en
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Open in Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 413 subscribers, ranking 5 577 in the Religion & Spirituality category and 2 192 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 413 subscribers.

According to the latest data from 13 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 71 over the last 30 days and by -3 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.53%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 9.38% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 933 views. Within the first day, a publication typically gains 1 446 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 23.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 14 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 413
Subscribers
-324 hours
+357 days
+7130 days
Posts Archive
፨፨ ሌሎች በሃገራችን የሚገኙ የመድኀኔ ዓለም አብያተ ክርስቲያናት፤ (ፎቶ ያላችሁ ላኩልን፡፡) ✤መቅደላ መድኀኔዓለም ✤ባሕር ዳር ድባንቄ መድኄኔዓለም ✤አዴት መድኃኔዓለም ✤አዲስ አምባ መድኃኔዓለም ከ1600 ዓመት በላይ ዕድሜ ያለው በግብፃዊው ጻድቅ አቡነ ሙሴ የተፈለፈለ የዋሻ ገዳም ✤በቅሎ አግት / ዝንጀሮ አስጨብጭብ/ ጨጨሆ መድኃኔዓለም ገዳም ✤ወንጪት መድኃኔዓለም በአብርሃ ወአጽብሃ ዘመነ መንግስት ተመስርቶ እስካሁን ድረስ ነብር በቤተ መቅደሱ እየኖረ በሚጠብቀው በታላቁ ወይን እንጨት ቅዱስ ሚካኤል ገዳም ውስጥ የተሰራ ✤መቀሌ መድኃኔዓለም ✤አድግራት መድኃኔዓለም ወቅድስት ሥላሴ ወቅዱስ ቂርቆስ ገዳም ብዙ ድንቅ ታሪክ ያለው ✤ደባርቅ መድኃኔዓለም ✤የሽረት መድኃኔዓለም እጅግ ተደንቀውና ተደምመው ምስጋናዎ ኢምንት ሆናብዎት የሚመለሱበት ✤ኮሶ በር መድኃኔዓለም ✤ሐረር መድኃኔዓለም ✤ምስካበ ቅዱሳን ጻድቃኔ ዋሻ መድኃኔዓለም ገዳም ✤እመኪና መድኃኔዓለም ገዳም በመናኔው ጻድቅ ንጉሥ በአጼ ካሌብ ልጅ በጻድቁ ንጉሥ በአጼ ገብረ መስቀል በ6ኛው መ.ክ.ዘ. የተመሰረተ ታሪካዊ ገዳም ✤በሬ አገር መድኃኔዓለም ገዳም 1000 ሜትር ፍልፍል ዋሻ ገዳም ✤ተከዜ መድኃኔዓለም ገዳም በ11ኛው መ.ክ.ዘ. የላስታ ንጉሥ ቅዱስ ገብረ ማርያም /ታላቁ ሐርቤይ/ ደቀመዝሙር እንደነ ነቢዩ ኤልያስና ወንጌላዊው ቅ.ዮሐንስም ሞትን ሳያይ እስከ ምጽዓተ ሐሳዊ መሲህ /ዳግም ምጽአተ ክርስቶስ ዋዜማ/ ድረስ የተሰወረው ጻድቁ አቡነ ሐዋርያ ክርስቶስ ታቦተ ኪዳነ ምሕረትን ከሰማይ ተቀብሎ የመሰረተው ንዑድ ክቡር የሆነ መካነ ጸሎት ወአርምሞ ወትኅርምት ✤ሬማ መድኃኔዓለም አንድነት ገዳም፦ በ1414 በአባ ኖብ የተመሰረተና የብዙ ቅዱሳን መካነ ጸሎት የነበረ በዘመነ ሱስንዮስ ሰማእትነትን የተቀበለቺው ጻድቅት ወሰማእት ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ አጽሟ ያለበትና የከበረና የማይሻር ቃልኪዳኑን ከአምላከ ቅዱሳን የተቀበለችበት እፁብ ድንቅ ሥፍራ ሲሆን የሰማእቷን ጨምሮ በርካታ ቅዱሳን አጽማቸው የሚገኝበት ጥንታዊ ገዳም ✤ደብረ ታቦር መድኃኔ ዓለም ✤ናዝሬት መድኃኔዓለም

በኢትዮጵያና በአሜሪካ የሚገኙ የመድኀኔዓለም ገዳማትና አድባራት፤ የፎቶ ስብስብ 7፤ 1. ✤ላፍቶ ሌንቃ መድኀኔዓለም ቤተክርስቲያን፤ 2. ✤መድኃኔዓለም ቤ.ክ፤ ደብረ ሊባኖስ አጠገብ 3. ✤የቲሊሊ ደብረ ገነት መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን 4. ✤ሚዛን ተፈሪ መድኀኔዓለም ቤተክርስቲያን 5. ✤ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም 6. ✤ኒውዮርክ መድኀኔ ዓለም

በኢትዮጵያ የሚገኙ የመድኀኔዓለም ገዳማትና አድባራት፤ የፎቶ ስብስብ 6፤ 7. ✤ደጀን አበ ብዙኃን አብርሃም ወመድኃኔዓለም፤ ደጀን ጎጃም 8. ✤አርባምንጭ ደብረ መድኃኒት መድኀኔዓለም ቤተክርስቲያን፤ አርባ ምንጭ ከተማ 9. ✤ቦራራ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን 10. ✤ደብረ ቀራንዮ መድኀኔዓለም ወቅዱስ ላሊበላ ቤ.ክ፤ ጎንደር 11. ✤ጌቴ ሴማኔ ፈረስ ቤት መድኀኔዓለም ቤተክርስቲያን፣ ደብረ ማርቆስ 12. ✤ወልዲያ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም፡፡

በኢትዮጵያ የሚገኙ የመድኀኔዓለም ገዳማትና አድባራት፤ የፎቶ ስብስብ 5፤ 1. ✤ዋሻ መድኃኔ ዓለም አቡነ ሙሴ ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም 2. ✤አርብዓሐራ ምስካበ ቅዱሳን መድኀኔዓለም ገዳም(ምስካበ ቅዱሳን መድኀኔዓለም ገዳም)፦ ደመ ክርስቶስን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል የተቀበለበትን የብርሃን ጽዋ የሚያጥኑና ሌሎችንም ቅዱሳንን አጽም በንሥር አሞራ የተመሰለ የጌታ መልአክ በቀስተ ደመና ተከብቦ በቀን የሚያመጣበት እልፍ ታሪክና ብዙ የብዙም ብዙ ገቢረ ተአምራት የሚፈጸሙበት ለተፈቀደላቸውና እንደሚገባ ሆነው በቦታው ላይ በበጎ ኅሊና ለሚጸልዩ ምዕመናን ሥውራኑ እየተገለጡ ጥያቄያቸውን የሚመልሱበት ግርማ ያለው ክቡር ንዑድ የ40ዎቹ ቅዱሳን ሰማእታት መካነ ጸሎት የአቡነ ሐራ ግብፃዊ የቃልኪዳን ሥፍራ 3. ✤ጨጨሆ መድኀኔዓለም፤ ወሎና ጎንደር ድንበር ላይ 4. ✤በደሌ ደብረ ሣህል መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን፤ ከ100 ዓመት በላይን ያስቈጠረ ጥንታዊ ቤ.ክ. 5. ✤ደሴ መድኃኔዓለም 6. ✤ወዘም ባሕታዊ መድኃኔዓለም፣ ፍቼ አጠገብ ሰሜን ሸዋ

፨፨ በአዲስ አበባ የመድኀኔ ዓለም ክብረ በዓል ያለባቸው አብያተ ክርስቲያናት እንጠቁማችሁ፤ (ስብስብ 4) (ፎቶ ያላችሁ ላኩልን፡፡) ✤ደብረ ቀራንዮ መድኀኔዓለም ቤ.ክ ✤ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምወደ.ት. ቅ. ገብርኤል ቤ.ክ ✤ምስካዬ ኅዙናን መድኀኔዓለም፤ (ታቦተ ሕጉ ባይወጣም በሰዐታትና በቅዳሴ ይከበራል፡፡)፤ 6 ኪሎ ✤አቃቂ ጋራው መድኀኔዓለም፤ ✤ረጲ መካነ ጎልጎታ መድኀኔዓለም፤ረጲ ✤መንበረ ሕይወት መድኀኔዓለም፤ አቃቂ ክ/ከተማ ✤ደብረ ቅዱስ ደብረ ቀራሜሎስ ካራአሎ መድኀኔዓለም ወአቡነ ገሪማ፤ የካ ክ/ከተማ ✤መካነ ሰላም መድኀኔ ዓለም፤ የካ ክ/ከተማ ✤ቦሌ ቡልቡላ ደብረ ገነት መድኀኔ ዓለም፤ቦሌ ቡልቡላ ✤ድልበር መድኀኔዓለም፤ ጉለሌ (ቶታል) ✤ማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያምና ደብረ መድኀኒት መድኀኔዓለም ቤ.ክ ልደታ ሜክሲኮ ✤ደብረ ሳሌም ቦሌ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ቤተ ክርስቲያን (የመድኀኔዓም ታቦት በድርብነት ይገኛል)፤ ቦሌ ✤ምሥራቀ ፀሐይ ቀበና መድኀኔዓም ቤተክርስቲያን፤ቀበና ✤አያት መድኃኔዓለም፤ አያት ✤ደብረ ኢያሪኮ መድኀኔዓለም፤ደቡባዊ አ.አ ✤ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን፤ የመድኀኔዓለም ታቦት በድርብት ይገኛል፡፡ ✤ደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤተክርስቲያን የመድኀኔዓለም ታቦት በድርብት ይገኛል ፡፡ ጎተራ ✤የመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ወኢሉጣ ቤ.ክ የመድኀኔዓለም ታቦት በድርብት ይገኛል፤ ለገሃር ✤ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ፤ የመድኀኔዓለም ታቦት በድርብት ይገኛል፡፡ ✤ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ (የመድኀኔዓለም ታቦት በድርብነት ይገኛል) ✤መንበረ ንግሥት ቊስቋም ማርያም ቤ.ክ (የመድኀኔዓለምና የመብዓ ጽዮን ታቦት በድርብነት ይገኛል) ✤ደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤ.ክ (የመድኀኔዓለም ታቦት በድርብነት ይገኛል) ✤ ኮተቤ(ሲምሲ) ደብረ ጽባሕ ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ.፤ (የመድኀኔዓለም ታቦት በድርብነት ይገኛል)

5. ✤ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም ቤተ ክርስቲያን፤ (ስብስብ 3)፤ የ108 ዓመታት ዕድሜ ያለው ጥንታዊ የኢያሱ ደብር፡፡ ‹‹በወርቅ ወበዕንቊ ሥርጉት ደብረ ሰላም፤ ወነገሥት ይትቀነዩ ለኪ›› ለዛቲ ቤት ሣረራ ኢያሱ ቀዲሙ ለዛቲ ቤት፤ ወፈጸመታ ንግሥት ዘውዲቱ፡፡ (ይህችን ደብረ ሰላምን በመጀመሪያ አቤቶ ኢያሱ /አልጋ ወራሽ ልጅ ኢያሱ/ (ክፍለ ያዕቆብ) በሐምሌ 26 ቀን 1903 ዓ.ም. መሠረታት፤ ንግሥት ዘውዲቱ አሁን ያለውን ሕንፃው ቤ.ክ ጥቅምት 27 ቀን 1913 ዓ.ም አስፈጸመች፡፡) ስለ ታላቁ ደብር ብዙ ነገር ባወራን ደስ ባለን ነበር ….. የሰላም አምላክ የፍቅር ጌታ ያደረባት ደብረ ሰላም ብዙ ነገሮች አሏት፤ የብዙ ሊቃውንት መፍለቂያ፤ የላይ ቤት አቋቋም፣ የተክሌ ዝማሜና የሸዋና የራሱ የደብሩ ቀለም እንደ ወንዝ የሚፈስባት፤ ታሪካዊ ቅርሶችን የያዘ ቤተ መዘክር (Museum)ና ቤተ መጻሕፍት የሚገኙበት፤ ደብሩን አገልግለው ወደ ሌላ ደብር የሚዛወሩ ካህናት ኹሌም በዓይናቸው የደብሩ ፍቅር ውልብ የሚልባቸው፤ ምዕመናኑ በአጸዱና በግርማ ሞገሱ ኹሌም የሚደነቁበት፤ ስዕለት ሰሚ ታቦታት ያሉበት፤ 4ት የሚጠጉ ፈዋሽ ጠበሎች የሚገኙበት፡፡ ጽዶቹ ሳይቀሩ በ72 አርድዕት ቅዱሳን አምሳያ የተተከሉበት፤ በቀድሞ ዘመን መዐዛ ቅዳሴ የተሰኘው የአባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ቅዳሴ በወርኃ ጽጌ የሚቀድስበት፤ 3 ጳጳሳትን ያፈራ፣ ……. ደብር ነው፡፡ ✣ ለደብረ ሰላም ይደልዋ ስብሐት፤ እስመ በውስቴታ ኀደረ መድኀኔዓለም (በደብረ ሰላም በውስጧ መድኀኔዓለም ስላደረ ምስጋና ይገባታል፡፡)

በሃገራችን ከሚገኙ በመድኀኔዓለም ስም የተሰየሙ አብያተ ክርስቲያናት፤ ስብስብ 2፤ ጨነቅ ዋሻ መድኀኔዓለም፤ በቅዱስ ላሊበላ በዋሻ ውስጥ እንደገና ፎቅ ተደርጎ የተፈለፈለ፤ በሰሜን ተራሮች (በራስ ደጀን) እግር ሥር የሚገኝ፤ በፓርክ ክልል ውስጥ በመኾኑ በብዙ ኢትዮጵያውያን የማይታወቅ፤ ነገር ግን ብዙ ተዓምራትን እጅጉን ፈዋሽ የኾነ ጠበል የሚገኝበት፡፡ 1. ✤መናገሻ ጋራ መድኀኔዓለም፤ ግማደ መስቀሉ ያረፈበት፤ ቀድሞ የቅዳሴ ቤቱን ታላቁ አባት አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ (ቀድሞ የልደታ ቤ.ክ) በአካል በመገኘት በመስቀሉ የባረከው፤ በድርሳነ ራጕኤል ላይ የተገለጸና ቅዱስ ራጕኤል የማይለየው፤ በአረማዊው ግራኝ ወረራ ጊዜ ቤተ ክርስቲያኑ ካህናቱን መነኮሳቱንና ምዕመናኑን እንደያዘ በምድር ውስጥ ገብቶ የተሰወረበት በሥጋ ዕረፍተ ሞት ያልተገቱ ሥውራን ግሩማን አበው የሚኖሩበት "ዛቲ ይእቲ አምባ ማርያም መካነ ክብሮሙ ወጸሎቶሙ ለቅዱሳን ወለነገሥታተ ኢትዮጵያ በሐ በልዋ ተሳለምዋ ጊሱ ሐቤሃ ኢትርሐቁ እምኔሐ" ብለው አበው ያወደሷት የጸሎት የአርምሞና የትኅርምት ቦታ፡፡ 2. ✤ገዳመ አባ ጽጌ ድንግል (መድኀኔዓለም ቤ.ክ)፤ ማኅሌተ ጽጌ የተደረሰበት ወሎ፤ ወግዲ፤ ወለቃ ወንዝ አጠገብ፤ የበረሃው ዕንቊ ገዳም፤ አባ ጽጌ ድንግል የፈለፈሉት ባለ 3 መቅደስ እጅግ ሰፊ ዋሻ ቤ.ክ፡፡ 3. ✤ደብረ ቀራንዮ መድኀኔዓለም ቤ.ክ፥ አዲስ አበባ፤ በአዲስ አበባ ከተመሠረተ ከ1826 ዓ.ም ጀምሮ ፍልሰት ሳያጋጥመው በመቆየቱ፤ የመጀመሪያው የአዲስ አበባ ቤ.ክ፡፡ (ነገር ግን በመሃል ፍልሰት እያጋጠማቸው እንጂ በአዲስ አበባ ከ1600 ዓመታት በፊት ደብረ ኤረር፣ የካ ዋሻ ተክለሃይማኖትና /ኋላ የካ ሚካኤል/ በአብርሃ ወአጽብሃ ዘመን፤ እንዲሁም እንጦጦ ኪዳነ ምሕረት በአልአሜዳ ዘመነ መንግሥት መመሥረታቸውን ልብ ይሏል)

እንኳን ለመድኀኔዓለም ክብረ በዓል (ለመጋቢት 27 ጥንተ ስቅለት ልዋጭ በዓል)ና ለአቡነ መብዓ ጽዮን ክብረ በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡ በሃገራችን ከሚገኙ የመድኀኔዓለም ገዳማትና አድባራት ጥቂቶቹ፤ ፠ ለየብቻቸው ያሉት፤ ዋልድባ አበረንታት መድኀኔዓለም ገዳምና ኤልሻማ ደብረ ማኅቶት መድኀኔዓለም ቤ.ክ. ፠ አንድ ላይ ያሉት፤ ✤1. ዋልድባ አበረንታት መድኀኔዓለም ገዳም፤ ✤2.ላሊበላ መድኀኔዓለም ✤3. ጎንደር መንበረ መንግሥት መድኀኔዓለም ✤4. መንዳባ አቡነ ያሳይ መድኀኔዓለም፤ ጣና ✤5. ሽረ እንዳሥላሴ መድኀኔዓለም ወመስቀል ክብራ ✤6. ቆላድባ መድኀኔዓለም፤ ጎንደር ከተማ አጠገብ ✤7.ቦሌ ደብረ ሳሌም መጥምቁ ዮሐንስ፤ (የመድኀኔዓለም ታቦት በድርብ አለ) ✤ 8.ድሬዳዋ መድኀኔዓለም ✤9.ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም

ስታ ደስ አሰኝህ ዘንድ ወደ እኔ ልወስድህ መጣሁ፣ ስምህን ለሚጠራ፣ መታሰቢያህን ለሚያደርግ እኔ ኃጢአቱን አስተሠርይለት ዘንድ በራሴ ማልኩልህ፣ ወይም በስምህ ለተራቆተ የሚያለብሰውን፣ ለተራበ የሚያጠግበውን፣ለተጠማ የሚያጠጣውን፣ የገድልህን መጽሐፍ የሚጽፈውን የሚያነበውንና የሚሰማውን፣ በጸሎትህም የሚታመኑትን ሁሉ እስከ ዐሥር ትውልድ እምራቸዋለሁ፤ አቅም ቢያጣ 'አምላከ አቢብ ማረኝ' ብሎ 3 ጊዜ በዕለተ ዕረፍትህ የሚለምነኝን፤ በስምህ እንኳን ቁራሽ የሚበላውን ሁሉ እምርልሃለሁ" የሚል ድንቅ ቃልኪዳን ሰጣቸውና አቅፎ ቢስማቸው ቅድስት ነፍሳቸው ከሥጋቸው ተለየች፡፡ የመላእክትን ዝማሬ እያሰማቸው በደረቱ አቅፎ ወደ ሰማያዊት ኢየሩሳሌም ወሰዳቸው፡፡ በዚሁ ዕት መታሰቢያ የሚደረግላቸው አባ ዕብሎይም የአቡነ አቢብ ደቀ መዝሙር ናቸው፤ የአቡነ አቢብና የአባ ዕብሎይ በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን፡፡ ‹‹ሰላም ለዝክረ ስምከ ዘተጸውዓ እምቅድም፤ በመርኅበ ቤቱ ለአብ ኀበ ዘበቈለ ኦም፡፡ አቢብ አቡየ ዝክረ ስምከ ጥዑም፤ በዘሊተ ሥጋሁ ወበዘዚአየ አጽም፤ ተጽሕፎ ይትረከብ በሐዳስ ዓለም፡፡›› /መልክአ አቡነ አቢብ ቀዳማይ/ /ምንጭ፤ የቃል ትምህርት በላስታ ላሊበላ አበው፤ ገድለ አቡነ አቢብ፤ የዲ.ን ዮርዳኖስና ከገድላት አንደበት ገጽ/ /ይህንን ታሪክ ከቦታው ድረስ ሂዶ ከገድሉና ከሌሎችም ጽሑፎች አቀነባብሮ ያዘጋጀልን ወንድማችንን አምላከ አቡነ አቢብ ወዕብሎይ በረድኤት በጤና ይጠብቅልን፡፡/ ስዕሉ፤ ✤✤ የአቡነ አቢብ ቤ.ክ በሃገራችን የሚገኝባቸው ቦታዎች፤ ✣ ላሰታ ዳሪያ አቡነ አቢብ፡፡ ከ1500ዓመታት በላይ ያስቈጠረ፤ ከደረቅ ዐለት ላይ ፈዋሽ ጠበል የሚፈልቅበት፤ ላስታ ዳሪያ አቡነ አቢብ ዋሻ ቤ.ክ.፤ ከላስታ ላሊበላ በቅርብ የሚገኝ ሲኾን፤ አፄ ካሌብ ከመንገሳቸውና በላስታ አካባቢ የሚገኙትን ውቅር አብያተ ክርስቲያናት (ቂርቆስ፣ ዐርባዕቱ እንሰሳ፣ ብልብላ ጊዮርጊስ፣…) ከመፈልፈላቸውም 7 ዓመት ቀድሞ በአባ ሳዊሮስ (ታውረስ?) አማካኝነት በተዓምራት በሰይፍ ነው የገመሱት፡፡ በአቡነ አቢብ ቤ.ክ ውስጥ ብዙ ተዓምራቶች ሲኖሩ ማንኛውንም የጆሮ በሽታ የሚያድን ሴቴ ጭረት የሚባል ቄጠማ ነው፤ በመቅደሱ ውስጥ ከደረቅ ዓለት (ድንጋይ) ላይ የሚወጣ ተዓምራታዊ ጸበል አለ፡፡ በቅርቡ ምዕመናኑ ሁሉ ገብቶ እንዲያየው ተደርጓል፡፡ ………5ት አባቶና 1 እማሆይ አገልጋይ ብቻ ያሉት ገዳም፤ ቅዳሴ የሚቀደሰው በየወሩ በ25፣ በፍልሰታ በዓል፣ በሰንበት /በ15ቀን አንዴ፤ ከጃሮ ሚካኤል ጋር በፈረቃ/ ይቀደሳል፡፡……. በልደት ወደ ላሊበላ የምትሔዱ ምዕመናን፣ የጉዞ ማኅበራት ከላሊበላ በቅርብ ስለሚገኝ ተባርካችሁ ኑ፡፡ ✣ አቡነ አቢብ (ጎንደር አርማጭሆ ከደብረ መጕና አቡነ አብሳዲ ገዳም አጠገብ) ✣ አቡነ አቢብ (ጎጃም ዳንግላ አካባቢ)፡፡

✤✤ ሰው ቢረሳ ቢረሳ ምግቡን አይረሳምና በእንተ(ስለ) አባ ቡላ ብሎ በሚመገብ ጊዜ ያሰበውን ማርልኝ ብለው ታላቅ ቃል ኪዳንን መድኀኔዓለም የሰጣቸው አባት ናቸው፡፡ በዚህም ኹል ቀን /ከተመገብን ‹‹ስብሐት ካልን›› በኋላ ስለ አባ ቡላ/አቢብ/ ብለን የምናዘክረው ታላቅ አባት ነው/ **** እንኳን ለታላቁ ቅዱስ አባት አባ ቡላ (አቡነ አቢብ) በዓለ ዕረፍት በሰላም አደረሳችሁ፡፡ ✤ አቡነ አቢብ በሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ በነገሠ ዘመን የነበረ፤ እንደ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰማዕት የኾነና 3ት ጊዜ ሞቶ 3 ጊዜ የተነሣ (በተጋድሎ ሕይወቱ 10ር ጊዜ ሞቶ የተነሣ) ታላቅ ሰማዕተ ጽድቅ ነው፤ በሃገራችን በኢትዮጵያ በስማቸው 3ት ታላላቅና ጥንታዊ ገዳማት አሏቸው፡፡ ✣✣ የስሙ ትርጓሜ፣ ልደቱ፣ ጥምቀቱና እድገቱ፤ ቡላ ማለት አቢብ ማለት ነው፤ ቡላ ማለት ትርጓሜውም የእግዚአብሔር አገልጋይ ማለት ሲኸን፤ አቢብ ማለት የብዙዎች አባት፥ የመልካም ሥራ ኹሉ ባለቤት ማለት ነው፡፡ ገድሉ አብ ክቡር፤ ወትሩፈ ትጋህ አባ ቡላ ዘውእቱ አቢብ መክብበ ኵሉ ሠናያት (የተከበረ አባት፥ በትሩፋት የተጋ፥ የመልካም ነገሮች ኹሉ አባት) ይለዋል፡፡ አቡነ አቢብ የተወለደው በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ አካባቢ በሮም ሉፊ ከሚባል አውራጃ የካቲት 16 ነው የተወለደው፤ ወላጆቹ ቅዱስ አብርሃምና ቅድስት ሐሪክ ሲባሉ እጅግ ጽኑዕ ክርስቲያኖች ነበሩ፤ ልጅም አልነበራቸውም፤ በዘመነ ሰማዕታት በመክስምያኖስ ዘመን ስደት በሆነ ጊዜ በስደት በበረሃ ሳሉ በመልአክ ብሥራት ወለፉት፤ ቅዱሱ ሲጸነስም ማንም ሳይተክለው የበቀለው ዛፍ ላይ መልአኩ በሮማይስጥ ቋንቋ "ቡላ ገብሩ ለእግዚአብሔር: ወቅዱሱ ለአምላከ ያዕቆብ: ዘየኀድር ውስተ ጽዮን" (‹‹ቡላ የእግዚአብሔር አገልጋይ በጽዮንም አድሮ የሚኖር የያዕቆብ ፈጣሪ ያከበረው›) የሚል የብርሃን ጽሑፍ ጽፎበት ወላጆቹ ዐይተዋል:: ቅዱሱ የተወለደው በዘመነ ሰማዕታት በመኾኑ ለ1 ዓመት ሳይጠመቅ ከቆየ በኋላ እመቤታችን ለሮሙ ሊቀ ዻዻሳት አባ ሰለባስትርዮስ ውደ በረሃ ወርዶ እንዲያጠምቀው አዘዝችው፤ ሊያጠምቀው ሲምል ሕፃኑ ተነስቶ እጆቹንም ዘርግቶ "አሐዱ አብ ቅዱስ: አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውዕቱ መንፈስ ቅዱስ …." ብሎ አመስግኖ ተጠመቀ:: ከሰማይም ሕብስትና ጽዋዕ ወርዶላቸው ሊቀ ዻዻሳቱ ቀድሶ ሁሉንም አቆረባቸው:: የሕፃኑ ወላጆች "ለልጃችን ስም አውጣልን" ቢሉት "ቡላ" ብሎ ሰየመው:: እነርሱም በዛፉ ላይ የተገለጸውን ምሥጢሩን ያውቁ ነበርና አደነቁ:: ✣✣ ሰማዕትነት ውላጆቹ ገና የ10 ዓመት እድሜ ላይ እንዳለ ድንገት ሕዳር 7 ቀን ተከታትለው ዐረፉ፡፡ ቅዱሱን ሕፃንም ጎረቤቶች ማሳደግ ጀመሩ፤ ሃገረ ገዢውም ለጣዖት ስገዱ ብሎ አዋጅ ባስነገረ ጊዜ በሕፃን አንደበቱ አምልኮተ ክርስቶስን ሰበከ:: በዚህ የተበሳጨ መኮንኑ ስቃያትን አዘዘበት፤ ትላልቅ ችንካሮችን ቸንክረው በጅራፍ ገረፉት፥ በዘንግ ደበደቡት:፥ ቆዳውን ገፈፉት፥ በመጋዝ ቆራርጠውም ጣሉት በሾተሎችና በጦሮች መካከል አድርገው በመንኮራኩር ውስጥፈጩት፡፡ ነገር ግን ኀይለ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበርና ከሞት ተነሳ፡፡ ዳግመኛም መኮንኑ የሕፃኑን ሰውነቱን አሥሮ በመሬት ላይ እንዲጎትቱት አዘዘ አሁንም ግን መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል መጥቶ አዳነው፣ ያለ ምንም ጉዳት ፍጹም ጤነኛ አደረገው፡፡ ቅዱስ ቡላ ዳግመኛም ወደ ሌላ ከሃዲ መኰንን ዘንድ ሄዶ እርሱንም ከነአምልኮ ጣዖቱ ገሠጸው፡፡ ያም ከሃዲ መኰንን ብዙ ካሠቃየው በኋላ ሚያዝያ 18 ቀን ራሱን በሰይፍ አስቆረጠው፤ ነገር ግን አሁንም ለ2ኛ ጊዜ ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ከሰማይ ወርዶ ቅዱስ ቡላን ከሞት አስነሣው፡፡ ወደ አንድ ገዳምም ወስዶ የምንኵስና ልብስንና አስኬማን በመስቀል ምልክት አለበሰውና ‹‹ከቅዱሳን ጻድቃን አንድነት ትሆን ዘንድ እግዚአብሔር አዞሃል›› አለው፡፡ አባ ቡላም ከአንድ ደረቅ ተራራ ላይ ወጥቶ በታላቅ ተጋድሎ መኖር ጀመረ፡፡ ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ በነገሠ ጊዜ ሳያውቅ በመንገድ ሊያልፍ ሲል መልአኩ መጥቶ እንዲሰግድለት አድርጓል፡፡ ✣✣ ገዳማዊ ሕይወቱና ተጋድሎው ቅዱስ ቡላ ሰማዕትነቱን ከፈጸመ በኋላ ቅዱስ ሚካኤል በአክሊላት አክብሮ ወስዶ በገነት አኖረው:: ከሰማዕታትም ጋር ደመረው:: በዚያም ቡላ ቅዱስ ጊዮርጊስን ተመልክቶ ተደነቀ:: መንፈሳዊ ቅንዐትን ቀንቷልና "እባክህን ወደ ዓለም መልሰኝና ስለ ፍቅርህ እንደ ገና ልጋደል" ሲል ጌታን ለመነ:: ጌታችን ግን "ወዳጄ ቡላ! እንግዲህስ ሰማዕትነቱ ይበቃሃል:: ሱታፌ ጻድቃንን ታገኝ ዘንድ ግን ፈቃዴ ነውና ሒድ" አለው:: ቅዱስ ሚካኤልም የቅዱስ ቡላን ነፍስ ከሥጋው ጋር አዋሕዶ: ልብሰ መነኰሳትንም አልብሶ ግብጽ በርሃ ውስጥ አኖረው:: አባ ቡላ ወደ በርሃ ከገባ ጀምሮ ዐርብ ዐርብ የጌታችን የመድኀኔ ዓለምን ሕማማት እያሰበ ራሱን ያሰቃይ ገባ:: ራሱን ይገርፋል: ፊቱን በጥፊ ይመታል: ሥጋውን እየቆረጠ ለአራዊት ይሰጣል: ከትልቅ ዛፍ ላይ ተሰቅሎ ወደ ታች ይወረወራል:: ሌላም ብዙ መከራዎችን የጌታን ሕማማት እያሰበ ይቀበላል:: ጌታችንም ስለ ክብሩ ዘወትር ይገለጥለት ነበር፤ የሚታየውም እንደ ተወለደ፥ እንደ ተጠመቀ፥ እንደ ተሰቀለ፥ እንደ ተነሳ፥ እንዳረገ እየሆነ ነበር፡፡ ስለ ጌታ ፍቅርም ብለው፤ ✤ ምንም ነገር ሳይቀምስ፤ መዝሙረ ዳዊትን ጥራዝ እስከ ጥራዝ (15ውን መዝሙራት) እየጸለየ ለ42 ዓመታት ጹሟል:: ✤ በአንዲት ዕለትም የጌታችንን መከራውን አስበው ሰይፍ አምጥተው ስለቱን ወደላይ አቁመው በአንጻሩ ከተከሉት በኋላ ናላው ፈሶ እስኪያልቅ ድረስ አንድ ዓመት በራሱ ተዘቅዝቆ ኑሯል፤ ‹‹ወኀልቀ ናላሁ›› እንዲል ገድሉ፡፡፡፡ ✤ ፊታቸውን እየጸፉ ሥጋቸው ተቆራርሶ እስኪወድቅ ድረስ ጀርባቸውን ሰባት መቶ ጊዜ እየገረፉ ኖሩ፡ ✤ ከረጅም እንጨት ላይ በመውጣት ከዚያ ላይ ራሱን ወደታች ሁልጊዜ ይወረውር ነበር፤ ጦርም ሰክቶ ከላይ ይወድቅበት ነበር፤ ነገር ግን ጦሩ እየተጣመመ አይገድለውም ነበር፤ በአንዲት ቀንም ከረጅም ዛፍ ላይ በተወረወረ ጊዜ ሰይጣን በረታበትና ገደለው፡፡ በአንዲት ቀንም ከረጅም ዛፍ ላይ በተወረወረ ጊዜ ሰይጣን በረታበትና ገደለው፡፡ ነገር ግን ጌታችን ተገልጦለት ከሞት አስነሣውና ‹‹ከእንግዲህ ስምህ ቡላ አይሁን አቢብ (ሃቢብ) ተባል እንጂ የብዙዎች አባት ትሆናለህ›› አለው፡፡ "እስከ ይቤሎ አምላክ ቃለ አኮቴት ማሕዘኔ፤ ረሰይከኑ ለባሕቲትከ ኩነኔ፤ ዘመጠነዝ ታጻሙ ነፍስከ በቅኔ፡፡" እንዲል:: ✣✣ ዕረፍት አቡነ አቢብ ታላቁ ዕብሎይን ጨምሮ በርካታ ደቀ መዛሙርትን አፈራ:: ከእመቤታችን ጋርም ዕለት ዕለት እየተጨዋወተ ዘለቀ:: በተጋድሎ ሕይወቱም ከ10 ጊዜ በላይ ሙቶ ተነስቷል:: በዚህች ቀን ሲያርፍ ገዳሙ በመላእክት ተሞላ:: እመቤታችንም ከእልፍ አእላፍ ቅዱሳን መላእክት ጋራ መጥታ ‹‹የእኔና የልጄ ወዳጅ አቢብ ሆይ! ሰላምታ ይገሃል›› አለቻቸው፡፡ በዚህም ጊዜ ከበድናቸው ቃል ወጥቶ ‹‹የሰማይና የምድር ንግሥት እመቤቴ ሆይ! ሰላምታ ይገባሻል›› አላት፡፡ እመቤታችንም በከበሩ እጆቿ ዳሰሰቻቸውና ከሞት አስነሣቻቸው፡፡ ሰው ቢረሳ ቢረሳ ምግቡን አይረሳምና በእንተ(ስለ) አባ ቡላ ብሎ በሚመገብ ጊዜ ያሰበውን ማርልኝ ብለው የለመኑትን ልመና አምላካችን ተቀብሎላቸው ዛሬም ድረስ፤ ወደፊትም በዚህ በቃል ኪዳናቸው የሚያስምሩ ሆነዋል፤ ጌታችንም ከድንግል እናቱ ከእልፍ አእላፍ ቅዱሳን መላእክት ጋራ መጥቶ ልዩ የሆኑ አክሊላትን የሚያበሩ ልብሶችንም ይዞ መጥቶ ተገለጠላቸውና ‹‹ወዳጄ አቢብ ሆይ! ወደማያልቅ ተድላ ደ

ሥርዐተ ማኅሌት ዘወርኀ ጽጌ (‹ዘላይ ወዘታች› ቤት)፤ ፬ኛ ሳምንት፥ዘጥቅምት ፲፰፤ በዓለ ኤዎስጣቴዎስ ወአቡነ ቴዎፍሎስ ወቅዱስ ሮማኖስ፡፡ በቴሌግራም ማግኘት ከፈለጉ፤ https://t.me/joinchat/AAAAAE2hgYCjGkwz9N1jIw Shareee, invite በማድረግ ለሌሎችም ያስተዋውቁ፡፡ ✤ ልዩ አዋጅ ዘወርኃ ጽጌ ✤  የማኅሌቱ ሥርዐት የላይ ቤት (የጎንደር መካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም አብነት) እና የታች ቤት (የጎንደር ደብረ ኀይል ዑራኤል ወደብረ ጥበብ በዓታ ለማርያምን አብነት) የሚያደርግ ሲኾን፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ የማኅሌት ቁመትም የላይ ቤትን አብነት የተከተለ ሲኾን፤ የዚቁ ወረብ ግን የደብሩን የራሱን (የሸዋን) የተከተለ ነው፤  የላይ ቤት ቁመት የሚቆሙ አድባራት ዘግምጃ ቤት የሚለውን እንዲከተሉ፤ የታች ቤትን ቁመት የሚቆሙ አድባራት ዘበዓታ የሚለውን እንዲከተሉ፤ እንዲሁም ምንም ያልተጻፈበት ከኾነ በላይ ቤትም በታች ቤትም የሚባል መኾኑን እያሳሰብን፡፡ የዚቁ ወረብን ግን የቀጨኔ ደብረ ሰላም የቤቱን ቀለም አስቀድመን ቀጥሎ ደግሞ ዓዲ (ወይም) በማለት የጎንደርን ስላስቀመጥነው እንደ ደብራችሁ ይትበሃል መርጣችሁ እንድትጠቀሙበት ኹሉንም አስቀምጠነዋል፡፡