡ ✤✤ አቡነ ሳሙኤል ዘደደብረ ወገግ፡ ፠ በታላቁ አባት አቡነ ተክለሃይማኖት ‹እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ፥ ጣዖታትን የሚሰብር፣ የሚያጠፋ፣ አጋንንትን በጸሎቱ የሚያርቅ፣ ሕዝብን ከኀጢአት በሽታ የሚያድን፣ ፈጣሪውን የሚያስደስት ደግ ልጅ› ተብሎ በተነገረለት ትንቢታዊ ብሥራት ከደጋግና ከበቁ አባታቸው እንድርያስና ከእናታቸው አርሶንያ ሐምሌ 10 ቀን 1248 ዓ.ም. በቡልጋ ተወለዱ፤ ሲወለዱም መልካቸው በአራት ልዩ ልዩ ሕብረ መልክ እየተለዋወጠ አንድ ጊዜ እንደ በረዶ፣ አንድ ጊዜ እንደ እሳት፣ አንድ ጊዜ እንደ ልምላሜና ቢጫ ሆነው ታይተዋል፡፡ ፠ስማቸውን ሳሙኤል በብለው የሰየሟቸውና ክርስትናም ያነሷቸው፤ ኋላም መዓርገ ምንኵስናን የሰጧቸው አቡነ ተክለሃይማኖት ናቸው፡፡ ፠ ብዙ ጻድቃንን (አቡነ ተክለሃይማኖትን፣ ታዴዎስ ዘደብረ ድኁኃን፣ ሮማኖስ ዘደብረ ዋምን፣ አቡነ አኖሬዎስ ዕንቈ ባሕርይ ዘመረግድ ወመስተጋድል ወምግባር ንጹሕን) በሥጋ የሚዛመዱ ናቸው፡፡ ፠ ሃይማኖቱ የቀና ደግ ጻድቅ ንጉሥ ዳዊት በነገሠ ጊዜ አባታችን ሳሙኤል ዘወገግን አገኘውና አባቱ ዓምደ ጽዮን ለሠራው ክፉ ሥራ ‹‹መማጸኛ እንዲሆነኝ በእንድርያስ መቃብር ላይ ቤተክርስቲያን ሥራልኝ›› ብሎ ለመነውና የሩፋኤልን ቤተ ክርስቲያን ሠራለት፡፡ የእንድርያስንም አጽም ከመቅደሱ ስር አኖረው፡፡ ንጉሡም በዚያ በእንደግብጦን አውራጃ ሁሉ ላይ ፓትርያርክ አድርጎ ሾመው፡፡ ፠፠ አቡነ ተክለሃይማኖት ትንቢት እንደተናገሩላቸው አቡነ ሳሙኤል፤ * በሰዎች፣ በባሕርና በዛፍ ላይ እያደሩ ይመለኩ የነበሩ በጣም ብዙ አጋንንትን አጠፏቸው፡፡ * ጠንቋዮችንም በውስጣቸው ካደረባቸው ሰይጣን እያላቀቁ የእግዚአብሔር አገልጋይ ያደርጓቸውና ያመነኩሷቸው ነበር፡፡ * ወንጌልን ዞረው በማስተማር ሐዋርያትን መሰሉ፥ * ከዓላውያን ጋር ለመዋጋት ሰውነታቸውን ለሞት በመስጠት ሰማዕታትን መሰሉ፥ * በጾም በጸሎት በስግደት በተጋድሎ ቅዱሳን ጻድቃንን መሰሉ፥ * ይህን ኀላፊና ጠፊ ዓለም ንቀው በመተው ባሕታውያንን መሰሉ፥ * በደልንና ኃጢአትን በማስተሠረይ ካህናትን መሰሉ፥ * በጽሕናና በቅድስና መላእክትን መሰሉ፤ * ብዙ አስደናቂ ተአምራትንም በማድረግም ይታወቃሉ፤ ከእነዚህም ጥቂቶቹ በትእምርተ መስቀል አድርገው እንደሙሴ ባሕርን ለሁለት ከፍለዋል፣ እንደ ኢያሱ በጸሎታቸው ፀሐይን አቁመዋል፡፡ አቡነ ሳሙኤል ተጋድሎአቸውን ፈጽመው ከጌታችን ታላቅ ቃኪዳን ተቀብለው በዚህች ዕለት (በጥቅምት 29) በኦጋዴን ዘርዘር በተባለ ቦታ በሰላም አርፈዋል፤ ከ7 ወራት በኋላ ሠምረ ክርስቶስ የተባለ ልጃቸው ሥጋቸውን አፍልሶ በደብረ ወገግ በክብር አሳርፎታል፡፡ ፠ የአሰቦት ደብረ ወገግን (ምስራቅ ሐረርጌ) ና ደብረ ኪሩብ (አፋር) ገዳምን የመሠረቱ፥ ለብዙ አእላፍ ቅዱሳን ወላዴ የኾኑና፤ የመሠረቱት ገዳም የምሥጢርና የብዙ ስውራን መኖሪያ የኾነላቸው ታላቅ አባት ናቸው፡፡ ፠ ከአቡነ ተክለሃይማኖት በኋላ ከተሾሙት 12ቱ ንቡራነ ዕድ አንዱ ናቸው፤ ሃገረ ስብከታቸውም ሐረርና ሱማሌ ነው፡፡ ፠ ‹‹ደብረ ወገግ›› ከ2-5 ዓ.ም. እመቤታችን ከነልጇ ስተሰደድ ለ6 ወር የተቀመጠችበት ሲኾን፤ ደብረ ወገግ የሚለው ስያሜ የተገኘው ከመላእክት ነው፡፡ ድርሳነ ዑራኤል በሰፊው እንደሚያትተው ቅዱስ ዑራኤል በ34ዓ.ም. የጌታችንን ደም በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ ዓለምን እየረጨ ሲቀድሳት የያዘውን ጽዋ በደብረ ወገግ ላይ ቆሞ ሳለ ነው ጨልጦ ያንጠፈጠፈው፡፡ ያንጊዜም ደብረ ወገግን የብርሃን ውጋገን ሲያጥለቀልቀው መላእክትም ቦታውን ‹‹ደብረ ወገግ›› (የብርሃን ተራራ) ብለው ሰይመውታል፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም ‹‹ወደፊት ፈጣሪውን የሚያገለግል ታላቅ ጻድቅ ይወጣባታልና ይህችን ቦታ ባርካት›› ብሎ ቅዱስ ዑራኤልን በነገረው መሠረት ባርኳት አርጓል፡፡ ✤✤ ደብረ ወገግ፤ ፠ በደብረ ወገግ ቦታ ላይ ብዙ ጊዜ የብርሃን ምሰሶ ተተክሎ መታየቱን የበቁ ገዳማውያን ብቻ ሳይሆኑ በከተማ ያሉና ለመሳለም ወደ ቦታው የሄዱ ደገኛ ሰዎችም በዐይናቸው ያዩትን ይናገራሉ፡፡ በገዳሙ ዙሪያ እጅግ በጣም ብዙ ስውራን ቅዱሳን እንዳሉ በግልጽ ይታወቃል፡፡ ፠ ገዳሙ በግራኝ ወረራ ወቅት ከጠፋ በኋላ እንደገና መልሶ የቀናው በ1911ዓ.ም. በታላቁ ሊቅና መናኝ በአለቃ ገብረ መድኅን ነው፡፡ በ1912 ዓ.ም. የአቡነ ሳሙኤልን ቤተ ክርስቲያንን በሣር ክዳን ሠሩ፤ በዓመቱ በ1918 ዓ.ም. ደግሞ የቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያንን መሥራት ጀምረው ፍጻሜውን ሳያዩ እርሳቸው ቢያርፉም፤ በ1919 ዓ.ም. የሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ ሥራ ተጠናቋል፡፡ በ1929 ዓ.ም. በሶማልያ በኩል በገባው የፋሽስት ኢጣልያ ጦር ገዳሙ ተዘርፏል፥ የቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያንም ፈርሷል፡፡ በወቅቱ በገዳሙ ከነበሩት ከ500 በላይ መነኰሳት መካከል ከፊሉ ታቦቱን ይዘው ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ሲሸሹ ከፊሎቹ ደግሞ ወደ ሞቃዲሾ ተወስደው ታስረዋል፡፡ ከጣሊያን ወረራ በኋላ መነኰሳቱ በ1936 ዓ.ም. ተሰባስበው ወደ አሰቦት መጡ፡፡ ከ22 ዓመት በኋላ ደግሞ የቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን በግርማዊ ቀዳማዊ ንጉሠ ነገሥት ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ትእዛዝ በ1952 ዓ.ም. ተሠራ፡፡ በደርግ ዘመነ መንግሥት ሶማሊያ ኢትጵያን ስትወርር ገዳሙ ላይ አደጋ ለመጣል የመጡ ጠላቶች በተአምራት ያለቁበት ነበር፤ የጃራ ጦር የሚባሉ ገዳሙን ለማጥፋትም መጡ ጠላቶች እንዲሁ በተአምራት አብደው የተመለሱበት ታላቅ ገዳም ነው፡፡ ግንቦት 16 ቀን 1984 ዓ.ም. በአክራሪ ኃይል የገዳሙን መነኰሳትና የአካባቢው ምዕመናን ላይ የከፋ አደጋ ጥሏል፤ ብዙዎችም ሰማዕት ሁነዋል፡፡ በአሰቦት ደብረ ወገግ ገዳም ውስጥ የተሰወሩ እጅግ በርካታ ቅዱሳን ስለመኖራቸው በገድለ አቡነ ሳሙኤል መቅድም ውስጥ በሰፊው ተጠቅሷል፡፡ አሁንም ሆነ ወደፊት በቦታው ላይ የተሰወሩት ቅዱሳን ለገዳማውያኑም ሆነ በዓለም ለሚኖሩ ምግባርን ከሃይማኖት አስተባብረው ለያዙ ሰዎች እየተገለጡላቸው ይታዩዋቸዋል፣ መልእክትም ይነግሯቸዋል፡፡ እንዲሁም ስውራኑ ባሉበት ቦታ የከበሮ ድምጽ ይሰማል፣ ዕጣን ይሸታል፣ ቀንና ሌሊት አራዊት ሲሰግዱበትና ሲጠብቁት ይታያል፡፡ ለአብነትም በ1972ዓ.ም. ሐምሌ 7 ብዙ ሰው እያያቸው አባ መዘምር የተሠወሩበት ታለቅ ገዳም ነው፡፡ የአቡነ ሳሙኤል ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን፡፡ ሰላም ለዝክረ ስምከ ዘፍቅዳቲሁ ራብዕ፤ ውእቱ ልኩእ ዲበ ረቀ ሰማይ ሳብዕ፡፡ ሊቀ ካህናት ሳሙኤል ዘደብተራ ሐዲ ምሥዋዕ፤ አስተስሪ ኀጣውእየ በደመ ነቢብ በግዕ፤ ለቤዛ ሙታን ዘሞተ በግፍዕ፡፡ (ሳሙኤል ሆይ ቊጥሩ ዐራት ለኾነ በሰባተኛው የሰማይ ብራና(ወረቀት) ለተጻፈ ስም አጠራርህ ሰላምታ ይገባል፤ የሐዲስ መሠዊያ አገልጋይ፥ የካህናት አለቃ ሳሙኤል ሆይ፤ ለሰዎች ቤዛ ለመኾን በግፍ በሞተ በነባቢ ክርስቶስ ደም ኀጢአቴን አስተሥርይ፡፡) /ታሪኩን ለዘገበልን ወንድማችን አምላከ አቡነ ሳሙኤል በረድኤት በበረከት በጤና ይጠብቅልን፡፡/

4ኛ) ክብረ በዓል፤ ፨፨በቦታ ርቀት ላልተገኛችሁ፤ የጥቅምት 27 ክብረ በዓልን በአጭሩበፎቶ እናስቃኛችሁ፡፡ ** በዕለቱ ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ፤ የቅዱስ ሲኖዶስ አባልና በሰሜን አሜሪካ የሚኒሶታ ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፥ ከብዙ ዓመታት የአሜሪካ ቆይታ በኃላ ከልጅነት እስከ እውቀት በዲቁናና በቅድስና ባገለገሉበት ደብራችን ኪዳንና ቅዳሴው መርተዋል፥ ትምህርት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጥተዋል፨ ፨፨፨ በነገራችን ላይ ደብራችን ፬ት ሊቃነ ጳጳሳትን አፍርታለች። እነርሱም፤ ፩ኛ. ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ፤ የትግራይ ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፪ኛ. ብፁዕ አቡነ ተክለሃይማኖት፤ የወሊሶ ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፫ኛ. ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ፤ የቀድሞው በመኪና አደጋ አምላክ የጠራቸው ፬ኛ. ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ፤ የሚኒሶታ ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፠፠ በክብረ በዓሉ ላይም የቤተ ክህነት ኃላፊዎች፥ የ4 አድባራት አስተዳዳሪዎችና የ3 አድባራት ጸሓፊዎች፥ የደብራችን የቀድሞ አገልጋዮች፥ በርካታ የአ.አ. አድባራት ካህናትና ምዕመናን በተገኙበት ዕፁብ ድንቅ በኾነ ኹኔታ ተከብሯል፨

3ኛ) ዑደትና ወረብ፤ በቦታ ርቀት ላልተገኛችሁ፤ የማኅሌቱን ሥርዐት (ቅኝት) በፎቶ እናስቃኛችሁ፡፡ማኅሌቱንም በዚሁ በታላቁ ደብር ከቀድሞዎቹ ዐበይት መምህራን (ከመምህር ገብረ ማርያም የላይ ቤት አቋቋምንና ከመምህር መንግሥቱ ቅኔን አብረው የተማሩትና በውጣትነት ጓደኞች በኾኑት በመሪነት 2ቱ ሊቃነ ጠበብት፤ 1ኛ. ሊቀ ጠበብት ዘሚካኤል አየነው፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም ሊቀ ጠበብት 2ኛ. ሊቀ ጠበብት ኀይለ መሰቀል፤ የእንጦጦ ማርያም ሊቀ ጠበብት መርተውታል፡፡ ሃሌ ሉያ በአማን በአማን ቃልከ አዳም፤ በእንተ ኀጥኣን ዘተሰቀልከ መድኀኔዓለም፡፡ (ስለ ኀጥአን ብለህ የተሰቀልክ መድኀኔ ዓለም፤ እውነት በእውነት ለአዳም የገባህለትን ቃል ኪዳንን እውን አደረግህ ፡፡)

2ኛ) ወረብ፤ በቦታ ርቀት ላልተገኛችሁ፤ የማኅሌቱን ሥርዐት (ቅኝት) በፎቶ እናስቃኛችሁ፡፡ (በነገራችን ላይ በአ.አ አድባራት ያሉ ዐበይት መምህራን ከየደብሮቻቸው የተሰባሰቡበት ማኅሌት ነበር፡፡) ማኅሌቱንም በዚሁ በታላቁ ደብር ከቀድሞዎቹ ዐበይት መምህራን (ከመምህር ገብረ ማርያም የላይ ቤት አቋቋምንና ከመምህር መንግሥቱ ቅኔን አብረው የተማሩትና በውጣትነት ጓደኞች በኾኑት በመሪነት 2ቱ ሊቃነ ጠበብት፤ 1ኛ. ሊቀ ጠበብት ዘሚካኤል አየነው፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም ሊቀ ጠበብት 2ኛ. ሊቀ ጠበብት ኀይለ መሰቀል፤ የእንጦጦ ማርያም ሊቀ ጠበብት መርተውታል፡፡ ሃሌ ሉያ በአማን በአማን ቃልከ አዳም፤ በእንተ ኀጥኣን ዘተሰቀልከ መድኀኔዓለም፡፡ (ስለ ኀጥአን ብለህ የተሰቀልክ መድኀኔ ዓለም፤ እውነት በእውነት ለአዳም የገባህለትን ቃል ኪዳንን እውን አደረግህ ፡፡)

1ኛ) የወረብ ቅኝት፤ በቦታ ርቀት ላልተገኛችሁ፤ የማኅሌቱን ሥርዐት (ቅኝት) በፎቶ እናስቃኛችሁ፡፡ (በነገራችን ላይ በአ.አ አድባራት ያሉ ዐበይት መምህራን ከየደብሮቻቸው የተሰባሰቡበት ማኅሌት ነበር፡፡) ማኅሌቱንም በዚሁ በታላቁ ደብር ከቀድሞዎቹ ዐበይት መምህራን (ከመምህር ገብረ ማርያም የላይ ቤት አቋቋምንና ከመምህር መንግሥቱ ቅኔን አብረው የተማሩትና በውጣትነት ጓደኞች በኾኑት በመሪነት 2ቱ ሊቃነ ጠበብት፤ 1ኛ. ሊቀ ጠበብት ዘሚካኤል አየነው፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም ሊቀ ጠበብት 2ኛ. ሊቀ ጠበብት ኀይለ መሰቀል፤ የእንጦጦ ማርያም ሊቀ ጠበብት መርተውታል፡፡ ሃሌ ሉያ በአማን በአማን ቃልከ አዳም፤ በእንተ ኀጥኣን ዘተሰቀልከ መድኀኔዓለም፡፡ (ስለ ኀጥአን ብለህ የተሰቀልክ መድኀኔ ዓለም፤ እውነት በእውነት ለአዳም የገባህለትን ቃል ኪዳንን እውን አደረግህ ፡፡)

እርማት፤ ነግሡ ከነዚቁ፤ በቀጨኔ የሚለውንና በመ.መ.መ. ከሚለው ጋር ማቀያየር፨ የነግሡ ዚቅን ብለህ የሚከተለውን ወረብ ወርብ፨ ወረብ ፩፤ ሃሌ ሃሌ ሉያ፥ ሃሌ ሉያ፤፪) ተንሥዒ ወንዒ ቅርብተ ዚኣየ ዘበእንቲአኪ ተረግዘ ገቦየ።(፪)

እንኳን ለመድኀኔዓለም ክብረ በዓል (ለመጋቢት 27 ጥንተ ስቅለት ልዋጭ በዓል)ና ለአቡነ መብዓ ጽዮን ክብረ በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡ ✤፨✤ አቡነ መብዓ ጽዮን አቡነ መብዓ ጽዮን ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓል (ጥቅምት 27 ቀን) ጋር አብረው የሚታሰቡ ታላቅ የተጋድሎ አባት ናቸው፡፡ የፃድቁ አቡነ መብዓ ጽዮን መታሰቢያቸው ከመድኃኔዓለም በዓል ጋር ስለሆነ በዚህ ጽሁፍ ሥር ታሪካቸውን ይዘን ቀርበናል፡፡ መልካም ንባብ! አቡነ መብዓ ጽዮን የተገኙት እግዚአብሔርን እያስደሰቱ ያለነቀፋ ከሚኖሩ ቅዱሳን ነው፡፡ በክህነታቱ፣ በየዋህነቱ ከሰዎች የተስማማው አባታቸው ሀብተጽዮን፣ በደግነቷና በቸርነቷ የምትታወቀው እናታቸው ጽዮንትኩና በሕግ በንፅህና በጋብቻ ተወስነው ሲኖሩ የተባረከ ልጅ ይሰጣቸው ዘንድ ወደ ጌታ ይለምኑ ነበር፡፡ የለመኑትን የማይነሳ መድኃኔዓለም ክርስቶስም መብዓ ጽዮን የተባለ ደግ ልጅ ሰጣቸው፡፡ መብዓ ጽዮን ከልጅነቱ ጀምሮ ማስተዋል እና የእግዚአብሔር ፍቅር ያደረበት ሰው እንደነበር ገድሉ ይናገራል፡፡ ይኸውም በአንዲት ቀን ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ተቀብሎ ከቤተክርስቲያን ወጥቶ ይሄድ የነበረ ሰው እግሩን እንቅፋት ተመቶ ደሙ ከመሬት ሲፈስስ በአየ ጊዜ እውቀት በልጅነቱ የሞላ መብዓ ጽዮን የደማው ጣቱ እስኪደርቅ ድረስ ጠባው፡፡ በመሬት የፈሰሰ ደሙን ከአፈሩ ጋር በላ፡፡ ይህ ሥራው ከልጅነቱ የመስቀሉ ፍቅር በልቡ የቸነከረ መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡ #ያገባ ሰው ሚስቱን ደስ የሚያሰኝበትን ሥራ ያስባል፡፡ ያላገባ ግን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውን ሥራ ያስባል$ የሚለው የመጽሀፍ ቃል ያፀናው ወጣቱ መብዓ ጽዮን ከቤተሰቡ የመጣለትን የጋብቻ ጥያቄ አልተቀበለውም፡፡ ኃጢአትን ከመጨመር ውጭ ምን እጠቀማለሁ እያለ የዚህችን ዓለም ጣዕም ናቃት፡፡ በዚህም ቤተሰቦቹ ተውት፣ እርሱም ራሱን ይበልጥ ለእግዚአብሔር አስገዛ፡፡ የምንኩስና እና ተጋድሎ ሕይወቱ የምንኩስ እና የተጋድሎ ሕይወት የጣመ የላመ የሌለበት ፍፁም ራስን ለእግዚአብሔር ማሳለፍ ነው፡፡ ይህንን የማይወድ ጠላት ዲያብሎስ ደግሞ ፍፁም ፈተናን ያበዛል፡፡ ቅድሳንም በረድኤተ እግዚአብሔር እና በተጋድሏቸው ያልፉታል፡፡ ሠይጣንን ድል ይነሡታል፡፡ አቡነ መብዓ ጽዮንም የምንኩስና ቀንበር ከተሸከመ ጊዜ ጀምሮ ከፈረስ፣ ከበቅሎ፣ ከአልጋ፣ ከምንጣፍ ላይ ሳይቀመጥና ሳይተኛ መኖሩን ገድሉ ይነግረናል፡፡ ለዚህም ተጋድሎ ሕይወቱ ያግዘው እና ይረዳው ዘንድ ክህነትን አባ ገብርኤል ከተባለ ጳጳስ ተቀብሏል፡፡ ቄስም ሆኖ የመድኃኔዓለምን ሥጋው እና ደሙን እያቀበለ ብዙ ዘመን ኖሯል፡፡ የምንኩስና ሕይወቱና ትጋቱም ታላቅ አባት እንደሆነ ያስረዳል፡፡ ትልቅ ድንጋይ በደረቱ ተሸክሞ ከምድር ከአመድ በተቀመጠም ጊዜ በራሱ ተሸክሞ፣ በሚሰግድም ጊዜ በጀርባው አዝሎ ስለ ክርስቶስ መከራ ያስባል፡፡ ራሱን ይበድላል፣ ስጋውን ያደክማል፡፡ ይኸውም ያለሰንበት እና ያለበዓላት በቀር በዚህ ተጋድሎ የምንኩስና ሕይወቱን ቀጠለ፡፡ ከዛም ወደ ደብረ ሊባኖስ በመሄድ ከአቡነ ተክለሃይማኖት መቃብር በረከትን እንደተቀበለ ገድለ መብዓ ጽዮን ይነግረናል፡፡ አቡነ መብዓ ጽዮን ራሱን ለእግዚአብሔር በሰጠ ቁጥር መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ በስጋወደሙ እየተገለፀ፤ እመቤታችንም እየታየች ትመክረው ታስተምረው ነበር፡፡ ቅዱሳንን ማክበር በዓላቸውን መዘከር እንዲገባ ከምንማርባቸው ታሪኮች አንድ የአቡነ መብዓ ጽዮን ታሪክ ነው፡፡ የመድኃኔዓለምን እና የእናቱን የቅድስት ድንግል ማርያምን በዓል አብዝቶ ያከብር ነበር፡፡ በዚህም መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ እና ከቅድሳን ጋር መጥቶ ባርኮታል፡፡ የመለኮት ምሥጢርም ሥርዓትም በአካባቢው ላሉ ሠዎችም ተሠጥቷቸዋል፡፡ መናፍቃን በዓል ማክበር አይገባም ቢሉ የበዓል ማክበር ውጤቱ እዚህ ድረስ መሆኑን እናያለን፡፡ በፀሎቱም #ኦ እግዚኦ አንተ ትብለኒ ሰአል ኩሎ ዘፈቀድከ ወአነ እሁበከ፣ ጌታ ሆይ አንተ የወደድከውን ሁሉ ለምን እኔ እሠጥሃለሁ አልከኝ፡፡ አሁንም የለመንኩን ግለጽልኝ$ በማለት የቀራንዮን መስቀል መከራውን ያሳየው ዘንድ ሁልጊዜ ይለምን ነበር፡፡ የለመኑትን የማይነሳ መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስም ቅዱሳን የሆኑ እጆቹን በመስቀሉ እንዲዘረጋ፣ እግሮቹም እንዲቸነከሩ፣ የሾህ አክሊልም በራሱ ተሸክሞ የጥቅምት 27 ቀን ታየው፡፡ ለሙሴ ሊታያቸው እንዳልቻለ አባ መብዓ ጽዮን ከመሬት ወደቀ፡፡ እንደ ሞተም ሆነ፡፡ ማንም የመስቀሉን መከራ ሕማሙን ማየት እንደማይችል ነገረው፣ በቸርነቱም አነሳው፡፡ የሞቱ ገናንነት የሚያስፈራ እና የሚያስደነግጥ መሆኑን አሳውቀው፡፡ መከራው ታላቅ በሰው አእምሮ አይታሰብምና ነው፡፡ ኃጢአትን ያልሠራ ሐሰትም በአፉ ያልተገኘበት ስለሠው ኃጢአት ስለሞተው ስለመድኃኔዓለም ክርስቶስ የሞቱ መታሰቢያ በምትሆን በዕለተዓርብ ታላቅ ተጋድሎን በማድረጉ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የስቅለት በዓል በሚታሰብበት በ27 በመድኃኔዓለም ዕለት የአቡነ መብዓ ጽዮን መታሰቢያ ተደረገ፡፡ ይኸውም ጥቅምት 27 ነው፡፡ /ከቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ሰሌዳ መጽሔት የተወሰደ/ የጻድቁ የአባታችን የአቡነ መብዓ ጽዮን በረከት ከእኛ ጋር ትሁን!!! የመስቀሉ ፍቅር በልባችን ይኑር አሜን!!!