uz
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Kanalga Telegram’da o‘tish

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት analitikasi

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 369 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 5 619-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 193-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 369 obunachiga ega bo‘ldi.

24 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -18 ga, so‘nggi 24 soatda esa 1 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 23.10% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 8.16% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 551 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 254 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 22 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 25 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 369
Obunachilar
+124 soatlar
+477 kunlar
-1830 kunlar
Postlar arxiv
"መንግስት ቤተ ክርስቲያንን ለማፍረስ ከተሰበሰበ ወራሪ ቡድን ጋር በማበር በጠራራ ፀሐይ ሕግ ሲጥስና የሕግ አፍራሾች ተባባሪ ሆኖ ማየት እጅግ አሳፋሪ እና አንገት የሚያስደፋ ድርጊት ነው" - ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጥር 27 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ) ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል የበላይ ጠባቂ በዛሬው ዕለት በሻሸመኔ ኦርቶዶክሳውያን ላይ በመንግሥት አካላት የተፈጸመውን ግድያና ማዋከብን አስመልክቶ ጥሪ አቅርበዋል። ብፁዕነታቸው በማኅበራዊ የትሥሥር ገጻቸው ባሠፈሩት መልእክት የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በቤተ ክርስቲያን እና በክርስቲያኖችን ላይ እያደረሰ የሚገኘውን የማሳደድ ተግባር በአስቸኳይ እንዲያቆም ጠይቀዋል። በሰሜን ኢትዮጵያ ሕግ እናስከብራለን በሚል በትግራይ እንቅስቃሴ ሲያደርግ የነበረው የኢትዮጵያ መንግስት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ለማፍረስ ከተሰበሰበ ወራሪ ቡድን ጋር በማበር በጠራራ ፀሐይ ሕግ ሲጥስና የሕግ አፍራሾች ተባባሪ ሆኖ ማየት እጅግ አሳፋሪ እና አንገት የሚያስደፋ ድርጊት ነውም ሲሉ ድርጊቱን ኮንነዋል። የተፈጸመው ድርጊት ከዘር ጭፍጨፋ የሚተናነስ አይደለም ያሉት ብፁዕነታቸው የሕዝቡን ሰብዓዊ መብት ካላስከበረ መንግሥትነቱ ምን ላይ ነው ሲሉም ጠይቀዋል። ብፁዕነታቸው ለሻሸመኔ እና ምዕራብ አርሲ ኦርቶዶክሳውያን ከዘመነ ዲዮቅልጥያኖስ ያልተናነውን ይህንን ዘመን በጾም በጸሎትና በክርስቲያናዊ ጥንካሬ እንዲያልፉ ያሳሰቡ ሲሆን የፌደራልና የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የሚፈስሰውን በግፍ የኦርቶዶክሳውያን ደም እንዲያስቆሙ ጥሪያቸውን አቅርበዋል። #TMC_Addia_Ababa

በሻሸመኔ ከተማ አንድ ኦርቶዶክሳዊ ወጣት ሰማዕትነትን ተቀበለ! ጥር 27 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ) በዛሬው ዕለት ሕገ ወጡ ቡድን ወደ ሻሸመኔ ይመጣል መባሉን ተከትሎ ጠዋት ሁለት ሰዓት ላይ ሥርዓተ ቅዳሴ እንደተፈጸመ ሕዝቡን ለመጥራት በከተማዋ ያሉ አድባራት ደወል ደውለዋል። ይህንን ጥሪ ሰምቶ ሁሉም ምእመን ወደ ቤተ ክርስቲያን መሔድ ይጀምራል። በዚህ ጊዜ ወደ ሻሸመኔ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን የሔዱ ምእመናን የቤተ ክርስቲያኑ በር በመዘጋቱ ከውጪ ቆመው ነበር። በእንዲህ ሁኔታ ውስጥ እያለ የከተማው ፖሊስ ሕዝቡን ለመበተን ተኩስ መክፈቱም ነው የተነገረው። እስካሁን ድረስ አንድ ኦርቶዶክሳዊ ወጣት ሰማዕትነትን መቀበሉንና በውል ያልታወቀ ሰውም በጥይት መመታቱን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ከጥቂት ዓመታት በፊት አስከፊ እልቂትና ውድመት የደረሰባት የሰማዕታት ከተማ ሻሸመኔ ዛሬም በሕገ ወጡ ቡድን ምክንያት ሞት ተደግሶላታል። ያለውን ሁኔታ ለማጣራት ወደ መልአከ ፀሐይ ቀሲስ ዮሐንስ ዘለዓለም የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ክፍል ኃላፊ የስልክ ቃለ ምልልስ አድርገን ነበር። ኃላፊውም ሁላችንም ለመሞት ተዘጋጅተናል ብለዋል። በመንግሥት በኩል ያለው ተጽዕኖም ከባድና መራር ነው ሲሉ አንስተዋል። ከጠዋት አንስቶ የአብያተ ክርስቲያናቱ በር በጸጥታ ኃይሎች ቢዘጋም ሕዝቡ አጥሩን እየገነጠለ ወደ ቤተ ክርስቲያኗ ቅጽር ጊቢ እየገባ እንደሆነም ነው የተሰማው። በሌላ በኩል በምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት በጭሮ ከተማ በሕገ ወጥ መንገድ የተሾሙት ኤጲስ ቆጶሳት ዛሬ ጥር 27 ቀን 2015 ዓ.ም እንደሚመጡ መረጃ ስለደረሳቸው የጭሮ ከተማ ሕዝበ ክርስቲያን በከተማው የሚገኙትን 4 አብያተ ክርስቲያናት በንቃት እየጠበቀ ይገኛል። ትናንት ሌሊት ሊቀ ጳጳሷ የታሠሩባትና መቆየት አይችሉምጨ ተብለው ወደ አዲስ አበባ እንዲመለሱ የተደረጉባት በአርሲ ሀገረ ስብከቷ መናገሻ አሰላ ኦርቶዶክሳውያን እየታሠሩ መሆኑንና በቤተ ክርስቲያን ቅጽር ያሉትም እንዲወጡ እየተነገራቸውና ያ የማይሆን ከሆነ የኃይል እርምጃ እንደሚወሰድባቸውም ተዝቶባቸዋል።

"ምዕመናን ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ለመጠበቅ በሚያደርጉት ጥረት ለሚፈጠረው ችግር መንግስት ኃላፊነቱን ይወስዳል" ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ ጥር 26 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ) +++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ሻሸመኔ ከተማ በሕገ ወጥ የተሾመው ቡድን መንበረ ጵጵስና እና ቤተ ክርስቲያን ሰብረን እንገባለን በማለት በምእመናን ላይ ስጋት መፍጠሩን ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የሲዳማ፣ ጌዲዮ፣ አማሮ፣ ቡርጂና ምዕራብ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ማምሻውን ለማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን አሳወቁ። ከሰሞኑን የሀገረ ስብከቱ አገልጋዮች ያለምክንያት እየታሰሩ ነው ያሉት ብፁዕነታቸው ይህንንም ለሚመለከተው የዞን ፀጥታ አካል ለማሳወቅና ጥበቃ እንዲያደርጉ ብንደውልም፣ መልእክት ብንጽፍም ሊመልሱልን አልቻሉም ብለዋል። በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ መሠረት ለኦሮምያ ክልል የሚመለከታቸው አካላት በተለይም ጥበቃና ከለላን በተመለከተ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አስቀድሞ ደብዳቤ ቢጻፍም ምንም አይነት የቃልም ሆነ የተግባር መልስ እንዳልተሰጣቸውም ተናግረዋል። ብፁዕነታቸው አክለውም መንግሥት በሕገ ወጡ ቡድን የሚደረገውን ድርጊት ማስቆም ካልቻለ ምእመናን ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ለመጠበቅ በሚያደርጉት ጥረት ለሚፈጠረው ችግር ኃላፊነቱን ይወስዳል ብለዋል። በመጨረሻም ምእመናን ቤተ ክርስቲያናቸውን እንዲጠብቁ መልእክት አስተላልፈዋል።

ብፁዕ አቡነ ያሬድ በአሰላ መቆየት አይችሉም ተብለው በዚህ ሰዓት ወደ አዲስ አበባ እንዲመለሱ ተደርገዋል።

ከአሰላ ያገኘነው መረጃ ብፁዕ አቡነ ያሬድ የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ዛሬ ምሽት 3:45 አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ከሚገኘው መንበረ ጵጵስናቸው ተወስደው መታሠራቸውን ለማወቅ ተችሏል። ሕገ ወጡ ቡድን ሾሜዋለሁ ያለው ግለሰብ በነገው ዕለት እንደሚመጣ የተነገረ ሲሆን በሌሎች ቤተእምነት ተከታዮችን በማስተባበር የአዲሱን ተሿሚ ፎቶ በባነር ለመስቀል ሲሞክሩ ተስተውሏል። በሐረር የተሐድሶ እንቅስቃሴ መሪና በይቅርታ ወደ ሥራው የተመለሰው ግለሰብ ለምዕራብ አርሲ ተሾሟል መባሉ ምእመናኑ አስቆጥቷል። EOTC TV +++++++++++++++++++++++++++++++++++

ልዩ መረጃ! ብፁዕ አቡነ ያሬድ ታሠሩ! ጥር 26 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ) ብፁዕ አቡነ ያሬድ የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ዛሬ ምሽት 3:45 አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ከሚገኘው መንበረ ጵጵስናቸው ተወስደው መታሠራቸው ተገለጸ። ብፁዕነታቸው በዛሬው ዕለት ማምሻውን ከአዲስ አበባ ወደ ሀገረ ስብከታቸው መድረሳቸውን ተ.ሚ.ማ ያገኘችው መረጃ ያመለክታል። በተጨማሪም የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ኅሩያን ታምራት ወልዴ ቤትም መከበቡንና እስካሁን ያለውን ሁኔታ ማወቅ እንዳልቻሉም ነው ምንጮቻችን የገለጹት። ሕገ ወጡ ቡድን ሾሜዋለሁ ያለው ግለሰብ በነገው ዕለት እንደሚመጣ የተነገረ ቢሆንም ምእመናኑ ሕጋዊውን ቅዱስ ሲኖዶስን ብቻ እንደሚቀበሉም ገልጸዋል። #Ethiopia #Tewahedo_Media_Center #TMC_Addia_Ababa

የእነ አቶ አካለወልድ ሞገስ ሕገወጥ ቡድን የምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳምን ለመውረር ዝግጅት እያደረገ መሆኑ ተገለጸ !!! ++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ (ጥር 26 ቀን 2015 ዓ.ም አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ) ሕገወጥ ቡድኑ በፔንሲዮን መሽጉ የሰነበተ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን በተለያዩ አህጉረ ስብከት የጸጥታ ኃይሎችን ተገን በማድረግ የአህጉረ ስብከት መንበረ ጵጵስናዎችን እየሰበረ ወረራ ሲፈጽም የቆየ ሲሆን እስከ አሁን ድረስ በወለጋ የሚገኙ አራት አህጉረ ስብከት መንበረ ጵጵስናዎችን በወረራ ተቆጣጥሯቸዋል። በተመሳሳይም በነገው ዕለት አቶ አካለ ወልድ ሞገስ ቀድሞ ሊቀ ጳጳስ በነበሩበት ወቅት የበላይ ጠባቂ ሆነው ሲመሩት የነበረውን የምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳምን ለመውረር ዝግጅት ማድረጋቸውን የተ.ሚ.ማ ምንጮች ጠቁመዋል። ቅዱስ ሲኖዶስ መንግሥት የቤተ ክርስቲያኒቱን ሕግና ሥርዓት እንዲያስከብር ጥሪ ቢያቀርብም እስከ አሁን ድረስ ከመንግስት የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም። ©ተ.ሚ.ማ