372
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#MinistryofLaborandSkills
ወደ ቴክኒክና ሙያ የመግቢያ ነጥብ በትላንትናው ዕለት ይፋ ተደርጓል።
አጠቃላይ የመግቢያ ነጥቡ ዝርዝር ከላይ ተያይዟል።
ተጨማሪ መረጃ ፦
(ከሥራ እና ክህሎት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል)
- ከባለፈው ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ እየተደረገ ባለው አዲሱ የትምህርትና ሥልጠና ፖሊሲ መሰረት ከዚህ ቀደም እስከ ደረጃ 5 ብቻ ተገድቦ የነበረው የቴክኒክና ሙያ ስልጠና የእድገት መሰላል እስከ ደረጃ 8 ድረስ እዲሆን ተደርጓል።
- አዲሱ ፖሊሲ ደረጃ ስድስትን ከመጀመሪያ ዲግሪ፣ ደረጃ ሰባትን ከማስተርስ እንዲሁም ደረጃ ስምንትን ከዶክትሬት ዲግሪ ትይዩ እንዲሆን አድርጓል።
- በዚህ ዓመት የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ነጥብ ያመጡ ተማሪዎች ወደ ቴክኒክና ሙያ መግባት ቢፈልጉ በደረጃ 6 ገብተው መሰልጠን ይችላሉ።
- ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ በደረጃ 6 የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞች ይስተናገዳሉ።
- በዚህ ዓመት በተቀመጠው መስፈርት መሰረት በክልሎች አማካኝነት የሰልጣኞች ምደባ ይካሄዳል።
- በተያዘው የሥልጠና ዘመን 632 ሺህ በላይ ተማሪዎች የሥራ ገበያውን የሰው ሃይል ፍላጎት መሠረት ባደረገ መልኩ ከደረጃ 1 እስከ ደረጃ 5 እንደ ውጤታቸው ተመድበው ይሰለጥናሉ።
- በወጣው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ደረጃ አንድ እና ሁለት 110 ሺህ 15 ፣ በደረጃ ሦሰት እና አራት 412 ሺህ 557 እንዲሁም በደረጃ አምስት 110 ሺህ 15 ፣ በደረጃ ስድስት 2 ሺህ የሚሆኑ ሰልጣኞችን ለቀበል ዝግጅት ተደርጓል።
- የ2016 የስልጠና ዘመን የተዘጋጀው መቁረጫ ነጥብ የ2015 ትምህርት እና የ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ላይ ተግባራዊ ይሆናል።
- ከ2014 ዓ.ም በፊት ለነበሩ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ደግሞ በስልጠና ዘመኑ በነበረው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ይስተናገዳሉ።
መረጃው የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ነው።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
Repost from Addis Ababa Education Bureau
የ2015 ዓ.ም 12ኛ ክፍል ተፈታኞች አቅም ማሻሻያ (Remedial Program) መከታተያ የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ።
በ2015 የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ወስደው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያላመጡ ተማሪዎች የአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም መከታተያ መቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆኗል።
የከፍተኛ ትምህርት የአስተዳደርና መሠረተ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር ) እንደገለጹት በ2016 በግልና የመንግስት ተቋማት የአቅም ማሻሻያ /Remedial Program / የሚከታተሉ ተማሪዎች መቁረጫ ነጥብ እንደተፈተኑት የትምህርት ዓይነት ብዛት 30% እና ከዚያ በላይ ሆኗል ።
በዚህም መሠረት በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ለመማር የመቁረጫ ነጥብ የተፈጥሮ ሳይንስ ለመደበኛና የማታ ወንድ ተማሪዎች 255 የተፈጥሮ ሳይንስ ለመደበኛና የማታ ሴት ተማሪዎች 234 መሆኑን አስታውቀዋል።
የማህበራዊ ሳይንስ ለመደበኛና የማታ ወንድ ተማሪዎች 218 የማህበራዊ ሳይንስ ለመደበኛና የማታ ሴት ተማሪዎች 200 መሆኑን ተናግረዋል።
ታዳጊ ክልሎች የተፈጥሮ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች 224 ታዳጊ ክልሎች ተፈጥሮ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች 210 መሆኑን ተናግረዋል።
ታዳጊ ክልሎች የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች መግቢያ 192 ታዳጊ ክልሎች ማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች መቁረጫ180 መሆኑን አመልክተዋል።
አርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ በሁለቱም ፆታ 210 መሆኑን ተናግረዋል።
Repost from N/a
ማስታወቅያ
ለመጋላ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትት/ቤት መምህራን በሙሉ
ለ2016 የትምህርት ዘመን የአክሽን ሪሰርቻችሁ ርዕስ እስከ16/2/2016 እ .እ ድረስ ለም/ር/መራን ሪፖርት እንድታደርጉ እናሳውቃለን።
ከሠላምታ ጋር
ታአዮራብራ አበራ
BEEKSISA
BARSIISOTA MANA BARUMSAA WALIIGALAA SADARKAA 2FFAA MAGAALAAF
Bara barnootaa 2016 A.L.I f mata duree AKSHIIN RIISERCHII keessanii hanga16/2/2016 A.L.I tti I/A/Dayirekteeraa mana barumsichaatti akka galchitan isin beeksifna.
Nagaa Wajjin
Ta'ayoorrabbirraa Aberraa
ቅዳሜና እሁድ በደራርቱ ት/ቤት የመ/ራን ስልጠና ስላለ ሁላቼሁም ሰዓት አክብራችሁ ተሳታፊ እንድትሆኑ ፡፡ፍቃድ አይሰጥም ፡፡
